TheDeepThingsOfGod
Открыть в Telegram
1 810
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 день
Архив постов
1 810
የሰባት ቀን ጾምና ጸሎታችንን ጨርሰናል። መጸለይ እና መጾም ግን የሚያበቃ አይደለም፥ ከእግዚአብሔር ጋር የሚሰሩ ሰዎች ሁሉ ጸሎትና ጾም ባሕላቸው ነዉ።
አብራችሁኝ የጾማችሁ እና የጸለያችሁ ሁሉ 2014 ከእግዚአብሔር ጋር ለመሄድ እና ለመስራት እንድትችሉ ስለእናንተ እጸልያለሁ።
1 810
ከእግዚአብሔር በተቃራኒው የሚደረግ ጉዞ (ሁልጊዜ ወደታች)
~ከተራራማው ጋትሔፌር እስከ ባሕር ጥልቅ!
እግዚአብሔር ነቢዩ ዮናስን በተራራማው በዛብሎን ምድር በጋትሔፌር እያለ ወደ ነነዌ በመሄድ የፍርድን ቃል በጆሮአቸው እንዲናገር አዘዘው፥ ዮናስ ግን እግዚአብሔር ከነገረው በተቃራኒው በደቡብ ምዕራብ ወደምትገኘው ወደ ተርሴስ ለመሄድ እና ከእግዚአብሔር ለመኮብለል ጉዞውን ጀመረ። ነቢዩ ከእግዚአብሔር በተቃራኒው ለመሄድ ከወሰነበት ጊዜ ጀምሮ ጉዞው ሁሉ ወደታች ሆነ።
እግዚአብሔር መጀመሪያ የተናገረው በተራራማው ሃገር በጋትሔፌር ነበር። ነቢዩ ከእግዚአብሔር በተቃራኒው ለመሄድ ከወሰነ በኋላ ወደ ኢዮጴ ወረደ፥ በመቀጠልም ወደ ባሕር ዳርቻው ወረደ ፥ ከዛም ዋጋ ከፍሎ ወደ ተርሴስ ለመኮብለል በመርከብ ተሳፈረ። በጣም የሚደንቀው መርከቢቱ ውስጥም ወደታችኛው ክፍል ወርዶ ተኛ፥ ይሄ ብቻ አይደለም በኋላ መርከቢቱ ስትናወጥ እና የነውጡ ምክንያት እርሱ እንደሆነ ስታወቅ፥ ከመርከቧ አስወጥተው ወደታች ወደ ባሕር ውስጥ ጣሉት፥ በዚህ አላበቃም ከባሕሩ ላይ ተንሳፎ እላይ አልቀረም እየዋኘም ወደ ዳርቻው አልወጣም ነገር ግን ወደ አሳ ሆድ ውስጥ ገባ፥ ይህንን በራሱ ቃል የገለጸው እንደዚህ በማለት ነበር:
ዮናስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³ ጥልቅ ወደ ሆነው፣ ወደ ባሕሩ መካከል ጣልኸኝ፤ ፈሳሾችም ዙሪያዬን ከበቡኝ፤ ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ፣ በላዬ አለፉ።
⁴ እኔም፣ ‘ከፊትህ ጠፋሁ፣ ነገር ግን እንደ ገና፣ ወደ ቅዱስ መቅደስህ፣ እመለከታለሁ’ አልሁ።
⁵ ውሃ እስከ ዐንገቴ አጠለቀኝ፤ ጥልቁም ከበበኝ፤ የባሕርም ዐረም በራሴ ላይ ተጠመጠመ።
⁶ ወደ ተራሮች መሠረት ሰመጥሁ፤ የምድርም በር ለዘላለም ተዘጋብኝ፤ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ አንተ ግን ሕይወቴን ከጒድጓድ አወጣህ።
ከእግዚአብሔር በተቃራኒው መሄድ መቼም የሚያዋጣ አይደለም። መታዘዝ ከሚያስከፍለው ዋጋ በላይ አለመታዘዝ ዋጋ ያስከፍላል።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ክርስቲያኖች በአፍጋኒስታን😭
በአፍጋኒስታን ከምድር በታች የነበረችው የክርስቶስ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን አሁን ወደቤት ሄዳለች ከጌታችን ጋር ናት።
በአፍጋኒስታን ከምድር በታች የነበሩ ቅዱሳን ትላንት ለእግዚአብሔር ቃልና ለኢየሱስ ክርስቶስ ምስክር ተሰውተዋል። ከሰዓታት በፊት ቅዱሳን ለመጸለይ ከምድር በታች በለ መሰብሰቢያ ተገናኝተው ነበር፥ በስልክም ውጭ ካሉ ወንድሞች ጋር ግንኙነት ነበረቸው።
በዚያ መሰብሰቢያ የነበረች አንድ እህት ከመሰዋታቸው በፊት በስልክ የተናገረችው የመጨረሻ ቃል: 'ጸሎታችሁ እየተሰማን ነው፥ መለኮታዊ የሆነ ድፍረት አብሮን ነው እናም በመንፈስ ቅዱስ እየዘመርን ነው፥ ሕጻናት እንኳ ኢየሱስን አንክድም እያሉ ነበር...' ይህንን በስልክ በመናገር ላይ እያለች ከፍተኛ የመሳሪያ ድምጽ እና የጩኸት ድምጽ ተሰማ።
እግዚአብሔር ይመስገን፥ በብዙ ደስታ ተሞልተው ወደ ጌታቸው ተሰብስበዋል።
እባካችሁ በአፍጋኒስታን ላሉ ቅዱሳን እንጸልይ፥ በከባድ መከራ እና ግዲያ ውስጥ ናቸው።😭
1 810
“እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው።”
— ማቴዎስ 4፥4
1 810
የእግዚአብሔር ልጆች በጾምና ጸሎት ጊዜ መረሳት የሌለባቸው ነጥቦች:
1-ምግብ አለመብላት አንድን ሰው መንፈሳዊ አያደርገውም።
~በጾምና ጸሎት ጊዜ መንፈሳዊ የሚያደርገን ምግብ መብላት ከማቆማችን በላይ መንፈሳዊ ምግብ( የእግዚአብሔር ቃል ) መብላት መጀመራችን ነዉ። ስለዚህ አንድ ሰው ምግብ መብላት ለ 7 ቀን ቢያቆም እና በእነዚህ 7 ቀናት የእግዚአብሔርን ቃል ባይመገብ ከሰባት ቀን በኋላ በስጋም በመንፈስም ደካማ ሆኖ ይጨርሳል። ስለዚህ በእነዚህ የጾምና የጸሎት ቀናት የእግዚአብሔርን ቃል ማንበብ፣ ማሰላሰል እና በአንደበት መናገር ምግብ ከለመብላታችን የላቀ ዋጋ እና ውጤት ያለው ነዉ።
2- በጾምና በጸሎት ጊዜ ከምግብ የመራቃችንን ያህል መንፈሳዊ ከልሆኑ መረጃዎች( Informations) መራቅ ትልቅ መንፈሳዊ ትርፍ ያለው ነዉ። ከመጽሐፍ ቅዱሳችን እና መንፈሳዊ ትርፍ ከላቸው ነገሮች በስተቀር በአይናችን እና በጆሮዎቻችን በር ወደ አእምሮአችን እንዳይገቡ መጠበቅ አለብን። ለምሳሌ ፊልም፣ መንፈሳዊ ያልሆኑ መጽሐፍት፣ ዜና... ወዘተ መስማት እና ማየት የለብንም። በጾምና በጸሎት ቀናት ሙሉ በሙሉ ማለት በሚቻል ደረጃ ትኩረታችን መሆን ያለበት እግዚአብሔር ላይ ነዉ። እራሳችንንም በእግዚአብሔር ፊት ትሁት የምናደርገው በዚህ መልኩ ነዉ።
1 810
የጾምና የጸሎቱ አካል የሆናችሁ የእግዚአብሔር ልጆች፥ ዛሬ ማታ መሶብ አስጨንቃችሁ ብሉ😂፥ ያው ከምግብ ጋር የምንገናኘው ነገ ማታ ነው ለማለት ነው😂😂😂
JUST FOR FUN🥰
“እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው።”
— ማቴዎስ 4፥4
1 810
“ቃሉን ስበክ፤ ጊዜው ቢመችም ባይመችም ዝግጁ ሁን፤ በታላቅ ትዕግሥትና በማስተማር አቅና፤ ገሥጽ፤ አበረታታም።”
— 2ኛ ጢሞቴዎስ 4፥2
ከፀሀይ በታች ለሁሉም ጊዜ አለው፥ ነገር ግን አንድ ነገር ብቻ ጊዜ የለው እርሱም 'የወንጌል ስብከት ነዉ'።
ወንጌልን ለሰዎች ለማጋራት ሁሉም ጊዜ ትክክለኛ ነዉ!
1 810
🔥አብራችሁኝ ለሰባት ቀን የምትጾሙ እና የምትጸልዩ የእግዚአብሔር ልጆች ማታ 3 ሰዓት ከመሆኑ በፊት የጸሎት ርዕስ እና መልእክት እልክላችኋለሁ።🔥
1 810
LIFE IS NOT A GAME DON'T PLAY WITH IT, GET SERIOUS ABOUT LIFE. COUNT THE COST, PAY THE PRICE AND BE A MAN THAT GOD USES!
-victor
ሕይወት ጫዋታ አይደለችም፥ በሕይወትህ አትጫወት፥ ትርጉም ያለው ኑሮ ለመኖር የሚጠይቀውን ሒሳብ ቁጠር የሚከፈለውን ዋጋ ክፈል እና እግዚአብሔር የሚጠቀመው ሰው ሁን።
1 810
ጸሎት ~ከልጅ ዳን ጋር፥ በእምነት አብረን እንጸልይ የሆነ ነገር ያገኛችኋል🔥!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ልጅ ዳን ገና 18 አመቱ ነዉ ነገር ግን ትልቅ ተማሪ እና አስተማሪ ነዉ። እስከመጨረሻው ስሙት፥ ለምታውቋቸው አገልጋዮች ሁሉ ሼር እንድታደርጉ በጌታ ፍቅር እጠይቃለሁ።
1 810
ክፍል 3
~"የእግዚአብሔርን ክብር ማየት"
የእግዚአብሔር ክብር እንዴት ማየት ይቻላል?
~ልጅ ዳን 🔺🀄️🀄️🀄️🀄️🀄️🀄️🀄️🔺
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
ክፍል 3 ~የእግዚአብሔር ክብር እንዴት ማየት ይቻላል?
በልጅ ዳን የተዘጋጀ ትምህርት የመጨረሻ ክፍል ነገ ይለቀቃል። ከዛ በኋላ የ 7 ቀን ጾም ጸሎት እንጀምራለን፥ አዲሱን አመት በክብር እንጀምራለን።
1 810
"የእግዚአብሔር ክብር ምንድነው?" ይሄንን እስከመጨረሻ ስሙ። ደግሞም እናንተ ለምታውቋቸው የትም በምንም ለሚያገለግሉ ሰዎች ሁሉ share አድርጉ። ክፍል ሦስትን ከመልቀቄ በፊት ከላይ ያሉትን ደጋግማችሁ ስሙ፥ ላልሰሙ አሰሙ፥ በትህትና የምትታዘዙኝ የሚያስፈልጋችሁ ፀጋ ሁሉ ይብዛላችሁ።
