ለምን ይመስልሀል!?
ባለንበት ዘመን ለብዙ ወንዶች የቀረበን እንጀራ እንደመጉረስ የቀለላቸው ርዕስ ቢኖር ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት የሚለው ርዕስ ነው። እኔ ለዚህ ርዕስ የምመጥን ሰው አይደለሁም ነገር ግን ብዙ አሊሞች ደፍረው ለመነጋገር ያልቾኮሉበት ነገር ሆኖ ሳለ ጣሊበል ኢልም ላይ ያለ ያልበሰለ ወጣት ገብቶ የሚያቦካው ርዕስ መሆኑ ነው።
ወዳንተ ስመለስ ከአንድ በላይ ስለማግባት በተወራ ሰአት ሁሉ አብዛኛው ሴቶች ጩኸት የሚያሰሙት ለምን ይመስልሀል? ለምንስ ሀያዕ የሚያጡ ይመስልሀል?
አዎ ያንተ ማንነት በገሐድ እያየች እየሰማች ስለሆነ ያንገሸግሻታል ይህ ማለት አብዛኛው ወጣት ትዳር ማለት ልክ ኳስ ሜዳ እየመሰለው ነው ዘው ብሎ ይገባል በዛው ቅፅበት ይወጣል።
ይህ ማለት ያንተ መዘላዘል በትክክል ሸሪአውን ተከትሎ ለሴቶች ክብር አለመስጠት ያመለክታል አዎ ሴት ልጅ ቆፍጠን ያለ ወንዳ ወንድ 1 2 3 4 አግብቶ በፍትህ የሚያስተዳድር እንጂ የሚዘላዘል በሄደበት ሁሉ ጎፍ የሚል ወንድ አይመቻትም። ያንተ መስተካከል ወይም ፍትሐዊ መሆን ለሸሪአው ታዛዥ እንድትሆን ስለሚያደርጋት ነገር ግን ተግባርህና ሸሪአው አይገናኙም።
ያንተ ማንነት በስራዎችህ እያሳየሀት ነው እንዴት በለኛ? ከአንድ በላይ ሸሪአው ፈቅዶልኝ የለም ወይ ትለኝ ይሆናል አዎ ፈቅዶልሀል! ይህ ማለት ግን እንደፈለክ በሴት ህይወት ላይ ቀልድ ድንበር እለፍ ማለት ግን አይደለም። ታዳ መች አለፍኩ ትለኝ ይሆናል ያለፍክበት ቦታ በትሽ በጥቂቱ ልገርህ ተከተኝ
1 አግብተህ አርአያ ስትሆን አትታይም
1 አግብተህ አንድ አመት ሲሆንህ ልጅ አሳቅፈህ ወደ ቤተሰቧ ትመልሳለህ
3 በትክክለኛ ሰሪአ ሳትዳኝ ፍትሀዊ ሳትሆን ሁለት አግብተህ ትበድላለህ
4 አንዷን በትክክል ሳታስተዳድር 4ቱ አምፖሎች ትላለህ
5 ሁለት እንኳ ቢኖሩህ ወደ አንዷ ታጋድላለህ
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
አላህ ሱብሀለሁ ወተአላ እንዲህ ይላል
وَمَن يَفْعَلْ ذَٰلِكَ عُدْوَانًا وَظُلْمًا فَسَوْفَ نُصْلِيهِ نَارًا ۚ وَكَانَ ذَٰلِكَ عَلَى اللَّهِ يَسِيرًا
(ሱረቱ ኒሳ) ቁ 30
ወሰን በማለፍና በመበደልም ይህንን የሠራ ሰው እሳትን እናገባዋለን፡፡ ይኸም በአላህ ላይ ገር ነው፡፡
ለሰው ልጆች ብርሀን ተደርገው የተላኩት (ረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሞዴሉ አድርጎ የያዘ ወንድ ይህን በደል በሩቁ ይሸሻል። ታዳ አብዛኛው ወንዶች ግን በደልን እንደ ሸሪአ አድርገው የቀየሩ እስኪመስል ደረስ ብዙ ሰቆቃዎች እያየን ነው ለምን ለሴትች ማንባት ምክንያት ትሆነለህ? አይ አታግባ እያልሽኝ ባልሆነ እንዳትል ባይገርምህ የረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ኡማ እንዲበዛ ከሚፈልጉ እንስቶች አንዷ ነኝ !! ወሊላሂል ሐምድ ነገር ግን በሴቶች ላይ ድንበር ሲታለፍ ዝም የሚል አዕምሮ የለኝም።
አብኛው ኢትጲያዊ ወንድ እንኳንስ 2 3 4 ይቅርና ለአንዷም የሚሆን ጥሩ ስብዕና የለውም።
አዎ የሩል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ኡማ እንዲበዛ የሚመኙ በጣም መልካም የሆኑ በዲናቸው ጠንካራ ከራሳቸው አልፈው ለብዙዎቹ አርአያ የሆኑ ምርጥ ወንድሞች አሉ ታዳ እነዚህ ወንድሞች ከአንድ በላይ ማግባትን ጠፍቷቸው እንዳይመስልህ ነገር ግን በነፍሶቻቸው ላይ ፍትሀዊ መሆንን ይፈራሉ እና።
አንተ ግን ይህን የሚያክል ግዙፍ ሀላፍትና ወደ ኋላ ጥለህ የራስህን ምቾት ብቻ የምትፈልግ ራስን ወዳድ ነህ አዎ።
በስደቱ አለም እንኳ ብንመለከት ብዙዎቹ ወንዶች ኑሮን ለማሸነፍ ሚስቶቻቸውንና ልጆቻቸውን ጥለው ይሰደዳሉ ። ከሀገር የወጣው አጅሬ በሄደበት ይሰፍራል ይህ ማለት የወጣው ኑሮን ለማሸነፍ ነበር ነገር ግን እሱ ኢላማውን ስቶ እንደራሱ በስደት ላይ ያለች ከርታታ ሴት እንደምንም በሹል መላሱ ያጠምዳል እና ልትከለኪይኝ ነው? ትል ይሆናል ምን በወጣኝ! ነገር ግን ያ የልጅችህ እናት ቤቴን ልጆቼን ጠብቂ ብሐት የሄድከው ደካማዋ ሴት ትዝ አትልህም ምን አይነት ጨቃኝ ነህ? አዎ ቢያንስ በየቀኑ ሄደህ ማየት ባትችል ቢያንስ 4 እና 6 ወር ሄዶ የመዘየር ሀላፍትና አለብህ።
ነገር ግን ማግባትህን ሳትነገራት ባለ ትዳር መሆንህ ስታቅ ያልጠበቀችው ነገር ስለሆነ በንዴት ብዙ ነገሮችን ልትናገር ትችላለች በዛን ግዜ ያሳለፋችሁትን ሁሉ ነገር ትረሳና ከፈለግሽ ኑሪ ካልፈለግሽ ሂጅ ነው ያንተ መልስ አንተ ግን ሌላ አለም ላይ ነህ።
እንደዚህ አይነት የወረደ አስተሳሰብ ያላቸው ወንዶንች ምንም የማያቁ ቢሆኑ ኑሮ አይገርመኝም ነበር ነገር ግን ቀርቼ ሸሪአን እተገብራለሁ አዋቂ ነኝ ብሎ ትልቅ ሀላፍና የተሸከመ ሰው ሲሆን ነገሩ ያባብሰዋል።
በመጨረሻም በተለይ ስደት ላይ ያለሽው እህቴ ሆይ ማንም አረብኛ አቀላጥፎ ስላወራ አላህን ይፈራል በሸሪአው መሰረት ይጓዛል ማለት አይደለም እና አይሸውድሽ በተለይ ሁለተኛ ሆነሽ ለመግባት ስታስቢ መቅደም ያለበትን ነገር አስቀድመሽ አስተውይ ወንድ ልጅ አላህ ካዘነለት ውጭ ለራሱ እንጂ ቅድሜያ የሚሰጠው ላንቺ ዴንታ እንደሌለው አስረግጬ እነግርሻለሁ በቃ ጨካኝ ነው። ነገ ብታረግዢ ወደ ሀገር ይወረውርሽና ከዛ ብትታመሚ፣ ወጪ ቢኖርሽ፣ ባይኖርሽ ብትለብሺ ባትለብሺ፣ማረፌያ ኖረሽ አኖረሽ አያሳስበውም ስለዚህ ከደዚ አይነት አፈ ቀላጤ ደዩስ ወንድ ራስሽን ታደጊ መልዕክቴ ነው።
By Sofiya Bint Yassin