148
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней
- Подписчики
- Просмотры постов
- ER - коэффициент вовлеченности
Загрузка данных...
Прирост подписчиков
Загрузка данных...
ቀን 12 / 1 / 2013 ዓ.ም
በሀገር አቀፍ ደረጃ ትምህርት የሚጀመርበት ቀን ነገ ከቀኑ 9 ሰአት ላይ ይፋ ይደረጋል ተባለ፡፡
አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ በማድረግ በሀገር አቀፍ ደረጃ የመማር ማስተማር ስራው በቅርብ ቀን እንደሚጀመር የትምህርት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
"ትምህርት ቤቶች በምን መልኩ እና እንዴት ይጀምሩ?" በሚለው ዙሪያ ከሁሉም ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ጋር ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡
ውይይቱ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚካሄድ ሲሆን ነገ ከቀኑ 9 ሰአት ላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ትምህርት የሚጀመርበት ቀን ይፋ ይደረጋል ተብሏል፡፡
በተጨማሪም የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ቀንም በነገው ዕለት ይገለፃል ነው የተባለው፡፡
ምንጭ- EBC
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የዩቲዩብ ፣ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ እና የትዊተር ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!
ቀን 11 / 1 / 2013 ዓ.ም
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርት መጀመር በሚቻልበት ላይ የምክክር ጉባኤ እየተካሄደ ነው::
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርት ለመጀመር በሚቻልበት ላይ የሚመክር ጉባኤ በጅማ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው ፡፡
በጉባኤው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ2012 የስራ ዘመን ኮሮናን ለመከላከል ያከናወኗቸው አበይት ተግባራትና ያስገኙት ውጤት ይገመገማል።
ትናንት በተጀመረው በዚሁ ጉባኤ የዘንድሮ ትምህርት በሚጀመርበት ሁኔታ ላይ ጉባኤው እንደሚመክረና መረሃ ግብሩ ዛሬ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።
ከጉባኤው ጎን ለጎን ኮሮናን ለመከላከል በዩኒቨርስቲዎች የተሰሩ የፈጠራ ምርቶችን የሚያሳይ አውደ ርዕይ በጅማ ዩኒቨርሲቱ ዋናው ግቢ ተከፍቷል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በምርምር፣ በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎትና በቴክኖሎጂ ሽግግር ያከናወኗቸውን አበይት ተግባራት ይዘው ቀርበዋል።
አውደ ርዕዩ ለአንድ ሳምንት እንደሚቆይ ከኢዜአ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በመክፈቻ ስነ-ስርዓት የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ሳሙኤል ኡርካቶ እንዲሁም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቴክኖሎጂና የሰው ሃብት ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ እምዬ ቢተው እንዲሁም ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የዩቲዩብ ፣ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ እና የትዊተር ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
#Update
ትምህርት ሚኒስቴር ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ ለማድረግና ኮሮናን በመከላከል ትምህርት መጀመር የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እያጠና እንደነበር ይታወሳል።
እንዲሁም በተደረጉ የዳሰሳ ጥናቶች ተማሪዎች የትምህርት መጀመርን በጉጉት እየጠበቁ መሆናቸውን ለመረዳት እንደተቻለ ሚኒስቴሩ ገልጿል።
እንደሚታወቀው ከነሃሴ 20/2012 ጀምሮ የግል ትምህርት ቤቶች ምዝገባ እየተካሄደ እንዳለ ይታወቃል። ትምህርት የሚጀምርበት ጊዜ በፌደራል እና በሚመለከታቸው አካላት ውሳኔ መሰረት እንደደሚወሰን ተገልፆ ነበር።
እንደተገለጸውም በ 2013 ዓ.ም. ትምህርት ለመጀመር በተለያዩ ቅድመ ሁኔታዎች ተዘጋጅተን ጨርሰናል። በዚህም መሰረት ሁሉም ተማሪዎች ከመጪው ሰኞ (11/01/2013 ዓ.ም.) ጀምሮ በትምህርት ቤቶቻቸው ጥሪ መሠረት መጀመር እንደሚችሉ ተወስኗል።
ትምህርት ሚንስቴር
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Показать все...