ru
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Открыть в Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Больше
1 810
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 день
Архив постов
የሮሜ ጥናት ከምዕ 1 እስከ ምዕ 3፥20 ድረስ ዋና ዋና ትምህርቶች ከላይ☝️

የሮሜ መጽሐፍ ጥናት: ከምዕራፍ አንድ ጀምሮ እስከአሁን የተመለከትናቸው ዋና ዋና ትምህርቶች። ሮሜ 1፥1-16 --- ጳውሎስ ማነው? ---ወንጌል ምንድነው?---በሮም ያሉ ክርስቲያኖች ምን ይመስላሉ?--- በመጀመሪያዎቹ አስራ ስድስት ቁጥሮች ለእነዚህ ጥያቄዎች መልስ ተሰጥቷል። ሮሜ 1፥17-32 --- የሰው ዘር ሁሉ ውድቀት--- እግዚአብሔር ለሰዎች ሁሉ የገለጠው የራሱ መገለጥ *አምላክነቱ እና ዘላለማዊ ሃይሉ* ---የሰዎች እንቢተኝነት---ለእግዚአብሔር ክብርን አለማቅረብ እና ምስጋናን አለመስጠት---የሰዎች እንቢተኝነት ውጤት ---በመጀመሪያ ሁለት ውጤቶች የጣዖት አምልኮና ቅዱስ ያልሆነ ሩካቤ ስጋ---በመቀጠል ለማይረባ አእምሮ ታልፎ መሰጠት--- ውጤቱ በሁሉም አይነት ክፋት መሞላት/21 ክፉ ባሕሪያት ተዘርዝረዋል/። የመጀመሪያዎቹ ሁለቱ ውጤቶች በቀዳሚነት ስጋን የሚያረክሱ ስሆን የቀጠለው ውጤት ደግሞ አእምሮንም የሚያረክስ ነው። ሮሜ 2፥1-16 ---አምስት የእግዚአብሔር ፍርድ መርሆች---እውነት፣ ስራ፣ አድሎ አልባነት፣ ብርሃን(እውቀት)፣ በሰዎች ልብ የተሰወረ ሚስጥር---በተጨማሪም የእግዚአብሔር ፍርድ የማይመረመር እና ከሰዎች አእምሮ የበለጠ ነው ሮሜ 11፥28--- ሮሜ 2፥17-29 --- የኃይማኖተኛ ሰዎች በደል---በምሳሌነት የቀረቡት አይሁድ ናቸው። የአይሁድ ኃጢአት ምንድነው? ---ከእግዚአብሔር ሕግን ቢቀበሉም መጠበቅ አልቻሉም---በተጨማሪም ኃይማኖተኛ ሰዎች የሚያደርጓቸው ውጫዊ ስርዓቶች ሰዎችን ለማጽደቅ ዋጋ የሚኖራቸው አይደሉም ---በተጻፈ ሕግና ግዝረት አይሁድ በእግዚአብሔር ፊት መጽደቅ አልቻሉም። ሮሜ 3፥1-7 ---ይሁዲ የመሆን ብልጫው እና የመገረዝ ጥቅሙ በብዙ መልኩ ብዙ ነው---በመጀመሪያ ይሁዲዎች ናቸው የእግዚአብሔር ቃል በአደራ የተሰጣቸው ---አይሁድ ለተቀበሉት ቃል ታማኞች ባለመሆናቸው እግዚአብሔር ታማኝነቱን አይለውጥም---በአይሁድ እምቢተኝነት የእግዚአብሔር ጽድቅ የበለጠ ጎልቶ ታይቷል--- የአይሁድ እምቢተኝነት የእግዚአብሔር ታማኝነት የሚያጎላ ቢሆንም እግዚአብሔር ግን እውነተኛ በመሆኑ ፍርዱ የማይቀር ነው። ሮሜ 3፥9-20 ---አይሁድም ሆኑ አሕዛብ ከኃጢአት በታች በመሆናቸው መበላለጥ የለም---በድጋሚ የሰዎች ውድቀት ከብሉይ መጽሐፍት በመጥቀስ ተብራርቷል---ሁሉም ተሳስተዋል የሚለው ሐረግ የሰውን ዘር ሁሉ የሚመለከት ነው---የብሉይ መጽሐፍት ግን የተጻፉት ለአይሁድ ስለሆነ የሰዎችን ኃጢአተኝነት የሚገልጸው የመዝሙር ክፍል በቀዳሚነት ይሁዲን የሚመለከት ነው (ሕግ የሚናገረው ሕጉ ለተሰጣቸው ነው)-- ሕግ የተሰጠው ዓለምን ሁሉ ከእግዚአብሔር ፍርድ በታች ለማድረግ ነው ሌላው ደግሞ የኃጢአት ምንነት እንድታውቅ ነው---በመጨረሻም ማንም ሰው ሕግን በመጠበቅ በእግዚአብሔር ፊት መጽደቅ አይችልም። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ ጥናት ምዕ 3፥9-20 ሦስተኛው ደረጃ የቀደሙት ትምህርቶች ማጠቃለያ። ማንም በሕግ ስራ መጽደቅ አይችልም! ሕግ የተሰጠበት ምክንያቶች? @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

☝️ ሌላ መልስ ከቻናሉ አባል በሮሜ 3፥9-20 ላይ አንብቡት

ሮሜ3፥9-20(KJV bible) በዚህ ክፍል Paul እስከ ምዕ 3፥8(አስቀድሞ) ያደረጋቸውን ሙግቶች ሚያጠቃልል ይመስለኛል፦ 1)ሁሉ ከኃጢአት በታች(3፥9) 2)ሁሉ ከፍርድ በታች (3፥19) 1)"ሁሉ ከኃጢአት በታች"= "all under sin"- የሚለው ሀረግ ሰዉ ሁሉ ከኀጢአት ሀይል በታች መሆኑን የሚያሳይ ይመስለኛል። So, God የሚፈልጋቸው ዋና ነገሮች በሰው ውስጥ ሊገኙ አልቻሉም፦ i)ጽድቅ(3፥11)&(1፥18) ii)እግዚአብሔርን ለማወቅ መፈለግ(መውደድ ) (3፥11)&(1፥28) iii)እግዚአብሔርን መፍራት(እንደ እግዚአብሔርነቱ መጠን ማክበር/ማመስገን) (3፥18)&(1፥21) እነዚህ ሁሉ በሰው ዘንድ አልተገኙም! ሮሜ 3 ¹ እንግዲህ የአይሁዳዊ ብልጫው ምንድር ነው? ⁹...ከእነርሱ እንበልጣለንን? ከቶ አይደለም፤ አይሁድም የግሪክ ሰዎችም ሁሉ ከኃጢአት በታች እንደ ሆኑ አስቀድመን ከሰናቸዋልና፤” 2)ሁሉ ከፍርድ በታች (3፥19) ሰው ከኃጢአት በታች ከሆነ ከፍርድ በታች መሆኑ ግድ ነው ። b/c God is righteous. ቁ19-20፤ "ህግ በታች"👉👉 "ከኃጢአት በታች " b/c "ኃጢአት በሕግ ይታወቃልና" 👉ሕግን በማድረግ ማንም በ God ፊት ሊጸድቅ(ጻድቅ ነው ሊባል) አይችልም። 👉ከ God ፍርድ ነፃ ሚሆንበትን ምክንያት ማንም ሊያገኝ አይችልም። " ቃሉን ገልጦ የሚያስተምረን እግዚአብሔር ይባረክ!! God bless you all!

በጥያቄው መሰረት ከተሰጡኝ መልሶች አንዱ ነው። ተባርከሻል ፀጋ ይብዛልሽ!

“እንግዲህ ምን እንላለን? እኛ ከእነርሱ እንበልጣለንን? ከቶ አይደለም፤ አይሁድም ሆኑ አሕዛብ፣ ሁሉም ከኀጢአት በታች እንደሆኑ አስቀድመን ከሰናቸዋል፤” ፓውሎስ ጥያቄ እየጠየቀ ነው እና መልሱንም እዛው አስቀምጦታል 👉 አይሁድ ከ አረማዊያን ( ከ አህዛብ ) ይበልጣሉ ወይ ?? አይበልጡም ምክነያቱም ሁሉም ከ ሀጢያት በታች ስለሆኑ አይሁዳውያንም ሆኑ አረማውያን ሁሉም ሀጢተኞች እንደሆኑና አንድም ጻድቅ ሰው እንደሌለ ይነግረናል 👉(ሮሜ 3:10_18) 👈 በዚህ ክፍል ጻድቅ ማንም እንደሌለና አስተዋይና እግዚአብሔርን የሚፈልግ እንደሌለ ................ሁሉም ሀጥያተኛ እንደሁኑ ያስረዳናል ከዛም ወረድ ብሎ 👉.(19_20) ድረስ ስለ ህግ ይነግረናል 🗝አይሁድ ህግ ስላላቸው በህግ እንደሚጸድቁ ነው ሚያስቡት ነገር ግን 👉የ ህግን ስራ በመስራት ስጋ የለበሰ ሁሉ በ እግዚአብሔር ፊት ብቁ መሆን ስለማይችል ማንም በህግ በኩል ሊጸድቅ አይችልም ማለት ነው 👉ህግ ሀጥያትን እንድናውቅና ስለ ሀጥያት እንድንገነዘብ ያደርጋል እንጂ ፈጽሞ ሊያጸድቀን እንደማይችል በዚህ ክፍል ማየት እንችላለን ይንን ከ ገላትያ ( 2:16) ጋር 👈 እያነጻጸርን ማየት እንችላለን

በጥያቄው መሰረት ከተሰጡኝ መልሶች አንዱ ነው። ተባርከሻል ፀጋ ይብዛልሽ!

☝️ ዛሬ የምናጠናበት መንገድ የተለየ ነው። Comment section ላይ የእናንተን መረዳት አስቀምጡ።

ሮሜ 3 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁹ እንግዲህ ምን እንላለን? እኛ ከእነርሱ እንበልጣለንን? ከቶ አይደለም፤ አይሁድም ሆኑ አሕዛብ፣ ሁሉም ከኀጢአት በታች እንደሆኑ አስቀድመን ከሰናቸዋል፤ ¹⁰ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፤ “ጻድቅ ማንም የለም፤ አንድም እንኳ፤ ¹¹ አስተዋይ የለም፤ እግዚአብሔርንም የሚሻ አንድም የለም። ¹² ሁሉም ተሳስተዋል፤ በአንድነት የማይጠቅሙ ሆነዋል፤ በጎ የሚያደርግ ማንም የለም፤ አንድም እንኳ።” ¹³ “ጒሮሮአቸው የተከፈተ መቃብር ነው፤ አንደበታቸው ሽንገላን ያዘወትራል።” “በከንፈሮቻቸው የእባብ መርዝ አለ።” ¹⁴ “አፋቸው ርግማንና ምሬት ሞልቶበታል።” ¹⁵ “እግራቸው ደም ለማፍሰስ ፈጣን ነው፤ ¹⁶ በመንገዳቸው ጥፋትና ጒስቊልና ይገኛል፤ ¹⁷ የሰላምንም መንገድ አያውቁም።” ¹⁸ “በዐይናቸው ፊት የእግዚአብሔር ፍርሀት የለም።” ¹⁹ እንግዲህ አፍ ሁሉ እንዲዘጋና ዓለም በሙሉ ለእግዚአብሔር መልስ እንዲሰጥ ሕግ የሚናገረው ሁሉ ከሕግ በታች ላሉት እንደሆነ፣ እናውቃለን፤ ²⁰ ስለዚህ ሕግን በመጠበቅ ማንም በእርሱ ፊት ጻድቅ ነው ሊባል አይችልም፤ ይልቁንም በሕግ አማካይነት ኀጢአትን እንገነዘባለን።

አይሁድ ከምድር ሕዝቦች ሁሉ ተለይተው ያገኙት የበለጠ ጥቅምና ብልጫ(የተጻፈ ሕግና ግዝረት) ማግኘታቸው ታማኝ ያለመሆናቸውን በደል የባሰ ያደርገዋል--- በሌላ በኩል ደግሞ ይሄ የእግዚአብሔርን ታማኝነት የበለጠ አጉልቶ ያሳያል ---- አይሁድ ታማኝ አለመሆናቸው የእግዚአብሔርን ታማኝነት የሚያጎላ ቢሆንም ---እግዚአብሔር ጻድቅ በመሆኑ ፍርዱን የማይቀር ያደርገዋል።

የሮሜ ጥናት 3፥1-8 ይሁዲ መሆን ጥቅሙ ምንድነው? የአይሁድ ዓመጽ የእግዚአብሔር ታማኝነትና ክብር የሚያጎላ ከሆነ ታዲያ ኃጢአተኛ ተብለው ለምን ይፈረድባቸዋል?🤔 የእግዚአብሔር ፍርድ ትክክለኛ (ጻድቅ) ነው! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ይሁዲ እውነተኛ ይሁዲነት ውስጣዊ እንደሆነ ግዝረትም በተጻፈ ሕግ ሰይሆን በመንፈስ የልብ ግዝረት እንደሆነ በማስተማር አይሁድንም ኃጢአተኞች እንደሆኑ በቀደመው ጥናታችን ሐዋሪያው ጳውሎስ ከሷቸዋል። ታዲያ በስጋ ይሁዲ ሆኖ የመወለድ (ከአብርሃም ከይስሐቅና ከያዕቆብ ነገድ መሆን) ጥቅሙ ምንድነው? የተጻፈ ሕግም ሆነ ግዝረት አይሁድን በእግዚአብሔር ፊት ማጽደቅ የማይችሉ ከሆነ ለምን እነዚህን ስርዓቶች እግዚአብሔር ሰጣቸው? እነዚህን ሁሉ ከተቀበሉም በኃላ ኃጢአተኞች እንደሆኑ ተከሰዋልና። በእግዚአብሔር ፈቃድ ዛሬ ማታ ጠብቁኝ! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ ጥናት የሮሜ ምዕራፍ ሁለት አጭር ማጠቃላያ: ሃያ ዘጠኝ ቁጥሮች በሉት በዚህ ምዕራፍ በዋናነት ሁለት ትምህርቶችን እናገኛለን። የመጀመሪያው ትምህርት አምስት የእግዚአብሔር ፍርድ መርሆች የቀረቡበት ነው። እግዚአብሔር የትኛውንም አይነት ፍርድ በሰዎች ላይ ሲሰጥ በእነዚህ አምስት መርሆች መሰረት ነው። መርሆዎቹ:- እግዚአብሔር በእውነት (በእግዚአብሔር ቃል) ይፈርዳል፣ እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ እንደስራው ይፈርዳል፣ እግዚአብሔር ያለአድልዎ ይፈርዳል፣ እግዚአብሔር እያንዳንዱን ሰው በተሰጠው እውቀት ይፈርዳል እና እግዚአብሔር በልብ ተሰውሮ ባለው ሚስጥር ይፈርዳል (ሮሜ 2፥2-16 ተመልከቱ)። ሁለተኛው ትምህርት ሕግን የተቀበሉ የኃይማኖት ሰዎችን ኃጢአት የሚያስተምር ነው። ሐዋሪያው ጳውሎስ ይህንን ለማስተማር በምሳሌነት የተጠቀመው የራሱን ሕዝብ አይሁድን ነው። በሕግ በመመራት በነገሮች መካከል ያለውን ልዩነት በጥንቃቄ ማወቅ ብቻውን አንድን ሰው በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ አያደርገውም። እንደውም እውቀት ሰዎችን ትዕቢተኛ ሊያደርግ ይችላል (1ኛ ቆሮ 8፥1) ይሄ ደግሞ በአይሁድ ላይ በግልጽ ይታያል። አንዱ የኃይማኖተኛ ሰዎች ኃጢአት ትዕቢት ነው። በመቀጠል ሐዋሪያው ሕግ የተቀበሉ ሰዎች ሌሎችን አታድርጉ በማለት የሚያስተምሩትን ነገር እራሳቸው የሚያደርጉና ሌሎች እንዲያደርጉት የሚያስተምሩትን እራሳቸው የማያደርጉ እንደሆነ ይገልጻል። ይሄንን በአንድ ቃል ግብዝነት እንለዋለን፥ ይህ ሁለተኛው ግልጽ ኃጢአታቸው ነው። በተጨማሪም ሐዋሪያው አይሁድ የሚመኩበትን የመገረዝ ስርዓት በማንሳት ውጫዊ ስርዓቶች ዋጋ የሚኖራቸው ውስጥ እውነተኛ ከሆነ ብቻ እንደሆነ ያስተምራል። በመጨረሻም ከስሙ ትርጉም በመነሳት ይሁዲ ማለት ውጫዊ ስርዓቶችን በመጠበቅ በሰዎች የሚመሰገን ሰይሆን እውነተኛ ይሁዲ ምስጋናው ከእግዚአብሔር ዘንድ መሆኑን ያስረዳል (ሮሜ 2፥17-29)። ተጨማሪ ብርሃን ለማግኘት በድምፅ የቀረበውን ጥናት ስሙ እናንተም በግላችሁ ጠለቅ ያለ ጥናት እንድታደርጉ አበረታታለሁ። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

We can't fully understand the working of God on earth until we clearly see the depth of human depravity. የሰዎችን የውድቀት ጥልቀት እስካልተራዳን ድረስ እግዚአብሔር አሁን በምድር ላይ እየሰራ ያለውን ሥራ በሙላት መረዳት አንችልም።

የሮሜ ጥናት ሮሜ 2፥17-29 የአይሁድ ኃጢአት፤ የኃይማኖተኛ ሰዎች ኃጢአት። ትዕቢትና ግብዝነት። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ዛሬ ማታ 3 ሰዓት በሮሜ ጥናት እንገናኛለን። 👉 አይሁድም የውድቀቱ አካል መሆናቸውን ለማስረዳት የተሰጠ ትምህርት። 👉የኃይመኖተኛ ሰዎች ትልልቅ ኃጢአቶች። 👉አይሁድ የሚመኩባቸው ነገሮች። ይሁዲ የሚለው ስም፥ የተጻፈ ሕግ ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸው ግንኙነትና ግዝረት። 🚨ዛሬ ማታ ልክ ሦስት ሰዓት ላይ ጠብቁኝ🚨 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ሕግ እና ሕሊና (Law Vs Conscience) ሮሜ 2 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁴ ሕግ የሌላቸው አሕዛብ ሕግ የሚያዝዘውን ነገር በተፈጥሮ ሲያደርጉ፣ ሕግ ባይኖራቸውም እነርሱ ለራሳቸው ሕግ ናቸው። ሕግና ሕሊና እንዴት ይገናኛሉ? በግልጽ እንደምናውቀው አምላካዊ የሆኑት የሙሴ ሕግች የተሰጡት ለአይሁድ ነው። በጥንቃቄ ቅዱሳት መጽሐፍትን ስንመረምር ሕግ የተሰጠው ኃጢአትን ለመግለጥ እንጅ ሰዎች ኃጢአትን እንዳይሰሩ ለማስቻል አይደለም። በሕግ የሰዎች ኃጢአተኝነት ይገለጣል፥ የሕግ ስራ ይሄ ነው። ሕሊናም በአሕዛብ ልብ የተጻፈ የሕግ ስራ ተብሎ ነው በሐዋሪያው የተገለጸው፡ 2¹⁵ ኅሊናቸው ስለሚመሰክር፣ ሐሳባቸው ስለሚከሳቸው፣ ደግሞም ስለሚከላከልላቸው የሕግ ስራ በልባቸው የተጻፈ መሆኑን ያሳያሉ። ቀድሜ እንደገለጽኩት የሕግ ስራ የሰዎችን ኃጢአተኝነት መግለጥ ነው የሕሊናም ስራ ይሄው ነው። ሕግ በአይሁድ የሚሰራውን ስራ ሕሊና በአሕዛብ ይሰራል፤ ሕግ ለአይሁድ የሚያስገኘውን ውጤት ሕሊና ለአሕዛብ ያስገኛል። አንድ ሰው ኃጢአተኝነቱ ስገለጥ ቀጥሎ ሊሰማው የሚችለው ምንድነው? የእግዚአብሔር ምህረት የሚያስፈልገው የወደቀ መሆኑ ነው። ሕግም ሕሊናም ይሄንን ነው የሚሰሩት፤ ሕግ በአይሁድ ሕሊና ደግሞ በአሕዛብ። ነገር ግን ሕግና ሕሊና አንድ ናቸው ማለት አይደለም። ሕግ በጽላት የተጻፈ ነው ሕሊና ግን በሰዎች ልብ የተጻፈ የሕግ ስራ ነው። በተጨማሪ ሕሊና ደካማ ልሆን ይችላል (1ኛ ቆሮ 8፥7) --- ሕሊና የደነዘዘ ልሆን ይችላል (1ኛ ጢሞ 4፥2) --- ሌላው ሕሊና የረከሰ ልሆን ይችላል (ትቶ 1፥15) በእነዚህ ሦስት ምክንያቶች ሕሊና ኃጢአተኝነትን በመግለጥ የሕግን ያህል ውጤታማ ላይሆን ይችላል። እግዚአብሔር ሰዎች ሁሉ የእርሱ ምህረት እንደሚያስፈልጋቸው እንዲያውቁ ይፈልጋል፤ የሕግ ስራ የሰዎችን ኃጢአተኝነት መግለጥ እንጂ ሰዎችን ማጽደቅ አይደለም። ሕግ የሚያዘውን በጥንቃቄ የሚጠብቁትን እንኳ እግዚአብሔር እራሱ በፊቱ ያጸድቃቸዋል እንጂ በራሳቸው በእግዚአብሔር ፊት አይጸድቁም፡-- “ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን የሚባሉት ለሕጉ የሚታዘዙ እንጂ፣ ሕጉን የሚሰሙ አይደሉም።” — ሮሜ 2፥13 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

#ተዘጋጁ ወደ ታች ስር የሰደደውን ቅሬታ ወደ ላይ እንዲወጣ እግዚአብሔር እያዘጋጀው ነው! “እንደ ገናም የይሁዳ ቤት ቅሬታ፣ ሥሩን ወደ ታች ይሰዳል፤ ከላይም ፍሬ ያፈራል፤” — ኢሳይያስ 37፥31 (አዲሱ መ.ት)

የሮሜ ጥናት ሮሜ ምዕ 2፥17-3፥8 ድረስ ያለው ቃል በቀዳሚነት አይሁድን የሚመለከት ነው። ሐዋሪያው ጳውሎስ በምዕ 1፥17-32 ድረስ የሰው ዘር ሁሉ እንደወደቀ አስተምሯል በመቀጠልም በምዕ ሁለት በመጀመሪያዎቹ አስራስድስት ቁጥሮች እግዚአብሔር ፍርድ የሚሰጥባቸውን አምስት መርሆች አስተምሯል፥ ምዕራፉን ስጀምር የሞራል እውቀት በማግኘታቸው በሌሎች ላይ የሚፈርዱ ሰዎች ራሳቸው ማመካኛ እንደሌላቸው በመናገር ነው የጀመረው ይህንን ሐሳቡን ገታ አድርጎ የእግዚአብሔር ፍርድ መርሆችን ያስተማረው እነርሱ እንኳን ከፍርድ የማያመልጡ መሆናቸውን ለመጠቆም ነው። አምስቱን የእግዚአብሔርን ፍርድ መርሆች ከስተማረ በኋላ የበለጠ ትንተና ለመስጠት ወደቀደመው ሐሳብ ይመለሳል። ስለዚህ ከምዕ 2፥17 ጀምሮ የሞራል እውቀት(ሕግ) የተቀበሉ ሰዎች በቀዳሚነት (አይሁድ) ኃጢአታቸው ምን እንደሆነ በማስተማር እነርሱም በሌላ መልኩ በምዕራፍ አንድ ላይ የተዘረዘረው ውድቀት አካል መሆናቸውን ያሳያል። የተጻፈ ሕግ የግዝረት ስርዓትም ቢቀበሉ የእግዚአብሔርን ሕግ በመተላለፍ በእግዚአብሔር ስም ላይ ስድብን እንዳመጡ ይነግራቸዋል፤ ሕግን ቢያስተምሩም አላደረጉትም። ይህ እኛን ክርስቲያኖችም የሚመለከት ይሆን? ወንጌልን እየሰበክሁ ወንጌልን የማልኖረው ከሆነ በእኔ ምክንያት የእግዚአብሔር ስም ይሰደብ ይሆን? ሃይማኖተኛ ሰዎችም የውድቀቱ አካል ናቸው፥ ስለዚህ ከእግዚአብሔር ፍርድ የሚያመልጡ አይደሉም። አይሁድም ቢሆኑ ሌሎች የሙሴን ሕግ የተቀበሉም ሆነ ሌሎች የሞራል ሕጎች የተሰጣቸው ሰዎች ሁሉ ከእግዚአብሔር ፍርድ የሚያመልጡ አይደሉም! ተጠያቂ ናቸው። በወንጌል የተገኘው ጽድቅ ለሁሉም መነገር ያለበት በዚህ ምክንያት ነው። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod