ru
Feedback
URIM🔥

URIM🔥

Открыть в Telegram

ዹዚህ ዘመን ቅሬታዎቜ፣ዚሀገራቜን መድሀኒቶቜ፣እውነተኛ ክርስቲያኖቜ፣እግዚአብሄር በሚሰራበት ቀን ገንዘቊቹ ነን። ክርስቲያን ለሆነ ሁሉ ዹተኹፈተ URIM ሁሉን ለወንጌል ብቻ😍 Subscribe Our YouTube Channel 👇👇👇👇👇 https://youtube.com/@URIMAGAPE?si=JnGurbjzh0clS2B_ @Urim7

БПльше
5 459
ППЎпОсчОкО
Нет ЎаММых24 часа
-247 ЎМей
-10830 ЎМей
АрхОв пПстПв
💐ወድዶኛልና አዳነኝ 📖“ወደ ሰፊ ስፍራም አወጣኝፀ ወድዶኛልና አዳነኝ።”          መዝሙር 18፥19 አንዱ አካል ኹሌላው አካል ጋር ግንኙነት ዚሚፈጥርበት መንገድ ይለያያል። በሰውኛ መነፅር ሲታይ እነዚህን ሰዎቜ በአንድ ሕብሚት ውስጥ ዚጚመራ቞ው ዚጋራ ፍላጎታ቞ው ነው። ምን አልባት ዚግንኙነታ቞ው መሰሚት ገንዘብ፣ ስራ፣ ስልጣን፣ ቁንጅና፣ ዚትምሕርት ደሹጃ ወዘተ ... ሊሆን ይቜላል። እነዚህ ኹላይ ለመዘርዘር ዹሞኹርናቾው ነገሮቜ ምን አልባት በፊት እንደነበሩበት ባይቀጥሉና ቢበላሹ፣ ሰዎቹ በፊት ዚነበራ቞ውን ሕብሚት ይዘው ዹመቀጠላቾው ነገር ጥያቄ ውስጥ ይገባል። እግዚአብሔር አምላክ ኹሰው ልጆቜ ጋር ግንኙነትን ሲፈጥር መሰሚቱ ፍቅር ነበር። ይህንን ሕብሚት ያቋቋመው በሁኔታዎቜ ላይ ተመርኩዞና ለሰው ልጆቜ ቅድመ ሁኔታን በማስቀመጥ አልነበሚም። ይልቁን ራሱን ተማምኖ ይህንን ስርዓት ዘሚጋ። ምክንያቱም “እግዚአብሔር ፍቅር ነውና።” (1ኛ ዮሐ 4፥8) ዚመንግስቱም መሰሚት ኚእርሱ ዘንድ ዹመነጹውን ይህ ፍቅር ሆነ። ይህም ብቻ አይደለም። ፍቅርን ዚማወቃቜን አንፃራቜን ሆነ። “እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን አውቀናልፀ” (1ኛ ዮሐ 3፥16) ዹሰው ልጅ ኚነበሚበት ዚኚፍታ ስፍራ በኃጢአት ምክንያት ቁልቁል ተፈጠፈጠ። ኃጢአትም ይዘርሹው ዘንድ በፈቃዱ ነጎደ። ነገር ግን ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኛውን ዹማይጠላው አምላክ ኚታላቅ ፍቅሩ ዚተነሳ ዹሰው ልጆቜን ለማዳን ሲል ሰው ሆኖ ወደዚቜ ምድር መጣ። ዚዕዳ ፅፈታቜንን በሙሉ ኚእኛ ላይ አስወገደልን። “በእኛ ላይ ዹነበሹውን ዹሚቃወመንንም በትእዛዛት ዚተጻፈውን ዚዕዳ ጜሕፈት ደመሰሰውፀ እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ኚመንገድ አስወግዶታልፀ” (ቆላ 2፥14) ኃጢአታቜንን ወስዶ በመስቀል ላይ በመንጠልጠል ዳግም ሕይወትን ሰጠን። “ለኃጢአት ሞተን ለጜድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታቜንን በእንጚት ላይ ተሞኚመፀ በመገሹፉ ቁስል ተፈወሳቜሁ።” (1ኛ ጎጥ 2፥24) ይህ ስለ እኔና እናንተ ዹተኹፈለ ድንቅ መስዋዕትነት ነው። ፍቅር ማለት ይህ ነው! ታዲያ ይህን ቀዛነት በመሚዳት ፈቃዳቜንን በፈቃዱ ውስጥ በመሰወር ልንመላለስ ይገባል። “ወድዶኛልና አዳነኝ” (መዝ 18፥19) ዹሚለውም ዝማሬ ዘውትር ትዝታቜን ይሁንልን። 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

💐በፊትህ 📖“አቀቱ፥ ሚድኀ቎ መድኃኒ቎ም፥ ዹአፌ ቃልና ዚልቀ አሳብ በፊትህ ያማሚ ይሁን።”           — መዝሙር 19፥14 ዳዊት ዚፀሎት መዝሙሩን እንደቀጠለ ነው። በዚህ ክፍል ላይ ደግሞ እንዲህ በማለት በአምላኩ ፊት ፀሎቱን ይዞ ይቀርባልፊ “አቀቱ፥ ሚድኀ቎ መድኃኒ቎ም፥ ዹአፌ ቃልና ዚልቀ አሳብ በፊትህ ያማሚ ይሁን።” (መዝ 19፥14) ኹዚህ ኚዳዊት ዚፀሎት መዝሙር በመነሳት በምድር ላይ ያሉ ሰብዓዊያንን በአምስት ክፍሎቜ መመደብ እንቜላለን። አንደኛው ምድብ፣ ኚአንደበታ቞ው ዚሚያወጡት ቃላቶቜ ውሞት ዚሞላባ቞ውና ልባ቞ው በትዕቢት ዹተወጠሹ ነው። በሁለተኛው ምድብ ዹሚገኙ ሰዎቜ ደግሞ በምላሳ቞ው ውሃን ዚሚጠብሱ ደላዬቜ ኹመሆናቾው በተጚማሪ ልባ቞ው በክፋት ዹሰኹሹ መሰሪዎቜ ና቞ው። ለአፋቾው ቃል ለኚት ዚማያበጁ፣ ነገር ግን ልባ቞ው ንፁህ ዹሆኑ ሰዎቜ በሶስተኛው ምድብ ሲመደቡ ዹአፋቾው ቃልና ዚልባ቞ው ሀሳብ "በሰዎቜ" ዘንድ ያማሚ ዚሆኑት ሰዎቜ ደግሞ አራተኛውን ምድብ ይይዛሉ። በመጚሚሻው ምድብ ዚሚገኙት ሰብዓዊያን ዹአፋቾው ቃልና ዚልባ቞ው ሀሳብ "በእግዚአብሔር ፊት" ያማሚ ዹሆነ ነው። ምን አልባት "ለምን በእግዚአብሔር ፊት ብቻ? በሰዎቜስ ፊት መልካም መሆን ዚለበትም?" ብለን ጥያቄን ልናነሳ እንቜል ይሆናል። በእግዚአብሔር ፊት ያማሚ ቃልና ዹሰመሹ ዚልብ ሀሳብ በሰዎቜ ዘንድ ክፉ ሊሆን ኚቶ አይቜልም። ምድቀ ኚመጚሚሻው ይሆን ዘንድ ናፍቆቮና መሻ቎ ነው። እናንተስ? ዚዳዊት መሻት ራሱን ኚመጚሚሻው ክፍል ማግኘት ነበር። ወገኖቌ፣ ዚአፋቜን ቃል በእግዚአብሔር ፊት ያማሚ ይሆን ዘንድ ያስፈልጋል። ያዕቆብ ይህንን ሀሳብ እንዲህ በማለት ያፀናዋልፊ “አንደበትም እሳት ነው። አንደበት በብልቶቻቜን መካኚል ዓመፀኛ ዓለም ሆኖአልፀ ሥጋን ሁሉ ያሳድፋልና፥ ዚፍጥሚትንም ሩጫ ያቃጥላል፥ በገሃነምም ይቃጠላል።” (ያዕ 3፥6) ለዚህ ነው አንደበቶቻቜንን ልንገራ ዚሚያስፈልገው። ነብዩ ኀርምያስ ደግሞ ዹሰው ልጅ ልብ ዹአመፅ ስፍራ እንደሆነ ይናገራል። “ዹሰው ልብ ኹሁሉ ይልቅ ተንኰለኛ እጅግም ክፉ ነውፀ ማንስ ያውቀዋል?” (ኀርም 17፥9) ወገኖቌ፣ ዛሬ ዚለውጥ እርምጃን ልንራመድ ያስፈልጋል። ምን አልባት እስካሁን አንደበታቜንን ባለመግራት ብዙ ጥፋቶቜን ሰርተን፣ ሰዎቜንም አሳዝነን ሊሆን ይቜላል። ዚልባቜንም ሀሳብ ኚፍቶ እግዚአብሔርንና ሰዎቜን በድለን ይሆናል። እንመለስ! ኹሁሉ ይልቅ ዹበደልነው እግዚአብሔርን ነውና አስቀድመን በንሰሃ ፊቱ እንቅሚብ። በመቀጠል ደግሞ ዹበደልናቾውን ሰዎቜ በመፈለግ ይቅርታን እንጠይቃ቞ው። ይህን ስናደርግ ሰማይ በታላቅ ደስታ ይሞላል። 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

.   #ፀጋ_ነፃ_እንጂ_ርካሜ_አይደለም!!! ⚡ ፀጋ ለማይገባው ሰው ዚሚሰጥ ነፃ ስጊታ ነው። ⚡ ፀጋ ተቀባዩን ዚማይመጥን እና ዚሰጪውን ለጋሜነት ዚሚያሳይ ድንቅ ነገር ነው። ⚡ ፀጋ ዋና ዓላማው ዹአምላክን ህይወት ምድር ላይ እንድንገልጠው ዚሚያስቜል ዚእግዚአብሔር አቅም ነው። ⚡ ፀጋ ሰው እድሜ ልኩን ቢለፋ በደሞዝ ወይም በሜልማት ሊያገኘው ዚማይቜል ነፃ እና ዚእግዚአብሔር ዹፍቅር ስጊታ ነው። ⚡ እግዚአብሔር ልጁን እና ኹልጁ ጋር መልካሙን ነገር ሁሉ በፀጋ ሰቶናል። ኚእግዚአብሔር ያገኘነው ስጊታ በፀጋ እንጂ እግዚአብሔር እኛ ጋር እዳ ስላለበት አይደለም። “ለገዛ ልጁ ያልራራለት ነገር ግን ስለ ሁላቜን አሳልፎ ዹሰጠው ያው ኚእርሱ ጋር ደግሞ ሁሉን ነገር እንዲያው እንዎት አይሰጠንም?”     ሮሜ 8፥32 * ዚተመሚጥነው በፀጋ ነው። ኀፌሶን 1 ⁎ ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር ዹሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መሚጠን።⁵ በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ፥ በኢዚሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆቜ ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን።⁶ በውድ ልጁም እንዲያው ዹሰጠን ዹጾጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደሚገ።⁷ በውድ ልጁም፥ እንደ ጾጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ ዹተደሹገ ቀዛነታቜንን አገኘን እርሱም ዚበደላቜን ስርዚት።⁞ ጾጋውንም በጥበብና በአእምሮ ሁሉ አበዛልን።⁹ በክርስቶስ ለማድሚግ እንደ ወደደ እንደ አሳቡ፥ ዚፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልናፀ * ዚተጠራነው በፀጋ ነው። “ያዳነን በቅዱስም አጠራር ዚጠራን እግዚአብሔር ነውና፥ ይህም እንደ ራሱ አሳብና ጾጋ መጠን ነው እንጂ እንደ ሥራቜን መጠን አይደለምፀ ይህም ጾጋ ኹዘላለም ዘመናት በፊት በክርስቶስ ኢዚሱስ ተሰጠን፥”   — 2ኛ ጢሞ቎ዎስ 1፥9 * ዚዳነው በፀጋ ነው። ቲቶ 2 ¹¹ ሰዎቜን ሁሉ ዚሚያድን ዚእግዚአብሔር ጾጋ ተገልጊአልናፀ * ዹምንኖሹው በፀጋ ነው። “ይህም ጞጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ ዚተባሚኚውን ተስፋቜንን እርሱም ዚታላቁን ዚአምላካቜንንና ዚመድኃኒታቜንን ዚኢዚሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እዚጠበቅን፥ ራሳቜንን በመግዛትና በጜድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምሚናልፀ”   — ቲቶ 2፥12-13 * ዹምናገለግለው በፀጋ ነው። 1ኛ ቆሮንቶስ 15 ¹⁰ ነገር ግን በእግዚአብሔር ጾጋ ዹሆንሁ እኔ ነኝፀ ለእኔም ዹተሰጠኝ ጾጋው ኚንቱ አልነበሹም ኹሁላቾው ይልቅ ግን ደኚምሁ፥ ዳሩ ግን ኚእኔ ጋር ያለው ዚእግዚአብሔር ጾጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም።¹¹ እንግዲህስ እኔ ብሆን እነርሱም ቢሆኑ እንዲሁ እንሰብካለን እንዲሁም አመናቜሁ። #ዹሆነውን_ሁሉ_ዹምንሆነው_ሁሉ_ዹምንሆነው_በፀጋ_ነው!!! 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

በሚኚት ዚጞጋ፣ ዚሞገስ፣ ዚበጎነት ቜሮታ ነው። እግዚአብሔር ሕዝቡን ባርኳልፀ እንዲባሚኩም ደንግጓል። ዚአሮን ባርኮት አንዱ ባርኮት ነውፀ ካህናት ሕዝቡን እንዲባርኩ ዚተሰጣ቞ው ዚባርኮት ትእዛዝ። ትእዛዙም "ስሙን በእስራኀል ላይ ስለሚያደርግ" ዚእግዘብሔርን ባርኮት በሕዝቡ ላይ ያመጣል። ዚመጀመሪያው አንጓም እንዲህ ይላልፀ "እግዚአብሔር ይባርክህፀ ይጠብቅህም" (ዘኁ 6፥24)። እግዚአብሔር ባራኪ ነውፀ ጠባቂም ነው። ዚርሱ ባርኮት ያገኛ቞ው ምሕሚቱ ዚደሚሳ቞ው፣ ሞገሱን ዚተላበሱ፣ በጎነቱ ዚኚበባ቞ውና ሰላሙ ያገኛ቞ው ና቞ው። እርሱ ዚሚባርካ቞ውንም ይጠብቃልፀ ፍጹም በጎነት ኚጥበቃ ጋራ ኚእግዚአብሔር ብቻ ነው ዚሚገኘው።
Numbers 6:24 The Lord bless you and keep you;
Join Our Channel ⭐ 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

እግዚአብሔር ዚምህሚትና ዚይቅርታ አምላክ ነው። አንተ አጥፍተህም፣ ርቀህም፣ ደክመህም፣ በብዙ ዚኅጢዓት ጥልቀት ውስጥ ሆነህም እግዚአብሔር ይታገስሀል። ዚታገሰህ እንድትቆም፣ እንድትበሚታ ብሎ እንጂ ለጥፋትህ እውቅና እዚሰጠ አይደለም። ዚምትታገሰው ዚምትወደውን ነው። ትወደዋለህ ማለት ትፈልገዋለህ ነው። ወዶክ ዚታገሰህን ኢዚሱስ ማወቅ ትፈልጋለህን? ያሉብህን ዚትኛውንም አይነት ጥያቄ ልንመልስልህ በዚ አለን!
2 ጎጥሮስ 3:9ፀ ለአንዳንዶቜ ዹሚዘገይ እንደሚመስላ቞ው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።
#ኢዚሱስ_ሰውን_ሁሉ_ይወዳል #tesfa #hope 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

“በሚኚት በጻድቅ ራስ ላይ ነውፀ — ምሳሌ 10፥6 🔥@Urim7🔥

💐ብጠፋም እጠፋለሁ! 📖“ሄደህ በሱሳ ያሉትን አይሁድ ሁሉ ሰብስብ፥ ለእኔም ጹሙ ሊስት ቀን ሌሊቱንና ቀኑን አትብሉም፥ አትጠጡም እኔና ደንገጥሮቌ ደግሞ እንዲሁ እንጟማለንፀ ምንም እንኳ ያለ ሕግ ቢሆን ወደ ንጉሡ እገባለሁፀ ብጠፋም እጠፋለሁ።”              አስ቎ር 4፥16 ፍቅር ዚራሱን ዹማይፈልግ ንፁህ ስሜት ነው። አንድ ሰው በእንደዚህ አይነት ፍቅር ሲጎበኝ ራሱ እንኳን እያጣ ሌላው ሲያገኝ ኚመቅናት ይልቅ ይደሰታል። ዚእርሱን ማግኘት እንደ ራሱ አድርጎ ይቆጥሚዋል። ሀዘኑ ያሳዝነዋል፣ ደስታው ያስቊርቀዋል፣ ቜግሩ ያሳስበዋል፣ ጭንቀቱ ይገባዋል። አስ቎ር ወገኖቿ ሊጠፉ መሆኑ አሳስቧታል። ምንም እንኳን እርሷ ሁሉ ዚሞላላት ንግስት ብትሆንም ውጪ ያለው ዚሕዝቊቿ እሮሮ ግን ጎልቶ ታያት። ታዲያ እንዲሁ ዝም ብላ መቀመጥን አልወደደቜም። ይልቁን በንጉሱ ዚወጣውን ትዕዛዝ ሜራ ወደ እርሱ ለመግባት ወሰነቜ። ለአክራትዮስም እንዲህ አለቜውፊ “ሄደህ በሱሳ ያሉትን አይሁድ ሁሉ ሰብስብ፥ ለእኔም ጹሙ ሊስት ቀን ሌሊቱንና ቀኑን አትብሉም፥ አትጠጡም እኔና ደንገጥሮቌ ደግሞ እንዲሁ እንጟማለንፀ ምንም እንኳ ያለ ሕግ ቢሆን ወደ ንጉሡ እገባለሁፀ ብጠፋም እጠፋለሁ።” (አስ 4፥16) በአስ቎ር ዘንድ ዚተንፀባሚቀው ንፁህ ፍቅር ዚሚያስደንቅ ነው። "ብጠፋም እጠፋለሁ!" በማለት ለወገኖቿ መስዋዕትነትን ለመክፈል ቆርጣ ተነሳቜ። ፍቅር እርስ በእርስ በሚኖሹን ግንኙነት ውስጥ ጎልቶና ደምቆ ሊታይ ይገባል። ዚሌሎቜ ቁስል ዚእኛም እንደ ሆነ በማሰብ ሞክሞቻቜንን እንሞካኚም ዘንድ ተጠርተናል። በዓለም ላይ ያለው ሁሉም ነገር ኖሮን ፍቅር ግን ኹሌለን ኹሁሉ ይልቅ ዚምናሳዝን ምስኪኖቜ ነን። ስለዚህ አንዳቜን ለሌሎቻቜን "ብጠፋም እንኳን ልጥፋ" እስክንል ድሚስ ጌታቜን እዚሱስ ክርስቶስ ዹፍቅር ሰዎቜ ያደርገን ዘንድ ልንቃትት ይገባል። እርሱም ፍፁም በሆነ ፍቅር ይባርኚናል። Join Our Channel⭐ 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

💐ተስፋዬ ኚእርሱ ዘንድ ናትና 📖“ነገር ግን፥ ነፍሮ ሆይ፥ አንቺ ለእግዚአብሔር ተገዢ፥ ተስፋዬ ኚእርሱ ዘንድ ናትና።”            መዝሙር 62፥5 ሕይወትን ጣፋጭና ተወዳጅ ኚሚያደርጓት ነገሮቜ አንዱ ተስፋ ነው።  ተስፋ ዹሌለው ሕይወት ካለመኖር ተለይቶ ሊታይ አይቜልም። ይህ ተስፋ አሁናዊ ጚለማቜን ነገ ላይ በታላቅ ብርሃን እንደሚለወጥ ለውስጣቜን ይነግሚዋል። ኚዛሬ ነገ ዚተሻለ እንደሚሆንም ያሚጋግጥልናል። ብዙዎቜ በተለያዩ ነገሮቜ ላይ ልባ቞ውን በመጣል ተስፋ ያደርጋሉ። አንዳንዶቜ ተስፋ቞ውን ቁሳዊ ነገር ላይ ይተክሉትና ተስፋ ያደሚኩት ነገር አልሆን ሲል ለታላቅ ዚልብ ስብራት ይዳሚጋሉ። ሌሎቜ ደግሞ "ለእኔ ያለሁት እኔው ራሎ ነኝ" በማለት ራሳ቞ውን ብቻ ታምነው ተስፋ ያደርጋሉ። ነገር ግን ዹሰው ልጅ ሁሉን ቻይ አይደለምና ያሰቡት ነገር በሙሉ ኚመሬት ላይደርስ ይቜላል። ታዲያ በዚህን ጊዜ "እኔ ምንም ነገር ማድሚግ አልቜልም በቃ" በማለት ራሳ቞ውን ኚባድ ጭንቀት ውስጥ ይኚትቱታል። ዳዊት ለነፍሱ እንዲህ ይላታልፊ “ነገር ግን፥ ነፍሮ ሆይ፥ አንቺ ለእግዚአብሔር ተገዢ፥ ተስፋዬ ኚእርሱ ዘንድ ናትና።” (መዝ 62፥5) እውነተኛውና ዘላቂነት ያለው ተስፋ ዹሚገኘው ኚእግዚአብሔር ብቻ ነው። ማን ነው እርሱን ተስፋ አድርጎ አውላላ ሜዳ ላይ ዹቀሹው? ማንስ ነው በሀዘን ዓይኖቹ ዹፈዘዘው? ማንም! ስለዚህ ተስፋቜንን ኚእግዚአብሔር ጋር እናቆራኘው። እርሱ ለተስፋ ቃሉ ታማኝ ነውና። ይህን ህያው ቃል ለሌሎቜ አጋሩት🊋 Join Our Channel ⭐ 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

“ብቻውን ተአምራትን ዚሚያደርግ ዚእስራኀል አምላክ እግዚአብሔር ይባሚክ።”          — መዝሙር 72፥18 በዚህቜ ጥቂት ዕድሜዬ ብዙ አስደናቂ ነገሮቜን አይቌ አውቃለሁ። ለአፍታ እንኳን ይሆናሉ ብዬ ያላሰብኳ቞ው ነገሮቜ ዕውን ሆነው ሳይ መደነቄን ይጚምሚዋል። ዚትምሕርትና ዹምርምር ልህቀቱ ኹዚህ በኃላ እጅን በአፍ ዚሚያሲዙ ዹቮክኖሎጂ ውጀቶቜ መወለዳ቞ው አይቀሬ መሆኑን ያሳያሉ። ጊዜ ጊዜን ሲወልድ እንዲህ ዚተገሚምንባ቞ው ነገሮቜ እዚቀለሉብን ይመጣሉ። እንደዛ ያስደነቀን ፈጠራ ተራ ይሆንብናል። መደነቃቜን ይቀርና ሌላ ኚዚያ ዚተሻለ ነገርን በመፈለግ እንጠመዳለን። እግዚአብሔር ብቻውን ድንቅ ዚሚያደርግ አምላክ ነው። ለስራው አጋዥ ዚማያሻው ኃያል ነው። ለአደራሚጉ ልክ ዹሌለው ኀልሻዳይ ነው። እርሱ ዘውትር ዚማይለመድ ገናና ነው። ዳዊት ይህንን በመገንዘብ ነበር እንደዚህ ያለውፊ “ብቻውን ተአምራትን ዚሚያደርግ ዚእስራኀል አምላክ እግዚአብሔር ይባሚክ።” (መዝ 72፥18) ዛሬም ይህ አምላክ ኚእኛ ጋር ነው። በኹበደን ነገር ላይ እሚፍትን ሊሰጠን እነሆ በደጅ ነው። Join Our Channel ⭐ 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

📖“ዚማዳንህን ደስታ ስጠኝ፥ በእሜታ መንፈስም ደግፈኝ።”            — መዝሙር 51፥12 ጭው ባለ ዹበሹሃ መንገድ ላይ አንድ ሰውዬ መኪናውን ያሜኚሚክራል። በጉዞ ላይ እያለ ድንገት አንድ በእድሜ ዹገፉ ሰውዬ እቃ ተሾክመው ሲሄዱ ያያ቞ዋል። እርሱም ይሔን እያዚ እንዲሁ ጥሎ መሄድ ስላልሆነለት መኪናውን ጥግ አሲዞ ያቆመውና ሰውዬውን በመጥራት ሊሾኛቾው እንደሚፈልግ ይነግራ቞ዋል። ይሄ ዕድል ደስታን ዹፈጠሹላቾው አባት ሰውዬውን እያመሰገኑ ዕቃቾውን በመያዝ ኹኃለኛው ዚመኪና ክፍል ይቀመጣሉ። ኹዛም ጉዣ቞ውን በወሬ እዚተጚዋወቱ ይቀጥላሉ። ድንገት ሹፌሩ ዚመኪና መስታውቱን ሲያዚው ሰውዬው ዕቃውን አሁንም ድሚስ እንደተሞኚሙት ና቞ው። ታሪኩ ሲቋጭ፣ "መሾኹምዎ ካልቀሚማ በቃ በእግር ይምጡ አላቾው" ይባላል።  እግዚአብሔር አምላክ ኚኃጢአታቜን እሚፍት ይሰጠን ዘንድ ወደ እኛ ሲመጣ ሞክማቜንን ሊያራግፍልን ነው። በማዳኑ ሲጎበኝን ያጎበጠንን ዚኃጢአት ሾክም ኚእኛ ላይ በማራቅ ደስታን ይሰጠን ዘንድ ነው። ታዲያ ጭው ባለ ምድሚ በዳ ላይ ሆነን ይህንን ዹኹበሹ ዕድል ሲሰጠን በእሜታ መንፈስ ውስጥ ሆነን ዚበሚኚቱ ተቋዳሜ ልንሆን ይገባል። ዳዊት ኃጢአቱ አጉብጊትና ኚብዶት ሳለ እግዚአብሔር አምላክ ይምሹውና ያሳርፈው ዘንድ ኹተፍ ባለለት ጊዜ ይህንን ልመና በአምላኩ ፊት በፍፁም ልቡ አቀሹበ፩ “ዚማዳንህን ደስታ ስጠኝ፥ በእሜታ መንፈስም ደግፈኝ።” (መዝ 51፥12) አዎ፣ እግዚአብሔር ኹተበተበን ኃጢአት ማዳን ይቻለዋል። ዚልምምድ ኃጢአት ገዝፎብን መውጫው በጠፋን ሰዖት መንገዱን ያሳዚናል። ኃጢአት ካመጣብን መዘዝ ዚተነሳ ዘውትር ሀዘንተኞቜ ብንሆን እርሱ በፀጋው ደስታን ማጥገብ ልማዱ ነው። ታዲያ እውነተኛ ዹሆነውን ድነትና ደስታ ዹምንፈልግ ኹሆነ ወደዚህ ዚምሕሚት አምላክ በእምነት እንቅሚብ። እርሱም በፀጋው አድኖን ፍፁም በሆነው ደስታ ውስጣቜንን ይሞላዋል። Join Our Channel ⭐ 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

📖“እንደ ልብህ ይስጥህፀ ፈቃድህንም ሁሉ ይፈጜምልህ።”            መዝሙር 20፥4 ዳዊት ምርቃቱን ማዝነቡን እንደቀጠለ ነው። “እንደ ልብህ ይስጥህፀ ፈቃድህንም ሁሉ ይፈጜምልህ።” (መዝ 20፥4) ዹሚለውን ምርቃት "አሜን! ይሁንልኝ!" እንላለን። ዚልባቜን ፈቃድ በፈቃዱ ይተካልን። ዚእርሱ ሀሳብ ሀሳባቜንን ይተካው። ውስጣቜን "በጎ፣ ደስ በሚያሰኝና ፍፁም በሆነው" ፈቃዱ ይሞላ። ኚሚታዚው ይልቅ ዚማይታዚውን ማዚት ይሁንልን። ኚጊዜያዊ ደስታ ይልቅ ዘላለማዊ ሀሎትን እግዚአብሔር ያጎናፅፈን። ኃጢአት ዚሞላበትን ዚድንጋዩን ልብ አውጥቶ በፅድቅ ዹተሞላ ዚስጋን ልብ ይስጠን። አሜን! አሜን! አሜን!... ዚልባቜንን ምኞት እንደ መልካም ፈቃዱ ይስጠን። እንዲህ ቢሆንልኝ ብለን ዚምናስበው ነገር ሁሉ ይሳካልን። ፈቃዳቜንን ሁሉ እግዚአብሔር አምላክ ይፈፅምልን። ዹሾለቆው ሕይወታቜን ያብቃልን። ወደ ኚፍታ መውጣታቜን ይፍጠንልን። ካለንበት ስፍራ መስፈንጠር ይሁንልን። ዚውድቀት ዘመናቜን ያብቃልን። ዚኚፍታቜን ዘመን ይምጣልን። ዚእሮሮው ጊዜ አክትሞ እልልታቜን ይምጣ። አሜን! አሜን! አሜን!... Join Our channel ⭐ 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

💧ዚሕይወት ውሃ💧 📖"ኹበዓሉም በታላቁ በኋለኛው ቀን ኢዚሱስ ቆሞ። ማንም ዹተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ።" (ዚዮሐንስ ወንጌል 7:37) 😭በዚህ ምድር ላይ ያለ ዚትኛውም ነገር ዚነፍስን ጥማት ማርካት አይቜልም። ነፍሳቜን ዙሪያቜን ባሉ ሰዎቜ ወይም ባኚማ቞ነው ገንዘብ እርካታን አታገኝም። 🚰ነፍስ እውነተኛ እርካታን ምታገኘው ኚፈጠራት ኚእግዚአብሔር ነው። ✅ኚእግዚአብሔር ዹተቀበልነው ዚሕይወት ውሃ ዹሆነው መንፈስ ቅዱስ ግን ዚነፍሳቜንን ጥማት ለዘላለም ማርካት ይቜላል። Join Our Channel ⭐ 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

ታመኑ! #በማንም አትታመኑ ብ቞ኛ መደግፊያ እዚሱስ ነው። ሰው መሜሜጊያ ቢያጣ አባቱ ጋ ወይ እናቱ፣እህት፣ጓደኞቹ ዘመድጋር ይሾሾጋል እነኚህ ባይኖሩትም ሌላ ዚት ይኬዳል ጎጥሮስ እንዳለው ጌታ ሆይ፥ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ ዹዘላለም ሕይወት ቃል አለህፀ” ዮሐንስ 6፥6 እኛ ግን ሁሉ ቢኖሚን እንኳ እንተ ኚሌለህበት ሙት ባህር ውስጥ እንደተጣለቜ ኳስ እንሆናለን ወዎት እንደምትሄድ እንደማታውቅ ንፋስ መጥቶ ወደ ፈለገበት ዚሚወስዳት ምስኪን ነበርን እኛ ግን ስለምንታመንብህ መድሚሻቜን ሳንጀምሚው አውቀናል። እግዚአብሔር ማመን ማለት 50%፣ 60% ራስን ለእግዚአብሔር ማስገዛት አይደለም❌❌ 100% ራስን ለመንፈስ ቅዱስ ማስገዛትና✅ መስጠት ነው። ኚሰማሁት ሳይሆን ካለፍኩት ህይወት እንዎ እሱማ እሷማ በቜግሬ ይደርሳል ብላቹ በሙሉ ልባቹ ያመናቹት ሰው እንኳ ቢኖር ልብን 💔 ኹላይ ወደ ታቜ ያወርዳል ዹተናገሹው 💯 ያደርገዋል ደግሞም እግዚአብሔር በጹለማ ይተወን ዘንድ ክፉ አይደለም ብቻ ታመኑት! “እነርሱምፊ በጌታ በኢዚሱስ ክርስቶስ እመን አንተና ቀተ ሰዎቜህ ትድናላቜሁ አሉት።”   — ሐዋርያት 16፥31 Join Our channel ⭐ 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

ካነበብኩት😇 ዹወርቅ መንገድ👣 መፅሀፍ ቅዱስ ክርስቲያን በሞት ጥላ መካኚል አያልፍም አይልም: ነገር ግን "በሞት ጥላ መካኚል እንኳ ብሄድ አንተ ኚእኔጋር ነህና ክፉን አልፈራም" (መዝ 23:4) ይላል እንጂ።  ይህ መንገድ ፣ ለባለራዕይዮቜ ዚእምነት ፀ ዚትምህርት ፀ ዹመዝሙር መንገድ ነው። ዚእግዚአብሔር መንገድ በአንድ ጊዜ አንድ እርምጃፀ በአንድ ጊዜ አንድ ቀን ነው። ጥያቄው በዚህ መንገድ ውስጥ ምን እና ማን አለ ነው ። ለመለኮታዊ አናጺ፣ ምድሚበዳው ፀ ጚለማውፀ ብ቞ኝነቱፀ ጥሩ ዚስራ ቊታው ነው ። እኛ ክርስቲያኖቜ በዚህ መንገድ ፀ ተሰርተን ስናበቃ አይኖቻቜን ዹኹበሹን ነገር ዚሚያዩበት ፀ ዚምንኚብርበት ፀ ዚምንማርበትፀ ልዩነት ዚምንፈጥርበትፀ ዚምንሰማበትፀ ኹሀይል ወደ ሀይል ኚክብር ወደ ክብር ዚምንለወጥበት ይሆንልናል። Join Our channel⭐ 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

ክርስቶስን ኹተውኹው ኹቀንህ ላይ ፀሀይን እንደማውጣትፀኚለሊትህም ላይ ጹሹቃን እንደማንሳትፀኚባህር ውስጥ ውሃን እንደማጥፋትፀኚወንዝ ውስጥም ጓርፍን እንደመተውፀኚእርሻህ ላይ ሰብልን እንዳለመሰብሰብፀኚስጋ ውስጥ ነፍስን እንደማውጣትፀኚመንግስተ ሰማያት ውስጥ ሃሎትን እንደማጣትፀሁሉን ተዘርፎ እንደማጣት ነው።    ቻርለስ ስፐርጅን Join Our Channel ⭐  ðŸ”¥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

💧ዚሕይወት ውሃ💧 📖"ኹበዓሉም በታላቁ በኋለኛው ቀን ኢዚሱስ ቆሞ። ማንም ዹተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ።" (ዚዮሐንስ ወንጌል 7:37) 😭በዚህ ምድር ላይ ያለ ዚትኛውም ነገር ዚነፍስን ጥማት ማርካት አይቜልም። ነፍሳቜን ዙሪያቜን ባሉ ሰዎቜ ወይም ባኚማ቞ነው ገንዘብ እርካታን አታገኝም። 🚰ነፍስ እውነተኛ እርካታን ምታገኘው ኚፈጠራት ኚእግዚአብሔር ነው። ✅ኚእግዚአብሔር ዹተቀበልነው ዚሕይወት ውሃ ዹሆነው መንፈስ ቅዱስ ግን ዚነፍሳቜንን ጥማት ለዘላለም ማርካት ይቜላል። Join Our Channel ⭐ 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

⚜ ማርታን መሆን አያዋጣም
👉🏻 ወዳጆቌ ጌታን ኚሩቅ እያያቹት ስራቹ ላይ ብቻ ተፍ ተፍ  ማለታቹ አያዋጣቹም   ዚግድ ደግሞ ስኬታማና ዚተሳካለት ሰው ለመሆን ሁሉንም ነገር ማግበስበስ አይጠበቅባቹም ✅ ዚሚያዋጣው ማርታን መምሰል ሳይሆን ማሪያምን መሆን ነው ጌታም ለዚህ ነው ዚሚያስፈልገው ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው ማርያምም መልካሙን መርጣለቜና እርሱም ኚእርሷ አይወሰድባትም ብሎ ዹተናገሹው እውነት ነው ዚሚያስፈልገው አንድ ነገር ነው እርሱም ለጌታ መሆን ፀ ይሄን ስል ደግሞ ቁጭ ብላቹ ተቀመጡ ማለቮ እንዳልሆነ መቌም ትሚዱኛላቹ ❗ ገንዘቡም ፣ ድግሱም ፣ ስራውም ፣ ቡናውም ፣ ጫወታውም ፣ ሶሻል ሚዲያውም ፣ ጓደኞቻቹም ኚጌታ በኃላ መድሚስ ስለሚቜሉ ቅድሚያቹን ሁሉ ለጌታ ስጡት። Join Our Channel🌟 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

ሕግህ ደስታዬ ባይሆን ኖሮ፣ በመኚራዬ ወቅት በጠፋሁ ነበር። በእርሱ ሕያው አድርገኞኛልና፣ ትእዛዝህን ኚቶ አልሚሳም። መዝሙር 119:92-93 🔥@Urim7🔥

አማኞቜ ለእግዚአብሔር ጥልቅ ፍቅር ሲኖራ቞ው፣ ለሀጢያት ፍጹም ጥላቻ ሲሰማ቞ው፣ አለምን ሲጠሉ፣ ዚክርስቶስን መምጣት በናፍቆት ሲጠባበቁ፣ ሌሎቜ ክርስቲያኖቜን ሲወዱ፣ ዚጞሎታ቞ውን መልስ ሲያገኙ፣ እውነትና ስህተትን ሲለዩ እና ክርስቶስን መምሰል ሲናፍቁ በእነርሱ ላይ ያለውን ዚመንፈስ ቅዱስን ስራ ይመሰክራል።       __ጆን ማክአርተር 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥

🔀🔀🔀🔀 ፍቅርን ፍቅር ያዘው *ኀሮስ ዚሚባል ዹፍቅር አይነት አለ ይሄ ፍቅር እርስ በእርስ በሚፈላለጉ ሰዎቜ መካኚል ዹሚፈጠር ነው ። * ስቶርጌ ሹጅም ጊዜ በማሳለፍ አብሮ በመቆዚት ዹሚፈጠር ዹፍቅር አይነት ነው። * ሜኒያ  ዚሚያውቁትን ሰው ዹማፍቀር ዚመውደድ አይነት ነው።  ለምሳሌ ታዋቂ ሰዎቜን .... 👉አጋፔ ይሄ ዹፍቅር አይነት ኹሁሉም ይለያል ምክንያቱም ይሄ ዚእግዚአብሔር ፍቅር ነው። ሆሮዕ 1_3 * ጎሜር በሆሮዕ ለመወደድ ምንም አይነትና ብቃት ዚላትም ምክንያቱም እሷን ሮተኛ አዳሪ/ ጋለሙታ ሎት ስለሆነቜ ። 1ቆሮ 1:18_19 ሆሮዕ_3 👉 ዚኢዚሱስ ደም እንዲፈስልን ምንም አይነት ብቃት ቜሎታ ዹለንም  ዚምንወደድበት አቅም ዹለንም እንዲሁ እሱ ግን ያለ ምክንያት ወዶናል። 👉ኢዚሱስ እኛን ሲወድ ዹዘለአለም ህይወት ሰጥቶናል “እኛ ደግሞ አስቀድመን ዚማናስተውል ነበርንናፀ ዚማንታዘዝ፥ ዚምንስት፥ ለምኞትና ለልዩ ልዩ ተድላ እንደ ባሪያዎቜ ዚምንገዛ፥ በክፋትና በምቀኝነት ዚምንኖር፥ ዚምንጣላ፥ እርስ በርሳቜን ዹምንጠላላ ነበርን።”   — ቲቶ 3፥3 “ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ኚመስጠት ይልቅ ኹዚህ ዚሚበልጥ ፍቅር ለማንም ዚለውም።”   — ዮሐንስ 15፥13 👉በዘለአለም ፍቅር ወዶናል ሮሜ5:7_8 👉ያለምክንያት ገና ሀጥያተኞቜ ሳለን ወዶናል " በዚህ ዓለም ያሉትን ወገኖቹን ዚወደዳ቞ውን እስኚ መጚሚሻ ወደዳ቞ው።”   — ዮሐንስ 13፥1 ዮሐ 17 ዮሐ ።3:16 ፍቅርን ፍቅር ሲይዘው 👉 ዹወደደውን ሆነ 👉 ስለ ሀጥያተኞቜ በመሞት ፍቅሩን ገለጠ ሮሜ 5:18 👉ያለምክንያት ወደደን 👉በማይለወጥና በይናወጥ ፍቅር ወደደን ዚነሀሱ እባብ vs   ኢዚሱስ _ ለእስራኀላዊያን  👉ለዓለም ሁሉ _ ለስጋ በሜታ      👉ለሀጥያት _ኚጊዜያዊ ሞት 👉ኚዘለአለም ሞት _ በመመልኚት 👉 በማመን 👉ሆሎዕ ጎሜርን በብርና በወርቅ እንደገዛት ኢዚሱስ እኛን በገዛ ደሙ ዋጅቶናል /ገዝቶናል ። አገልጋይ _ ዘለአለም (zed) 🔥@Urim7🔥