ru
Feedback
G-Tutorialclass

G-Tutorialclass

Открыть в Telegram

Impossible is possible with learning & reading.

Больше
904
Подписчики
Нет данных24 часа
-57 дней
-1530 дней
Архив постов
+2
OS Chapter 1- Introduction.ppt

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ከጥር 15 ጀምሮ ባሉት ቀናት ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል። በርካታ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በሁለት ዙር ለመጀመሪያ ጊዜ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተሰጠው የ
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ከጥር 15 ጀምሮ ባሉት ቀናት ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል። በርካታ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በሁለት ዙር ለመጀመሪያ ጊዜ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ የሚደረግበትን ቀን እየጠየቁ ይገኛሉ። በቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የመልዕክት መቀበያ አድራሻም እጅግ በርካታ መልዕክቶች ከውጤት ጋር ተያይዞ ከተማሪዎች እና በተማሪ ወላጆች ደርሶናል። የፈተናው ውጤት መዘግየቱን የሚገልፁት ተማሪዎች እና ወላጆች ትምህርት ሚኒስቴር ውጤቱ መቼ ይፋ እንደሚደረግ እንዲያሳውቅ ጠይቀዋል። " የትምህርት ዓመቱ እየገፋ ነው ፤ ገና ከውጤት በኃላ ምደባ አለ ፤ ልጆቻችን ከመደበኛ ትምህርት ርቀው ቤት ከሆኑ በርካታ ሳምንታት አልፈዋል ፤ የሁሉም ውጤት ከ2ኛ ዙር ተፈታኞች ጋር ይገለፃል ቢባልም ዛሬም ድረስ ቀኑ መቼ እንደሆነ አይታወቅም ፤ የተማሪዎችን የትምህርት ዓመት ታሳቢ በማድረግ ቀኑ ቢገለፅ " ሲሉ ወላጆች መልዕክታቸውን ልከዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ውጤት መቼ እንደሚገለፅ ለማወቅ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችን ለማግኘት ጥረት አድርጓል። መልዕክት የላኩልን አንድ የትምህርት ሚኒስቴር አመራር ፤ ምንም እንኳን ቁርጥ ያለው የውጤት መግለጫ ቀን ባይታወቅም ነገር ግን ከጥር 15 ጀምሮ ባሉት ቀናት ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል። ለመጀመሪያ ጊዜ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የተሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ930 ሺ በላይ ተማሪዎች መውሰዳቸው መገለፁ የሚዘነጋ አይደለም። Via Tikvah @Free_Education_Ethiopia Stay Safe!

በመጪው ሰኔ ከ256 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ይሰጣል። ለተመራቂ ተማሪዎቹ የመውጫ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ የትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። ከመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት 146 ሺህ እና ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት 110 ሺህ በድምሩ ለ 256 ሺህ ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና እንደሚሰጥ በሚኒስቴሩ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) ለኢፕድ ገልጸዋል። የፈተናውን መመሪያ ሰነድ ከማዘጋጀት ጀምሮ ለፈተናው የሚያስፈልጉ ነገሮችን የማሟላት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል። በዩኒቨርሲቲዎች ያለውን የኮምፒዩተር አቅርቦት እና የተፈታኞች ብዛት በመለየት የመውጫ ፈተናውን በኦንላይን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል። ሚኒስቴሩ ለፈተናው መሳካት ከኢትዮ ቴሌኮም እና ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ጋር በቅንጅት ይሠራል ብለዋል። https://t.me/Timhrtministers

📢 በዚህ አመት 12ተኛ ክፍል የተፈተኑ ተማሪዎች አቤቱታ ነው። ❗️ይድረስ ለትምህርት ሚኒስቴር!!! እኛ የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መግቢያ ፈተና ተፈታኞች ይኸው ፈተና ከተፈተንን አራት ድፍን ወራት ተቆጥረዋል። ነገር ግን ትምህርት ሚኒስቴር "ውጤት የሚለቀቀው የሁለተኛው ዙር ፈተና ከተሰጠ በኋላ ነው" የሚል መረጃ አውጥቶ ነበር። እኛም ይሁን ብለን በተለያዩ ምክንያቶች ፈተና ሳይፈተኑ የቀሩ እህት ወንድሞቻችን ይፈተኑ ብለን  በትዕግሥት ስንጠባበቅ ነበር😊  እንደሚታወቀው የሁለተኛው ዙር ፈተና ከታህሳስ 18 እስከ 21/2015 ዓ.ም እንደተሰጠ ይታወቃል።ነገር ግን ትምህርት ሚኒስቴር ሁለተኛው ዙር ፈተና ከተሰጠ በኋላ በሁለት ሳምንት ውስጥ የሁለቱንም ዙር ውጤት ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቆ ነበር። ነገር ግን የሁለተኛው ዙር ፈተና ከተሰጠ ይኸው ሁለት ሳምንታት ተቆጥረዋል ነገር ግን እስካሁን ውጤታችንን ማየት አልቻልንም። ስለዚህ ትምህርት ሚኒስቴር በአስቸኳይ ውጤታችንን ይፋ እንዲያደርግልን እናሳስባለን!!!  በተያያዘም ከታች ለቀረቡት ጥያቄዎች ትምህርት ሚኒስቴር በአስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጥበት እናሳስባለን‼️ 📌 ትምህርት ሚኒስቴር ቃል በገባው መሠረት ውጤት በአጭር ጊዜ ውስጥ ይፋ አደርጋለሁ ብሎ ነገር ግን እስካሁን ምንም ፍንጭ የለም ለምንድነው?? 📌 ውጤታችን የሚገለፅበት ትክክለኛው ቀን መቼ ነው?? 📌 ውጤት እስካሁን የዘገየበት ምክንያት ግልጽ ይደረግልን!! 📌 ትምህርት ሚኒስቴር በአስቸኳይ አቤቱታችንን ተቀብሎ መልስ ይስጠን ጊዜያችን በከንቱ እየባከነ ነው ስለዚህ አፋጣኝ ምላሽ ይሰጠን!!! ሁላችሁም ይህን መልዕክት ለሁሉም Share Share በማድረግ ሀላፊነታችሁን እንድትወጡ እናሳስባለን!!! 🎖📖🎖 @aplusacademyy @aplusacademyy ▬▬▬▬▬▬▬▬

📢 በዚህ አመት 12ተኛ ክፍል የተፈተኑ ተማሪዎች አቤቱታ ነው። ❗️ይድረስ ለትምህርት ሚኒስቴር!!! እኛ የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መግቢያ ፈተና ተፈታኞች ይኸው ፈተና ከተፈተንን አራት ድፍን ወራት ተቆጥረዋል። ነገር ግን ትምህርት ሚኒስቴር "ውጤት የሚለቀቀው የሁለተኛው ዙር ፈተና ከተሰጠ በኋላ ነው" የሚል መረጃ አውጥቶ ነበር። እኛም ይሁን ብለን በተለያዩ ምክንያቶች ፈተና ሳይፈተኑ የቀሩ እህት ወንድሞቻችን ይፈተኑ ብለን  በትዕግሥት ስንጠባበቅ ነበር😊  እንደሚታወቀው የሁለተኛው ዙር ፈተና ከታህሳስ 18 እስከ 21/2015 ዓ.ም እንደተሰጠ ይታወቃል።ነገር ግን ትምህርት ሚኒስቴር ሁለተኛው ዙር ፈተና ከተሰጠ በኋላ በሁለት ሳምንት ውስጥ የሁለቱንም ዙር ውጤት ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቆ ነበር። ነገር ግን የሁለተኛው ዙር ፈተና ከተሰጠ ይኸው ሁለት ሳምንታት ተቆጥረዋል ነገር ግን እስካሁን ውጤታችንን ማየት አልቻልንም። ስለዚህ ትምህርት ሚኒስቴር በአስቸኳይ ውጤታችንን ይፋ እንዲያደርግልን እናሳስባለን!!!  በተያያዘም ከታች ለቀረቡት ጥያቄዎች ትምህርት ሚኒስቴር በአስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጥበት እናሳስባለን‼️ 📌 ትምህርት ሚኒስቴር ቃል በገባው መሠረት ውጤት በአጭር ጊዜ ውስጥ ይፋ አደርጋለሁ ብሎ ነገር ግን እስካሁን ምንም ፍንጭ የለም ለምንድነው?? 📌 ውጤታችን የሚገለፅበት ትክክለኛው ቀን መቼ ነው?? 📌 ውጤት እስካሁን የዘገየበት ምክንያት ግልጽ ይደረግልን!! 📌 ትምህርት ሚኒስቴር በአስቸኳይ አቤቱታችንን ተቀብሎ መልስ ይስጠን ጊዜያችን በከንቱ እየባከነ ነው ስለዚህ አፋጣኝ ምላሽ ይሰጠን!!! ሁላችሁም ይህን መልዕክት ለሁሉም Share Share በማድረግ ሀላፊነታችሁን እንድትወጡ እናሳስባለን!!! 🎖📖🎖 @aplusacademyy @aplusacademyy ▬▬▬▬▬▬▬▬

+4
🎯 Global power points. NEW🤗 ⭕️TOP STUDENTS " TOPPERS HOME" #ለፈጣን እና ታማኝ መረጃ 👇👇👇👇👇👇 #share #share 🙏🙏🙏🙏🙏 🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝 ▶️🌟💧@ethio_schools ▶️🌟💧@ethio_schools ▶️🌟💧@ethio_schools 🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝

Civic Mid Exam – Debre Berhan University – Campus Handout

የ 12ኛ ክፍል ውጤትን አስመለክቶ በርካታ ጥያቄዎች እየደረሱን ስለነበር ከሚመለከተው አካል ለማጣራት ሞክረን ነበር። ከትምህርት ሚኒስቴር አካላት የተሰጠን መልስ የ1ኛ ዙር ፈተና እርማት ተጠናቋል።
የ 12ኛ ክፍል ውጤትን አስመለክቶ በርካታ ጥያቄዎች እየደረሱን ስለነበር ከሚመለከተው አካል ለማጣራት ሞክረን ነበር። ከትምህርት ሚኒስቴር አካላት የተሰጠን መልስ የ1ኛ ዙር ፈተና እርማት ተጠናቋል። አሁን የ 2ኛው ዙር እርማት እየተደረገ ነው። ስለዚህ የተማሪዎች ውጤት ወደ ሲስተሙ ከገባ ቡሃላ ለተማሪዎች ይፋ ይሆናል። ትክክለኛው ይፋ የሚሆንበት ቀን መቼ ነው? እስካሁን ይህ ነው የሚል ቀን አልተወሰነም። ነገር ግን በቅርቡ ይፋ ይሆናል። ተማሪዎች መታገስ አለባቸው ። ውጤቶች ላይ ምንም ስህተት እንዳይኖር ጥንቃቄዎች ከተሰወዱ ቡሃላ ይለቀቃል።

ባልና ሚስት ተጣልተው ለፍቺ ፍርድ ቤት ይቆማሉ ዳኛው፦ 3 ልጆች አሏችሁ እንዴት ነው የምትካፈሉት? ባል ናሚስት ለብዙ ግዜ ከተማከሩ በዃላ፤ 'የተከበረው ፍርድ ቤት ፤ አንድ ልጅ ጨምረን ቀጣይ አመት ለመመለስ ተስማምተናል።' * * * * * * የሚገርመው ከ 9ወር በዃላ መንታ ተገላግላ አረፈችው።😆😆 መቼ ይፋቱ ይሆን።፨፨፨፨ 👍 እና share ግድ ነው Join us for more @feta_enebel

የህይወት ጎበዝ ሁን! ከክፍል አንደኛ መውጣትህ፣ ሰቃይ ተማሪ መሆንህ፣ በማዕረግ መጨረስህ- በህይወትህ ስኬታማ እንድትሆን ዋስትና ይሆንሃል ማለት አይደለም። በኢኮኖሚክስ በማዕረግ ልትመረቅ ትችል ይሆናል፣ ይሁንና ከሁሉ የተሻለ ገቢ ታገኛለህ ማለት አይደለም። ጎበዝ የህግ ተማሪ ነበርክ ማለት ጎበዝ ጠበቃ ትሆናለህ ማለትም አይደለም። ይሀውልህ፤ ህይወት- ፅንሰ ሃሳብን (concept) ከመረዳት፣ ነገሮችን ከማስታወስ (Memoriase ize)ና፣ ፈተና ላይ ከመተግበር (reproduce) በላይ አቅም ትፈልጋለች። • ትምህርት ቤቶች፣ ሰዎችን 'ለማስታወስ ችሎታቸው' ዕውቅና ሲሰጡ፤ ህይወት ግን፣ ሰዎችን 'ለተግባራቸው' ዕውቅና ትሰጣለች። • ትምህርት ቤቶች ማስጠንቀቂያ (caution) ሲሰጡ፤ ህይወት ግን ድፍረትን ትሰጣለች። • ትምህርት ቤቶች በ"ደንብ" የሚኖሩትን ሲያመሰግኑ፤ ህይወት ግን ደንብን ጥሰው፣ አዲስ ህግን ያስቀመጡትን ታወድሳለች። ታዲያ ሰዎች በትምህርት ቤት ጠንክረው መማር የለባቸውም እያልኩ ነው?- በፍፁም። መማርህ የግድ ነው። ይሁንና "አንደኛ" ለመውጣት ብለህ ሌሎች ነገሮችን ሁሉ መስዋእት አታድርግ እያልኩህ ነው። ያንተ ጉብዝና በ10ኛ ክፍል ውጤት አዘለለህ፣ በ12ኛ ክፍል ውጤት አስፈነደቀህ፣ በከፍተኛ ትምህርት ውጤትህ አስወደሰህ...ከዛስ? - ከዛማ ቅጥረኛ ሆነሃል። የወር ደሞዝ ትጠብቃለህ፣ ፍቃድህ በአለቃህ (ሰቃይ ተማሪ ባልነበረው) ላይ ወድቋል። ትላንት ግብረገብ ላይ ጥሩ ሆኖ በሌላ ዘርፍ ግን ደክሞ የናቅከው ተማሪ፣ ዛሬ የሞራል አለቃህ (የሃይማኖት ሰው) ሆኖ ይመራሃል፤ ትላንት ስነ-ዜጋ ላይ በርትቶ በሌላው ግን ደክሞ የተቸኸው ተማሪ፣ ዛሬ ባለስልጣን ሆኖ አጠገቡ ለመድረስ የምትናፍቀው ሰው ሆኗል፤ ትላንት ስእልና ሙዚቃ ላይ ጊዜውን እያጠፋ በሌላው ግን ስለደከመ የናቅከው ተማሪ፣ ዛሬ የምታደንቀው አርቲስት ነው፤ ትላንት ሽቦ ሲወጥር፣ እንጨት ሲቆርጥ- ከነጓደኞችህ ያሾፍክበት ተማሪ፣ ዛሬ እርሱ ጋር ለመቀጠር በብርቱ የምትፈልገው የትልቅ ኢንዱስትሪ ባለቤት ሆኗል። የትምህርቱ ጎበዝ በህይወት ጎበዞች ተበልጠሃል። ዛሬ ላይ ቆመህ የነርሱን ህይወት ትናፍቃለህ። ደስታህ በደስታቸው፣ ሀዘንህ በሀዘናቸው ላይ ተመሥርቷል። አሁንም ግን ጊዜው አልረፈደም። እስትንፋስህ እስካለች ህይወት ትቀጥላለች። ራስህን በክፍል አትገድበው፤ በምግባርህ ጎልተህ ውጣ፤ የመሪነቱንም ድርሻ ውሰድ። እስቲ የንግድ ሥራ ጀምርና አይሳካልህ፣ ብዙ አማራጮችን ትቀስምበታለህ። ለምርጫ ተወዳደርና ተሸነፍ፣ የፓለቲካ ሳይንቲስት የማያስተምርህን ነገር ያስተምርሃል። ውስጥህ ያለውን ተሰጥኦ አውጣውና ይታይ፣ አጎልብተውም፤ በሙያህ ዘርፍ ብቻ ሳትገደብ መፅሐፍትን አንብብ፣ ያመንክበትን ነገርም አድርግ። በቃ! ጎበዝ ተማሪ ለመሆን ከማሰብ ይልቅ፣ ጎበዝ ሰው ለመሆን አስብ። ትምህርት ቤትህን አለምህ አታድርገው፣ አለምህን ትምህርት ቤትህ እንጂ!። ልብ በል፤ ፈጣሪም የሚረዳው የሚሞክሩትን ነው። ከሰማይ ይልቅ በምድር ያስቀመጠህም በአላማ ነው። የምትበርበት ክንፍ ያልሰጠህ አውሮፕላን ሰርተህ እንድትበር፣ ተሽከርካሪ እግር ያላደለህ መኪና ሰርተህ እንድትሽከረከር ነው። ከርሱ ዘንድ፣ በየቀኑ የሚሰጥህን ዕድል ያለመሰሰት ተጠቀምበትና የህይወት ጎበዝ ሁን! ስለዚህ አንድ ምክር ልምከራቹ በሰዎች ሳይሆን በራሳቹ ተመሩ። ምክንያቱም እናንተ ሰው እንጂ ወንዝ አደላችሁም። ግቢ ውስጥ በራሳችሁ ዛቢያ ተንቀሳቀሱ። ሌሎችን አታዳምጡ ማለቴ ግን አደለም። የህይወት መንገዳችሁን ራሳችሁ ምረጡ መክሊታችሁንም እንደዛው። በቀጣይ አመት የህይወታችሁን ወሳኝ ምዕራፍ ትወስናላችሁ። ማለትም የ ዲፓርትመንት ምርጫ። እዚክ ላይ እራሳችሁን እወቁ ምን መሆን እችላለሁ ምን ያስፈልገኛል የሚለውን ልባችሁን አዳምጡ። ግን ከሁሉም በላይ የህይወት ጎበዝ ሁኑ። ©Berhanu ከGondar university 🎖📖🎖 @aplusacademyy @aplusacademyy ▬▬▬▬▬▬▬▬

📚 Addis Ababa University. 📚 Logic Mid Exam. ━━━━━━━━━━━━ 🎯 Join & Share @Aconcise 🎯 Contact & Ads @Concise_bot ━━━━━━━━━━
+3
📚 Addis Ababa University. 📚 Logic Mid Exam. ━━━━━━━━━━━━ 🎯 Join & Share @Aconcise 🎯 Contact & Ads @Concise_bot ━━━━━━━━━━━━

📚 Anthropology Mid Exam 2014. 📚 Hawassa University. 📌 Join and Share 👇👇👇 @Aconcise @Aconcise
+1
📚 Anthropology Mid Exam 2014. 📚 Hawassa University. 📌 Join and Share 👇👇👇        @Aconcise        @Aconcise

📚 Addis Ababa University. 📚 Global trend mid exam 2014. 📌 Join and Share 👇👇👇 @Aconcise @Aconcise
+3
📚 Addis Ababa University. 📚 Global trend mid exam 2014. 📌 Join and Share 👇👇👇        @Aconcise        @Aconcise

የዩኒቨርሲቲ ምደባ እንዴት ይሰራል⁉️ የዩኒቨርሲቲ ምደባ የሚሰራው እንደድሮው ጊዜ በቀጥታ በሰዎች ሳይሆን ዘመናዊ እና አለምአቀፋዊ ተቀባይነት ባለው ማሽን ነው። ታድያምደባው ሲካሄድ በዋነኝነት የተማሪዎችን ውጤት መሰረት በማድረግ ነው፡፡ ይኸውም:- ምደባው በቅድሚያ ምደባውን ለሚያከናውነው ማሽን እነዚህ የመረጃ ግብዓቶች inpute ይሰጡታል። እነሱም 👉 ከመቁረጫ ነጥብ በላይ ያመጡ  ተማሪዎች ስም ዝርዝር 👉 የዩኒቨርሲቲዎች የመቀበል አቅም 👉 የመቁረጫ ነጥብ 👉 የተማሪዎች ውጤት 👉 PHASE (ምድብ) PHASE  ማለት ለምሳሌ እነሱ inpute ሲያስገቡ PHASE 1 ከ አንደኛ ምርጫ እስከ አምስተኛ ምርጫ PHASE 2 ከ አምስተኛ ምርጫ እስከ አስረኛ ምርጫ ወ.ዘ.ተ እያለ እንዲሰጥ አድርገው program ያደርጉታል ማለት ነው። ከላይ ያሉት የመረጃ ግብዓቶች ከገቡለት በኋላ ማሽኑ 1⃣ የተማሪውን ውጤት (ነጥብ) 2⃣ የተማሪውን የምደባ ምርጫ አሞላል 3⃣ የዩኒቨርሲቲዎች የመቀበል አቅምን መሰረት በማድረግ ተማሪዎችን ይመድባል፡፡ በዚህ መልኩ ምደባ ሲሰራ እነሱ ብቻ በሚያውቁት scale መሰረት: ➖ በጣም ጥሩ ውጤት ያመጣ ተማሪ PHASE = ONE , CHOICE = ONE ይደርሰዋል ማለት ነው። ማለትም የመጀመሪያ ምድብ የመጀመሪያ ምርጫ ማለት ነው፡፡ ➖ ከዚያ scale ቀጥሎ ያመጣ ተማሪ ደግሞ:  PHASE = 1 , CHOICE = 2 ይደርሰዋል ማለት ነው። ማለትም የመጀመሪያ ምድብ ሁለተኛ ምርጫ ማለት ነው። የምደባ ውጤት በቅርብ ቀናት ውስጥ ይፋ ይደረጋል። 🎖📖🎖 @aplusacademyy @aplusacademyy ▬▬▬▬▬▬▬▬

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!

Anthropology Mid Exam – Wollo University – Campus Handout

Civic Mid Exam – Debre Tabor University – Campus Handout

Geography Test One – Hawassa University – Campus Handout

📚 Communicative English Skill II. 📚 Unit 2 - Speculation about the Future of Science. 📚 Grammar - Future Tenses. 🙌 እሺ ተወዳጆች ሆይ እንዴት ናችሁ😊❓unit 2 ላይ እንግዲህ እስካሁን ስለ Present Continuous(Present Progressive) Tense እና ስለ Simple Future Tense ተምረናል። ዛሬ ደግሞ ስለ Going to እንማራለን። በሌላ አባባል የ will እና የ going to ልዩነትን እንመለከታለን ማለት ነው። ፈተና ስለሚወጣበት በደንብ ተረዱት🙏። ዳይ ወደ ክላስ attendance ይያዛል መቅረት አይቻልም😁። 📚 Will Vs Going to 🔷 1) Going to is used to express planned future action.(intentions). 🎯 ወደፊት ወይም future ላይ ለሚከናወነው ድርጊት ፡ ዛሬ ላይ ዕቅድ ከወጣለት ወይም program ከተያዘለት፡ ያ ወደ ፊት ለመከናወን ዛሬ ወይም አሁን ላይ ዕቅድ የወጣለትን ድርጊት በ Going to ይገለፃል ማለት ነው። ስለዚህ ሁለት ሀሳቦችን ልንረዳ ይገባል። 🔰 ሀሳብ 1 - ወደፊት ወይም future ላይ የሚከናወነው ድርጊት። 🔰 ሀሳብ 2 - ወደፊት ወይም future ላይ ለሚከናወነው ድርጊት ዕቅድ መውጣቱ ወይም program መያዙ። 🎯 ስለዚህ ወደፊት ለሚከናወነው ድርጊት አሁን ዕቅድ መውጣቱ ወይም program መያዙ ፡ Going to እንድንጠቀም ያስገድደናል። ስለዚህ Going to እና Present Progressive የሚያመሳስላቸው ወይም አንድ የሚያደርጋቸው አገልግሎት አለ። ሁለቱም planned future action ንን ነው የሚገልፁልን። 🌹 Examples 1 📚 ምሳሌ፡ ኮሮና ከጠፉ በሗላ ላሊበላን ለመጎብኘት ዕቅድ ካወጣህ ወይም program ከያዝክ፡ 🔰 ሀሳብ 1 - ወደፊት የሚከናወነው ድርጊት ማለትም ኮሮና ከጠፉ በሗላ ላሊበላን መጎብኘት። 🔰 ሀሳብ 2 - ወደፊት ለሚከናወነው ድርጊት ማለትም ላሊበላን ለመጎብኘት አሁን ላይ ዕቅድ ወይም program መያዝህ። ስለዚህ፡ ✈️ I am going to visit Lalibela after corona Virus. ✈️ I am visiting Lalibela after Corona Virus. 📚 ሁለቱም ምሳሌዎች possible ናቸው። ትርጎማቸውም፡ ከኮረና በሗላ ላሊበላን እጎበኛለሁ ማለት ነው። 🌹 Example 2 ✅ ለምሳሌ - ክላስ ውላችሁ ወደ ዶርም ስትመለሱ ዶርሙ ቆሽሿል😢። 🙆‍♀🙆‍♂ኸረ ዶርሙ ቆሽሿል። ነገ ማፅዳት አለብን ብላችሁ ወሰናችሁ ወይም ዕቅድ ያዛችሁ። ስለዚህ ነገ ለማፅዳት ዕቅድ ስለያዛችሁ በ Going to ትገልፁታላችሁ ማለት ነው። ስለዚህ🙇‍♂ 🚰🛁 The Dorm is Very dirty. We are going to clean it tommorow. 🔶 2) Going to is used to predict the future on the basis of the present evidence.( predictions based on current circumstance). 🎯 አሁን ላይ(present) ያለውን ተጨባጭ ማስረጃ መሰረት በማድረግ ስለ ወደፊቱ ለመተንበይ Going to ን እንጠቀማለን። ስለዚህ ሁለት ሀሳቦችን እንረዳ😎። 🔰 ሀሳብ 1 - ወደፊት(future) ላይ ይከናወናል ወይም አይከናወንም ተብሎ የተተነበየው ድርጊት። 🔰 ሀሳብ 2 - ድርጊቱ ወደፊት(future) ይከናወናል ወይም አይከናወንም ተብሎ ለተተነበየው ድርጊት አሁን(present) ላይ ያለው ተጨባጭ ወይም በቂ ማስረጃ። ስለዚህ😊 🎯 ወደፊት ይከናወናል ወይም አይከናወንም ተብሎ ለተተነበየው ድርጊት አሁን ላይ ያለን ማስረጃን መሰረት አድርጎ ከተነነበዬ፡ ያ ወደፊት(future) ላይ ይከናወናል ወይም አይከናወንም ተብሎ የተነነበዬው ድርጊት በ Going to ይገለፃል ማለት ነው። 🌹 Example 1 ✅ አንተና ጓደኛህ walk እያረጋችሁ፡ ከዛ አንተ ወደ ሰማይ ቀና ስትል፡ ዳመናው በጣም ዳምኗል ወይም ጠቁሯል። ከዛ ጓደኛህን ተመልከት፡ የጠቆረውን ደመና፡ ዝናብ ሊዘንብ ነው አልከው። ስለዚህ 🔰 ሀሳብ 1 - ወደፊት ይከናወናል ብለህ የተነበይከው ድርጊት ማለትም ዝናብ ሊዘንብ ነው ብለህ መተንበይህ ወይም predict ማድረግህ። 🔰 ሀሳብ 2 - ዝናብ ሊዘንብ ነው ብለህ ለመተንበይህ አሁን ላይ ያለው ማስረጃ ማለትም ደመናው መጥቆሩ። ስለዚህ😎 🙌ዝናብ ሊዘንብ ነው ብለህ ለመተንበይህ ደመናው መጥቆሩ ማስረጃ ስለሆነ፡ ትንቢትህን በ Going to ትገልፀዋለህ ማለት ነው። 🌧🌨 Look at the dark clouds. It is going to rain. 🌹 Example 2 ✅ አንተ ጥሩ ስሜት እየተሰማህ አይደለም። ጥሩ ስሜት ስላልተሰማህ ለጓደኛህ ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ አይደለም ሊያመኝ ነው መሰል አልከው። ስለዚህ፡ 🔰 ሀሳብ 1 - ወደፊት ይከናወናል ብለህ የተነበይከው ማለትም መታመምህ። 🔰 ሀሳብ 2 - ልታመም ነው ብለህ ለመተንበይ አሁን ላይ ያለህ ማስረጃ ማለትም ጥሩ ስሜት አለመሰማትህ። ስለዚህ ፡ 😣😫 I feel bad. I am going to sick. 🙌 የዛሬውን ክላስ ከመጨረሳችን በፊት የትናንትናው ትምህርት ላይ አንድ የረሳሁት ነገር አለ። ትናንት ስለ Simple future tense ተምረናል አይደል። አንዲት የተረሳች ነገር አለች ሞጁላችሁ ላይ ያለች። እርሷም👇 📚 Simple Future Tense is used to express Future Facts. 🎯 ወደፊት(future) የሚከናወኑ ነባራዊ ዕውነታዎችን በ simple future እንገልፃቸዋለን። ለምሳሌ አሁን ህዳር ወር ላይ ነን። የሚቀጥለው ወር ደግሞ ታህሳስ ነው። so, ⏱ The Next Month will be December. 🙌 የዛሬውን ክላስ በዚህ ጨረስን። ነገ ስለ simple present ተምረን chapter 2 ን እንጨርሳለን። ከዛ ቀጣይ ሳምንት Mid Exam ፈተና ትፈተናላችሁ። ከፍተኛ ውጤት ላመጡ 3 ተማሪዎች ሽልማት ይኖረናል። 📌 መልካም ቀን❗️ ©A+ Tutorial Class. © Your Success is guaranted with A+ Tutorial Class. ━━━━━━━━━━━━ 📚 JOIN :@GTutorialclass JOIN :@GTutorialclass