cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

اللهم ثبتنا على الحق(التوحيد أولآ)

السلفية منهجنا

Больше
Страна не указанаЯзык не указанКатегория не указана
Рекламные посты
269
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

እራስን መመልከት ~~~~~~ እየውልህ ወንድሜ! ህሊና አልባ በድን ማሽን አትሁን። የምትገባው ከራስህ እንጂ ከኡስታዝህ ቀብር አይደለም። ሲራጥን የምትሻገረው በራስህ ስራ መጠን እንጂ ኡስታዝህ እጅህን ይዞ አያሻግርህም። ያለ አስተርጓሚ ራቁትህን ከጌታህ ፊት ለምርመራ ስትቆምም ኡስታዝህ ከጎንህ አይቆምልህም። ይህንን ሁሉ የምልህ ማንንም በጭፍን እንዳትከተል ነው። በአሁኑ ሰዓት በየሰፈሩ ያሉ ሸይኾችና ኡስታዞች አብይ መታወቂያ ጭፍንነትን ሥራዬ ብለው የሚግቱ፣ ተማሪዎቻቸውን በጭፍንነት የሚኮተኩቱ መሆናቸው ነው። የወደዱትን በጭፍን እንድትወድላቸው፣ የጠሉትን በጭፍን እንትጠላላቸው እስከ ደም ጠብታ ይታገሉሃል። ቁርኣን፣ ሐዲሥ፣ የዑለማእ ንግግር ተንኮለኛ በሆነ መልኩ ከአውድ ውጭ እያገናኙ የሃሳብ ሽብር ይነዙብሃል። እዚህ ላይ "ለምሳሌ እነ እንትናን ብንወስድ… " ብዬ ባጣቅስ የእነ እንትና ጭፍራ ጦር ሰብቆ ይነሳል። ከነሱ ውጭ ያለው ደግሞ በአመዛኙ ይደግፋል። እውነት ለመናገር ግን ጣት መቀሰሩ ስለሚቀለን እንጂ ይሄ በሽታ ይብዛም ይነስም በየቤቱ ይገኛል። ችግራችን ግን አይናችን ውስጥ ያለውን ግንድ ጥለን ከሌሎች አይን ያለን ጉድፍ ነው የምንመለከተው። የሌሎችን ጥፋት ለማጋለጥ እንረባረባለን። እሺ የራሳችንንስ ማን ያርመው? ለማነው የምንተወው? ኧረ ልባችን ፈቃጅ ተመልካች አጣ!! ድባቡ የተበከለ ሆኖ መገሳሰፅ አልቻልንም። እኛም ለራሳችን ተገቢውን ትኩረት አልሰጠንም። ግን እስከመቼ? እና ወንድሜ ከማንም ጎጠኛ ቡድን ጋር ጭፍን ተሰላፊ አትሁን። ከዑለማእ ንግግር ውስጥ ከስሜቱ ጋር በሚገጥምለት መልኩ እየመረጠ የሚያቀርብ ሰው ስታይ በችኮላ እጅ አትስጥ። የትኛውም ቡድን ጋር የተሰለፈው ሁሉ ይህንን እያደረገ ነውና የሱ ከሌሎች በምን እንደሚለይ ረጋ ብለህ መርምር። የማይነቃነቅ ነባራዊ ሐቅ፣ የአህለ ሱና ዋና መታወቂያ አስመስሎ ያቀረበልህ ጉዳይ አብዛኞቹ ዑለማዎች ዘንድ ያለው አቋም እሱ ካወራህ ተቃራኒ ሆኖ ልታገኘው ትችላለህና ከስሜት ነፃ ሆነህ በሚገባ ፈትሽ። ደግሞ ቆም ብለህ ታዘባቸው። ብዙዎቹ ቡድናዊነት የሰበሰባቸው አካላት — "እነ እከሌ ጠርዘኞች ናቸው፣ ድንበር አላፊዎች ናቸው" እያለ ከፍ አድርጎ ያስተጋባል። የሚያስከነዱ ጠርዘኞችን ግን አቅፎ ያሽሞነሙናል። ምክንያቱም እነዚህኞቹ እሱ ሲስል የሚስሉ፣ ሲያነጥስ የሚያነጥሱ የገደል ማሚቶዎች ናቸውና። — "እነ እከሌ ጃሂሎች ናቸው" ይልሃል። በምንም መመዘኛ ከነሱ የማይሻሉ ሰዎችን ግን በትልልቅ መድረክ ላይ ያስተዋውቃል። ምክንያቱ አቋማቸው ከአቋሙ ስለገጠመለት ብቻ ነው። — "እነ እከሌ አቋም የሌላቸው ወላዋዮች ናቸው" ያለህ ስብስብ በየክስተቱ ባደባባይ የሚዋልሉ ሰዎችን ከጎናቸው አሰልፈው ታገኛቸዋለህ። ምክንያቱም መመዘኛው ርካሹ ቡድናዊ ሚዛን እንጂ ኢኽላስ አይደለምና። ወንድሜ ሆይ! አላህን አስበህ ስለምትሰራው ነገር የማንንም ጭብጨባ አትጠብቅ። የማንም ተቃውሞም አይጠፍህ። ይልቅ ውስጥህን አዳምጥ፣ ኢኽላስህን ፈትሽ። ያለ ኢኽላስ ጩኸትህ የቁራ ጩኸት ነው። ልፋትህም ከንቱ ድካም። በደዕዋህ ቀዳሚው ትኩረትህ ሰፊው ህዝብ ይሁን። አትዘንጋ! ዛሬም አብዛኛው ወገናችን ከተውሒድ ግንዛቤ የራቀ ነው። ሺርክ ላይ የሚማቅቀው ብዙ ነው። ከባባድ አጥፊ ወንጀሎች ላይ እስከ አፍንጫው የተነከረው ቀላል አይደለም። ቀዳሚው ጥረትህ የዚህን ወገንህን ሸክም ለመቀነስ ይሁን። ይህንን መሰረታዊ ጉዳይ ገሸሽ በማድረግ ውሃ ቀጠነ፣ ከሰል ጠቆረ ብሎ ለሚነታረክ ጀርባህን ስጠው። የጊዜ ጉዳይ እንጂ ሁሉም አረፋ ነው። በኢኽላስ እስከሰራህ ድረስ የማንም ጫጫታ ቅስምህን አይስበረው። ሰዎች እንቅፋት ሲያበዙ አንተ ፅናትህን ጨምር። ወደፊት እንጂ ወደ ኋላ አትበል። የሌሎችን ጩኸት ሳታጣራ የምታስተጋባ በቀቀን አትሁን። በጭፍን አትደግፍ። በጭፍን አትንቀፍ። እወቅ! እውር ጥላቻና እውር ውዴታ ነገ ከአላህ ፊት ያሳፍርሃል። ማንንም በእውር ድንብር አትከተል። ጭፍን ወገንተኝነት በቃላት ቢያሸበርቅም፣ በሱና፞ ስም ቢቀርብም የተወገዘ ነው። የአሳማ ስጋ በወርቅ ሰሀን ስለቀረበ አሳማነቱ አይቀየርም። አሳማ አሳማ ነው። የመዝሀብ ሰዎች ዘንድ የምናውቀው ጭፍን ወገንተኝነት ተቀባብቶ ተከሽኖ በሱና፞ ዑለማዎች ስም ሲቀርብ ማየት እየተለመደ መጥቷል። ይበልጥ የሚያሳፍረው ደግሞ አንዳንዶች በየሰፈሩ በየመንደሩ እየተቧደኑ ‘ወላእ’ እና ‘በራእ’ የሚቋጥሩባቸው አካላት መመደባቸው ነው። ደግሞም በልክ እንሁን። በሌሎች ሃገራት ወይም አካባቢዎች ያየነውን ወይም የሰማነውን ኺላፍ ሁሉ ሰበብ እየፈለጉ እየጎተቱ ማምጣት ግልብነት ነው። ወላጆችህ ወገኖችህ በሺርክ እየተጨማለቁ አንተ በሸይኽ እንትናና በሸይኽ እከሌ መካከል ስለተፈጠረው ኺላፍ ጧት ማታ እያቦካህ በአካባቢህ ያሉ ዱዓቶችን ለመፈረጅ አድፍጠህ ብትጠባበቅ የፊትና ጥማትህን እንጂ ንቃትህን አያሳይም። በአካባቢህ ይሄ ነው የሚባል የደዕዋ ተሳትፎ ሳይኖርህ እንዳቅማቸው እየደከሙ ያሉ አካላትን ትንሽዬ ጥረት አይኗን ለማጥፋት ጦር ብትሰብቅ ጥሬነትህን ብቻ ነው የሚያሳየው። ወንድሜ ከቻልክ አግዝ። ክፍተት ካየህ አርም። አቅሙ ከሌለህ ባላቸው አስመክር። በምትችለው ከጎናቸው ቁም። ለሰፈርህ ለአካባቢህ የደዕዋ እንቅስቃሴ አጋዥ እንጂ አፍራሽ አትሁን። ለደዕዋ እንቅፋት በመሆን ሌሎች እንዳይለወጡ መሰናክል አትፍጠር። ሰዎች የሚተላለፉበት መንገድ ላይ አስቸጋሪ ነገሮችን መጣል ፀያፍ ጥፋት ነው። ወደ ኣኺራ በሚወስደው የደዕዋ መንገድ ላይ እንቅፋት መጣል ግን እጅግ አደገኛ ወንጀል ነው። እንዲህ አይነቱን የወንጀል ሸክም የምትቋቋምበት ጫንቃው የለህምና ዛሬውኑ ሚናህን ለይ። ዛሬውኑ ለደዕዋ ያለህን አስተዋፅኦ ገምግም። ……………………………………………… Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር) የቴሌግራም ቻናል። ይቀላቀሉ። ሌሎችንም ይጋብዙ። https://t.me/IbnuMunewor
Показать все...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

ቻናሉን ይቀላቀሉ። ሌሎችንም ይጋብዙ። መልእክቱን ለሌሎች በማሰራጨት የአጅሩ ተቋዳሽ ይሁኑ።

#ወሎ_ላይ #ሽርክ_በየ_አይነቱ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ሰኞ ለነብዩ ማክሰኛ ኑር ሁሴን ረቡዕ አብዶየ፡ ሀሙስ ኸሚስ ናቸው ጫት ግዛማ አንተዬ፡ ሁሌ አሏህን ማመፅ ጁሙዐም አባዬ፡ የከውኑ ጠባቂ ከድር ነው ቅዳሜ፡ እሽራለሁ በሱ ተኝቸ ታምሜ፡ ሸሆቸን ስጠራ ይበረታል አቅሜ፡ ቁጥቡ–ዳዒር ናቸው በሣምንቱ እሁድ፡ አምልኮው ተረስቷል አሀዱ ሶመድ፡ ሙታን ያመለከ የለውም ተውሒድ፡ <========\\\=========> መወከል ደግሞ አለ አንበሶና ሰራን፡ ተውሒድ ሱና ጠፍቶ መኖርኮ ፈራን፡ ጥቁርና ቀዩ አለ ነጭ ዶሮ፡ ታርዶ ይቀበራል ጉድጓድ ተቆፍሮ፡ ወይ ደግሞ ለጂኑ ይጣላል በጓሮ፡ ወሏሂ እንደዚህ ነው የብዙው ሰው ኑሮ፡ አለ ደግሞ ሌላ ሾናትና ጭሌ፡ አረቂና ጠላ ይቀዳል በፎሌ፡ ይቀርባል ተውቦ ጠጁም በብርሌ፡ ከዚያ ሴቱም ወንዱም በአንድ ያጎራሉ፡ አድነን እያሉ ጂን ይለምናሉ፡ ዳንስና ቀረርቶ በፉከራው ሁሉ፡ <=======\\\========> በህሊና ቋጥኝ ዘልቀው ሲራመዱ፡ ጌታቸውን ትተው ጠንቋይ ሲያስፈርዱ፡ ዳገቱን ለመግፋት ቁልቁል ከወረዱ፡ የተውሒድን ጥቅም ሰወች ካልተረዱ፡ የጌታን ህግ ጥሰው ሰውን ካስፈረዱ፡ ብለው ከተመኙ ጀበናዬ ይርዳኝ፡ ማን ነው በዚህ ዘመን በእውነት የሚዳኝ፡ ሰማይ ደመና አዝሎ ተስፋን ካረገዘ፡ ህዝቡ ሽርክን ቋጥሮ ቂም ካመረቀዘ፡ በኑሮ ስንክሳር ብዙ ከተጓዘ፡ ክቡር ሰውነቱ ከንቱ ከናወዘ፡ ሰው የለኝም ብለህ ፍለጋማ አትውጣ፡ ከጠበከው ቦታ ራስክን ስታጣ ፡ አትጨክን ህዝቦችህ በሽርክ ሲዋኙ፡ ዳና ከረም ገታን ተማፅኖ ሲመኙ፡ <=======\\\=========> እንጨትና ድንጋይ እየተመለከ፡ ዑማው የሽርክ አይነት እየፈበረከ፡ እንደት ነው ነገሩ እጂጉን ይከብዳል፡ ተውሒድ እያለለት ሰው ሽርክን ይወዳል? አሳዛኝ ክስተት አጂብ ዘግናኝ ነገር፡ ተውሒድ የለም በቃ ሽርክ ነው ገር በገር፡ በሰሜን በደቡብ ወሎ እሚባል ሀገር፡ #ስለዚህ____!! እውነት እንናገር ቃልቻውም ንቃ፡ ሞት ሳይመጣህ በፊት ውጣ ከዚህ ጭቃ፡ ከኩፋር ጭቆና ለመላቀቅ በእውነት፡ ተውሒድ ሳይሰበክ አይመጣም ነፃነት፡ ደከመኝ አትበል ተውሒዲን አስተምር፡ አለ ብዙ ኮተት ብዙ ጥመት ክምር፡ ቅቤ እሚቀቡትን ድንጋዩን አፍርሰው፡ አጂር አለህ አብሽር በፋስ ፈረካክሰው፡ ሽርክ አትፈፅም በለው፤ ከሸሆቹ ቀብር አፈር ለሚልሰው፡ <=======\\\=========> በዕውቀትህ ተጣራ ተነሳ ቃልቻው፡ የሽርክ ግሳንግስ ይልቀቅ አራሙቻው፡ ወደ ፊት እንቀጥል ይጠንክር ዘመቻው፡ ተውሒድን ከተከልን ያኔ ነው መሞቻው፡ በጫሊ በገታ በዳና በከረም፡ በምስላይ በዳድ በደላንታ ኮረም፡ በሰሜን በደቡብ በምዕራብ በምስራቅ፡ ተውሒድ ስላነሰ አለ ብዙ ጭራቅ፡ የሱናችን መንፈስ እጂጉን ደብዝዟል፡ ይሔ ወሎ ምድር ብዙ ሽርክ አርግዟል፡ የሱና ወንድሞች እንንቃ በእውነቱ፡ ሀቅን እናግዘው እንዳንቀር ከንቱ፡ ይፈፀማል ወሎ ሽርክ በየ አይነቱ፡ <=========\\\=========> ወሎላይ ከጠቀስኳቸው በላይ ብዙ የሽርክ አይነት ይፈፀማል ሁላችንም ከራሳችን ጀምረን ሽርክን እንዋጋ እላለሁ። <==========\\\=============> #በኑረዲን_አል_አረቢ <=========================> http://t.me/nuredinal_arebi http://t.me/nuredinal_arebi http://t.me/nuredinal_arebi <============\\\===========>
Показать все...
شـبـاب السـلـــفــــيــــيــن

#ሰለፍያ_ቀጥተኛ_የሀቅ_መንገድ_ብሎም_አይነኬ_ፅኑ_ተራራ_ነው አስተያየት መስጫ ቦት ይህን ይጠቀሙ t.me/nuredinal_arebi_bot

የጂን ወሬ ሰምተህ ሰው ጋር አትጣላ ~~~~~~~~~~~~~~~ ብዙ ሰዎች የጂን ወሬ ይዘው ከጎረቤት፣ ቤተሰብ፣ ጓደኛ ጋር ሲቀያየሙ ያጋጥማል። ይህም የሚሆነው ለምሳሌ አንዲት ጂን የያዛት ሴት ቁርኣን በሚቀራላት ጊዜ "እከሊት ልካኝ ነው"፣ "እከሌ ደግሞባት ነው"፣ ወዘተ በማለት ጂኑ ይለፈልፋል። ይህንን የሰሙ ቤተሰቦች የተባለውን በመቀበል ስሟ/ሙ የተጠቀሰውን አካል በክፉ ማየት ይጀምራሉ። በአብዛኛው ጂኑ የሚጠራው ደግሞ ቅርብ ሰዎችን ነው። በዚህም የተነሳ በዘመዶች፣ ቤተሰቦች፣ ጎረቤቶች፣ ጓደኞች መካከል ከባድ መቃቃር ይከሰታል። ይህ የሸይጧን አላማ ነው። በአንድ ሰው አንደበት አስታኮ ድፍን ቤተሰብን ከሌሎች ጋር በማነካካት ሰላም ያደፈርሳል። "አንዲት ጎረቤታችን እህቴ ላይ ድግምት ሰርታባት ነበር። እንዴት እናድርግ?" አይነት ጥያቄ የሚጠይቅ ብዙ ሰው አለ። "ድግምቱን የሰራችው እሷ እንደሆነች እንዴት አወቅክ?" ስትለው "ቁርኣን ሲቀራ ጂኒው ነግሮናል" ይላል። እኔ እምልህ ወንድሜ! እንዴት እህትህን እያሰቃየ ያለውን ጂን በዚህ ደረጃ አመንከው? ትተዋወቃላችሁ እንዴ? ካላወቅከው እንዴት አመንከው? እሺ በሆነ ምክንያት ትተዋወቃላችሁ እንበል። ታማኝነቱን በምን አረጋገጥክ? አብራችሁ ቢዝነስ ሰርታችኋል? ነው ወይስ ታማኝ ሸይኽ፣ ኡስታዝ፣ ኢማም ሆኖ ነው የምታውቀው? ነው ወይስ በቅርብ የሚያውቀው ጓደኛ ታማኝ እንደሆነ ነግሮሃል? ካልሆነ ባላየኸው፣ ባላወቅከው ጉዳይ ላይ የማታውቀው የማታምነውን አካል ውንጀላ ተቀብለህ እንዴት ጎረቤትህ ጋር ትቀያየማለህ? ቢገባህ ይሄ ተንኮለኛ ጂን ከእህትህ ጤና አልፎ ጎረቤት ወይም ዘመድ አዝማድ ጋር እያነካካ ህይወታችሁን እየበጠበጠ፣ ድርብርብ ጉዳት እያደረሰባችሁ ነው። እስኪ አንድ ማንነቱን የማታውቀው ሰው እህትህን ሲደበድብ ደርሰህበት ስትይዘው የራስህን አጎት ስሙን ጠርቶ "እሱ ልኮኝ ነው" ቢልህ ምን ትላለህ?? እሱን አምነህ ከአጎትህ ጋር ትጣላለህ? ይህም ልክ እንደዚያው ነው። ኧረ እንዲያውም "እከሌ ነው የደገመብህ" ማለት የከፋ ወንጀል ነው!! ይሄ "ምሴ አመድ ነው"፣ "ነጭ ዶሮ እረዱልኝ"፣ "የጠላ አተላ አምጡልኝና ልልቀቅ" የሚልህ ጂን፣ ይሄ ሳይለቅ "ለቅቄያለሁ" እያለ እየዋሸ በመመላለስ የሚያንገላታ ጂን፣ ይሄ ሰዎችን ወደ ሺርክና ወንጀል የሚወስድ ጂን #በአብዛኛው ከሃዲ ነው፤ አለያ ደግሞ አመፀኛ ነው። እንዲህ አይነቱን ቆሻሻ ቢምልልህ እንኳ እሱን አምነህ ሙሲባህን አትጨምር። የላቀው ጌታ እንዲህ ይላል:— (وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافࣲ مَّهِینٍ) "መሀላ የሚያበዛ ወራዳን ሁሉ አትታዘዝ፡፡" [አልቀለም: 10] (یَـٰۤأَیُّهَا ٱلَّذِینَ ءَامَنُوۤا۟ إِن جَاۤءَكُمۡ فَاسِقُۢ بِنَبَإࣲ فَتَبَیَّنُوۤا۟ أَن تُصِیبُوا۟ قَوۡمَۢا بِجَهَـٰلَةࣲ فَتُصۡبِحُوا۟ عَلَىٰ مَا فَعَلۡتُمۡ نَـٰدِمِینَ) "እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነገረኛ ወሬን ቢያመጣላችሁ በስህተት ላይ ሆናችሁ ሕዝቦችን እንዳትጎዱና በሰራችሁት ነገር ላይ ተፀፃቾች እንዳትሆኑ አረጋግጡ፡፡" [አልሑጁራት: 6] የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor
Показать все...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

የቴሌግራም ቻናል። ይቀላቀሉ። ሌሎችንም ይጋብዙ።

"አር ማረኝ" ~ ተውሒድን አጥብቀህ ተማር። ተውሒድ ለኣኺራ ብቻ አይደለም ፋይዳው። ለዱንያም መከበሪያህ ነው። ተውሒድ #ካልተማርክ • ጉጉት ትፈራለህ፣ • አይጥ ትለማመጣለህ፣ • ውሻ አላዘነ ብለህ ትሸበራለህ፣ • የቁራ ድምፅ ከመንገድ ይመልስሃል፣ • እጅ ወይም አንገት ላይ በታሰረ እርባ ቢስ ክር ትተማመናለህ፣ • ዛፍ ላይ ክር ትተበትባለህ፣ ቅቤ ትቀባለህ፣ • እጅህን ስላሳከከህ ትደሰታለህ፣ (ሰዎች እጃቸውን ሲያሳክካቸው ምን እንደሚሉ አስታውስ) | • ተውሒድ ካልተማርክ ከሶላት የተኳረፈ ገሪባ "ዐርሽ ላይ ነው የምሰግደው" እያለ ይጫወትብሃል። ጠንቋይና ወልይ ይምታታብሃል። • ሃያሉን ጌታ ጥለህ ሙታን ትማፀናለህ፣ (ይልቅ እነሱን መለመንህን ትተህ ለነሱዱዓእ አድርግላቸው) • ተውሒድ ካልተማርክ "ማርያም በሽልም ታውጣሽ"፣ "የማርያም መቀነት"፣ "የማርያም ፈረስ"፣ "ማርያም ስማህ ነው"፣… እያልክ ክርስትና ክርስትና የሚሸት ኹራፋት ታራምዳለህ። • የአምስት ብር ጎመን የማያክል አረንጓዴ መርዝ (ጫት) መቶ ሁለት ብር ገዝተህ "የዱዓእ መሳሪያ" እያልክ ትጃጃላለህ፣ • የሁለት አመት ህፃን የሚፀየፈውን አፈር "ቱራብ" እያልክ በጥብጠህ ትጠጣለህ፣ • አዎ ተውሒድ ካልተማርክ የተቀበረ ብር አገኛለሁ ብለህ ጠንቋይ እየቀለብክ በእጅህ ያለውን ገንዘብ ታጣለህ፣ • ልጅህ ሲባልግ፣ ሲያፈነግጥ ዝም ብለህ ተውሒድ ሲማር፣ ሶላት ሲሰግድ፣ መስጂድ ሲያዘወትር፣ ጥሩ ጓደኛ ሲይዝ እሪ ትላለህ፣ (እንዲህ ነው የሸይጧን መጫወቻ መሆን) • ተውሒድ ካልገባህ ከሺርክ የሚያስጠነቅቁ ተቆርቋሪዎችን እንደ ጠላት እየቆጠርክና ጧት ማታ እያጠለሸህ ሶሐቦችን የሚያወግዙ፣ ቁርኣንን የሚያረክሱ ሺዐዎችን ታወድሳለህ። አልተማርክማ! እንዲሁ "ሲሉ ሰማሁ ብየ እላለሁ ነብዬ" ብቻ! • ተውሒድ ካልተማርክ ለቶንሲል ህመም "አር ማረኝ" እያልክ በአይነ ምድር ታሻርካለህ፣ (ሰው እንዴት ካካውን ይማፀናል?) ወላሂ ከእንዲህ አይነቱ የሰው ዝቃጭ ካካውን የሚያቦካ የአእምሮ በሽተኛ ሺ ጊዜ ይሻላል። ጎንበስ ብለህ ተውሒድህን ተማር። አካዳሚ ትምህርት ከሺርክ አያወጣህም። ስንት እንጨት፣ ላም፣ ድንጋይ፣ ሰው፣… የሚያመልኩ፣ ጠንቋይ ለጠንቋይ የሚርመጠመጡ ዶክተሮችና ፕሮፌሰሮች አሉ መሰለህ? \=\ የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor
Показать все...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

የቴሌግራም ቻናል። ይቀላቀሉ። ሌሎችንም ይጋብዙ።

ለዐረብ ሀገር ወንድምና እህቶች ~~~~~~~~~~~~~ ① ከሁሉም በፊት ለዲናችሁ ቅድሚያ ስጡ። ከተውሒድ ጀምራችሁ ግንዛቤያችሁን በተለያዩ መንገዶች አስፉ። ለአላህ ምስጋና ይግባውና በዚህ በኩል ብዙ ወንድሞችና እህቶች ዘንድ ጥሩ ተነሳሽነት ይታያል። ② ለአሰሪዎቻችሁ ታማኞች ሁኑ። የሰው ሀላፊነት እስከተቀበላችሁ ድረስ አላህን ፈርታችሁ ሀላፊነታችሁን ባግባቡ ተወጡ። በሰዐትም፣ በስራም፣ በገንዘብም፣ በክብርም፣ በልጆችም የምትታመኑ ሁኑ። አማናን መወጣት ትልቅ ሃላፊነት ነው። ③ በተቻላችሁ ከአላስፈላጊ የወንድና የሴት ቅልቅል ተጠንቀቁ። በጋራ የኪራይ ቤቶች ሊፈፀሙ ከሚችሉ አደጋዎች እራሳችሁን ጠብቁ። ④ እርስ በርስ ተዛዘኑ። ስራ ለሌለው ስራ በመፈለግ፣ ለተቸገረው በብድር ወይም እራስን በማይጎዳ መዋጮ ተጋገዙ። ⑤ ከወንጀለኞች ራቁ። አረብ ሀገር በርካታ ኢትዮጵያውያን በወንጀል ስራ ላይ መሰማራታቸው የሚታወቅ ነው። በነሱ ሳቢያ ኢትዮጵያውያን ባጠቃላይ በተደጋጋሚ ስማቸው ይጠፋል። የሚገርመው ብዙ ለነዚህ ወንጀለኞች ሽፋን የሚሰጡ ኢትዮጵያውያን መኖራቸው ነው። በነሱ ጥፋት አብራችሁ እንዳትጎዱ ተጠንቀቁ። እንዲያውም ለሌላ የሚተርፍ የተረጋገጠ ወንጀል ካያችሁ ለሚመለከተው አካል ጠቁሙ። ይሄ ለዲናችሁም ለገፅታችሁም ዋጋ አለው። ⑥ ቤተሰቦቻችሁን አትርሱ። ወላጅ ወላጅ ስለሆነ ብቻ ከባድ ሐቅ እንዳለው እሙን ነው። ከዚያም ባለፈ ስንት ፍዳቸውን አይተው አሳድገዋል። አረብ ሀገር ትሄዱ ዘንድ የተቸገሩላችሁም ብዙ ናቸው። እነዚህን ታሳቢ በማድረግ ወላጆቻችሁን አትርሱ። በዚያ ላይ አንዳንዶቻችሁ ወደ ወላጆቻችሁ ልጅ የላካችሁ ትኖራላችሁ። በዚህን ጊዜ ሐቁ ድርብርብ ነውና ኣኺራችሁን እንዳታጨልሙ ተጠንቀቁ። ⑦ እራሳችሁን አትርሱ። የወጣችሁት እንጀራ ፍለጋ ነው። ከፋም ደላ የሰው ሀገር የሰው ነው። ህልማችሁ ቋጥሮ ወደ ሀገር ለመመለስ እንጂ በልቶ ለመውዛት፣ ለብሶ ለመድመቅ አይደለም። ለዚህ ደግሞ ብልጥ መሆን ያስፈልጋል። መስራቱን ቻሉበት። መያዙንም ቻሉበት። ለቤተሰብ ስትልኩም አቅማችሁንም፣ ኑሯቸውንም፣ ሁኔታቸውንም እያገናዘባችሁ ይሁን። ለጎረምሳ ጫት መቃሚያና መንሸራሸሪያ አትላኩ። በዚህ ወንድሞቻችሁን ታበላሻላችሁ እንጂ አትጠቅሟቸውም። ገንዘባችሁንም አጥታችሁ ወንጀለኛም ትሆናላችሁ። ባጭሩ የምትሰሩትን ገንዘብ ቁም ነገር ላይ ለማዋል ተጣጣሩ። ባዶ እጃችሁን ላለመግባት በተቻላችሁ ተጠንቀቁ። ችግር መጥፎ ነው። ቤተሰብ እንኳን እንዲገፋችሁ ያደርጋል። አገራችን ለባዶ እጅ ቀርቶ ለያዘም እየከበደ ነው። ⑧ እቅድ ይኑራችሁ። ለቆይታችሁ ገደብ አስቀምጡለት። በግምት አትኑሩ። ሁለት አመት ሰራርቼ አገሬ እገባለሁ ብለው ሃያ አመት የኖሩ አሉ። ከአላማ ካልተወጣ ክፋት አልነበረውም። እየባከኑ ሲሆን ግን ያሳዝናል። "ምን ይዤ ልግባ?" እያሉ እየተብከነከኑ መኖር ይጎዳል። ስለዚህ ገደብ ያለው እቅድ ይኑራችሁ። ለእቅዳችሁም በትጋት አስቡ፣ በትጋት ስሩ። መገናኘታችሁ እቅዳችሁን የሚያሰናክል፣ ለትርጉም የለሽ ወጭ የሚዳርግ ከሆነ ተራራቁ። ⑨ ሴቶች ሆይ! መንገደኛ አታግቡ። እስኪ አሁን ሂንዲ፣ ፓኪስታኒ ማግባት ምን ይባላል? እንዲህ አይነቱ ትዳር ዘላቂ የመሆን እድሉ እጅግ የጠበበ ነው። ልጅ ከመጣም ከነ ጭራሹ አባቱ ጋር አይኖርም። ስለዚህ ለራስም ለልጅም ፈተና ነው። (10) ለኸይር ስራ እጃችሁን ስትዘረጉ ጥንቁቅ ሁኑ። ኸይር አትስሩ አይባልም። ግን በትክክል ለታለመለት ግብ የሚደርስ መሆኑን ቢያንስ ሚዛን የሚደፋ ግምት ያዙ። (11) ለትዳር ክብር ይኑራችሁ። ትዳርን መስፈርት በማያሟላ በተጨመላለቀ መልኩ ሳይሆን በሥርዓት ፈፅሙ። አትበዳደሉ። ኣኺራችሁን በማይጎዳ መልኩ በስርኣት ኑሩ። ለጋብቻ የተጋነነ ወጭ አታውጡ። ከሰሞንኛ ሆይሆይታ ይልቅ ለዘላቂው ትዳራችሁ ቅድሚያ ስጡ። መለያየት ግድ ካለም ባግባቡ ይሁን። የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor
Показать все...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

የቴሌግራም ቻናል። ይቀላቀሉ። ሌሎችንም ይጋብዙ።

👉 ባልሽን የግልሽ አድርጊው ብዙ እህቶች ባሎቻቸው የራሳቸው ብቻ ቢሆኑ ይመኛሉ ይህ ከፍቅር የመነጨ እንደሆነ ግልፅ ነው የአንድ ሴት ባልዋን በማፍቀር የግሏ እንዲሆን መመኘት ሙሉነቷን እንጂ ጉለቷን አይደለም የሚያመለክተው ነገር ግን አንዳንድ እህቶች ይህን ፍላጎታቸውን ለማሳካት የሚሄዱበት መንገድ ምኞታቸው ከንቱ ከማድረጉም በላይ የሁለት ሀገር ኪሳራ ያጎናፅፋቸዋል ከእነዚህ ተግባራት መካከል አንዱ መስተፋቅር ( ድግምት ) ማሰራት ይህ ተግባር ከእስልምና የሚያሰወጣ ከመሆኑ ሌላ በዱንያ ላይ የሚያስከስተው ጉዳት አለው አንደኛ ድግምተኛው ከሷ ውጪ ያሉ ሴቶችን እንዲጠላ በማድረግ ባልየው እናቱን እህቱን የራሱን ሴት ልጅ ጭምር እንዲጠላ ማድረግ ሁለተኛ ብዙ ድግምተኞች የተካኑ ባለመሆናቸው ተቀላቅሎባቸው ሁሉንም ሴት እንዲጠላ በማድረግ እሷንም ጭምር ጠልቶ እንዲፈታት ማድረግ ሶስተኛ በዚህ መንገድ የሚመጣ ፍቅር በጤነኛ አዕምሮ ባለመሆኑ የውሸት ተፈቀርኩኝ በሚል ራስን መሸወድ አራተኛ ዋናውና ትልቁ ከአላህ መንገድ መውጣት ናቸው ሌላው አንዳንድ እህቶች ባሎቻቸውን በሴቶች መብት እከስሃለሁ በሚል በማስፈራራት የግላቸው ማድረግ ያስባሉ የዚህ አይነቱ አካሄድም ባልዋ ካለው ፍቅር አንድ ፐርሰንት እንኳን እንዳታገኝ ከማድረጉም በላይ ህይወቷ ጎምዛዛ ትርጉም የለሽ እንዲሆን ያደርግባታል ባልየው ምናልባት ካንቺ ጋር መኖር አልፈልግም ሂጂ ከሰሽ የፈለግሽውን ንብረት ውሰጂ ብሎ አደገኛ ውሳኔ ውስጥ እንዲገባ ሊያደርገው ይችላል ይህ ተግባር የአማኝ ሴት ተግባር አይደለም የኢስላም ጠላቶች የሙስሊሞችን ህይወት ምስቅልቅሉ እንዲወጣና ከጌታቸው ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማበላሸት አኼራቸውን ማሳጣት የሚፈልጉበት መንገድ ነው ባልሽን የግልሽ ለማድረግ ትክክለኛው መንገይ ለባልሽ ታዛዥ መሆን ያለሱ ፈቃድ ከቤት አለመውጣት ቤተሰቦቹን ማክበር ባልሽ ከስራ ሲገባ ንፁህ ሆነሽ ቤትሽን አሳምረሽ በፈገግታና በናፍቆት መቀበል በማንኛውም ሁኔታ ሀይለቃል ከሱ ጋር አለመጠቀም በምንም አይነት ካንቺ መጥፎ ጠረን እንዳያገኝ መጠንቀቅ ለግንኙነት ሲጠራሽ በሞቀ ፍቅር መቀበል ሲገባ ወይም ሲወጣ ገንዘብ አለመጠየቅ ወጪ ሲያስፈልግሽ የኔ ፍቅር ካለህ እንዲህ አይነት ነገር ፈልጌ ነበር ከሌለህ ምንም ችግር የለም ብለሽ ከድካሙ በፍቅርሽ ካገገመ በኀላ ጥያቄ መቀበል የሚችልበት ሁኔታ መመቻቸቱ ስታውቂ መጠየቅ በባልሽ አጠገብ በምንም መልኩ ሌላ ወንድ አለማድነቅ የባልሽን ሚስጥር ለማንም አለመናገር ያለሱ ፈቃድ ምንም አይነት እቃ አለማዋስ የሚበቃሽ ወጪ እስከሰጠሽ ድረስ እሱ ሳያውቅ በፍፁም ከሱ ገንዘብ አለመውሰድ በምንም መልኩ የፍች ጥያቄ አለማቅረብ ለኔ ክብር የለህም አለማለት በቤተሰቦችሽ እሱን አለማስፈራራት በሚሰጥሽ ነገር መብቃቃት ሰው ቤት ያየሽውን ካልገዛህ አለማለት የቤትሽንና የልጆችሽን አማና በቻልሽው አቅም ለመወጣት መጣር እነዚህን ነገሮች ለመተግበር ከጣርሽ በአላህ ፈቃድ ባልሽ ያንቺ ታደርጊዋለሽ ለሸሪዓዊ ምክንያት እንኳን ባንቺ ላይ ሌላ ቢያገባ ልቡ አንቺ ጋር ነው የሚሆነው እነዚህን ነገሮች ስታደርጊ ባልሽን በማስደሰትሽ የአላህ ውዴታ ፈልገሽ ለመስራት ሞክሪ አላህ ለመልካሙ ሁሉ ይርዳሽ http://t.me/bahruteka
Показать все...
Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

#የንሃሴና ፀጉሜ ኮተቶች #1/ ንሃሴ ከገባ ራሳቸውን የማይላጩ ሰዎች አሉ ምክንያት ሲሏቸው ራስ ያሸብታል ብለው የጅል እምነታቸውን ያንፀባርቃሉ #2/ ቋጉሜ ብለው የሚያምኗት 5/6 ቀን ከገባች ጀምሮ ዱዓ እያሉ ሲሯሯጡ ይታያሉ #የሚግርመው ለሊት ቀን ያለ የሌላቸውን አቅም አሟጠው ድግስ ሳይቀር ደግሰው የተለያዩ መተቶችን በማዘጋጀት ዱዓ ሲሉ ምን ያህል እስልምናቸውን የሳቱ ሰዎች እንደሆኑ ያሳያሉ #3/ በነሱ አባባል ቋጉሜ ከገባተች ጀምሮ እስከመጨረሻው ገላውን መታጠብ ይወደዳል ብለው ያምናሉ ሰውነትን ለሚያሳክክ ነገርም መድኃኒት ነው ብለው ያምናሉ #ለዚህም ነው ልጆቻቸውን ገና ለሊት ወፍ ጭጭ ሲል ቀስቅሰው ወደ ወንዝ ሂደው እንድታጠቡ የሚያስገድዷቸው። #4/ የቋጉሜ ውሃ ከሌለኛው ወር ውሃ በበለጠ ኪሎው ይከብዳል ይላሉ #5/ ቋጉሜ ለ አዝማራም ይሁን ለፅንስ የአንድ ወር ያህል ታሳድጋለች ቀኗ አምስት ቀን ብትሆንም ሚስጥሯ የወር ነው ይላሉ #6/ ቋጉሜ 3 ሶስተኛው ቀን ላይ ዝናብ ከጣለ እባብና የእባብ ዘሮች አይናቸው ይጠፋል ይላሉ #7/ ቋጉሜ ስታልቅ ማታ የጭራሮ ችቦ በማዘጋጀት ምሽት ላይ ወደ ጨለማ ወጥተው እዮሃ የመስከረም ውሃ በማለት ሲተራኮሱ ያመሻሉ #8/ ቋጉሜ ስታልቅ መስከረም 1 አንድ ሲል ጧት ማለዳ ህፃናቱን ሁሉ ወፍ ሳይጮህ ሳይፈጅር ቀስቅሰው ወደ ሸለቆ ሂደው ገላቸውን እንድታጠቡ በሞራል ይገፈፏቸዋል። #9/ ልጆቹ ሰውነታቸውን ታጥበው ሲመለሱ ፌጡና ቃሪያ ሽንኩርት እና መሰሎችን አንድ ላይ በመፈጥፈጥ ልጆቹም ራሳቸውም ይመገባሉ #10/ መስከረም አንድ ቀን ልክ እንደ ኢስላማዊ በዓሎች ጎዝጉዘው አዳድስ ጨርቅ ለብሰው እያጨሱ እንኳን ለ አድሱ አመት አደረሳቹህ እየተባባሉ ሁላቸውም በየቤታቸው ይውላሉ #11/ መስከረም አንድ ቀን ከቤታቹህ ውጭ አትንከልከሉ ወደ ውጭ አትውጡ የዛኔ ወደ ውጬ ከወጣቹህ አመቱን ሙሉ ስትሮጡ ትከርማላቹህ ብለው ያምናሉ። <><> #እነኚህ ከቡዙ በጥቂቱ ናቸው አሏሁ_ልሙስተዓን!!! #ሙስሊሙ ውብ የሆነ ቁርኣንና ሐዲሥ መመሪያ እንደሌለው በኩፋሮች ባህልና እምነት ተወጥሮ ሲታይ ምንኛ ልብ ያደማል⁉️ #ሲጀመር ቋጉሜ በእስልምና ውስጥ አትታወቅም ጌታችንም አሏህ እንድህ ሲል ነግሮናል ﴿ﺇِﻥَّ ﻋِﺪَّﺓَ ﺍﻟﺸُّﻬُﻮﺭِ ﻋِﻨْﺪَ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺍﺛْﻨَﺎ ﻋَﺸَﺮَ ﺷَﻬْﺮًﺍ ﻓِﻲ ﻛِﺘَﺎﺏِ ﺍﻟﻠَّﻪِ . الأية ‏[ﺳﻮﺭﺓ ﺍﻟﺘﻮﺑﺔ 36:‏] . #ትርጉም የወራቶች ቁጥር አሏህ ዘንድ 12 አስራ ሁለት ናቸው። #መልእክተኛችንም የሚከተለውን ብለዋል ﺭﻭﻯ ﺍﻹﻣﺎﻡ ﺃﺣﻤﺪ ﻋﻦ ﺃﺑﻲ ﺑﻜﺮﺓ  ، ﺃﻥ ﺍﻟﻨﺒﻲ ﷺ ﺧﻄﺐ ﻓﻲﺣﺠﺘﻪ ﻓﻘﺎﻝ: ‏« إن ﺍﻟﺴﻨﺔ ﺍﺛﻨﺎ ﻋﺸﺮ ﺷﻬﺮًﺍ، ﻣﻨﻬﺎ ﺃﺭﺑﻌﺔ ﺣﺮﻡ، ﺛﻼﺛﺔ ﻣﺘﻮﺍﻟﻴﺎﺕ : ﺫﻭ ﺍﻟﻘﻌﺪﺓ، ﻭﺫﻭ ﺍﻟﺤﺠﺔ، ﻭﺍﻟﻤﺤﺮﻡ، ﻭﺭﺟﺐ ﻣﻀﺮ ﺍﻟﺬﻱ ﺑﻴﻦ ﺟﻤﺎﺩﻯ ﻭﺷﻌﺒﺎﻥ ‏» #አመት መሰለት 12 አስራ ሁለት ወር ነው ከነዚያ አራቶቹ ክቡሮች ናቸው ሶስቶቹ ተከታታይ ናቸው ዙል ቀዐደህ ዙል ሒጀህ ሙሐረም #ሌላው በጁማዳና በሸዕባን መከሰከል ያለው ረጀብ ነው። <><>\><><>\<><><> #ስለዚህ ቋጉሜ ከነጥቅሷም የለች በውስጧ የሚታተው መተትና ኮተትማ ሽርክና ቢድዓ ነው #ተጠንቀቁ ቋጉሜ አለች በሚሉ ሰዎች እንኳ ከሌሎቹ ወራቶች የተለየ መአረግ የላትም ግንዷ የሌለ ቀንዘል ሊኖራት አይችልም። http://t.me/abumuazhusenedris
Показать все...
አቡ ሙዓዝ(ሀሰን ኢድሪስ)(ቻናል)

ወደ ቻናሉ⬇ መግባት⬇ ከፈለጉ http://t.me/abumuazhusenedris አሰተያየትና⬇ጥያቄዎች ⬇ካለዎት

https://t.me/abumuazhusen_bot

ይጠቀሙበት!!!

ለምን ይመስልሀል!? ባለንበት ዘመን ለብዙ ወንዶች የቀረበን እንጀራ እንደመጉረስ የቀለላቸው ርዕስ ቢኖር ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት የሚለው ርዕስ ነው። እኔ ለዚህ ርዕስ የምመጥን ሰው አይደለሁም ነገር ግን ብዙ አሊሞች ደፍረው ለመነጋገር ያልቾኮሉበት ነገር ሆኖ ሳለ ጣሊበል ኢልም ላይ ያለ ያልበሰለ ወጣት ገብቶ የሚያቦካው ርዕስ መሆኑ ነው። ወዳንተ ስመለስ ከአንድ በላይ ስለማግባት በተወራ ሰአት ሁሉ አብዛኛው ሴቶች ጩኸት የሚያሰሙት ለምን ይመስልሀል? ለምንስ ሀያዕ የሚያጡ ይመስልሀል? አዎ ያንተ ማንነት በገሐድ እያየች እየሰማች ስለሆነ ያንገሸግሻታል ይህ ማለት አብዛኛው ወጣት ትዳር ማለት ልክ ኳስ ሜዳ እየመሰለው ነው ዘው ብሎ ይገባል በዛው ቅፅበት ይወጣል። ይህ ማለት ያንተ መዘላዘል በትክክል ሸሪአውን ተከትሎ ለሴቶች ክብር አለመስጠት ያመለክታል አዎ ሴት ልጅ ቆፍጠን ያለ ወንዳ ወንድ 1 2 3 4 አግብቶ በፍትህ የሚያስተዳድር እንጂ የሚዘላዘል በሄደበት ሁሉ ጎፍ የሚል ወንድ አይመቻትም። ያንተ መስተካከል ወይም ፍትሐዊ መሆን ለሸሪአው ታዛዥ እንድትሆን ስለሚያደርጋት ነገር ግን ተግባርህና ሸሪአው አይገናኙም። ያንተ ማንነት በስራዎችህ እያሳየሀት ነው እንዴት በለኛ? ከአንድ በላይ ሸሪአው ፈቅዶልኝ የለም ወይ ትለኝ ይሆናል አዎ ፈቅዶልሀል! ይህ ማለት ግን እንደፈለክ በሴት ህይወት ላይ ቀልድ ድንበር እለፍ ማለት ግን አይደለም። ታዳ መች አለፍኩ ትለኝ ይሆናል ያለፍክበት ቦታ በትሽ በጥቂቱ ልገርህ ተከተኝ 1 አግብተህ አርአያ ስትሆን አትታይም 1 አግብተህ አንድ አመት ሲሆንህ ልጅ አሳቅፈህ ወደ ቤተሰቧ ትመልሳለህ 3 በትክክለኛ ሰሪአ ሳትዳኝ ፍትሀዊ ሳትሆን ሁለት አግብተህ ትበድላለህ 4 አንዷን በትክክል ሳታስተዳድር 4ቱ አምፖሎች ትላለህ 5 ሁለት እንኳ ቢኖሩህ ወደ አንዷ ታጋድላለህ . . . . . . . . . . . . . . አላህ ሱብሀለሁ ወተአላ እንዲህ ይላል وَمَن يَفْعَلْ ذَٰلِكَ عُدْوَانًا وَظُلْمًا فَسَوْفَ نُصْلِيهِ نَارًا ۚ وَكَانَ ذَٰلِكَ عَلَى اللَّهِ يَسِيرًا (ሱረቱ ኒሳ) ቁ 30 ወሰን በማለፍና በመበደልም ይህንን የሠራ ሰው እሳትን እናገባዋለን፡፡ ይኸም በአላህ ላይ ገር ነው፡፡ ለሰው ልጆች ብርሀን ተደርገው የተላኩት (ረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሞዴሉ አድርጎ የያዘ ወንድ ይህን በደል በሩቁ ይሸሻል። ታዳ አብዛኛው ወንዶች ግን በደልን እንደ ሸሪአ አድርገው የቀየሩ እስኪመስል ደረስ ብዙ ሰቆቃዎች እያየን ነው ለምን ለሴትች ማንባት ምክንያት ትሆነለህ? አይ አታግባ እያልሽኝ ባልሆነ እንዳትል ባይገርምህ የረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ኡማ እንዲበዛ ከሚፈልጉ እንስቶች አንዷ ነኝ !! ወሊላሂል ሐምድ ነገር ግን በሴቶች ላይ ድንበር ሲታለፍ ዝም የሚል አዕምሮ የለኝም። አብኛው ኢትጲያዊ ወንድ እንኳንስ 2 3 4 ይቅርና ለአንዷም የሚሆን ጥሩ ስብዕና የለውም። አዎ የሩል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ኡማ እንዲበዛ የሚመኙ በጣም መልካም የሆኑ በዲናቸው ጠንካራ ከራሳቸው አልፈው ለብዙዎቹ አርአያ የሆኑ ምርጥ ወንድሞች አሉ ታዳ እነዚህ ወንድሞች ከአንድ በላይ ማግባትን ጠፍቷቸው እንዳይመስልህ ነገር ግን በነፍሶቻቸው ላይ ፍትሀዊ መሆንን ይፈራሉ እና። አንተ ግን ይህን የሚያክል ግዙፍ ሀላፍትና ወደ ኋላ ጥለህ የራስህን ምቾት ብቻ የምትፈልግ ራስን ወዳድ ነህ አዎ። በስደቱ አለም እንኳ ብንመለከት ብዙዎቹ ወንዶች ኑሮን ለማሸነፍ ሚስቶቻቸውንና ልጆቻቸውን ጥለው ይሰደዳሉ ። ከሀገር የወጣው አጅሬ በሄደበት ይሰፍራል ይህ ማለት የወጣው ኑሮን ለማሸነፍ ነበር ነገር ግን እሱ ኢላማውን ስቶ እንደራሱ በስደት ላይ ያለች ከርታታ ሴት እንደምንም በሹል መላሱ ያጠምዳል እና ልትከለኪይኝ ነው? ትል ይሆናል ምን በወጣኝ! ነገር ግን ያ የልጅችህ እናት ቤቴን ልጆቼን ጠብቂ ብሐት የሄድከው ደካማዋ ሴት ትዝ አትልህም ምን አይነት ጨቃኝ ነህ? አዎ ቢያንስ በየቀኑ ሄደህ ማየት ባትችል ቢያንስ 4 እና 6 ወር ሄዶ የመዘየር ሀላፍትና አለብህ። ነገር ግን ማግባትህን ሳትነገራት ባለ ትዳር መሆንህ ስታቅ ያልጠበቀችው ነገር ስለሆነ በንዴት ብዙ ነገሮችን ልትናገር ትችላለች በዛን ግዜ ያሳለፋችሁትን ሁሉ ነገር ትረሳና ከፈለግሽ ኑሪ ካልፈለግሽ ሂጅ ነው ያንተ መልስ አንተ ግን ሌላ አለም ላይ ነህ። እንደዚህ አይነት የወረደ አስተሳሰብ ያላቸው ወንዶንች ምንም የማያቁ ቢሆኑ ኑሮ አይገርመኝም ነበር ነገር ግን ቀርቼ ሸሪአን እተገብራለሁ አዋቂ ነኝ ብሎ ትልቅ ሀላፍና የተሸከመ ሰው ሲሆን ነገሩ ያባብሰዋል። በመጨረሻም በተለይ ስደት ላይ ያለሽው እህቴ ሆይ ማንም አረብኛ አቀላጥፎ ስላወራ አላህን ይፈራል በሸሪአው መሰረት ይጓዛል ማለት አይደለም እና አይሸውድሽ በተለይ ሁለተኛ ሆነሽ ለመግባት ስታስቢ መቅደም ያለበትን ነገር አስቀድመሽ አስተውይ ወንድ ልጅ አላህ ካዘነለት ውጭ ለራሱ እንጂ ቅድሜያ የሚሰጠው ላንቺ ዴንታ እንደሌለው አስረግጬ እነግርሻለሁ በቃ ጨካኝ ነው። ነገ ብታረግዢ ወደ ሀገር ይወረውርሽና ከዛ ብትታመሚ፣ ወጪ ቢኖርሽ፣ ባይኖርሽ ብትለብሺ ባትለብሺ፣ማረፌያ ኖረሽ አኖረሽ አያሳስበውም ስለዚህ ከደዚ አይነት አፈ ቀላጤ ደዩስ ወንድ ራስሽን ታደጊ መልዕክቴ ነው። By Sofiya Bint Yassin
Показать все...
ስልጣኔ ይግባሽ! ቀጥ ብለሽ ሂጂ ፣ስልጣኔ ይግባሽ በቀደምቶች መንገድ፣ እህት አስተውለሽ ይግባሽ ስልጣኔ፣ ይኑርሽ እውቀቱ የስልጡኖች መንገድ ፣ ኢስላም ነው እውነቱ ያዥው መንገድ ግቢ ፣ ኋላ ቀሩን ትተሽ የምርጥ ሰለፎች ፣ ፈለግ ተከትለሽ ፋሽን ስልጣኔ ፣ በደንብ የገባቸው ከስር መሰረቱ ፣ እውቀቱ ያላቸው በቁርአን በሀዲስ ፣ አውቀው የሚመሩ በዲን የተብቃቁ ፣ምንም ማይጨምሩ መሰልጠን ገብቷቸው፣ በኒቃብ ያጌጡ ለሸሪአ ትእዛዛ ፣ክብር የሚሰጡ ተሸፋኞች ነቸው ፣ከላይ እስከ ታች አላህ ዕንዳዘዘው ፣ለሴት አማኞች ስልጣኔ ይግባሽ ፣ልክ እንደዚ ጀግኖች ካመኑም እምን ፣በሂጃብ ፅኑዎች ፋሽን ያማራቸው ፣የተፈጥሮ ውበት በጌታቸው ፀጋ ፣የተከበሩበት የጨዋ ተምሳሌት ፣ የሴትነት አርማሽ ያለ አርቴ ነገር ፣መዋቤያ ግርማሽ ሙሉ ሂጃብሽ ፣ነው ያዥው ተጠንቅቀሽ መራቆትን ራቂ ፣ስልጣኔ ይግባሽ By foziya mohammed https://t.me/joinchat/AAAAAELSF1aEIsVPuBhfXA
Показать все...
الدعوة السلفية

الدعوة السلفية〰 ⬇ ተቀርተው ያለቁ ኪታቦች ብቻ የሚገኝበት ቻናል

https://t.me/Umuyahya_Bintmuhammed&Rozia

¶ َ~~®

https://t.me/daawatusalfeyia

قال تعالىٰ ®وَلَقَدْ بَعَثْنَا فٍي كُلِّ أُمَّةٍ رَّسُولّاأَنِ اعْبُدُوا اللّهَ ...وَاجْتَنِنُوا الطَّاغُوتَ<<¶ َ

ጫት ከጎደኞቸ ጋር ቅመን እንተፋበታለን አንድ ቀን አያድርም እንደዚህ ካደረግን በሚባልበት ሀገር ቅድሚያ ለተውሒድ ካልተባለ የት ይባላል ። ። https://t.me/joinchat/AAAAAD6qlKpDpI78i8sjLA
Показать все...
اللهم ثبتنا على الحق(التوحيد أولآ)

السلفية منهجنا

Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.