ru
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Открыть в Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Больше
1 810
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней
Архив постов
ወደ አድስ ወቅት(season) እየገባን ነዉ። የእግዚአብሔር ልጆች አብራችሁኝ ጸልዩ! የጥበብ መንፈስ ይሰጣችኋል!🔥 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

አንዴ ነው የምኖረው እርሱንም ለጌታዬ #ኢየሱስ እኖራለሁ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ሁለቱ ትልልቅ ከዋክብት ጁፒተር እና ሳተርን ከተቀራረቡት በላይ: የንጋት ኮከብ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ እና ሙሽሪት የሆነችው የምድር ብርሃን ቤተክርስቲያን ተቀራርበዋል። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

The great conjunction ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ በሳይንስ አገላለጽ Great Conjunction የሚባለው ክስተት የሚከሰተው ዛሬ ታህሳስ 12/ 2013 በፈረንጆቹ የጊዜ አቆጣጠር ደግሞ: December 21/2020 ነዉ። ይህ ክስተት: በህዋ ውስጥ ካሉ በፀሐይ ዙሪያ ከሚዞሩ ትልልቅ ከዋክብት ሁለቱ: ጁፒተር እና ሳተርን በጣም ተቀራርበው ይሚታዩበት ነዉ። ክስተቱ በየ 19 አመት ከግማሽ ሁልጊዜ የሚከሰት ቢሆንም: ዛሬ በሚቀራረቡት ደረጃ የተቀራረቡት በዓለም ታሪክ በጣት የሚቆጠር ጊዜ ስሆን: የዛሬ 600 መቶ አመት እና ክርስቶስ ከመወለዱ ከ 7 አመት በፊትም ሁለቱ ከዋክብት ዛሬ እንደምሆነው: ተቀራርበው ነበር። ሳይንስ እንደዚህ አይነት ክስተቶችን የሚያብራራበት የራሱ መንገድ ያለው እንደሆነ ይታወቃል። በተለይ ደግሞ ናሳ: እንደስሙ: አሳች የሆነ ተቋም: እንደዚህ አይነት ክስተቶች ከሳይንስ ያለፈ ትንታኔ ልንሰጣቸው የማንችላቸው: መሆኑን አምነን እንድንቀበል እያደረገን ነዉ። ጨረቃ ቀይ ስትሆን የራሳቸውን ትንታኔ ይሰጣሉ: አስትሮይድ ምድርን ከመታት ወይም ሳይነካት በቅርበት ካለፈም የራሳቸውን ሳይንሳዊ ትንታኔ ተናግረው: ይሄው ነዉ ይሉናል። ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የቀረበ ግንኙነት ያለው: መንፈሳዊ ሰው ግን ሳይንስም ሆነ ናሳ የክስተቱን ሁኔታ ከማብራራት የዘለለ ከበስተጀርባ ያለውን ምክንያት እና መልእክት ማብራራት እንደማይችሉ ይረዳል። መንፈሳዊ ሰው "ሁሉን ይመረምራል" ይህ ካስፈለገ በህዋ ውስጥ ያሉ: እንቅስቃሴዎችንም ጭምር ያካትታል። የእግዚአብሔር ሕዝብ ግን "እውቀት በማጣት ጠፍቷል"። ጌታችን ኢየሱስ: ስለ ዘመን መጨረሻ እና ስለመምጣቱ ምልክት በጠየቁት ጊዜ አንዱ የተናገረው: ስለ ህዋ አካላት ነበር: ““ወዲያውኑ ከእነዚያ ከመከራው ቀናት በኋላ፣ ‘ፀሓይ ትጨልማለች፤ “ ‘ጨረቃ ብርሃኗን ትከለክላለች፤ ከዋክብት ከሰማይ ይረግፋሉ፤ የሰማይ ኃይላትም ይናጋሉ።’” — ማቴዎስ 24፥29 (አዲሱ መ.ት) የዛሬው ክስተት በቀጥታ: ይህን ትንቢት የሚፈጽም ነዉ እያልኩ አይደለም። ነገር ግን: አካላዊ ዓለም ለይ የሚሆነው ነገር መንፈሳዊ ዓለም ለይ እየሆነ ላለው ጠቋሚ ሆኖ እንደሚያገለግል አትርሱ። አካላዊው ዓለም የመንፈሳዊ ዓለም ነጸብራቅ ነዉ። የዛሬው ክስተት: ጁፒተር እና ሳተርን የመቀራረባቸው: ብዛት በመካከላቸው የሚቀረው ክፍተት 0.1 degree ብቻ ነዉ። ይህ በጥቅሉ በህዋ ውስጥ እና በምድር ላይ የሚያስከትለው ተጽእኖ: ምን እንደሆነ በሰዓቱ እና ከሁኔታው በኋላ የሚታወቅ ነዉ። አንዳንድ ሰዎች: የማያን ካላንደርም በዛሬው ቀን ማለቅ አመላክተው የዛሬው ክስተት የዓለም ፍጻሜ ልሆን እንደምችል ይናገራሉ። ነገር ግን ይህ የዓለም ፍጻሜ እንደማይሆን ቅዱሳን እናውቃለን: የቤተክርስቲያን መነጠቅ: የጥፋት ልጅ እርሱም የኃጢአት ሰው መገለጥ እና የጌታ ቀን ...ከመፈጸማቸው ቀድሞ ይህች ዓለም በአጠቃላይ እንደማትጠፋ እናውቃለን። የሆነው ሆኖ የእግዚአብሔር ልጆች: ጌታችን መድሃኒታችን የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ከመወለዱ ልክ ሰባት ዓመት በፊት የሆነው ይህ ክስተት ደግሞ ልሆን ነዉ: ከዚህ በኃላ ምድር ወደ አድስ ወቅት እየገባች እንደሆነ ጥያቄ የለው: የክርስቶስ አካል የሆነችው ቤተክርስቲያን ከዚህ በኋላ በየትኛውም ጊዜ ልትነጠቅ ትችላለች: ደግሞም ትነጠቃለች! ተዘጋጅተሃል!? ተዘጋጅተሻል!? ብዙ ዘመን የለንም: በክርስቶስ ለክርስቶስ እንኑር። ክስተቱን ሁላችንም በዓይናችን መመልከት የምንችለው ይሆናል: ዛሬ ማታ ፀሃይ ከጠለቀች በኃላ በስተ ደቡብ ምስራቅ ማየት ትችላላችሁ። በጣም ደማቅ ከዋክብት ነዉ የሚመስሉት። የእግዚአብሔር ልጆች የንጋት ኮከብ የሆነው ጌታች እና የምድር ብርሃን የሆነችው ሙሽራው ቤተክርስቲያን በቅርቡ ከ 0.1 ድግሪ በላይ ስለሚቀራረቡ የዚህ ትልቅ እና ዘላለማዊ ክስተት አካል ለመሆን ተዘጋጁ: ፀጋ ይብዛላችሁ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

እውነት! ስሙት! የእግዚአብሔር ልጆች @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“እውነትንም ታውቃላችሁ፤ እውነትም ነጻ ያወጣችኋል።”” — ዮሐንስ 8፥32 (አዲሱ መ.ት)

የምትሰሙትን ዛሬ ምረጡ! የምትሰሙት ድምጽ ነዉ ...የሚወስነው!! የአጋንንት ኤጀንት ከሆኑ የድምጽ ምንጮች: ራሳችሁን አፋቱ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

👉በመንፈስ መጸለይ “በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር #በመንፈስ_ጸልዩ፤...” — ኤፌሶን 6፥18 ✍️በመንፈስ መጸለይ ማለት ምን ማለት ነው? አይን ጨፍኖ እጆችን ወደ ሰማይ ዘርግቶ መጸለይ ይሆን? አይደለም! እነዚህ ድርጊቶች በጸሎት ጊዜ: ይፈጠሩ ይሆናል: በመንፈስ መጸለይ ማለት ግን ይሄ አይደለም: ብዙ ክርስቲያኖች ስለሚመስላቸው ነዉ። ታድያ በመንፈስ መጸለይ ማለት ምን ማለት ነው? በአጭሩ "በሌላ ልሳን የእናንተ መንፈስ" (human spirit) ስጸልይ ማለት ነዉ። መንፈስ ቅዱስ ሰይሆን የእናንተው "መንፈስ" በሌላ ቋንቋ ወይም በተለምዶ "በልሳን መጸለይ" ማለት ነዉ። ይህንን ጥቅስ በጥንቃቄ ስታነቡ "በልሳን ስትናገሩ" መንፈሳችሁ እየጸለየ እንደሆነ ታውቃላችሁ...“በልሳን ብጸልይ መንፈሴ ይጸልያል...” — 1ኛ ቆሮንቶስ 14፥14 አስተውሉ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ #መንፈሴ ይጸልያል ነዉ ያለው። በልሳን ስጸልይ መንፈሴ ይጸልያል: አእምሮዬ ግን ስለማይረዳው: ያለፍሬ ይሆናል። አእምሮዬ ያለፍሬ የሚሆን ከሆነ ታድያ ለምን "ዘወትር በልሳን ጸልይ" ተባልኩ? ምክንያቱም: በልሳን ስጸልይ "መንፈሴ ስለሚታነጽ" ነዉ። በልሳን ስትጸልዩ መንፈሳችሁን ቻርጅ እንደማድረግ ነዉ። ወድያው ሃይል ይሰማችኋል። እኔ በግል: በልሳን የምንጸልየው ሁልጊዜ ነዉ: ምክንያቱም "ሚስጥራትን" የማገኘው ከዚህ ልምምዴ ነዉ። በልሳን ስትጸልዩ ከዚህ ዓለም ውጪ የሆነ ሚስጥር ነዉ የምትናገሩት: በተለይ: የመተርጎም ስጦታ ካላችሁ: በየትኛውም ጊዜ: በሰማይ መረዳት ትችላላችሁ: “በልሳን የሚናገርስ ለእግዚአብሔር እንጂ ለሰው አይናገርም፤ የሚያስተውለው የለምና፥ በመንፈስ ግን ምሥጢርን ይናገራል፤” — 1ኛ ቆሮንቶስ 14፥2 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ: በልሳን ስለማናገር ልምምዱ የተናገረውን ተመልከቱ: “ከሁላችሁ ይልቅ በልሳኖች እናገራለሁና እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፤” — 1ኛ ቆሮንቶስ 14፥18 ሐዋርያው ከሁላችን በላይ በልሳን መናገር እንደምችል በግልጽ ነው የነገረን። ታድያ የአገልግሎት ስኬቱ: ያን የህል ብሆን ይገርማል!? 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ቅዱሳን በልሳን ስንጸልይ ለጨለማው ዓለም ልክ እንደዚህ ነዉ: የሚታየው: በከባድ ድንጋጤ ውስጥ ነዉ የሚወድቁት! 👉“በልሳን የሚናገርስ ለእግዚአብሔር እንጂ ለሰው አይናገርም፤ የሚያስተውለው የለምና፥ በመንፈስ ግን ምሥጢርን ይናገራል፤” — 1ኛ ቆሮንቶስ 14፥2 #When you don't understand what's happening blast in other tongues! And see what happens Next.😁🔥 -Archbishop DUNCAN williams💪 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ᴛ𝚑𝚎 ᴡɪsᴇ Ʀᴇᴀᴄᴛs 𝚘𝚗𝚕𝚢 𝚏𝚘𝚛 𝚝𝚑𝚎 ʀɪɢʜᴛ 𝚊𝚌𝚝𝚘𝚛. -𝓿𝓲𝓬𝓽𝓸𝓻 #𝚜𝚙𝚒𝚛𝚒𝚝𝚜𝚝𝚢𝚕𝚎

-ዘማሪ ቴዲ ታደሰ -ከሰማይ የሆነ ሰላም! -4 MB audio #እግዚአብሔር_ሌላ_እንዲሰጣችሁ_ስለሰጣችሁ_ነገር_አክብሩት! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

I want one thing " Hell empty and Heaven full" @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

እናንተ ራሳችሁ ተዓምራት ናችሁ! *********************** የእግዚአብሔር ልጆች: ምድር ለይ መሆናችሁ እና እንደማንኛውም ሰው: መመላለሳችሁ: ራሳችሁን ከሆናችሁት: እውነት ዝቅ አድርጋችሁ እንድታዩ እንዲያደርጋችሁ አትፍቀዱ! ምድር ለይ ስመላለሱ ከምታውቋቸው ሰዎች ፈጽሞ የተለያችሁ እና እጅግ የላቃችሁ ናችሁ! አዲስ ፍጥረት ናችሁ: ይህች ምድር ቀድሞ የማታውቀው አድስ የፍጥረት አይነት ናችሁ: የእግዚአብሔር ዘር በእናንተ አለ! ይህ ሁሉንም ለውጦታል። ከአምላክ የመወለድን ሚስጥር እና ክብር ጥልቅ ነዉ: መጽሐፍ ቅዱስ ከእግዚአብሔር ተወልዳችኋል ስለን በቀጥታ ከእግዚአብሔር ተወልዳችኋል ማለቱ ነዉ። ወላጃችን ሌላ አሳዳጊያችን እግዚአብሔር አይደለም: እግዚአብሔር ወልዶናል! የእግዚአብሔር ልጆች የኢየሱስ ሰላም ያለው: ሰማይ ከኢየሱስ ጋር ሰይሆን ምድር ከእናንተ ጋር ነዉ። ሰላሙን ትቶላችኋል! በፍርሃት ላይ ሳቁ! ከእግዚአብሔር ሌላ ማንም አያስደንግጣችሁ! እግዚአብሔር ያላችሁን ለመፈጸም ከሰይፈ ፊት እንኳ አታፈግፍጉ! ወደፊት እና ወደላይ ብቻ ነው ሕይወታችሁ! አሜን! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።” — ዮሐንስ 14፥27 የእግዚአብሔር ልጆች ከላይ የተቀመጠውን የንባብ ክፍል በጥንቃቄ ከተመለከታችሁት: ጌታችን የተናገረው እና ያደረገው በጣም የሚደንቅ ነዉ። ጌታ ይህንን የተናገረው ከሞቱ እና ከትንሳኤው በፊት ጥቅት ቀናት ቀደም ብሎ ነዉ: ወደ አብ ልመለስ እና ሊከብር መሆኑን አውቋል: ወደ ሰማይ መሄዱ ስለሆነ ከአብ ስወጣ ይዞት የመጣውን: ሰላሙን ይዞት ለመመለስ አልወደደም: ነገር ግን ሰላሙን ከደቀመዛሙርቱ ጋር ትቶት ለመሄድ ወሰኑ። ቃሉን በጥንቃቄ ተመልከቱ: #ሰላምን_እተውላችኋለሁ: ሰላሜንም እሰጣችኋለሁ ነዉ የሚለው። የራሱን ሰላም ነዉ ለደቀመዛሙርቱ ትቶልን የሄደው! ይህ የእርሱ ሰላም አለም እንደምሰጠው ሰላም: ከሁኔታዎች ጋር የተያያዘ ሰላም አይደለም። የአባት ሰላም ነዉ። #ኢየሱስ_ሰላሙን_ትቶልን_ነዉ_የሄደው ይህ ማለት የኢየሱስ ሰላም ያለው ከኢየሱስ ጋር ብቻ አይደለም: ከደቀመዛሙርቱም ጋር ነዉ። የእግዚአብሔር ልጆች ይህንን እውነት ስታውቁ: መጽሐፍ እንደዚህ የሚለው በእናንተም ይፈጸማል: “በፍርሃት ላይ ይስቃል፥ እርሱም አይደነግጥም፤ ከሰይፍም ፊት አይመለስም።” — ኢዮብ 39፥22 በወጀብ ውስጥ: መረጋጋት እና ፈገግ ማለት ትችላላችሁ። ምክንያቱም ነገር ሁሉ ተያይዞ ለእናንተ መልካም እንደምሰራ ታውቃላችሁ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የተወደዳችሁ የአምላክ ልጆች: ዛሬ ይህንን በሕይወታችሁ ላይ ለመናገር በነቢያት እሳት ተቀብቻለሁ! አገልጋዮች ብትሆኑ: ተማሪዎች ብትሆኑ: ነጋዴዎች ብትሆኑ: የፖሎቲካ ሰዎች ብትሆኑ በየትኛውም መድረክ ለይ ያላችሁ በኢየሱስ ስም በዘመናችሁ ሁሉ ራስ ከሆነው ከኢየሱስ ክርስቶስ የተነሳ ራስ ትሆናላችሁ እንጅ ጅረት አትሆኑም! እግዚአብሔር የጥበብና የመገለጥ መንፈስ ያበዛላችኋል! በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ ሰፊ እና አስተዋይ ልብ ሆኖላችኋል! መውጣትና መግባታችሁ በብዙ ጥበብ ይሆናል: የሰው አእምሮ የማያስበውን ተዓምራት መፍጠር ትጀምራላችሁ: የምድርን ከፍታዎች የተቀደሱ እግሮቻችሁ ይረግጣሉ: በዚህ ሁሉ የተባረከው ጌታ በሕይወታችሁ ልቆ ይታያል!!!!!አሜን። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

sticker.webp0.26 KB

ስሙት የእግዚአብሔር ልጆች: ሚስጥር ነዉ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

That's who Jesus is #way_maker #miracle_worker #promise_keeper #light_in_the_darkness! 👉And He will do it for you NOW! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

““ቃሌ እንደ እሳት፣ ድንጋይንም እንደሚያደቅ መዶሻ አይደለምን?” ይላል እግዚአብሔር።” — ኤርምያስ 23፥29 (አዲሱ መ.ት) @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ғᴏʟʟᴏᴡ ᴛʜᴇ sᴄʀɪᴘᴛ! 👉𝚝𝚑𝚎 𝚜𝚌𝚛𝚒𝚙𝚝 𝚜𝚊𝚢𝚜, “Recompense to no man evil for evil. Provide things honest in the sight of all men.” ᴄʜɪʟᴅ ᴏғ ɢᴏᴅ 𝚎𝚒𝚝𝚑𝚎𝚛 𝚐𝚘𝚘𝚍 𝚘𝚛 𝚋𝚊𝚍 𝚙𝚎𝚘𝚙𝚕𝚎 𝚊𝚛𝚎 𝚙𝚕𝚊𝚢𝚒𝚗𝚐 𝚝𝚑𝚎𝚒𝚛 𝚙𝚊𝚛𝚝 𝚒𝚗 𝚝𝚑𝚎 𝚜𝚌𝚛𝚒𝚙𝚝. 𝚢𝚘𝚞 𝚜𝚑𝚘𝚞𝚕𝚍 𝚙𝚕𝚊𝚢 𝚢𝚘𝚞𝚛𝚜! ʟᴏᴠᴇ 𝚎𝚟𝚎𝚛𝚢𝚘𝚗𝚎! ʙᴇ ᴋɪɴᴅ 𝚝𝚘 𝚎𝚟𝚎𝚛𝚢𝚘𝚗𝚎! ғᴏʀɢɪᴠᴇ 𝚎𝚟𝚎𝚛𝚢𝚘𝚗𝚎! 𝚝𝚑𝚊𝚝 𝚒𝚜 𝚠𝚑𝚘 𝚢𝚘𝚞 𝚊𝚛𝚎 𝚒𝚗 𝚝𝚑𝚎 𝚜𝚌𝚛𝚒𝚙𝚝. #sᴘɪʀɪᴛ_sᴛʏʟᴇ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

TheDeepThingsOfGod - Статистика и аналитика Telegram-канала @thedeepthingsofgod