ባርሴሎና ኢትዮጵያ
👏 እምነት፣ ወኔ፣ ፍቅር፣ አልሸነፍ ባይነት የሚንፀባረቅበት የታላቁ ክለብ ባርሴሎና ቻናል ነዉ።
Больше231
Подписчики
-224 часа
-17 дней
+130 дней
- Подписчики
- Просмотры постов
- ER - коэффициент вовлеченности
Загрузка данных...
Прирост подписчиков
Загрузка данных...
00:37
Видео недоступноПоказать в Telegram
Pre-Season Begins! 💪
121123949617533530832.mp42.96 MB
Фото недоступноПоказать в Telegram
ባርሴሎና ብዙ የካሳ ክፍያ ያገኛል !
የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና በዘንድሮው የአውሮፓ ዋንጫ ውድድር ከዩኤፋ ለለቀቃቸው ተጨዋቾች የሚያገኘው የካሳ ክፍያ ከዚህ በፊት ካገኘው የበለጠ እንደሚሆን ተገልጿል።
የባርሴሎናን አራት ተጨዋቾች የያዘችው ስፔን ለአውሮፓ ዋንጫ ፍፃሜ መድረሷን ተከትሎ ክለቡ ከአውሮፓ እግርኳስ ማህበር ከ3.1 ሚልዮን ዩሮ በላይ እንደሚያገኝ ተነግሯል።
የአውሮፓ እግርኳስ ማህበር ተጨዋቾቹ በአውሮፓ ዋንጫ ውድድር በቆዩበት ቀን ልክ በአንድ ቀን 10,000 ዩሮ ለክለባቸው ካሳ የሚከፍል ይሆናል።
Фото недоступноПоказать в Telegram
" ላሚን ያማልን ምቾት ለማሳጣት እንሞክራለን " ራብዮ
የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ራብዮ በነገው የስፔን ጨዋታ ላሚን ያማልን ሜዳ ላይ ምቾት ለማሳጣት ጥረት እንደሚያደርጉ ገልጿል።
አድሪያን ራብዮ በንግግሩም " ላሚን ያማል በጨዋታው ምቾት እንዳይሰማው ለማድረግ እንጥራለን ፣ ለፍፃሜ መጫወት የሚፈልግ ከሆነ ከዚህ በፊት ካደረገው የበለጠ ማድረግ አለበት።"ብሏል።
" ስፔን በውድድሩ የሚጫወተው ምርጥ ቡድን እንደሆነ አይተናል ፣ እነሱ ላይ ምን ማድረግ እንዳለብን እናውቃለን ፣ ተጋጣሚዎቻቸው በነፃነት እንዲጫወቱ ፈቅደውላቸው ነበር።" ራብዮ
Фото недоступноПоказать в Telegram
" ኒኮ ዊሊያምስን የማስፈረም አቅም አለን " ላፖርታ
የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ፕሬዝዳንት ሁዋን ላፖርታ ክለባቸው አሁን ላይ በአውሮፓ ዋንጫው ጥሩ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ የሚገኘውን ኒኮ ዊሊያምስ ማስፈረም እንደሚችል ገልጸዋል።
ኒኮ ዊሊያምስን በጣም አደንቀዋለሁ በማለት የገለፁት ፕሬዝዳንት ሁዋን ላፖርታ " ባርሴሎና በአሁን ሰዓት እሱን የማስፈረም አቅም አለው " ብለዋል።
የ 21ዓመቱ የፊት መስመር ተጨዋች ኒኮ ዊሊያምስ በአትሌቲክ ቢልባኦ ቤት ያለው የውል ማፍረሻ 50 ሚልዮን ዩሮ መሆኑ ተነግሯል።
Фото недоступноПоказать в Telegram
" የክሩስ ጥፋት በእግርኳስ የሚፈጠር ነገር ነው " ፔድሪ
ስፔናዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ፔድሪ ጀርመናዊው አማካይ ቶኒ ክሩስ ለሰራበት ከባድ ጥፋት ላቀረበለት የይቅርታ መልዕክት አመስግኗል።
ፔድሪ በንግግሩም " ቶኒ ክሩስ ለመልዕክትህ አመሰግናለሁ ይህ እግርኳስ ነው የሚፈጠር ነገር ነው ፣ የአንተ የእግርኳስ ህይወት እና ስኬት ለዘለዓለም ይኖራል " በማለት ተናግሯል።
ለብሔራዊ ቡድኑ ደጋፊዎች መልዕክት ያስተላለፈው ፔድሪ " ጀርመን የመጣሁት ለአውሮፓ ዋንጫው ነው ፣ አሁንም ባልጫወትም እስከመጨረሻው እዚህ እቆያለሁ ምክንያቱም ህልም አለን።"ሲል ተደምጧል።
Фото недоступноПоказать в Telegram
ለሊት ላይ በተደረገ የኮፓ አሜሪካ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ኡራጓይ ብራዚልን በመለያ ምት በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ማለፍ ችለዋል።
Rapha😑
Фото недоступноПоказать в Telegram
ሮናልድ አራውሆ ለሊት በተደረግ ጨዋታ ጉዳት አስተናግዶ በ32 ተኛ ደቂቃ ተቀይሮ ወቷል።
Фото недоступноПоказать в Telegram
ትናንት ጆአዎ ፌሊክስ ፔናልቲ ከሳተ በኋላ ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በ IG ፌሊክስን UNFOLLOW አድርጓል።
Фото недоступноПоказать в Telegram
ላሚን ያማል አሁን በዩሮ 2024 የ UEFA የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች ለመሆን ሁለተኛው ተመራጭ ተጫዋች ነው።
Выберите другой тариф
Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.