ru
Feedback
ከቃሉ ማዕድ

ከቃሉ ማዕድ

Открыть в Telegram

☀️ ክርስቶስን መስለን በመኖር ፣ ላልተደረሱት የሕዝብ ክፍሎች በመፀለይ ፣ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ የሚፈልገውን እግዚአብሔርን የሙጥኝ የምንልበት ቻነል ነው። 1ጢሞ 2:1-4 ☀️ ደግሞም አብ የሰጠንን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በልተን ደግሞም ጠትተን ዕለት ዕለት ደግሞ 💥በሁለንተናችን የሚያሳድገንን የቃሉን🎯 ማዕድ የምንቆርስበት ትምህርታዊ እና መንፈሳዊ ቤት ነው። ዮሐ6:35

Больше
Страна не указанаКатегория не указана
323
Подписчики
Нет данных24 часа
+67 дней
+6630 дней
Архив постов
➫"...በዚህም ላይ ኢየሱስ በወንጀለኞች መካከል ነው የተሰቀለው በቤተ መቅደስ ውስጥ በሁለት መቅረዞች መካከል አይደለም። የቦታው ድባብ ሥቃይና ጣር፣ የለቅሶና ምሬት፣ የሌቦች ስድብና ርግማን፣የወታደሮች ዛቻና ማጉረምረም የሞላበት ነው። እግዚአብሔር እንዲህ አይነቱን ስፍራ ነው የመረጠው። እግዚአብሔር ለእኛ ካለው ፍቅር የተነሳ ይህንን ውርደት በፈቃዱ ተሸክሟል። እናም በመስቀል መሞት በሌላ መንገድ ከመሞት ይከፋል። “ለሞትም፣ ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ” በማለት ቅዱስ ጳውሎስ የሚገልጠው ለዚህ ነው። (ፊልጵ 2:8)።" 📖የተሰቀለው📝ጳውሎስ ፈቃዱ #ከቃሉ_ማዕድ

"ለእግዚአብሔር ፈቃድ ታዘህ ስትጓዝ ማዕበል ይነሳብሃል፣ ከተማ ይክድሃል፣ ሰማይ ናስ ፣ ምድር ብረት ይሆንብሃል፤ ያለህ ምርጫ መንገዱን እንድትጓዝ ወዳዘዘህ ጌታ ቀና ማለት ብቻ ይሆናል። ያኔ ከማታስበው ቦታ ዕርዳታ ይሆንልሃልበማጽናናቱም ደስ ይልሃል። በመንገዱም እስከ መጨራሻው ለመቀጠል የበለጠ አቅም ታገኛለህ። የትኛውም መከራ ፣ ማዕበልና ወጀብ የማያስቆምህ ብርቱ ሰው ትሆናለህ" 📖የፈቃዱ መንገድ ✍ዮናታን አክሊሉ #ከቃሉ_ማዕድ

🔆ሰላም ለእናንተ ይሁን ቅዱሳን🔆 ይህ መልዕክት የደረሳችሁ ሁሉ... ═════════════════════════════ 💥በዚህ ገጽ ካነበባችሁት ነገር ጥቂትም ቢሆን እየተማራችሁ እንደሆነ ያሳወቃችሁን እግዚአብሔር ይባርካችሁ። ♡ㅤ     ⎙        ⌲ ˡᶦᵏᵉ     ˢᵃᵛᵉ     ˢʰᵃʳᵉ በማድረግ አሁንም መጠቀማችሁን ብታሳዩን ይህ ለእናንተ በረከት ይሁናችሁ። 📌 ሌሎቻችሁም ለጌታ ክብር ለእናንተም ጥቅም 🔺ተ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 ስንል በጌታ ፍቅር እንጠይቃችኋለን። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/Kekalu_Maid 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 ══════════════════ #ከቃሉ_ማዕድ

ይህንን አጭርና አስተማሪ ታሪክ ካላነበባችሁት አዘንኩላችሁ።

✳️አጭር ታሪክ[በመስቀሉ መነካት] ═══════════════════════════════ "የፓሪስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት የነበሩት ዣን ማሪ ሊውስቲዤ (Jean-Marie Lustiger) ደጋግመው የሚያስታውሱት አንድ ታሪክ ነበራቸው። አንድ ጊዜ ሦስት ወጣት ወንዶች በአካባቢያቸው ወደ ነበረው ቤተ ክርስቲያን ይሄዱና ለመናዘዝ እንደሚፈልጉ ይናገራሉ፤ ዓላማቸው በቄሱ ላይ መቀለድ ብቻ ነበር። ከዚያም ወደ ኑዛዜ ክፍል ገብተው ክፉ ክፉ ኃጢአቶችን ለቄሱ ከተናዘዙ በኃላ ምክርም ተግሣጽም ሳይቀበሉ ሮጠው ይወጣሉ። ቄሱ የልጆቹ ዓላማ ገብቷቸዋል።ሁለቱ ልጆች ያሰቡትን ፈፅመው ሮጠው ከወጡ በኃላ የሦስተኛው ተራ ደረሰ። ልጁ አይሁዳዊ ነው። እርሱም ካህኑ ወደሚገኙበት የኑዛዜ ክፍል ውስጥ ገብቶ “ኃጢአቱን” ተናዘዘ። እርሳቸውም ኃጢአቱን በተመለከተ ምን ማድረግ እንዳለበት መመሪያ ሰጡት። የተሰቀለውን ኢየሱስን ወደሚያሳይበት በቤተክርስቲያኒቱ አንድ ጥግ ላይ በሚገኝ ምስል ተጠግቶ ፣ “ይህን ሁሉ ያደረግኸው ለኔ ነው። እኔ ግን ጉዳዬ አይደለም” እያለ ሦስት ጊዜ እንዲናገር አዘዙት። ልጅየውም ይህንንኑ ሊያደርግ ወጥቶ ሄደ። ይህ ለእርሱ የጨዋታው አካል ነው። ቀና ብሎ ወደ ኢየሱስ የስቅለት ምስል እየተመለከተ፡ “ይህን ያደረግኸው ለኔ ነው። እኔ ግን ጉዳዬ አይደለም” በማለት አንዴ ተናገረ።ደገመው። ከዚያም ሦስተኛ ... ለመናገር ሞከረ፤ አልቻለም። እያለቀሰ የቤተክርስቲያኒቱን ግቢ ለቅቆ ወጣ ። “ይህ ታሪክ ያወቅሁት” ይላሉ ጳጳሱ ሲናገሩ፣ “ያ ወጣት እኔ ስለነበርኩ ነው”። እናም የተለወጠው ወጣት፣ ማለትም ዣን ማሪ ሊውስቲዤ ሕይወታቸው ተለውጦ እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ ጌታን ሲያገለግሉ ኖሩ። ወደ መስቀሉ፣ ወደዚያ የወረደና የፍቅር ስፍራ የሄደ ሁሉ ይለወጣል።" ═══════════════════════════════ 📖የተሰቀለው📝ጳውሎስ ፈቃዱ #ከቃሉ_ማዕድ

"የኢየሱስ መስቀል ነባር ልማዳችንን ይነካል። የግል ሕይወታችንን ይጥሳል። ሥልጣናችንን ይነካል። አቅጣጫ ያስቀይረናል።ኢየሱስ የተሰቀለው ለእኛ ነውና! "
📖የተሰቀለው📚 📝ጳውሎስ ፈቃዱ #ከቃሉ_ማዕድ

"መስቀል☦ የሽንፈት ምልክት ቢሆንም ፣ የኢየሱስ መስቀል ግን የድል ምልክት ሆኗል።የተሰቀለው ጌታ ሕያው ነውና።ትንሣኤና ሕይወትም እርሱ ነውና።"
📖የተሰቀለው📖 ✍ ጳውሎስ ፈቃዱ ¶Follow | Join | Share #ከቃሉ_ማዕድ

👉"የኢየሱስ ተልዕኮ ሌሎችን ለማዳን ሕይወቱን ለአደጋ የማጋለጥ ብቻ ሳይሆን፤ ሕይወቱን ስለ ሌሎች አሳልፎ የመስጠት ነው።"
ጳውሎስ ፈቃዱ 📖የተሰቀለው📖 #ከቃሉ_ማዕድ

የተሻለ ና ምርጥ Bible App ነው እስካሁን ከተጠቀምኳቸው :- ◻️ተጫኑት ለማውረድ 👇 https://play.google.com/store/apps/details?id=com.mikios.amharicbib
የተሻለ ና ምርጥ Bible App ነው እስካሁን ከተጠቀምኳቸው :- ◻️ተጫኑት ለማውረድ 👇 https://play.google.com/store/apps/details?id=com.mikios.amharicbible.amharic_bible 🔴እዛው ላይ Bible ማብራሪያ አለው 🔴እዛው ላይ ከፈለጋችሁ በግሪኩ ቃል ማብራሪያ አለው 🔴ትወዱታላችሁ ብዙ አይነት አለው 👉 ማስታወቂያ አይደለም እኔ ስለተባረኩበት ነው።

https://www.youtube.com/watch?v=JpCR7F6C3Gk 📌ጠንካራ መልእክት አለው ተማሩት ትባረኩበታላችሁ❕

◦◦◦ሲገባኝ ገረመኝ◦◦◦
አሞጽ 5:3-4 3 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “አንድ ሺሕ ብርቱዎችን ለእስራኤል የምታዘምት ከተማ፣ አንድ መቶ ብቻ ይቀሯታል፤ አንድ መቶ ብርቱዎችን የምታዘምተውም፣ ዐሥር ብቻ ይቀሯታል።” 4 እግዚአብሔር ለእስራኤል ቤት እንዲህ ይላል፤ “እኔን ፈልጉ፤ በሕይወትም ትኖራላችሁ።
👉እንግዲህ እግዚአብሔር ፈልጉኝ ማለቱን ስናስብ የእኛ እርሱን ከመፈለግ በላይ እርሱ እኛን እንዴት እንደፈለግን ስናስብ የሚያስደንቅ ነው።እግዚአብሔር አዳም አና ሄዋን ፍሬዋን በልተው ዕርቃናቸውን መሆናቸውን ሲያውቁ በ ዘፍ 3:9 እግዚአብሔር አምላክም አዳምን ጠርቶ፦ “ወዴት ነህ?” ከሚለው ጥሪ እንኳ የእግዚአብሔር ፍለጋ ሰውን የሚቀድም መሆኑን ብሎም የእግዚአብሔር ልብ በሰማያት ሳይሆን ልቡ በእኛ ደጅ መሆኑን እንመለከታለን። 🔆 እንግዲህ ለእግዚአብሔር የልቤ ሰው ተብሎ ሀሳቡንም አገልግሎ ያንቀላፋውን ዳዊትን እግዚአብሔርን የመፈለጉን ልክ እስኪ እናስተውለው◦◦◦ 📌እንግዲህ ንጉሥ ዳዊት በብዙ ሰራዊት የተከበበ ማለትም የእርሱ ሰራዊት "እንደ እግዚአብሔርም ሠራዊት ታላቅ ሠራዊት እስኪሆን ድረስ" 1 ዜና 12:22 በዘመኑ የሰለጠኑ ጦረኞች ያሉት ሰው ነው። የሀይላቸውም ልክ አንዱ ጦረኛ እንኳን "ሲሄድ ሳለም አንበሳ መንገድ ላይ አግኝቶ ገደለው፤ ሬሳውም በመንገድ ላይ ተጋደመ፤"1 ነገሥት 13:24 ተብሎ ተነግሮለታል። 🎯በ 2 ሳሙ 5 መጨረሻው ቁጥር ላይ "ዳዊትም እግዚአብሔር እንዳዘዘው አደረገ፤ ከገባዖንም እስከ ጌዝር ድረስ ፍልስጥኤማውያንን መታ።"ይላል። ከዛም በዳዊት ቤት ድል ስላደረጉ ትልቅ ግብዣ ተደረገ አይልም! ይልቁንም 2 ሳሙ 6:1-2 "ዳዊትም ዳግም ከእስራኤል የተመረጡትን ሠላሳ ሺህ ያህል ሰው ሰበሰበ።...የእግዚአብሔርን ታቦት ከዚያ ያመጡ ዘንድ ሄዱ።" ይላል። 📌የዳዊት ክብሩ ድል ሳይሆን ያከበረው እግዚአብሔር ነበር።ስለዚህ የኪዳኑ ታቦት(የእግዚአብሔር ማደሪያ) 20 ዓመት ያህል በሳዖል ተረስቶ ከቆየበት የፈለገው ዳዊት ነበር። ከአሚናዳብ ቤት ወጥቶ ሲሄድ ዖዛ በድፍረቱ ስለተቀሰፈ ዳዊትም ስለፈራ በአቢዳራ ቤት ሦስት ወር ተቀመጠ።                   ...ከሦስት ወራት በኃላ... 🎯 ዳዊት በናፍቆት የሚጠብቀው የእግዚአብሔር ክብር ፣ የኪዳኑ ታቦት ወደ ከተማ ሲመጣ...👇 2 ሳሙኤል 6:13-15 13 የእግዚአብሔርንም ታቦት የተሸከሙ ስድስት እርምጃ በሄዱ ጊዜ አንድ በሬና አንድ ፍሪዳ ሠዋ። 14 ዳዊትም በሙሉ ኃይሉ በእግዚአብሔር ፊት ይዘፍን ነበር፤ ዳዊትም የበፍታ ኤፉድ ለብሶ ነበር። 15 ዳዊትና የእስራኤልም ቤት ሁሉ ሆ እያሉ ቀንደ መለከትም እየነፉ የእግዚአብሔርን ታቦት አመጡ። ✴️ ዳዊት እግዚአብሔርን ከድል ማግስት ብቻ አይደለም የሚፈለገው ፤ በይሁዳ ምድረበዳ በስደት ምድር እንኳን...👇 መዝሙር 63:1-2 1 አምላኬ፥ አምላኬ፥ ወደ አንተ እገሠግሣለሁ፤ ነፍሴ አንተን ተጠማች፥ ሥጋዬ አንተን እንዴት ናፈቀች፡ እንጨትና ውኃ በሌለበት በምድረ በዳ። 2 ኃይልህንና ክብርህን አይ ዘንድ፡ እንዲሁ በመቅደስ ውስጥ ተመለከትሁህ። ✳️ ከዳዊት ፍለጋ ምን እንማራለን❓ ❶ እግዚአብሔርን በፍጹም ልብ መፈለግ መዝሙር 42:1-3 1 ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ፥ አቤቱ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች። 2 ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች፤ መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ? 3 ዘወትር፦ “አምላክህ ወዴት ነው?” ሲሉኝ እንባዬ በቀንና በሌሊት ምግብ ሆነኝ። ❷ እግዚአብሔርን ከሁሉ አስበልጦ መፈለግ። 2 ሳሙኤል 6:16 16 የእግዚአብሔር ታቦት ወደ ዳዊት ከተማ ሲገባ፣ የሳኦል ልጅ ሜልኮል በመስኮት ሆና ትመለከት ነበር፤ ንጉሥ ዳዊት በእግዚአብሔር ፊት ሲዘልልና ሲያሸበሽብ ባየችው ጊዜ በልቧ ናቀችው።...
እረኝነቱ ያለቀቀው መሰላት
...ልትቀበለው ወጥታ፣ “ዛሬ የእስራኤል ንጉሥ በመኳንንቱ ገረዶች ፊት እንደ አንድ ተራ ሰው ዕራቍቱን መታየቱ ክብሩ ሆኖ ነው!” አለችው። 💫እርሱ ግን ዕራቍቱን መታየቱ ሳያንስ👇 ✳️👉 ዳዊትም እንዲህ አላት፤ “አዎን ከአባትሽና በቤቱ ካሉት ሁሉ አስበልጦ በእግዚአብሔር ሕዝብ በእስራኤል ላይ ገዥ አድርጎ በመረጠኝ በእግዚአብሔር ፊት አሸብሽቤአለሁ፤ አሁንም አሸበሽባለሁ። 22 እንዲያውም ከዚህ ይልቅ ራሴን በፊቱ ዝቅ አደርጋለሁከዚህም የባሰ የተናቅሁ እሆናለሁ፤ ነገር ግን በጠቀስሻቸው ገረዶች ፊት እከብራለሁ።” 💥እርሱ ከንግስናው ይልቅ አምላኩ እግዚአብሔር ክብሩ ነው። ይህንን ዝቅ ማለት እግዚአብሔር ሊያከብረው ሲወድ እንዲህ አለው፦ 👉 ቤትህና መንግሥትህ በፊቴ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል፤ ዙፋንህም እንደዚሁ ለዘላለም የጸና ይሆናል።’ ”2 ሳሙ 7:16                  👇👇👇 18 ከዚያም ንጉሥ ዳዊት ገባ በእግዚአብሔር ፊት ተቀምጦ እንዲህ አለ፤ “ልዑል እግዚአብሔር ሆይ፤ እስከዚህ ያደረስኸኝ ኧረ እኔ ማን ነኝ? ቤቴስ ምንድን ነው?
ኢየሱስ ከይሁዳ ነገድ የሳሌም ንጉስ ሆኖ እንደመጣ መ/ቅዱስ ያስተምረናል።
                        📌የመጨረሻ መልዕክት፧፦               🔆መንፈስ ቅዱስ ዛሬም ይፈለጋል!🔆 ኢሳይያስ 55:6 6 እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፤   ቀርቦም ሳለ ጥሩት። ══════════════✟═════════════ 💠 በልባችን ሲገኝ አንዳይቀልብን ፤ መንፈስቅዱስን መፈለግ ዕለት ዕለት ይብዛልን።🙏አሜን🙏 ══════════════✟═════════════ #እግዚአብሔርን_መፈለግ #መንፈስቅዱስን_መናፈቅ ¶Follow | Join | Share #ከቃሉ_ማዕድ

✔️"ሊቀካህናችን ክርስቶስ ኢየሱስ ከጠላት እጅ ማምለጫችን ፣ የቅርብ መሸሻችን፣ ከደም ተበቃያችን እጅ መዳኛችን ፣ በመልከጼዴቅ ሹመት ዘወትር በአብ ፊት የሚቆምልን ፣ ሊቀበለን ሁልጊዜ ዝግጁ ሆኖ የሚጠብቅ ወዳጃችን ነው።" ¶Follow | Join | Share #ከቃሉ_ማዕድ

═══════════════✝═══════════════ ◦◦◦የመጨረሻው ክፍል እነሆ◦◦◦🤗 ☑ ይህ ሁሉ ለምን አስፈለገ??? 👉እግዚአብሔር የሀጢአትን ይቅርታን ማድረግ ስለሚፈለግ እና ማንነቱ ፍቅር ስለሆነ። ለምን??? ✴️ ምህረቱ ለዘላለም ነውና። ✴️ ማ
ቴዎስ 26:28 28 ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።
🎯የመማፀኛ ከተማ ፧፦ ⓵ ማምለጫ ነው። ⓶ ምቅላት ቅርብ ነው። ⓷ ከደም ተበቃያችን እጅ መዳኛችን ነው። ⓸ ሊቀ ካህናቱም ያለበት ስፍራ ነው።... ⓹ በሩ ሁል ጊዜ ክፍት ነው። =24/7 ✴️ ሊቀካህናችን ክርስቶስ ኢየሱስ ከጠላት እጅ ማምለጫችን ፣ የቅርብ መሸሻችን፣ ከደም ተበቃያችን እጅ መዳኛችን ፣ በመልከጼዴቅ ሹመት ዘወትር በአብ ፊት የሚቆምልን ፣ ሊቀበለን ሁልጊዜ ዝግጁ ሆኖ የሚጠብቅ ወዳጃችን ነው። 💥 በደለኛው ግን ቶሎ መሸሽ አለበት። 💥ሊቀ ካህኑ እስከሚሞት ድረስ ሊቀካህኑ የበደለኛውን ሰው ሀጢአት ይሸከማል። 💥ሊቀ ካህኑ ሳይሞት በደለኛው ወደ ከተማው ቢወጣ ደም ተበቃዩ ሊገድለው ይችላል 💥ሊቀ ካህኑ ሲሞት በደለኛው ወደ ከተማ መውጣት ይችላል = የሊቀካህኑ መሞት ለበደለኛው አርነት የሚታወጅበት ዕለት ነው። ብራውያን 6:17-19 17-18 ስለዚህም እግዚአብሔር፥ የተስፋውን ቃል ለሚወርሱ ፈቃዱ እንደማይለወጥ አብልጦ ሊያሳያቸው ስለ ፈቀደ፥ እግዚአብሔር ሊዋሽ በማይቻል በሁለት በማይለወጥ ነገር፥ በፊታችን ያለውን ተስፋ ለመያዝ ለሸሸን ለእኛ ርቱ መጽናናት ይሆንልን ዘንድ፥ በመሓላ በመካከል ገባ፤ 19 ይህም ተስፋ እንደ ነፍስ መልሕቅ አለን እርሱም እርግጥና ጽኑ የሆነ ወደ መጋረጃውም ውስጥ የገባ ነው፤ ══════════════════════ ❄️ በሊቀካህናችን በክርስቶስ ምን አገኘን? ══════════════════════ 🎯በፊታችን ያለውን ተስፋ ለመያዝ ለሸሸን ለእኛ፦ ዕብ 6~17-18 💠 ብርቱ መፅናናት ሆነልን-📌ቦሶር/ብርታት/ የሚለውን ቃል ይጠቀማል። 💠 መሸሻ አገኘን-📌ጎላን/ሽሽት/ 💠 የነፍሳችን መልህቅ⚓ሆነልን-📌ኬብሮን /ህብረት/ 💠 ሊቀ-ካህናችን መጋረጃው ውስጥ የገባ ነው-📌ካዴሽ/ቅዱስ/ 💠 የሚሸከም ሊቀካህናት አለን-📌ሼኬም(ትከሻ/የሚሸከም) 💠 ታላቅ ሊቀ-ካህናት አለን;1ጢሞ3:16 ፦ 📌ገለዓድ/ከፍታ/ ☢በምቅላት ሁሉም አስፈላጊ ግብዓት የተሟላ ነው። አንዱ በአንዱ አይፈርድም ለምን❔ሁሉም አምልጦ የተገኘ ነው። 💥የመማፀኛ ከተማ ደም ተበቃዩ የማይደፍረው ከተማ ነው‼️ 💥ወደ መማፀኛ ከተማ አንዴ ከሸሹ መግባት እንጂ መውጣት የለም። 👉 እግዚአብሔር እንደ ማርያም ከክርስቶስ እግር የማንጠፋ ፣ እንደ ጴጥሮስ ብንስት መሸሻችንን ወደ ክርስቶስ ብቻ በምናደርግበት ህይወት ይባርከን።🙏 #የመማፀኛ_ከተሞች #ምቅላት #Ref:@Operationezra_bible_college ¶Follow | Join | Share #ከቃሉ_ማዕድ

የቀጠለ... ☑ ምቅላት የሚለው ቃል የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን የመማፀኛ ከተማ ለሚለው በምትክነት እንጠቀመዋለን። ✳️የመማፀኛ ከተሞች ልዩ ባህርያት
ዘኍልቍ 35:25 25 ማኅበሩም ነፍሰ ገዳዩን ከደም ተበቃዩ እጅ ያድነዋል፥ ማኅበሩም ወደ ሸሸበት ወደ መማፀኛ ከተማ ይመልሰዋል፤ በቅዱስ ዘይትም የተቀባው ዋነኛው ካህን እስኪሞት ድረስ በዚያ ይቀመጣል።
🌠 እንግዲህ ለበቀል የሚፈለገውን ሰው የማዳን ሥራ የግለሰቡ ብቻ ሳይሆን የአካበቢውም ጭምር ነው። 💢 ምቅላት = "Cities of refuge" (የመማፀኛ ከተሞች)፧፦ ☑ ጥርጊያ መንገድ 🛣 ☑ ጠቋሚ ምልክት ⬅️➡️↗️↖️ ☑ በማታ ብርሃን🏮 አላቸው። 🔑እነዚህ ከተሞች ለማን ተሰሩ?👇
ዘኍልቍ35:11 11 በስሕተት ነፍስ የገደለ ወደዚያ ይሸሽ ዘንድ የመማፀኛ ከተሞች እንዲሆኑላችሁ ከተሞችን ለእናንት ለዩ።
👉ዘፍ 9:6& ዘፀ 20, ሰውን መግደል ሀጢአት ሳይሆን በደል ነው
ዘኍልቍ 35:16-17 16 በብረት መሣርያ እስኪሞት ድረስ ቢመታው ነፍሰ ገዳይ ነው፤ ነፍሰ ገዳዩም ፈጽሞ ይገደል። 17 ሰውም በሚሞትበት በእጁ ባለው ድንጋይ ቢመታው የተመታውም ቢሞት፥ እርሱ ነፍሰ ገዳይ ነው፤ ነፍሰ ገዳዩም ፈጽሞ ይገደል።
🔱 “ ‘ሰው የገደለ ማንኛውም ሰው በሞት የሚቀጣው ምስክሮች ሲመሰክሩበት ብቻ ነው፤ ይሁን እንጂ ማንም ሰው በአንድ ምስክር ብቻ በሞት አይቀጣም። ዘኍ35:30 💥 Beyond reasonable doubt the judgement had better be catch red handed።{ከምክንያቶች ባለፈ እጅ ከፍንጅ መያዝ ይኖርበታል።ለምን? ልክ እንደ 'ናቡቴ' በሐሰት ምስክሮችም ሰው ሰውን ሊያስገድል ስለሚችል።} 👉ዘፍ 21:12 በአደጋ/በስህተት ለገደለ ግን ማምለጫው የመማፀኛ ከተማ ነው። ✳️ የከተሞቹ አመራረጥ ✳️
ኢያሱ 20:7-8 7 በንፍታሌም ባለው በተራራማው አገር በገሊላ ቃዴስን፥ በኤፍሬምም ባለው በተራራማው አገር ሴኬምን፥ በይሁዳም ባለው በተራራማው አገር ኬብሮን የምትባለውን ቂርያትአርባቅን ለዩ። 8 በዮርዳኖስም ማዶ ከኢያሪኮ ወደ ምሥራቅ ከሮቤል ነገድ በምድረ በዳው በደልዳላው ስፍራ ቦሶርን፥ ከጋድም ነገድ በገለዓድ ራሞትን፥ ከምናሴም ነገድ በባሳን ጎላንን ለዩ።
🔅ከዮርዳኖስ ወዲህ 📌ቃዴስ = ቅድስና ፧ በንፍታሌም ተራሮች 📌ሼኬም=ትከሻ ፧ በኤፍሬም ተራሮች 📌ኬብሮን=ሄብሮን= ሕብረት ፧ በይሁዳ ተራሮች 🔅ከዮርዳኖስ ወዲያ 📌ጎላን= መሻገሪያ ፧ በምናሴ ዳርቻ 📌ገለዓድ = ተራራ / ከፍታ ፧ በጋድ 📌ባሶር=ብርታት ፧ በሮቤል ነገድ ዳር ✴️ በዮርዳኖስ ማዶ እና በከነዓን ምድር ያሉ ከተሞች ናቸው። የስማቸው ትርጉም ከ ዕብ 6፥17-20 ካለው ሀሳብ ጋር ያላቸውን ተያያዥነት ቀጥሎ እንመለከታለን። ➠ ይቀጥላል ◦◦◦ #የመማፀኛ_ከተሞች #ምቅላት ¶Follow | Join | Share #ከቃሉ_ማዕድ Drop your rxņ❤️

📌እግዚአብሔርን ስለ እጁ በረከት ሳይሆን ስለማንነቱ መከተል ይብዛልን🙌 🔆 ኢየሱስ ክብራችን ነው። 🔆 #ከቃሉ_ማዕድ ¶Follow | Join | Share

══════════════☦☦☦═════════════               ☑ የመማፀኛ ከተሞች (ምቅላት) 👉በመጀመሪያ መሰረታዊ የመፅሐፍቅዱስ ጥቅሶችን እንመልከት፦ 📌ዘጸአት 21:13 13 ባይሸምቅበትም፥ ነገር ግን እግዚአብሔር ድንገት በእጁ ቢጥለው፥ የሚሸሽበት ስፍራ እኔ አደርግልሃለሁ። 📌 ዘኁ 35 (ለሌዋውያን ከተሰጡት 48 ከተሞች መሀል ስድስቱ የመማፀኛ ከተሞች ነበሩ ) 📌በተጨማሪም እነዚህ ጥቅሶች ማመሳከሪያ ይሁናችሁ (ዘዳ 4:41-43 ፣ ዘዳ 19 ፣ ኢያሱ 20፣ 21:13፣ 21፣ 27፣32፣36፣38) ✨በሁለተኛነት መፅሐፍ-ቅዱስ በአዲስ-ኪዳን ደግሞ የዕብራውያን ፀሐፊ የመንፈስ-ቅዱስን ሀሳብ እንደዚህ ያወጋናል፦ ዕብራውያን 6:17-20 17-18 ስለዚህም እግዚአብሔር፥ የተስፋውን ቃል ለሚወርሱ ፈቃዱ እንደ ማይለወጥ አብልጦ ሊያሳያቸው ስለ ፈቀደ፥ እግዚአብሔር ሊዋሽ በማይቻል በሁለት በማይለወጥ ነገር፥ በፊታችን ያለውን ተስፋ ለመያዝ ለሸሸን ለእኛ ብርቱ መጽናናት ይሆንልን ዘንድ፥ በመሓላ በመካከል ገባ፤ 19 ይህም ተስፋ እንደ ነፍስ መልሕቅ አለን እርሱም እርግጥና ጽኑ የሆነ ወደ መጋረጃውም ውስጥ የገባ ነው፤ 20 በዚያም ኢየሱስ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ሊቀ ካህናት የሆነው፥ ስለ እኛ ቀዳሚ ሆኖ ገባ። 🔅 እንግዲህ በሁለቱም ሀሳቦች ውስጥ ግን "መሸሽ" የሚል ሀሳብ እናገኛለን። በመጀመሪያ ደረጃ የሚሸሸው ወደ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ለምን??? 👉የማይለወጥ እግዚአብሔር ብቻ ስለሆነ።👇 ሚልክያስ 3:6 6 “እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም፤ ስለዚህ እናንተ የያዕቆብ ልጆች ሆይ፤ አልጠፋችሁም። አ.መ.ት ❇ ይህም ብቻ አይደለም ኪዳን ገብቶ መፈፀም የሚችል እግዚአብሔር ብቻ ስለሆነም ጭምር ነው። 👇
ዘፍጥረት 15:8-11,17-18 8 “አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ፥ እንድወርሳት በምን አውቃለሁ?” አለ። 9 እርሱም፦ “የሦስት ዓመት ጊደር፥ የሦስት ዓመት ፍየልም፥ የሦስት ዓመት በግም፥ ዋኖስም፥ ርግብም ያዝልኝ፡” አለው። 10 እነዚህንም ሁሉ ወሰደለት፥ በየሁለትም ከፈላቸው፥ የተከፈሉትንም በየወገኑ ትይዩ አደረጋቸው፤ ወፎችን ግን አልከፈለም። 11 አሞራዎችም በሥጋው ላይ ወረዱ፥ አብራምም አበረራቸው። 17 ፀሐይም በገባች ጊዜ ታላቅ ጨለማ ሆነ፤ የምድጃ ጢስና የእሳት ነበልባል በዚያ በተከፈለው መካከል አለፈ። 18 በዚያ ቀን እግዚአብሔር ለአብራም እንዲህ ብሎ ቃል ኪዳን አደረገ፦ “ከግብፅ ወንዝ ጀምሮ እስከ ትልቁ ወንዝ እስከ ኤፍራጥስ ወንዝ ድረስ ይህችን ምድር ለዘርህ ሰጥቼአለሁ፤
🌠 ይህን ጊዜ የተፈፀመ አንድ ታሪክ አለ👉 በብሉይ ታሪክ ኪዳን ከሚገባባቸው ስርዓቶች አንዱ እንስሳትን መርጦ በየሁለትም ማካፈል ፥ የተከፈሉትንም በየወገኑ ትይዩ አድርጎ ማስቀመጥ፤ እናም በተካፈሉት እንስሳት መካከል የኪዳኑ ባለቤቶች ይሻገራሉ። ትርጓሜውም ያስደነግጣችኋል። ምን ማለት መሰላችሁ፦ ይህንን ኪዳን ባፈርስ እኔም እንደዚህ ለሁለት ልከፈል ማለት ነው።...ነገርግን የኪዳን ባለቤት መሆን ካለበትም ሊሆን የሚገባው ታማኙ እግዚአብሔር ብቻ ስለሆነ የአብርሃም ድርሻ እዚህጋ "ማመን" ይባላል። 💢 ስለዚህ በእግዚአብሔር ኪዳንበእግዚአብሔር ታማኝነት እና አለመለወጥ ላይ የተመሠረተ መሸሻ ተዘጋጀ እነዚህም በብሉይ-ኪዳን "የመማፀኛ ከተሞች" ተብለው ተጠሩ። ይቀጥላል... #የመማፀኛ_ከተሞች #ምቅላት ¶Follow | Join | Share #ከቃሉ_ማዕድ Drop reaction🔥

══════════════💥═════════════ ቀጣይ...አርዕስት፦ 📌 "የመማፀኛ ከተሞች" ወይንም ምቅላት ምንድናቸው❔ ══════════════💥═════════════ #የመማፀኛ_ከተሞች #ምቅላት
+2
══════════════💥═════════════ ቀጣይ...አርዕስት፦ 📌 "የመማፀኛ ከተሞች" ወይንም ምቅላት ምንድናቸው❔ ══════════════💥═════════════ #የመማፀኛ_ከተሞች #ምቅላት ¶Follow | Join | Share #ከቃሉ_ማዕድ