ru
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Открыть в Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Больше
1 810
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 день
Архив постов
ሮሜ 1፥18-32 (የሰው ዘር ሁሉ የውድቀት ጥልቀት) ከላይ ባሉት ቁጥሮች ውስጥ የሰው ዘር ሁሉ የውድቀት ጥልቅ በግልጽ ተገልጻል፥ የሰው ልጅም ለውድቀቱ ማመካኛ(Justification) በማቅረብ ከእግዚአብሔር ቁጣ ራሱን መዳን እንደማይችል እንረዳለን። የሰዎችን የውድቀት ጥልቀት የሚለውጠው የእግዚአብሔር የፀጋ ክብር ከፍታ ብቻ ነው። @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ ጥናት ሦስት ሮሜ ምዕ 1፥18-32 ደረጃ 1 የእግዚአብሔር መገለጥ ፥ የሰዎች እምቢተኝነት እና ውጤቱ። ሁለት የተገለጡ የእግዚአብሔር ባሕሪያት፥ ሁለት የተፈለጉ ምላሾች ፥ ሁለት የእምቢተኝነት ውጤቶች ፥ ሁለት ዉድቀቶች። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

በእግዚአብሔር የተወደዳችሁ ዛሬ ማታ 3 ሰዓት ላይ በሮሜ ጥናታችን ከፍ ወዳለው መድረክ(የመንፈስ ሕይወት) ለመድረስ ከሚረዱን አስር ደረጃዎች የመጀመሪያውን ደረጃ እናያለን። ሮሜ ምዕ 1፥1-17 ያለውን ጥናት ያልሰማችሁ ስሙ ደጋግማችሁ ስሙ፥ ለሌሎችም አጋሩ።

ጥያቄ---- ሐዋሪያው ጳውሎስ ስለሮሜ ቤተክርስቲያን እግዚአብሔር አመስግኗል ምክንያቱም በኢየሱስ ያላቸው እምነት በዓለም ሁሉ በመሰማቱ ነው። እኔ የምጠይቃችሁ ጥያቄ:--- እንዴት ይመስላችኋል እምነታቸው በዓለም ሁሉ የተሰማው? እንዴትስ ነው የእኛም እምነት በያለንበት ዓለም ሁሉ እንዲሰማ ማድረግ የምንችለው? በComment section ወይንም በዚህ ግሩፕ ሃሳባችሁን አስቀምጡ👉 @TheMysteriesOfGod

ተጨማሪ ትንተና--- በሮሜ 1፥16-17 ሮሜ 1 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁶ በወንጌል አላፍርም፤ ምክንያቱም ለሚያምን ሁሉ ለድነት የሚሆን የእግዚአብሔር ኀይል ነው፤ ይህም በመጀመሪያ ለአይሁድ፣ ቀጥሎም ለአሕዛብ ነው። ሐዋሪያው በወንጌል የማያፍርበት ምክንያት ምንድነው? ወንጌል "የእግዚአብሔር ሃይል" በመሆኑ ነው። በሃይል የሚያፍር አንድም ሰው የለም እንደውም የሰው ልጅ አጥብቆ ከሚፈልጋቸው ነገሮች ትልቁ ሃይል ነው። በተጨማሪም ወንጌል የሚያድን ሃይል እንደሆነ ይገልጻል፥ የሚያወድም ወይም የሚያጠፋ አይደለም። የትኛውም ክርሲቲያን በዚህ መመካት እንጂ ማፈር የለበትም። ክርሲቲያን በወንጌል የሚያፍር ከሆነ ግን የዘነጋው አንድ ነገር 'ወንጌል የእግዚአብሔር አዳኝ ሃይል' መሆኑን ነዉ። በሁለቱ ቁጥሮች ውስጥ ትልቅ ትኩረት የሚሻው ቃል "እምነት" የሚለው ቃል ነው። በሁለቱ ቁጥሮች ውስጥ አራት ጊዜ ጥቅም ላይ መዋሉ ለዚህ ነው። እምነት የሚያድነውን የእግዚአብሔርን ሃይል የምንቀበልበት እና በእግዚአብሔር ፊት መጽደቅ የምንችልበት ብቸኛው መንገድ ነው። ¹⁷ በወንጌል የእግዚአብሔር ጽድቅ ተገልጦአልና፤ ጽድቁም ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በእምነት የሆነ ነው፣ “ጻድቅ በእምነት ይኖራል” ተብሎ እንደ ተጻፈው። ከላይ ባለው ቁጥር ሐዋሪያው ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት መጽደቅ የሚችሉት ወንጌልን (የኢየሱስን ለኃጢአተኞች መሞት፣ መቀበርና ከሙታን መነሳት) በማመን እንደሆነ ይገልጻል። ሌላው ከዚህ የምንረዳው በመሰረታዊነት እውነተኛው የእግዚአብሔር ወንጌል ጽድቅን የሚያስገኝ መሆኑን ነው፤ ሌሎች ነገሮች ሁሉ ጽድቅን የሚከተሉ ናቸው። በቁጥሩ መጨረሻም ሐዋሪያው በእምነት የመጽደቅ ትምህርት እርሱ ያመነጨው ሃሳብ እንዳልሆነ ለማስረገጥ ከነቢዩ ዕንባቆም መጽሐፍ ይጠቅሳል። ““... ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል።” — ዕንባቆም 2:4 (አዲሱ መ.ት) ይህም የጳውሎስ ወንጌል የብሉይ ቅዱሳት መጽሐፍትን መነሻው ያደረገ እንደሆነ የሚያስረዳ ነው። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ቅዱስ አባት ሆይ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በቤተክርስቲያን ከትውልዶች ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ለአንተ ይሁን፤ አሜን።

☝️ሮሜ ምዕ 1፥1-17 ስሙት!

አንድ ነገር ፈልጎ ሁሉን ማግኘት በዚህ ምድር ሰዎች የሚፈልጓቸው እጅግ ብዙ ነገሮች አሉ፥ ሆኖም ሰዎች በቦታና በዘመን የተወሰኑ በመሆናቸው እያንዳንዱን የሚያስፈልጋቸውን ነገር እያፈላለጉ አግኝቶ መጨበጥ የማይቻል ነው። ነገር ግን አንድ ነገር ፈልጎ አስፈላጊውን ሁሉን ማግኘት የሚቻልበት መንፈሳዊ መንገድ አለ! “ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።” — ማቴዎስ 6፥33 ብዙ ነገሮች መፈለግ አቁሙ! የእግዚአብሔርን መንግስት(ጽድቅ) መፈለግ ጀምሩ። ይሄ ነው መንፈሳዊው መንገድ። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ከሮሜ ጥናት የተወሰደ...(1) እንደ አንድ አገልጋይ በትክክል መረዳት ያለባችሁ ሦስት መሰረታዊ ነገሮች። 1) ወንጌል 2) ራሳችሁን ( እግዚአብሔር ማን እንዳደረጋችሁ እና ምን እንድትሰሩ እንደሚፈልግ ማወቅን ያካትታል። 3) የምታገለግሏቸውን ሰዎች። ለእነዚህ ሦስት ጥያቄዎች ጳውሎስ የነበረው መልስ:- 1ኛ ወንጌል: ኢየሱስ ክርስቶስ ለኃጢአተኞች መሞቱ፥ መቀበሩና ከሙታን መነሳቱ። 2ኛ ስለራሱ: የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ፥ ሐዋሪያ እና ለእግዚአብሔር ወንጌል የተለየ። 3ኛ የሚያገለግላቸው ሰዎች: የክርስቶስ ለመሆን የተጠሩ፥ ቅዱሳን፥ በእግዚአብሔር የተወደዱ እና እምነታቸው በዓለም ሁሉ የተሰማ። @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ ጥናት ሁለት ሮሜ ምዕራፍ 1፥1-17 ጳውሎስ ፥ ወንጌል እና በሮሜ ያሉ ክርሲቲያኖች። ሁልጊዜ ዕሮብ እና እሁድ @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ከሮሜ ጥናት መግቢያ የተወሰደ ጽድቅ አስፈላጊ እና ትልቅ ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ነው ወይ? የሚል ጥያቄ ይነሳ ይሆናል። መልሱ የሚሆነው አዎ ከምንም በላይ ጽድቅ አስፈላጊ ነው! የሚል ነው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዛሙርትን ከፍላጎቶቻቸው ዝርዝር ውስጥ የመጀመሪያውን ስፍራ መያዝ የለበት ጽድቅ እንደሆነ አስተምሯል። “ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፤ ይጠግባሉና።” — ማቴዎስ 5፥6 (አዲሱ መ.ት) ብዙዎቻችን የተለያዩ ነገሮች አጥብቀን እንፈልጋለን መንፈሳዊ ስጦታ፥ ሃይል፥ ልህቀት፥ ብልጽግና፥ ስኬት፥ እውቀት፥ በረከት... እንዚህን ሁሉ መፈለግ ትክክል ነው፥ ነገር ግን የብዙዎቻችን የፍላጎት ዝርዝር ውስጥ ጽድቅ አናሳ ስፍራ ያለው ወይንም ደግሞ ፈጽሞ የተዘነጋ መሆኑ ነው ትልቁ ችግር። ወንድሞቼ እና እህቶቼ በእናንተ የፍላጎት ዝርዝር ውስጥ ጽድቅ ምን ያህል ቦታ አለው? በመጀመሪያ መፈለግ ያለብን ጽድቅን ነው፥ ሌሎች ነገሮች ሁሉ ጽድቅን የሚከተሉ ናቸው። “ከሁሉ አስቀድማችሁ ግን የእግዚአብሔርን መንግሥትና ጽድቁን እሹ፤ እነዚህ ሁሉ ይጨመሩላችኋል።” — ማቴዎስ 6፥33 (አዲሱ መ.ት) ከዚህ በኋላ የፍላጎት ዝርዝራችሁ ቅደምተከተሉን የጠበቀ እንደሚሆን እምነቴ ነው፥ ጽድቅን በመጀመሪያ የሚፈልጉ እና የሚጠሙ በእግዚአብሔር ይሞላሉ። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የተወደዳችሁ ነገ ማታ 3 ሰዓት ላይ የሮሜ መጽሐፍ ምዕራፍ አንድን እንጀምራለን፥ መግቢያውን ያልሰማችሁ ስሙ ለሌሎችም ሼር አድርጉ።

ከላይ ባለው መግቢያ የተካተቱ ሃሳቦች 1- የሮሜ መልእክት የተጻፈበት ጊዜና ቦታ በተጨማሪም በማን ተጻፈ። (57 ዓ.ም ፥ ቆሮንቶስ ፥ ሐዋሪያው ጳውሎስ) 2-የሮሜ መጽሐፍ ማዕከላዊ ሐሳብ። (ጽድቅ) 3-የሮሜ መጽሐፍ ለመረዳት በሚመች መልኩ መክፈል። ( መጽሐፉ በጠቅላላ በሦስት ይከፈላል ከምዕ 1 እስከ ምዕ 8 /ክፍል አንድ/ ፥ ከምዕ 9 እስከ ምዕ 11 /ክፍል ሁለት/ ፥ ከምዕ 12 እስከ ምዕ 16 /ክፍል ሦስት/) የክፍል አንድ ትኩረት - ወንጌል። የክፍል ሁለት ትኩረት - መለኮታዊ ምርጫ። የክፍል ሦስት ትኩረት - በቀደሙት ምዕራፎች የተገለጠውን እውነት በሕይወት መተግበር። 4- ክፍል አንድን /ከምዕ 1 እስከ ምዕ 8 / ድረስ ያለውን ለመረዳት የተመቸ እንዲሆን በሁለት ክፍል መክፈል። የመጀመሪያው ክፍል- /ከምዕ 1- ምዕ 7/ ድረስ ያለው ነው። ይሄ ክፍል አስር ደረጃዎችን(ትምህርቶች) ይዟል። ሁለተኛው ክፍል- ምዕራፍ 8 ነው። ይሄ በመጀመሪያው ክፍል ያሉ ደረጃዎችን ወጥተን ስንጨርስ የምናገኘው መድረክ ወይም መዳረሻ /የመንፈስ ሕይወት/ ነው። ምዕራፍ ስምንት ላይ ለመድረስ የግዴታ በቀደሙት ሰባት ምዕራፎች ውስጥ ማለፍ ይኖርብናል። @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ መጽሐፍ ጥናት አንድ~ መግቢያ አንድ። -Victor ቀጣዩን ለመስማት 👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ሮሜ🔥 ተዘጋጁ ከ 2 ደቂቃ በኋላ😁 Group ላላችሁኝ ወዳጆች👇 https://t.me/TheMysteriesOfGod

ሮሜን ለሚያጠኑ ሁሉ የጸሎት ነጥቦች በእምነት አብራችሁኝ ጸልዩ! @TheDeepThingsOfGod

ስለ ኢትዮጵያ መጸለይ እንዳትረሱ! ቤተክርስቲያን ኢትዮጵያ ውስጥ በሰላም መኖር የምትችለው እና የምትታነጸው ኢትዮጵያ ሰላም ስትሆን ነው። ባለፈው አመት የካቲት ወር ላይ እግዚአብሔር ስለኢትዮጵያ በራዕይ ከሳየኝ በኃላ 5 የጸሎት ርዕሶች ሰጥቻችሁ ነበር በእነርሱ ላይ መጸለይ ቀጥሉ። የሮሜ ጥናት በእቅዱ መሰረት ነገ ማታ 3 ሰዓት እንጀምራለን።

ሮሜ የሮሜ መጽሐፍ በወንጌል የተገኘውን ጽድቅ ከሌሎች ቅዱሳት መጽሐፍት በበለጠ በመተንተን የሚያስተምር እና ቅዱሳንን በእግዚአብሔር እውነት እውቀት የሚያንጽ ነዉ። መልእክቱ መሰረታዊ የወንጌል እውነቶችን አንዴ በመደበኛ አገላለጽ የብሉይ ቅዱሳት መጽሐፍትን በመጠቀም፥ ሌላ ጊዜ ደግሞ የማሰብ አቅማችንን በሚፈታተኑ በአመክንዮ በቀረቡ ሃሳቦች ያስተምራል፥ በሌላ በኩል የሰውን ዘር የውድቀት ጥልቀት በማሳየት የሚፈትን፥ ከዛም የእግዚአብሔርን የፀጋ ክብር ከፍታ በማሳየት ደግሞ መንፈስን የሚቀሰቅስ እና የሚያበረታ በመሆኑ መልዕክቱን በጸሎትና በብዙ ትዕግስት ከልተማርነው ውስጡ የተሰወረውን ሕይወት እና መንፈስ ለመረዳት የበቃን አንሆንም፥ ስለዚህ በማጥናት ሂደት ውስጥ ሁላችንም ትሁት እና ለመንፈስ ቅዱስ ረዳትነት የተዘጋጀን እንድንሆን ይገባል። መንፈሱን በልባችን ያኖረ፥ የቃሉን ደጆች የሚከፍትልን፥ እውነቱን የሚያበራልን እና በስርዓቱ እንድንሄድ የሚያበረታን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባትና አምላክ ይባረክ፥ አሜን። @TheDeepThingsOfGod

ሮሜ 🔥 ተዘጋጁ! እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ ሕያው ቃሉ አእምሮአችሁን እያደሰ ፈጽሞ ይለውጣችኋል፥ በሮሜ እውነት ከተቀደሳችሁ በኋላ ሌላ ሰው ትሆናላችሁ! ቃሉን በትህትና ለመቀበልና በእምነት ለመታዘዝ ተዘጋጁ። እኔ በግሌ ለማስጠናት እየተዘጋጀሁ ቃሉ እንደ እሳት🔥 በመንፈሴ እየነደደ ነው።

ሰላም ለእናንተ ይሁን የአምላክ ልጆች! የሮሜን መልእክት ጥናት በድምጽ እንዲቀርብ የሚፈልጉ ብዙዎች ቢሆኑም፥ በጽሑፍም እንዲቀርብ የሚፈልጉ በመኖራቸው እንደአስፈላጊነቱ በድምጽና በጽሑፍ የማቀርብ ይሆናል። በድምጽም በጽሑፍም የሚቀርበው የእግዚአብሔር ቃል በመሆኑ አእምሮን የሚያድስ እናም ሕይወትን የሚለውጥ እንደሚሆን ጥርጥር የሌለበት ጉዳይ ነው፥ ስለዚህ በትህትና ቃሉን ለመቀበልና በእምነት ለመታዘዝ እንዘጋጅ። ጥናታችንን ከፊታችን ያለው እሁድ እንጀምራለን፥ ለሌሎች ሼር በማድረግ የእግዚአብሔር መንግስት እናገለግል። @TheDeepThingsOfGod