ru
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

Открыть в Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

Больше
1 721
Подписчики
Нет данных24 часа
-77 дней
-1830 день
Архив постов
Untitled one While her bower eyes cry In the middle of dark day She weaves by the long day She whisper to the blue sky With the powerful word But in her night the pain was obvious and clear Her shadow was scare and fear Not a single air was full of joy, Rather The magic was visible in her tear All her hope was inside the air The sparkle day was off and gone To the far and far away kingdom that won’t be visible to bee seen in trode❤️ May/2020 ©Tina https://t.me/joinchat/AAAAAEwq0Pmw61GSm7UoKQ https://t.me/GitemSitem #Tina’sview #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #poetry #poetrylovers #artinaddis

ፈጣሪ ታረቀን ታረቀን ታረቀን ይሉሀል ቀን ወጥቶ የራቁህ ቀን ወጥቶ ይሹሀል ይሁን እርቀ ሰላም ይሁን ታረቃቸው ቀን የወጣ ዕለት ነው አንተም የራቅሀቸው ©ባንችአየሁ አሰፋ https://t.me/GitemSitem #ባንች_አሰፋ (ባንች) #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #poetry #poetrylovers #artinaddis

በተረፈ ቀን ላይ በተረፈ ሠዐት እንዲህ አስባለሁ:(የሰማይ አዳም(በዘፍጥረት) እውሩ አሟራ, ወይስ ወፏ?) ወፏ መቼ ነው ክረምቷ? እህል ምትዘራበት መቼ ነው መኸሯ የምትወቃበት? መቼ ነው ፀደዯ የምታርምበት? እንጃ! ወፍ እህል በላ ናት? ይደናገረኛል.. እሺ ወፍ ለሰማይ ስንተኛ ልጁ ናት? ዝሪ እጨጂ ብሎ ማይቆነጥጣት ለምን ነው ፏላይ ልጅ አድርጎ ያሳደጋት? ሰማይ ሆይ! ምን በዘፍጥረትህ ከምድር ብትቀድምም አሰትሮ ማኖር፡ ልጅ አስተዳደግን ከታናሽህ ምድር ለምን አትማርም? ©ሳምራዊት ውለታው https://t.me/GitemSitem @gitmnlemadmet #ሳምራዊት_ውለታው #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #poetry #poetrylovers #artinaddis

ውበትን መገዘት ከፊቷ ፀዳል ላይ ጥላ ዐይኑን ጥሎ እድሜ ጅምር ማድያት ከመልኳ ላይ ስሎ ዘመኗ በክንዷ ደርሶ እያሸለበ ጊዜ ደም ግባቷን ገልጦ እያነበበ :: ውበቷን ልትገዝት ትነሳለች ፎቶ . . . የሳር መንገድ ወገብ ይቀራል በፎቶ ተውርጋራጊ ዳሌ ይታተማል ጎልቶ :: ፎቶ አንሺው ጨነቀው ፣ ያልተኖረ ዘመን የሚል የአኳሏን ቃል ከምን ላይ ያስቀምጠው :: ©መቅደስ ሞጎስ https://t.me/GitemSitem #መቅደስ_ሞገስ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #poetry #poetrylovers #artinaddis

ሁለተኛው የ Gitem Sitem - ግጥም ሲጥም ግጥም ሲጥም ፪ አንዱ እና ስራዎቹን እየዘከረች በአጃቢ አጣሚዎቹ ዲበኩሉ ጌታ፣ ሰይፉ ወርቁ፣ እቴናት አወል፣ ወንድማገኝ (የኔ አለም) ፣ ባንቺአየሁ አ
+6
ሁለተኛው የ Gitem Sitem - ግጥም ሲጥም ግጥም ሲጥም ፪ አንዱ እና ስራዎቹን እየዘከረች በአጃቢ አጣሚዎቹ ዲበኩሉ ጌታ፣ ሰይፉ ወርቁ፣ እቴናት አወል፣ ወንድማገኝ (የኔ አለም) ፣ ባንቺአየሁ አሰፋ፣ መንበረማርያም ኃይሉ፣ ፍጹም አበራ፣ ሳምራዊት ውለታው እና ሰይፈ ተማም እንዲሁም ምግባር ሲራጅ፣ ቶማስ አድማሱ፣ ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል እና ሌሎችም ጥማና ተጣጥማ አልፋላች። ትጉንጬ ካፌ እና ሬስቶራንት /Tigunche cafe and Resturant ለመልካም መስተንግዶዋችሁ እና ቤታችንን ስላበጃችሁልን ተመስገኑልን! https://t.me/seifetemam የቀጣዩ 'ራስ' ማን እንደሚሆን ገምቱ #አንዱ_ጌታቸው #1ዱ #ባዶ_ሰው_በባዶ_ቤት #ጥዑምግጥም2 #ግጥማዊቅዳሜ #gietmsitem #poeticsaturdays #Andu_Getachew #DND #artinaddis #poetry #poetrylovers

ሁለተኛው የ Gitem Sitem - ግጥም ሲጥም ግጥም ሲጥም ፪ Andu Getachewን እና ስራዎቹን እየዘከረች በአጃቢ አጣሚዎቹ ዲበኩሉ ጌታ Seifu Worku Etenat Awol የኔ አለም Banchi Assefa Menbi Blaki Hailu Fitsum Abera Samrawit Wuletaw እና Seife Temam እንዲሁም Migbar Siraj THomas Admasu Mitiku Midru ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል እና ሌሎችም ጥማና ተጣጥማ አልፋላጭ። ትጉንጬ ካፌ እና ሬስቶራንት /Tigunche cafe and Resturant ለመልካም መስተንግዶዋችሁ እና ቤታችንን ስላበጃችሁልን ተመስገኑልን! የቀጣዩ 'ራስ' ማን እንደሚሆን ገምቱ

Old Aterira, new page 🙂 በአንዳንድ የአጋች ታጋች ድራማች ምክንያት የቀድሞ የፌስቡክ ፔጃችንን ለመቀየር ተገደናል። የቀድሞ ገፅ ላይ ተልከው ነገርግን እትም16 ላይ ያልተካተተላችሁ ቤተ
Old Aterira, new page 🙂 በአንዳንድ የአጋች ታጋች ድራማች ምክንያት የቀድሞ የፌስቡክ ፔጃችንን ለመቀየር ተገደናል። የቀድሞ ገፅ ላይ ተልከው ነገርግን እትም16 ላይ ያልተካተተላችሁ ቤተሰቦቻችን በአዲሱ ገፅ ወይም እዚሁ ቴሌግራም ላይ (0925749956 ወይም 0911619673) በድጋሜ ብትልኩልን እትም 17 ላይ ለማካተት እንችላላን። አዲሱ ገፃችን፡ facebook.com/AteriraDigital እንዲሁም፡ twitter.com/aterira instagram.com/aterira_digital ላይ ይከተሉን። ለአጤሪራ ይፃፉ... አጤሪራን ያንብቡ... አጤሪራን ለወዳጆ ያጋሩ!

እድሜ ለባንቺ እንዲህ በዱዓ ነበር የጀመርነው #አንዱ_ጌታቸው #ባንቺ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም2 #Andu_Getachew #Banchi #DND #gitemsitem #poeticsaturdays #artinaddis #poetry #poetrylovers

Gitem Sitem is running perfectly
+6
Gitem Sitem is running perfectly

@etenatawol @seifu_worku @ The Horn of Africa International Poetry Festival Ethiopia is well represented! And we have three o
@etenatawol @seifu_worku @ The Horn of Africa International Poetry Festival Ethiopia is well represented! And we have three of the Ethiopians including our Headline Poet, Andu Getachew with us at Gitem Sitem 2 this Saturday

ጥበቃ ሲሰማኝ . . . . . የጸጉር አንዲት ቅንጣት፣ ከመሬት ስታርፍ የምታሰማው ድምጽ፤ ሲትየኝ. . . ዐይንን በባዶ ቦታ ላይ ሲተክሉ፣ የሚወርደው ቀለም አልባ ቅርጽ፤ . . . . . ያድቦለቦልኩት የምራቅ ኳስ፣ ከምላሴ ተነስቶ መሬት ላይ ሲደርስ፤ ፍ . . ዝ . . . ዝ ብዬ ሳይ መቅረትሽ. . . ያኔ ነው የገባኝ። አንዱ ጌታቸው ከባዶ ሰው በባዶ ቤት https://t.me/AndugetachewDnd https://www.youtube.com/channel/UCJI2mmHpHddlQJabYGekFEw #አንዱ_ጌታቸው #1ዱ #ባዶ_ሰው_በባዶ_ቤት #ጥዑምግጥም2 #ግጥማዊቅዳሜ #gietmsitem #poeticsaturdays #Andu_Getachew #DND #artinaddis #poetry #poetrylovers

የዚህ ወር 'ራስ' Andu Getachew ባዶ ሰው በባዶ ቤት የተሰኘች ግሩም የሥነ-ግጥም ስብስብ አለችው። ግድ የላችሁም አንብቧት በዩቱብና ቴሌግራም በምስልና ድምጽ የተቀናበሩ ግጥሞቹንም እንድትቃኟ
የዚህ ወር 'ራስ' Andu Getachew ባዶ ሰው በባዶ ቤት የተሰኘች ግሩም የሥነ-ግጥም ስብስብ አለችው። ግድ የላችሁም አንብቧት በዩቱብና ቴሌግራም በምስልና ድምጽ የተቀናበሩ ግጥሞቹንም እንድትቃኟቸው ተጋብዛችኋል! https://t.me/AndugetachewDnd https://www.youtube.com/channel/UCJI2mmHpHddlQJabYGekFEw ስነ-ግጥም፣ ሙዚቃ፣ የእሳት ዳር ጨዋታዎች፣ ምግብና መጠጥ እንዲሁም ሌሎች መዝናኛዎች አሉን። https://t.me/seifetemam በገለጥነው የኛው ቀለም ጥዑም ግጥም እናጣጥም የ'ራሱ'ንም የራሳቸውንም ግጥም ሊያቀርቡ እንዲሁም ዝግጅቱን ጠዓም ሊዘሩበት የተዘጋጁት አጣሚያን ደግሞ እኚሁላችሁ ! ሰይፉ ወርቁ፣ ዲበኩሉ ጌታ፣ እቴናት አወል፣ ቴዎድሮስ ወንድማገኝ፣ መንበረማርያም ኃይሉ፣ ፍጹም አበራ፣ ባንቺአየሁ አሰፋ፣ ሰይፈ ተማም፣ ሳምራዊት ውለታው እና ሌሎችም ትጉንጬ ካፌ እና ሬስቶራንት /Tigunche cafe and Resturant ካዛንቺስ ኢሲኤ መንገድ ከእፎይ ፒዛ ጀርባ Kazanchis ECA road behind Efoy Pizza http://shorturl.at/blAUY #አንዱ_ጌታቸው #1ዱ #ባዶ_ሰው_በባዶ_ቤት #ጥዑምግጥም2 #ግጥማዊቅዳሜ #gietmsitem #poeticsaturdays #Andu_Getachew #DND #artinaddis #poetry #poetrylovers

ለሚኖሮት ማንኛውም ጥያቄ ሆነ አስተያያት ወደ setaweetmovement@outlook.com መልክት በመላክ የሴታዊትን ቡድን ማግኘት ይችላሉ ፡፡
ለሚኖሮት ማንኛውም ጥያቄ ሆነ አስተያያት ወደ setaweetmovement@outlook.com መልክት በመላክ የሴታዊትን ቡድን ማግኘት ይችላሉ ፡፡

በጦቢያ፣ ሰም እና ወርቅ፣ ግጥማዊ ቅዳሜ እና ሌሎች በርካታ መድረኮች ላይ የምታውቁት ሰይፍሻ የበርካታ ጥዑም ግጥሞች ባለጸጋ ነው። በብዙዎች እንደሚባለው መጽሐፍ ማሳተም እንደመውለድ ከሆነ ይህ ሰው
በጦቢያ፣ ሰም እና ወርቅ፣ ግጥማዊ ቅዳሜ እና ሌሎች በርካታ መድረኮች ላይ የምታውቁት ሰይፍሻ የበርካታ ጥዑም ግጥሞች ባለጸጋ ነው። በብዙዎች እንደሚባለው መጽሐፍ ማሳተም እንደመውለድ ከሆነ ይህ ሰው የ 'ባዶ ሰው በባዶ ቤት' አዋላጅ ሳይሆን አይቀርም። መጽሐፏም ከአርትዖት እስከ መግቢያዋ ከዓይን ያውጣሽ እስከተባለላት ምርቃቷም የ'ርሱ ነች! #ሰይፈ_ወርቅ #Seifu_Worku #አንዱ_ጌታቸው #1ዱ #ባዶ_ሰው_በባዶ_ቤት #ጥዑምግጥም2 #ግጥማዊቅዳሜ #gietmsitem #poeticsaturdays #Andu_Getachew #DND #artinaddis

የገጣሚ ነፍስ የገጣሚ ነፍስ፣ ከእውር መንፈስ ነው ጥሏ፣ ከጽጌሬዳ ውበት ይልቅ - ስለ እሾኋ ሲዘምር። የገጣሚ ነፍስ፣ ከቆሰለ ቀን ነው ጥሏ፣ የሠይፍን መሳል - ለአፎቱ ሲነግር። ከመፀው ነፋስ ነው
የገጣሚ ነፍስ የገጣሚ ነፍስ፣ ከእውር መንፈስ ነው ጥሏ፣ ከጽጌሬዳ ውበት ይልቅ - ስለ እሾኋ ሲዘምር። የገጣሚ ነፍስ፣ ከቆሰለ ቀን ነው ጥሏ፣ የሠይፍን መሳል - ለአፎቱ ሲነግር። ከመፀው ነፋስ ነው ጥሏ፣ በፀሐይ ብርሃን - የጧፏን ጸዳል ሲሰርቃት፤ የገጣሚ ነፍስ ከአምላክ ነው ጥሏ፣ ‘እውነት እኔ ነኝ።’ ሲላት። የገጣሚ ነፍስ ከተረበበ ቅጠል ነው ጥሏ፣ ‘’ዛፉ ላይ እናምጽ” ብላ፤ ከቆራጭ ስትመክር። ከቸር መጽዋች ነው ጥሏ፣ ከማግኘት ጽዋ አጎንጭቷት ስጸክር። . . . . . . . የገጣሚ ነፍስ ከሁሉ ነው ጥሏ ! ከሁሉ ! . . . . . . . ከ. . . ሁ. . . ሉ. . . ! አንዱ ጌታቸው ከባዶ ሰው በባዶ #አንዱ_ጌታቸው #1ዱ #ባዶ_ሰው_በባዶ_ቤት #ጥዑምግጥም2 #ግጥማዊቅዳሜ #gietmsitem #poeticsaturdays #Andu_Getachew #DND #artinaddis

የገጣሚ ነፍስ የገጣሚ ነፍስ፣ ከእውር መንፈስ ነው ጥሏ፣ ከጽጌሬዳ ውበት ይልቅ - ስለ እሾኋ ሲዘምር። የገጣሚ ነፍስ፣ ከቆሰለ ቀን ነው ጥሏ፣ የሠይፍን መሳል - ለአፎቱ ሲነግር። ከመፀው ነፋስ ነው ጥሏ፣ በፀሐይ ብርሃን - የጧፏን ጸዳል ሲሰርቃት፤ የገጣሚ ነፍስ ከአምላክ ነው ጥሏ፣ ‘እውነት እኔ ነኝ።’ ሲላት። የገጣሚ ነፍስ ከተረበበ ቅጠል ነው ጥሏ፣ ‘’ዛፉ ላይ እናምጽ” ብላ፤ ከቆራጭ ስትመክር። ከቸር መጽዋች ነው ጥሏ፣ ከማግኘት ጽዋ አጎንጭቷት ስጸክር። . . . . . . . የገጣሚ ነፍስ ከሁሉ ነው ጥሏ ! ከሁሉ ! . . . . . . . ከ. . . ሁ. . . ሉ. . . ! አንዱ ጌታቸው ከባዶ ሰው በባዶ

Meet this Drum addict, Fitz who loves playing drum since childhood. Though he was a reserved and shy kid, he used to express
Meet this Drum addict, Fitz who loves playing drum since childhood. Though he was a reserved and shy kid, he used to express his thoughts through arts, he loves to sketch, sculpt, and drum. He studied architecture, which he considers as one stream of art. #ፍጹም_አበራ #ግጥምሲጥም #ጥዑምግጥም2 #ግጥማዊቅዳሜ #አንዱ_ጌታቸው #ባዶ_ሰው_በባዶ_ቤት #Fitsum_Abera #Djembe #gietmsitem #poeticsaturdays #Andu_Getachew #DND #artinaddis

...👓 . የሚያምር ነገር _ለምን ይሞታል ? የቀረኝ ስባሪ ልብ ነው ያጣሁሽ ዓይኔ ተሸፍኖ ሲገለጥ ባለ ቅፅበት - ባለ ቅጥፈት ነው ። ............. የቡና ፍቅሬን የጠላ ፍቅርሽ ያህል ብንዋደድ _ብዬ አሰብኩ ስንለያይ _ እንደ ውሻ አፍንጫ ቀዘቀዝኩ ። ... ህመሜ እስከማትወጂ ድረስ የወደድሽ ነገር ትግሌ ነበር ውስጥ እንደልከትሽ ነበር ። .. አውቃለሁ ግማሽ ሞት ነው _ መርጦ ማሞገስ አውቃለሁ ግማሽ ሞት ነዉ _በጋራ መውቀስ ታውቂያለሽ በጣም ረዥሙ መንገድ _ ወደ ኃላ መመለስ ።. . .(ወየው ..... ምኞታችን ከግብ _ ግባችን ከስራ አልገጠመ በርግጥ መውደቅ _ ሁለተኛ ስማችን ሆኖ ቀጠለ ። . #1ዱ (2012) #አንዱ_ጌታቸው #ባዶ_ሰው_በባዶ_ቤ #ግጥምሲጥም #ጥዑምግጥም2 #ግጥማዊቅዳሜ #gietmsitem #poeticsaturdays #Andu_Getachew #DND #artinaddis

መንቢ ከጥዑም አቀራረቧ ጋር ዝማሬዋን ከንባብ ንባብዋን ከዝማሬ የማትነጥል ሰናኝ ነች! በተለያዩ መድረኮች ላይ የምታውቋት በእኛም ላይ አግኟት እስካሁን ካላወቃችኋት ግን እንኋትላችሁ! #መንበረማርያም
መንቢ ከጥዑም አቀራረቧ ጋር ዝማሬዋን ከንባብ ንባብዋን ከዝማሬ የማትነጥል ሰናኝ ነች! በተለያዩ መድረኮች ላይ የምታውቋት በእኛም ላይ አግኟት እስካሁን ካላወቃችኋት ግን እንኋትላችሁ! #መንበረማርያም_ኃይሉ #ግጥምሲጥም #ጥዑምግጥም2 #ግጥማዊቅዳሜ #አንዱ_ጌታቸው #ባዶ_ሰው_በባዶ_ቤት #Menberemariam_Hailu #gietmsitem #poeticsaturdays #Andu_Getachew #DND #artinaddis