TheDeepThingsOfGod
Открыть в Telegram
1 810
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней
Архив постов
1 810
👉የማመናችን ግብ
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች: ይህንን በጥልቀት እንድታውቁ እወዳለሁ: በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ማመናችን ግልጽ የሆነ ግብ ያለው: መንፈሳዊ ጉዞ ነዉ: ያማንን እኛ ይህ ግልጽ የሆነ ግብ ሁልጊዜ ከፊታችን ይታየናል: ይህንንም ለመያዝ: ሸክም ሆና የሚተበትበንን ነገር ሁሉ እየጣልን: ወደ ፊት እንሄዳለን። ኢየሱስን ያመንነው ጴንጤ ወይንም ኦርቶዶክስ ወይንም ካቶሊክ ሆነን በየእሁዱ ቤተክርስቲያን ለመመላለስ አይደለም! ወይንም የአንድ ተቋም አበል ሆነን: በተቋሙ መርህ እና ስርዓት እየሄድን: በኃይማኖተኝነት መንፈስ እንድንመላለስ አይደለም!
👉ያመንነው ነቢይ ወይም ሐዋርያ ወይም አስተማሪ...ዘማሪም ለመሆን አይደለም: እነዚህ ሁሉ እግዚአብሔር እንደወደደ በሕይወታችን የሚሰራቸው ናቸው። ከእነዚህ ሁሉ የላቀ ያመንበት ምክንያት አለ: ይህም እውነተኛው የእምነታችን ግብ ነዉ!
👉በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ያመንንበት ምክንያት ይህ ነዉ: በኃጢአት ምክንያት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጠን #የመለኮቱ_ባሕርይ_ተካፋዮች ለመሆን ነዉ! ይህ በጣም የሚያስደንቅ ነዉ: የማይገባን ብሆንም እግዚአብሔር በፀጋው የተገባን አድርጎ ቆጥሯል! በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ባለ በእምነትም ይህንን አድርጎልናል! የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች: ይህንን እውነት በጥልቀት አሰላስሉ: "የመለኮት ባሕሪ ተካፋይ!"
👉መጽሐፍ ለዚህ ነዉ: "እግዚአብሔርን ለመምሰል ራስህን አስለምድ" የሚለው: በዚህ በአድሱ የመለኮት ባሕሪይ ለማዳግ: በየቀኑ ራሳችሁን አስለምዱ! ክርስቶስን ራሱን እስክትመስሉት ፍጹም ተለወጡ። አስተውሉ ይህንን ለማድረግ የምያስፈልገውን ሁሉ የመለኮቱ ሃይል በገዛ ክብሩና በበጎነቱ ሰጥቶናል! አንድ ሕፃን ስወለድ: ቤተሰዎቹን የመምሰልን አቅም: በመወለድ ብቻ እንደሚካፈል: ከእግዚአብሔር የተወለደም እንደዚሁ ነዉ: ነገር ግን ህጻኑ በተካፈለው እና ውስጡ ባለው ባሕሪይ ማደግ ካለበት ከእናንተ ጡት ወተት ጀምሮ እስከ ጠንካራ ምግብ ድርስ በጊዜ ህደት ይመገባል: ከእግዚአብሔር የተወለደም እንደዚሁ ነዉ: በተከፈለው እና ውስጡ ባለው የእግዚአብሔር ባሕሪይ ማደግ ካለበት: ከመጀመሪያዎቹ መንፈሳዊ እውነታዎች ጀምሮ ፍጹም እስከሆነው መንፈሳዊ እውነት በመመገብ ያድጋል! እመኑ! አድርጉ!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
Don't miss this❗️❗️❗️
ዛሬ ማታ 3:00 ጀምሮ #አምስተኛ ዙር በ ThingsOfGod~Group: ፈጹም ለውጥን (Transfiguration) እንዴት መለማመድ እንደምንችል #መንፈስ ያስተምረናል: ደግሞም እንጸልያለን! በዘመን መጨረሻ የእግዚአብሔር ሃሳብ ፍጹም የተለወጡ እና እንደ ክርስቶስ የሆኑ ልጆቹን በዓለም ሁሉ ላይ መግለጥ ነዉ!🔥
@TheMysteriesOfGod
@TheMysteriesOfGod
1 810
👉በፍጥነት ንዱ🔥! Drive furiously!
“ሰላዩም፦ ደረሰባቸው፥ ነገር ግን አልተመለሰም #በችኰላ_ይሄዳልና_አካሄዱ_እንደ_ናሜሲ_ልጅ_እንደ_ኢዩ_አካሄድ_ነው_ብሎ_ነገረው።”
— 2ኛ ነገሥት 9፥20
☝️☝️☝️ ይህ ንባብ እግዚአብሔር በበቀል ቅባት ስለቀባው ስለ #ኢዩ ነዉ: እግዚአብሔር በዚህ የበቀል ቅባት የሚቀባው አንድ ሰው በእስራኤል ስፈልግ #በችኮላ_የሚሄድ(በፍጥነት_የሚነዳ) ሰው ነበር የፈለገው። ምክንያቱም በጊዜው በእስራኤል ምድር መቀጣት ያለበት አመጽ: በቀል ማግኘት የነበረበት የነቢያት ደም ነበር: ይህንን መፈጸም የሚችል ደግሞ: በፍጥነት የሚነዳ ነዉ: መንገዱ ላይ ያለውን ሁሉ የለምንም ርህራሄ #የሚገጭ እንጅ ከእግዚአብሔር ጠላቶች ጋር የሚቻቻል አልነበረም። ለዚህ ነዉ እግዚአብሔር በእስራኤል ምድር ፈልጎ ኢዩን ያገኘው! በኢዩ ሕይወት የምትመለከቱት አንዱ በጣም የሚያስደንቀው ነገር ይህ ነበር መጽሐፍ ስናገር "በችኮላ ይሄዳል" ይላል እንጊሊዝኛው "He Drives furiously" ይላል። ወድያው ቅባት እንደፈሰሰበት ነበር ተነስቶ ወደ መበቀል ስራው የተሰማራው! አንድም ቀን አልጠበቀም! የእግዚአብሔርን ሕዝብ ጠላቶች ለመበቀል: በፍጥነት ወዳሉበት መንዳት ጀመረ: እናም ለእግዚአብሔር ተበቀለለት: ለዚህ ተመርጧልና። ይህንን የምላችሁ ለምንድነው? የእግዚአብሔር ልጆች: እኛም ልክ እንደ ኢዩ በችኮላ የምንነዳበት ጊዜ ላይ ነን! የእግዚአብሔርን ጠላቶች ለመበቀል የሚያስችል ፀጋ እና ቅባት #በፍጥነት_ለመንዳት የተዘጋጀ ሁሉ ላይ ይፈሳል!!! ከቤተክርስቲያን መነጠቅ በፊት ያለን ጊዜ ብዙ አይደለም: ይህንን የምለው እንደ ነብይ ነዉ! የእግዚአብሔር መንፈስ#ለኢዩ የሚለው ይህንን ነዉ: #በችኮላ_ንዳ!
(በችኮላ ንዱ ስላችሁ ደግሞ መኪናችሁን አይደለም🙄 😁 ፤ እግዚአብሔር በሰጣችሁ መንገድ ላይ በፍጥነት ንዱ! እግዚአብሔር የተናገራችሁን ለመፈጸም ፍጠኑ!)
የእግዚአብሔር ልጆች: ማህበራዊ ድረገጽ ላይ ያለምንም መንፈሳዊ ትርፍ ከሆነ 1 ሰዓት እንኳ የምታጠፋበት ጊዜ የለችሁም: ከእግዚአብሔር ቃል ጋር እንቆይ! ተከታታይ ፊልም የምታዩ የእግዚአብሔር ልጆች ተሸውዳችኋል! Video Game ስትጫወቱ የምትባክኑ ልጆች በጣም ተሸውዳችኋል: የእግዚአብሔር ልጆች: ንቁ! ያላችሁበትን ጊዜ በእግዚአብሔር መንፈስ ተመልከቱ: ደግሜ እላለሁ ከቤተክርስቲያን ንጥቀት በፊት ብዙ ጊዜ የለንም! እግዚአብሔር የሰጠንን ተግባር በፍጥነት እንከውን: በችኮላ እንንዳ! በንጉሱ ፊት ማፈር የማይፈልግ ሁሉ ሰምቶኝ ይፈጽመዋል!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ትንቢታዊ መልእክት ተዘጋጁ!
👉እውነተኛ መንፈሳዊነት የህልውና ጉዳይ ሆኗል!
👉የቤተክርስቲያን ንጥቀት ከዚህ በኋላ በዬትኛውም ጊዜ ይሆናል!
-Prophet Victor.
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
በመንፈስ ቅዱስ ተጽእኖ ውስጥ የመኖራችን ማረጋገጫ ኃጢአትን ለማድረግ: ፍላጎት ማጣታችን እንጂ በልሳን መናገራችን ወይም ትንቢት መናገራችን ብቻ አይደለም: የጌታዬ አካል በንጽሕና ክንፍ ከደመናት በላይ ከፍ ስትል እመለከታለሁ!😭
-𝓿𝓲𝓬𝓽𝓸𝓻
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
መንፈስ ቅዱስ የቤተክርስቲያን ሞገስ ነው። ያለ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ሞገስ አልባ ነት!!!
➤ እውነት ነው ስለ ቤተክርስቲያን ስናገር በትልቅ መንቀጥቀጥና ፍርሃት ነው ምክንያቱም #የኢየሱስ #አካል #ነት!! ነገር ግን ጌታ መንፈስ ቅዱስ ለቤተክርስቲያን እንደሚያስፈልገት አጥብቆ ነው የነገረን!!!!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
🔊ተዘጋጁ! አሁን ነዉ ጊዜው❗️
የእግዚአብሔር ልጆች ፍጹም ለውጥን በመለማመድ: ከዓለም ከኃጢአት እና ከሰይጣን በላይ በመሆን የእግዚአብሔርን ሕይወት የምንኖርበት ትክክለኛው ጊዜ ላይ ነን! ለእውነት የእውነት ለመኖር ወስኑ! ይህንን የምለው ያለምክንያት አይደለም: ለቤተክርስቲያን የቀራት የዝግጅት ጊዜ ነዉ! የቤተክርስቲያን ንጥቀት ሩቅ አይደለም! በፀጋው ላይ በመደገፍ ኃጢአተኝነት እና ዓለማዊ ምኞትና ካዱ!
“ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤”
— ቲቶ 2፥12-13
ይህንን እያደረግን እንደ እግዚአብሔር ልጆች መገለጥ አለብን! ፍጥረት በናፍቆት የሚጠብቀው የዓለም የኃጢአት ባሪያ ያልሆኑ ከሰይጣን እና ከመናፍስቱ በላይ የሆኑ የአምላክ ልጆችን መገለጥ ነዉ!!! አስተሳሰባችን ንግግራችን ድርጊታችን ሁሉ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይሁን!!! ጊዜው አሁን ነዉ!
(ይህንን ሰምቶ የሚያደርግ ሰው አስተዋይ ነዉ!)
#የተባረከው_ጌታችን_ተመልሶ_ይመጣል!!!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
“እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ።”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥1-2
ለመሪዎች እንድትጸልዩ ላሳስባችሁ ይገባኛል! በተለይ ለ ጠቅላይ ሚንሲትር አብይ አህመድ! የእግዚአብሔር ጥበቃ በእርሱ ዙሪያ እንድሆን ጸልዩ።
1 810
Don't miss this❗️❗️❗️
ዛሬ ማታ 2:30 ጀምሮ ሦሶተኛ ዙር በ ThingsOfGod~Group: ፈጹም ለውጥን (🦋Transfiguration) እንዴት መለማመድ እንደምንችል መንፈስ ያስተምረናል: ደግሞም እንጸልያለን! በዚህ በዘመኑ መጨረሻ የእግዚአብሔር ሃሳብ ፍጹም የተለወጡ እና ክርስቶስን የሚመስሉ ልጆቹን በዓለም ሁሉ ላይ መግለጥ ነዉ!🔥
@TheMysteriesOfGod
@TheMysteriesOfGod
1 810
በሕይወቴ እጅግ በጣም የምወዳቸው #ሁለት ጓደኞች አሉኝ ለእነርሱ ያለኝ #ፍቅር ጥልቅ ነው #ወንድሞቼ ይገርማችኋል እነርሱ ጓደኞቼ ስለሆኑ በሕይወቴ ለይ እየሆነ ያለው ነገር በቃላት የሚገለጽ አይደለም። በነገራችን ለይ ለእናተም #ጓደኛ መሆን ይችላሉ ስማቸው, የመጀመሪያው
#መንፈስ ቅዱስ ይበላል, ሁለተኛው ደግሞ
#መጽሐፍ ቅዱስ።
➤ እነዚህን ሁለቱን የዘላለም ጓደኛ ያደረገ ሰው ብዙ አተረፈ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ #ኪሳራ የሚባል ነገር #አያውቅም።
➤ኪሳራ ማለት ያልተማረቹበት ዘመን አይደለም ወይም ያልነገደቹበት ወይም ያለገባቹበት ዘመን አይደለም።
➤ኪሳራ ማለት ያለ መንፈስ ቅዱስ ወይም መንፈስ ቅዱስ #ሰንረዳ የኖርንበት ዘመን ነው።
መንፈስ ቅዱስ የዘላለም ጓደኛዬ ነህ!!!!
Join👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
እግዚአብሔር ለቀን ፀሃይን ለማታ ደግሞ ጨረቃን ብርሃንን ይሰጡ ዘንድ አድርጓል! ለመልካሙም ለክፉውም መልካም ሁን!
-𝓿𝓲𝓬𝓽𝓸𝓻
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ስጋዊ አባቴ: በጣም የተወደደ: ሰው ነዉ: በጣም እወደዋለሁ: ከእርሱ የተማርኩት ነገርም ብዙ ነዉ: ነገር ግን መንፈሳዊ እውነቶችን ደረጃ በደረጃ ያወቀ ሰው አይደለም: ስለዚህ የእግዚአብሔር ጥልቅ ነገሮች የተማርኩትም የምማረውም ከስጋ አባቴ አይደለም: ጋና በክርስቶስ ሕጻን እያለሁ: ነበር ...“ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም።”
— ምሳሌ 22፥6...የሚለውን ክፍል ያገኘሁት! የስጋ አባቴ እንዳልኳችሁ: ያስተማረኝ ነገር አለ: እውነት ለመናገር ትህትናን ሰዎችን መቀበልን እና መርዳትን ሰዎችን ሁሉ ማክበርን አስተምሮኛል! ነገር ግን: የመንፈስን ጥልቅ ሚስጢራት ሊያስተምረኝ እንደማይችል: የተረዳሁት ጋና በክርስቶስ ሕፃን እያለሁ ነበር: ይህንን ማድረግ ስላልቻለ: አልወቅሰውም! ምክንያቱም በእነዚህ መንፈሳዊ ሚስጢራት ረገድ እርሱም የተማረ አይደለም። ስለዚህ: ያኔ አንድ ጸሎት ጸለይኩ: ከሁሉም የላቀው እውቀት መንፈሳዊ እንደሆነ ስለገባኝ የመናፍስትን አባት እንደዚህ ነበር ያልኩት "የመናፍስት አባት: ስለ ስጋ አባቴ አመሰግንሃለሁ! ነገር ግን መንፈሳዊ ሚስጢራትን ልያስተምረኝ እንደማይችል አውቃለሁ: ስለዚህ አባት ሆይ በምሄድበት መንገድ ምራኝ: ከእነርሱም ፈቀቅ አልልም!" እነዚህን ቃላት ነበር የተናገርኩት: የመናፍስት አባት የሆነው እግዚአብሔርም ታማኝ ነበር! አሁንም ነዉ! የሕይወትን መንገድ አስተምሮኛል እያስተማረኝም ነዉ! ስለዚህ ላከብረው ይገባኛል!
“የሕይወትን መንገድ አስታወቅኸኝ፤ ከፊትህ ጋር ደስታን ትሞላብኛለህ።”
— ሐዋርያት 2፥28
👉የሕይወትን መንገድ አስተምሮኛል! ለዘለዓለም እኖራለሁ!
-𝓿𝓲𝓬𝓽𝓸𝓻
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
👉የእውቀት ሃይል!
👉ክርስቶስን ለማወቅ ትጉ!
👉ራሳችሁን በክርስቶስ እወቁ!
ስኬት በቀጥታም በተዘዋዋሪም ከእውቀት ጋር የተገናኘ ነዉ: በዚህ ምድር ላይ ተሳክቶላቸዋል የሚባሉ ሰዎች: አልተሳካላቸውም ከሚባሉ ሰዎች የሚለዩት ሁለት ጭንቅላት ወይም አራት እጅ ስላላቸው አይደለም! ወይም ደግሞ በቀን ውስጥ ከ 24 ሰዓት ያበለጠ ሰዓት ስላላቸው አይደለም! በሁለቱ ጎራዎች መካከል ያለው ልዩነት #የእውቀት ነዉ! ተሳክቶላቸዋል የሚባሉ ሰዎች አልተሳካላቸውም የሚባሉት ያላወቁትን ነገር አውቀዋል: በአንድ ሕብረተሰብ መካከል ያወቀ የሚባለው ሰው: በተቀረው በማያውቀው ቡድን ላይ እድል(advantage) ይኖረዋል። ያላችሁበት ማህበር የማያውቀውን ነገር የምታውቁ ከሆነ: በማህበሩ ላይ ማትረፍ ትችላላችሁ: ማህበሩ እናንተ የምታውቁትን ፈጽሞ እስኪያውቅ ድረስ: በእናንተ ላይ የመደገፍ ግዴታ ይወድቅበታል።
እኔ ዛሬ ግን ማውራት የፈለኩት: ባለማወቅ ለይ እድል አግኝቶ ስለሚገኝ ስኬት አይደለም ስለ እግዚአብሔራዊ ስኬት ነዉ ማውራት የፈለኩት።
እውነተኛ እና መንፈሳዊ ስኬት ኢየሱስ ክርስቶስን እና እራሳችንን በክርስቶስ ከማወቅ ይጀምራል። እግዚአብሔር ስኬት የሚለው ስኬት የሰዎችን አለማወቅ ተጠቅሞ በእነሱ ላይ ማትረፍ ሳይሆን: ለእነሱ መትረፍ ነዉ። ክርስቶስን ስታውቁት: ለሰዎች መትረፍ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ግልጽ ይሆናል! ራሳችሁን በክርስቶስ ስታውቁ ደግሞ ለሰዎች መትረፍ እሁን ይሆናል! እውነት ለመናገር ክርስቶስን ማወቅ ከዚህ የላቀ ዘላለማዊ ትርፍ አለው: ለእኛ ለምናምን የክርስቶስ እውቀት ሕይወታችን ነዉ!!!!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
በፊት በሰራኋቸው #ኃጢአቶች አሁንም እወቀሳለሁ! ለምን?😭 በዚህ ምክንያት ብዙ መጸለይ አልችልም!😭
#መንፈስ ቅዱስ ነዉ ወይስ #ሰይጣን?
እንዴትስ #ከበደለኝነት ስሜት ነጻ መውጣት እችላለሁ!?
#ሕልናዬ እንዴት ይነጻል???🤔
#የኢየሱስን #ደም መጠቀም የምችለው እንዴት ነዉ?
👉ይህንን ከሰማችሁ በኋላ: #የበደለኝነት ስሜት ቻው🖐 አበቃለት! በእግዚአብሔር ሕልውና ውስጥ #መኖር ብቻ ነዉ ከእንግዲህ!🤗
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
በፊት በሰራኋቸው #ኃጢአቶች አሁንም እወቀሳለሁ! ለምን?😭 በዚህ ምክንያት ብዙ መጸለይ አልችልም!😭
#መንፈስ ቅዱስ ነዉ ወይስ #ሰይጣን?
እንዴትስ #ከበደለኝነት ስሜት ነጻ መውጣት እችላለሁ!?
#ሕልናዬ እንዴት ይነጻል???🤔
#የኢየሱስን #ደም መጠቀም የምችለው እንዴት ነዉ?
👉ይህንን ከሰማችሁ በኋላ: #የበደለኝነት ስሜት ቻው🖐 አበቃለት! በእግዚአብሔር ሕልውና ውስጥ #መኖር ብቻ ነዉ ከእንግዲህ!🤗
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
መዝሙር 15
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ አቤቱ፥ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል? በተቀደሰውም ተራራህ ማን ይኖራል?
² በቅንነት የሚሄድ፥ ጽድቅንም የሚያደርግ፥ በልቡም እውነትን የሚናገር።
³ በአንደበቱ የማይሸነግል፥ በባልንጀራው ላይ ክፋትን የማያደርግ፥ ዘመዶቹንም የማይሰድብ።
⁴ ኃጢአተኛ በፊቱ የተናቀ፥ እግዚአብሔርንም የሚፈሩትን የሚያከብር፥ ለባልንጀራው የሚምል የማይከዳም።
⁵ ገንዘቡን በአራጣ የማያበድር፥ በንጹሑ ላይ መማለጃን የማይቀበል። እንዲህ የሚያደርግ ለዘላለም አይታወክም።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
Don't miss this❗️❗️❗️
ነገ ማታ 2:30 ጀምሮ ሦሶተኛ ዙር በ ThingsOfGod~Group: ፈጹም ለውጥን (🦋Transfiguration) እንዴት መለማመድ እንደምንችል መንፈስ ያስተምረናል: ደግሞም እንጸልያለን! በዚህ በዘመኑ መጨረሻ የእግዚአብሔር ሃሳብ ፍጹም የተለወጡ እና ክርስቶስን የሚመስሉ ልጆቹን በዓለም ሁሉ ላይ መግለጥ ነዉ!🔥
@TheMysteriesOfGod
@TheMysteriesOfGod
1 810
👉መንፈሳዊ ዓለም
መንፈሳዊ ዓለም ለይ ውሎ ማደር ሕይወት እና ሰላም ነዉ!
ዋናዎቹ የመንፈሳዊ ዓለም ቋሚ ነዋሪዎች:
1-የሁሉም ዳኛ የሆነው እግዚአብሔር።
2-የአድስ ኪዳን መካከለኛ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ።
3-ከአቤል ደም የተሻለ የሚናገር ደም።
4-ስማቸው በሰማይ የተመዘገቡ የበኩራት ማህበር።
5-ፍጹምነትን ያገኙ ጻድቃን መንፈሶች።
6-በደስታ የተሰበሰቡ የመላእክት አእላፍ ናቸው።
👉እነዚህን መንፈሳዊ አካላት ሁሉ: ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ባለን ህብረት ልክ ልንገናኛቸው እንችላለን!
(........HOLY SPIRIT.....YOU ARE ALL...I NEED...)
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
