4 956
Подписчики
-424 часа
-177 дней
-4030 день
Архив постов
4 957
Repost from TsiyonReads...
ሰላም የ ፅዮን reads ቤተሰቦች: ብዙዎቻችሁ ሰምታችሁ ሊሆን ይችላል። ቻኖሊ ኑድል የ follow challenge ሰጥቶኝ ነበር። ቀኑ ሊያበቃ የቀረኝ አምስት ቀን ብቻ ነው። የቀረኝ ፎሎወር ደሞ 38ሺህ ነው። ካላስቸገርኳችሁ የቲክቶክ ገፃቸውን ሄዳችሁ ፎሎው ብታደርጉልኝ ለኔ ትልቅ ውለታ ዋላችሁልኝ ማለት ነው። ወደ ንባባችንም እንመለሳለን።
https://www.tiktok.com/@chanoly_noodles_official?_r=1&_t=ZS-96p9r89OHwo
4 957
ያ ል ተ ላ ኩ ፡ አ ም ስ ት ፡ ቴ ክ ስ ቶ ች
[ Message -1 ች ግ ራ ች ን ፡ ም ን ፡ ነ በ ር ? ]
[ ል ዑ ል ፡ ዘ ወ ል ደ ]
ሌላ ያልነገርኩሽ ፥ የልደትሽ ቀን አበባ ገዝቼ ነበር ። አዎ ! እኔ ። የሚገርምሽ ባገሩ እንደጠፋ ሁሉ የትናየት ሄጄ መሰለሽ ? መጨረሻ ላይ ወሰን ምናምን እሚሉት ሰፈር ትንሽዬ ኪዮስክ ውስጥ ትልቅ መቀስ የያዘች ሻጭ አየሁ ፤ ፈንታቸው መርገፍ የሆኑ ቅጠሎችን እየከረከመች።
እንዲሁ ልጅ ሳለሁ ፥ ከትምህርት መልስ ሙሽራ የሚሉትን አበባ ከሰው አፀድ ቀጥፌ ወደቤቴ እሮጥልሻለሁ ። ቤት ልደርስ 'ከባቢ እጄ ከአበባው ተሻሽቶ ኖሮ ፥ ወየበ ። ከቆረጡት ኋላ ቶሎ የሚሞት አይነት ዘር ሆኖም ይሆናል ። ብቻ እጄ ላይ ከስሞ ፥ ነደደኝ ።
የቀጠፍኩት እንዲያ እንዳማረበት ለ'ናቴ ልሰጣት ነበር ። ያም ሆኖ አልተውኩትም ። ከስራ መምጫዋን ጠብቄ (አስራ ሁለት ሰዓት እንደምንም ሞልቶልኝ) ሰጠኋት ። የኔ ንጉሥ ብላ አቀፈቺኝ ፥ ከመቀበል ያለፈ ቁብ ሳትሰጠው ። ጭራሽ ወርውራው መክሰስ መብላቴን እየጠየቀች ወደቤት ይዛኝ ገባች ። እጄን ይዛኝ ስትዘልቅ ፊቴ ወደወደቀው አባባ እንደዞረ ነበር ።
እናልሽ ቤሎንዥ...
ኪዮስኩ ውስጥ ያለችው ልጅ የሚቀባውን ነገር ቀብታ የሆነ የሚነፋ ነገር'ም ነፍታበት አጋጊጣ ምናምን ሰጠችኝ ። እንዴት እንዳማረበት ። ገዝቻት ስወጣ አመስግኜ ፥ መልካም በዓል ! አልኹ ። የምን በዓል ደሞ ? በሚል ግርምታ ታየሁ ፥ ሃሃ።
እዝነ ገመዴን ከጆሮዬ ስላልተነሳ ዘፈን እንደምሰማ ሁሉ ምንም ሳልል እግሬን አዙሬ መንገዴን ጀመርኩ ። ለካ ሌላ ሰው የአንቺን ልደት አይቀድስም ። የለም? ፥ ለካ የነሱ ካለንደር በንግስሽ ቀን አይዘጋም ።
ከናቴ ለጥቆ አበባ ልሰጠው የነበረው ላንቺ ነበር ። የገዛሁት አበባ በትራንስፖርት ግፍፊ እንዳይጎዳ ወክ ማድረግን መረጥኩ ። አበባውን እንደያዝኩ ይዤ በቀትር ስንከላወስ አላፊ መንገደኛ እያየኝ በልቡ የሆነ ነገር ይላል ። መቼም አበሻ "ምኗ እድለኛ ነች ፥ አበባ የሚሰጣት " ማለት አይቀናውም ። ...አ...ዬ ባህላችን.. ገለመሌ ...እያሉ ይሆናል ።
ሰባት ሰዓት ላይ የሜክሲኮው ቶታል (ቦንዡ ካፌ) ደረስኩ ። ተረከዜን ከማቃጠል ውጪ በጉዞው ብዙ አልተሰማኝም ። ትዝ ይልሽ ከሆነ አራቴ ስደውልና በአምስተኛው ጥሪውን ስትጠረቅሚው ፥ እዛ ቁጭ ብዬ ነው ። ከተቀመጥኩ ሰዓት ሊደፍን ምናምን ደቂቃ ሲቀረኝ ያ...!...ሜሴጅ ገባ።
- Sorry, Je ne peux pas venir.
መምጣት አልቻልኩም ። እንደው እንደቀላል ፤ የአንድ ግድንግድ መፅሀፍን ግፍ በአንድ ነጠላ መስመር ። አለ አደል ፥ ሲቻኮሉ ከሰው ተገጫጭተው ይቅርታ እንደመጠየቅ አይነት ያለ ።
እና አበባው ሳይደርስሽ ከእጄ ቀረ ። እናቴም ያኔ አበባውን ስሰጣት እንዴት ሆኜ እንዳመጣሁት አልጠየቀችም ። ማለት ፥ ስላልጠየቀች ለመቅጠፍ የከፈለኩትን መስዋዕትነት አልተረዳችም ። በልጅ ሩሄ አበባ ያህል ነገር ከሰው አጥር ላይ አርጄላት ፥ በቅጡ እንኳ አልባረከችኝም ። ከንቱ ድካም ነበር ። አበርክቶቴ መገፋት የጀመረው ከያኔ አንስቶ ነው ፤ እርኩስ እንደሚሠዋው በግ ፥ እሳት ከራማ ወርዶ እንደማይበላው ...።
የዛን ቀን እራሮቴ ተፈቅፍቆ ከልቤ አልወድቅ አለኝ ። የልደትሽ ቀን ባለፈ በሆነኛው ቀን ስልኬን አውጥቼ መርዕዩ ላይ Qu'est-ce qui ne va pas entre nous , bel ange? ብዬ ፃፍኩ ። ችግራችን ግን ምን ነበር ...?
ችግራችን ፥ የፍዮሪ በእጄ ላይ መሞት ሳይሆን ፥ ተቀባይ ማጣት ነው ። አንዳችኝ ጉም ሰንጠቀን አንዳችንን ከህዋ ስናስስ ሌላችን ጣርማበር ጓሣ ውስጥ ለሽ ብለን ነበር ። በተራሽ ደሞ አንዳችን ባነን ሌላችንን ስናስስ የሂማልያ ክምር ጋርዶን ለአይን እንሰወራለን ።
መልሱን እያወቅሁ ያረቀቅሁትን ጥያቄ ላንቺ መላክ አልፈለኩም ። ከደመና በታች እንደቀረ ፀሎት ፥ ካፍ እንዳልወጣ ቃል ፥ እንዳልተኖረ ምኞት ፥ ሲባኑ እንደረሱት ህልም ፥ ደርሰው እንዳልሰበኩት ወንጌል ...
በድህሪት መደለዣ የፃፍኩትን የቃላት ድርድር አንድ በአንድ ከስልኬ መርዕይ ሰረዝኩ ። ሰሌዳው እስኪራቆት ፤ የመተየቢያዋ ከርሰር ግራዋን ሄዳ ውልብ ውልብ እስክትል። ፥ እ ...ን...ዲ..ሁ •••|
4 957
Repost from Leoul Zewelde
ቆላድባ ፤ አንዲት ፍየል ላይ የአላህ ስም ተፅፎ ...
[ ልዑል ዘወልደ ]
ጅግጅጋ ይመስለኛል ፥ አንዲት ፍየል ወጠጤ የአላህ ስም ተፅፎባት ተወለደች ። በፅሁፉ ጥርጣሬ ስለገባኝ ፥ የፍየሏ ሆድ ላይ የታተመውን አረቢኛ በፎቶ ወስጄ በአስተርጓሚ አሳየሁት ። ሲረጋገጥ ፥ በሐፍረት ሟሸሽኩ ። አይ ፈጣሪ ፥ መገለጫው ብዙ ! ሱብሀን አላህ አልኹ።
አንድ ግዜ እንዲሁ ፥ የጠፈር ሣይንቲስትና ሊቁ መጋቢ ሐዲሥ ሮዳስ በትምህርታቸው ፤ እመቤታችን በራዕይ አስራ ሁለት ላይ ጨረቃን ተጫምታለች ! ሲሉ ሰማሁና እፈር ሲለኝ ወጥቼ ጨረቃን አየኋት ። ያው እፍረት ገንዘቤ ነው ፤ እውነትም ልጇን አቅፋ በጨረቃ ላይ ትታያለች ፥ ክብሩን የሰማዩ ባለቤት ፈጣሪ ይውሰድ ።
ልጅ እያለን የመክሰስ ቂጣ ከታደልን ወዲያ የምናደርገው ድርጊት ነበር ። በጥርሳችን ቅርፅ በማውጣት ሆዳችን ከመግባት በተረፈው መጫወት ። የኔ ደሞ ይብሳል ፥ ቂጣ ቆርምሜ የማልሰራው አገርና አህጉር ካርታ አልነበረኝም ። የሚገርመኝ ፤ የጥበብ ስራዬን ለማመሳከር ለሰዎች ሳሳይ መልሳየው የሚሳሳት ሆኖ አላገኘውም ። ከምስክሩ በኋላ ታዲያ በራሴ በመደመም ውድ ሥራዬን መብላት ያሳሳኛል ።
መክሊቴን እያሳደግኹት የመጣሁት ፥ በግድ አጥና እየተባልኩ የግቢ በር በላዬ ላይ ሲቆለፍብኝ ግዜ ነው ። ከአሰልቺው ጥናት የሚያናጥበኝ ቅዱስ ምግባር ፥ በግድግዳና ኮርኒስ ላይ ፓተርን መፈለግ ሆነ ።
ከፊቴ ያለ አሸዋ ግርፍ ግድግዳ ላይ ከዚህ በፊት ያላየኋቸውን ግጥምጥሞሽ ፍለጋ በሰመመን እጠፋለሁ ። ጥንቸል ፣ የሊስትሮ እቃ ፥ ቀጭኔ ፣ እትዬ ወርቄ ፥ የበሪኪና ዋንጫ ፥ ኢትዮጵያ ( አፍሪካ ተገልብጣ ) ፥ ምሳ'ቃ ፥ ጥርስ ብሩሽ ፥ ሣይንስ ቲቸርን .... የማላገኘው ቁስና ግኝት አልነበረም ። ለጉድ እናውዘዋለሁ ።
አይምሮዬ እረፍት አልነበረውም ፤ ሲብስብኝ መንገድ ላይ ሁሉ በደመና ቅርፅ ደርዝ መስራት ጀመርኩ ። በዚህ ነገር አብረውኝ ያሉ ጓደኞቼና ወላጆቼ ለጉድ ተማረሩ ። ትንሽ የምትረዳኝና አብራ የምትዳረቀኝ በህሪያ ብቻ ናት ። በህሪያ አሳዳጊዬ እና የቤት ሰራተኛችን ናት ።
እየበሰልኩ ስመጣ ግን ፣ ይሄን ነገሬን ማስተዋል ጀመርኩ ። ሰዎች በውስጣችን ላልተጠየቅነው ጥያቄ መልስ ተሸክመን እንደምንዞር ። በምሳሌ ላስረዳ መሰለኝ ...
የቤት ኪራይ ክፍያ ቸግሮት አማቱ ቤት የገባ አዲስ ጎጆ ወጪ ነበር ። አንድ ፊት ብቻ በየሄደበት ሁሉ እየተደጋገመ ቢታየው ግዜ ፥ አዋቂ ሳይካትሪስት ጋር ይሄዳል ።
- እሺ ፥ ምንድነው ?
- ይኸውልህ ፥ ሁሉም ቦታ ላይ የሚታየኝ አንድ ፊት አለ !
- እንዴት ?
- በቃ ... ምንጣፍ ላይ ፣ ዳቦ ላይ ፣ ሶስት አይን ያለው ሶኬት ላይ ... ያን ፊት የላማየው ቦታ የለም !
- ይሄ እኮ የተለመደ በሽታ ማለቴ ብዥታ ነው ነው ። ፐሬዶልያ ይባላል ። በአንተ እድሜ ላይ ካሉ ሶስት ሰዎች ሁለቱ ይገጥማቸዋል ።
- ዶክተርዬ
- ወይ
- እነዛ ሁለቱ ሰዎች አማቻቸውን ነው የሚያዩት ?
- ምን ?!
- አይ ምንም ሃሃሃ
አብዛኛውን ግዜ የምናየውን አይደለም የምናስተውለው ፤ ከሱ ይልቅ ሁነትን በውስጣችን ከያዝነው እውነት ጋር እያመሳከርን ፥ እንቀበላለን ። ይህን የምናደርገው ሰልፍ እቲማችንን ለመጠበቅ ሲሆን እያደር ግን ወደ ምርቃና (*በኦሮምኛ confirmation bias ማለት ነው) ይመራል ።
ከያ ወዲህ አይምሯችን ተቃራኒ ሀሳቦችን ለማስተናገድ ክፍት አይሆንም ። የተለየ ሀሳብ ያላቸውን ሰዎች መጋፈጥ እንፈራለን ። በሶሻል ሚዲያ የምንከተለው የውስጥ ሀሳባችንን ቫሊዴት የሚያደርጉልንን ሰዎች ብቻ ይሆናል ። አካታችነትና ምክንያታዊት ይጎለናል ። በዚህ መጠቃቱ የሚብሰው በግትርነት የተለያዪ ሀሳቦችን ማሰባጠር ተስኖን ውሳኔዎችን ስናሳልፍ ነው ።
አንድ ግዜ ፥ ፓተርን በመፈለግ ባህሪዬ እንደሌላው ከማታገለኝ አሳዳጊዬ ከበህሪያ ጋር እየተከራከርን ነው ። እሷም ከኔ ተጋብቶባት ከኔው ብሳ ቁጭ አለች ። በስኒ ላይየቀረ ዳካ ሁሉ እያነበበች ፤ ትተነትን ገባች ። ይሄኔ ፥ እኔ በተቃራኒው መቆም ጀመርኩ ። የተሻለኝ ራሱ በዛው ቀጥዬበት ይመስለኛል ።
በዘይት የተጨማለቀ ሂጃቧን እያሳየቺኝ ፥ እስኪ እንካ አንበው አለቺኝ ። አይኗ በለቅሶ ቀልቷል ። ሂጃቧ ላይ ለደቂቃዎች አተኩሬ ከ"ላ" በስተቀር ምንም ፓተርን አልሰራልህ አለኝ ።
- እሺ ምንድነው በህሪያ ?
- አላህ ! ነው የሚለው
- ምን ?
- ሁለት ቀን ባልሰግድ አትሰግጂም ብሎ እያናገረኝ ነው ። ያረቢ አል-ረሕማን ፥ ባክህ ተዉሂዴ ያማረላት አርገኝ ።
- እንዴ...! ቆይ አላህ የምር መታየት ከፈለገ ለምን 120 ላይ አይመጣም ?
- እህ ! እኔ መች 120 የማየውን ነው ? በዛ የሚመጣው ፤ ቆሻሻዋን በሂጃቤ ቆሻሻ ይንገረኝ እንጂ ...
በህሪያ አሳዘነቺኝ ። በልጅ ልቤ ማፅናናት ግራ ገብቶኛል ። ትንሽ ቆይቼ የምትወደው ፕሮግራም ትዝ አለኝ ።
- እሺ የምር መገለጥ ከፈለገ ፥ ለምን በህብረ-ትርዒት ላይ አይመጣም ?
- ቢስሚላሂር አንተ ! ዘፈን እኮ ሀራም ነ ...
- ምን ?!
- ...እ...እ...እ... ፥ ሃሃሃ
4 957
Repost from Sost Kilo
It's been a long long time !
[ ል ዑ ል ፡ ዘ ወ ል ደ ]
ፅድ አናት ላይ የኮኮብ ዕድ ሳይ - በዝንፍ ቅርንጫፍ የተጥመለመለ ሲባጎ ብልጭ ድርግም ሲል - የሥጦታ ሙዳዮች ዙሪያው ሲቆለል - ዜማ ባየሩ ሲናኝ ፥
በዓመቱ ኦሜጋ ሁሉም ወደልጅነቱ ሲሰበሰብ - በቀለም ያሸበረቁ ሞሳዎች ተሰብስበው ሲዘምሩ - ኩርሽም ከረሜላዎች ከአፋቸው ሟሙቶ ሲወርድ - ህፃንነት ፍፅምና መሆኑን አምነው አዛውንቶች አሜን ሲሉ ፥
የበረዶ ጥጥ ብናኞችን አሳበው መላዕክት ሰብ'ን ሲስሙ - የከተማው ካቴድራሎች ስለግርግሙ ንጉሥ ብስራት ሲደውሉ - የተነጠፉ መንገዶች ሁሉ ወደቤት ሲወስዱ - በብልቃጥ የነበረ መንፈስ ተኖ ቤትን ሲሞላ ፥
የዛፉ ላይ ድቡል ኳሶች እየተብረቀረቁ ሲወዛወዙ - ቀያይ ሻማዎች ግለው የቤቱን ድባብ ሲለኩሱ - በቁር ቆፈን ውስጥ የነበሩ ጉንጮች ሲፈግጉ - ልጆቻቸው የታከቡላቸው እናቶች አይን እንደታጠበ ብርጭቆ ሲብለጨልጭ - ሳቆች ተርፈው ወለል ላይ ሲወዳድቁ ፥
በክፍት ልቦች ውስጥ የገባ ንዝረት መልሶ ሲፈስ - ፍልቅልቅ ብላቴኖች ጌታውን እንዳየ ውሻ ከግድግዳ ግድግዳ ሲዘሉ ። ምኞታቸውን ጦምረው የሚመጣውን ሽማግሌ በተስፋ ሲጠብቁ ፥
ቃጭል ያነገቱ አጋዘኖችን በየብስ ሠረገላ እየተጋለቡ ፥ በራማ ጋሪ እየከነፉ ሲመጡ - ጆንያ ተሸካሚው ሽማግሌ ሪዙን እየፈተለ ሲደውል - ቦቲውን እያማታ በየአጥቢያው ሆ'ሆይ ሲል …
ከአንቺ መሆን እመኛለሁ ። አድማስ ተሻግሮ የተኛ ልቤ ፥ ቀኑ ሲደርስ ጠብቆ ይቆሰቆሳል ። Carla Thomas ፥ እየዘፈነች ነው ፥
It's been a long long time ,
Cant' explain why you crossed my mind
I guess it's just to wish you ...
a merry Christmas ❄️
4 957
Listen to the most recent episode of sost kilo podcast: It's Christmas - ሽልም የኮኮብ ዕድ ሳይ •••https://anchor.fm/sostkilo/episodes/Its-Christmas-e1bt9ih 🎙️❄️
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 

