cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

👑Ethio pic

የ ኢትዮ pic አባል በመሆን በፎቶ ውድድር ይሸለሙ ለማንኛውም አስተያየት @yowbizz or @tteda @naniboy1 ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር ታላቅ የ pic Competition Telegram ላይ ታዋቂ famous ለመሆን ከፈለጉ የእርስዎን አሪፍ pic ይላኩ👌 👇👇 Join us👇👇 https://t.me/joinchat/AAAAAESVJQasdYJg0blmXQ

Больше
Страна не указанаЯзык не указанКатегория не указана
Рекламные посты
289
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

ትምህርት ተከፍቶ የዜግነት ክብር ሲባል ═══••🇪🇹••═══ የኮሮና ፍርሃት በኢትዮጵያችን ፀንቶ ታየ ቤት መቀመጥ ዳር እስከ ዳር ብርቶ ለሰላም ለፍቅር ለህዝቦች ነፃነት እጃችንን ታጥበን ቆመናል በርቀት መሰረቱ ፅኑ በሽታ መጥቶብን ህዝቦች ነን ከስራ ከስራ የራቅን ድንቅ ገዳይ በሽታ የሞትም ባለቤት የተፈጥሮ እርግማን የበሽታዎች ሁሉ እናት እንርቅሃለን አለብን አደራ ኮሮና ጥፋልን እኛም ስራ እንስራ የምን አንብቦ ማለፍ ነው ገባ ገባ በሉ እንጂ @ethiopicc01
Показать все...
AUD-20200425-WA0005.opus2.52 KB
#ኮቪድ19 በዓለም አቀፍ ደረጃ በማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚ ዘርፎች የሚያስከትለውን የጫና ክብደት በመገንዘብ፣ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ባለፉት ሳምንታት ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል ሲዘጋጅና ርምጃዎችን ሲተገብር ቆይቷል፡፡ እስካሁን ሊከሰቱ የሚችሉትን ፈታኝ ሁኔታዎች ያለማቋረጥ በመገምገም፣ ከሁኔታዎቹ ጋር ተመጣጣኝ የሆኑ ርምጃዎች ሲወሰዱ ቆይቷል፡፡ የኮቪድ19 ወረርሽኝ በዓለም አቀፍም ሆነ በሀገር ደረጃ መስፋፋቱን በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚኒስቴሮች ምክር ቤት፣ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 93 በተደነገገው መሠረት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ደንግጓል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሁሉም ሰው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ድንጋጌዎች ተፈጻሚ እንዲያደርግ እና የጤና ሚኒስቴር ያወጣውን ቫይረሱን የመከላከል መመሪያ በጥብቅ እንዲተገብር ይጠይቃሉ፡፡
Показать все...
የኢትዮጵያ መንግሥት የኮሮና ወረርሽኝ እየተባባሰ በመምጣቱ ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ ዐውጇል፡፡ #Ethiopia declares state of emergency to fight #COVID19 [Ministry of Health,Ethiopia]
Показать все...
እናሆ ምስጋና፤ ሰባራ ባቡር አካባቢ የሚገኘው ዕድገት በህብረት ህንጻ ባለቤቶች 150 ለሚሆኑ ተከራዪቻቸው ለሁለት ወር በነፃ እንዲገለገሉበት ፈቅደውላቸዋል። ለአከራዮች ያቀረብነውን ጥሪ ተከትሎ ይሄንን ውሳኔ በመወሰናቸው አክብሮቴን መግለጽ እፈልጋለሁ። ሌሎች አከራዮችም የእነሱን ፈለግ እንደሚከተሉ ባለሙሉ ተስፋ ነኝ። [Takele Uma Banti]
Показать все...
ኮቪድ -19፡ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ከኮሮናቫይረስ ጋር በተያያዘ መንፈሳዊ መዝሙር ለቀቁ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ዓለም እየተሸበረበት ያለው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት በማድረግ ፈጣሪን የሚማፀን ‘ማረን’ የሚል መንፈሳዊ መዝሙር አወጡ። መዝሙሩ በቀጥታ ቫይረሱን የተመለከተ ባይሆንም “ዓለም በመጥፎ ዜናዎች እየተሸበረ ባለበት በዚህ ጊዜ አትተወን” ሲሉ በመዝሙራቸው አምላካቸውን ለምነዋል። ‘ማረን’ የሚል ርዕስ ያለው ይህ መንፈሳዊ መዝሙር በዩቱብ የተለቀቀው ትናንት ሲሆን በርካታ ኢትዮጵያዊያን በማህበራዊ ሚዲያዎች ተጋርተውታል። በቪዲዮ ላይ ቀዳማዊት እመቤቷ ፈጣሪ ሕዝቦቹን እንዲጠብቅላቸው ተንበርክከው ሲፀልዩ ይታያል። በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሰው በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠው መጋቢት 3/2012 ዓ. ም ነበር። እስካሁን 55 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። [BBC]
Показать все...
ማረን.mp442.36 MB
ባለፉት 24 ሰዓት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 225 ሰዎች ውስጥ 3 ግለሰቦች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ተረጋገጠ፡፡ ቫይረሱ ወደ ኢትዮጵያ ከገባ ጀምሮ እስካሁን ባለው ሂደት ለ2 ሺህ 496 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተከናውኗል። ዛሬ የተገለጸውን ጨምሮ በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ወደ 55 ከፍ ብሏል ነው። ባለፉት 24 ሰዓታት ቫይረሱ እንዳለባቸው የተረጋገጠው ሶስቱም ግለሰቦች ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ ሁለቱ የውጭ አገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው ናቸው። ሁለቱ ግለሰቦች የ29 ዓመት እድሜ ያላቸውና ከዱባይ መጥተው በለይቶ ማቆያ ውስጥ ክትትል ሲደረግላቸው የነበሩ ናቸው፡፡ አንደኛው ግለሰብ የ36 ዓመት እድሜ ያለውና በአማራ ክልል የአዊ ዞን አዲስ ቅዳምን ከተማ ነዋሪ ነው። ግለሰቡ የውጭ አገር የጉዞ ታሪክ የሌለው ሲሆን፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ እንዳለው ተጠርጥሮ ምርመራ የተደረገለት ነው፡፡ ቫይረሱ ከተገኘባቸው መካከል አንድ ሰው ወደ ጽኑ ህሙማን ማቆያ ገብቷል፤ ይህም በጽኑ ህሙማን መቆያ ውስጥ ያሉ ዜጎች ቁጥር ሁለት ሆኗል፡፡ ቫይረሱ ከተገኘባቸው ጋር የቅርብ ንክኪ ያላቸው ግለሰቦች ባሉበት ክልል በተዘጋጀ የነጻ የስልክ መስመሮች በመደወል ሪፖርት እንዲያደርጉም ጤና ሚኒስቴር ያሳስባል፡፡ ህብረተሰቡ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የወጡ መመሪያዎችን ተግባራዊ እናድርግ፡፡ በኢትዮጵያ ቫይረሱ ከተገኘባቸው ሰዎች መካከል አራቱ ያገገሙ ሲሆን፤ ሁለቱ ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል። ሌላ ሁለት ግለሰቦች ደግሞ ወደ አገራቸው ተሸኝተዋል።
Показать все...
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.