Orthodox mezemur ኦርቶዶክስ መዝሙር
Открыть в Telegram
እኔ ግን በቸርነትህ ታመንሁ ልቤም በመድኃኒትህ ደስ ይለዋል የረዳኝን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ ለልዑል እግዚአብሔር ስምም እዘምራለሁ ። መዝሙረ ዳዊት 13 : 5 - 6 o:-)- ለማንኛውም ጥያቄ በስር ባስቀመጥነው ሊንክ ሊጠይቁን ይችላሉ 👇👇 - @tan_flf -
БольшеСтрана не указанаКатегория не указана
283
Подписчики
Нет данных24 часа
-17 дней
+2530 дней
Архив постов
ሐዋርያው መነኩሴ
ሐዋርያው መነኩሴ የመረጡህ ሥላሴ/2/ ዋስ ጠበቃ ሁናት ተክልዬ ለነፍሴ
አዝዳሞት ትናገረው የአንተን ሐዋርያነት የወንጌል ገበሬ የጣዖታት ጠላት ጸሎተኛው ቅዱስ አባ ተክለሐይማኖት ክንፍን የተሸለምክ እንደ ሰማይ መልአክ/2/
አዝብራናው ሲገለጽ ገድለ ተክለሐይማኖት ከሰወ ልጅ ልቦና ያወጣል አጋንት የቅዳሴው ዕጣን ሲወጣ ከዋሻው ምድርን ይባርካል ጸሎቱ ምህላው/2/
አዝየኢትዮጵያን ምድር አርስከው በመስቀል ጭንጫው ፈራረሰ ተዘራበት ወንጌል ትላንት የዘራኽው ዛሬም ለእኛ ሆኗል አምላከ ተክልዬ ብለን ዘምረናል /2/
አዝከሱራፌል ተርታ ቆመህ ስታጥን ሥሉስ ቅዱስ ብለህ ስታመሰግን ጸሎት ትሩፋትህ ትህትና ስግደትህ ፆምህ ከፍ አድርጎ ሰማይ አደረሰህ/2/
አዝዛፉ ሲመነገል አምላክ የተባለው መቶሎሚ ሲያፍር ትልቅ ሰው ነኝ ያለው የተክልዬ ጸሎት ብዙ ነው ምስጢሩ ስድስት ክንፍ አወጣ ቢቆረጥ አንድ እግሩ/2/ ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮ https://t.me/Qmamaaa ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
ፈተና ወጀብ ቢበዛ
ፈተና ወጀብ ቢበዛ
አይተናል ሕዝቡን ሲያበዛ
በሕይወት አንዴ ጠርቶናል
እግዚአብሔር መች ይተወናል/2/
አዝፍቅር ነዉ የናርዶስ ሽቶ ወደደን ተሰቅሎ ሞቶ ነጎድጓድ መብረቅ ቢሆንም በህይወት አለን አሁንም/2/
አዝመኳንንት ደጁን ክፈቱ የፀጋዉ ፈልቷል ዘይቱ ተራግፏል ሸክማችን ምህረቱ ቢፈስልን/2/
አዝተጽናንቷል አርፏል ልባችን በእሳት ታጥሮአል ቅጥራችን አንወድቅም አንሸነፍም ይዞናል የአምላካችን ስም/2/
አዝሕይወት ነህ የፅድቅ ጥላ ያውቅሐል ቃል የተመላ ነህ አንተ ጣፋጭ ምግባችን እግዚአብሔር ቸሩ አምላካችን/2/ ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮ https://t.me/Qmamaaa ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
🤩አበርታኝ ገብርኤል🤩
አንተ የልቤ ወዳጂ ከአንተ ጋር አለኝ ጉዳይ
አንተ የእኔ ድጋፍ ከአንተ ጋር አለኝ ጉዳይ
አበርታኝ ገብርኤል በምድር በሰማይ
ምስራች አሰማኝ ናልኝ ከአርያም ላይ
አዝሀዋርያ ልደት ፅድቅን ምታሰማ ከጥንት ጀምሮ የሆንክ የኔ ግርማ ስወጣ አይሀለሁ ሆነህ ከፍታዬ ክንፍህ ተዘርግቶ ለምህረት በላዬ
አዝገብርኤል ፀሀይ ወጣ በማለዳ ማእረግ ልትሆነኝ እኔን ልትረዳ የእሳቱ ወላፈን ሀይሉ ቀዘቀዘ ኩራት አለው ልቤ በአንተ እየታገዘ
አዝመልአከ አድኖ ተልከህ ከጌታ የመከራዬ ክንድ ጉልበቱ ተመታ ከእንግዲህ ሚያሰጋኝ ማነው በህይወቴ እያለኝ ማምለጫ ገብርኤል አባቴ
አዝማንም የማይፈታው የህይወት ቋጠሮ ሰም ወርቅ የሆነብኝ የነፍስ እንጉርጉሮ ብዙ የምነግርህ በውስጤ አለ እና ነፍሴን ልታዳምጥ ገብርኤል ቶሎ ና መዝሙር 🎙ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮ https://t.me/Qmamaaa ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
ወረት የሌለው
ወረት የሌለው መውደድ
ወረት የሌለው ፍቅር
አንተ ጋር ብቻ ነው
ያለው እግዚአብሔር /2/
አዝ
ዘመን የማይዘው ጊዜ የማይገድበው
ያንተ ፍቅር ብቻ ቀን በቀን አዲስ ነው
ከዴማስ ጋር ስሄድ ትቼው የአንተን መንገድ
ከቶ መች ቀነሰ ለእኔ ያለህ መውደድ
አዝ
በአመጽ ብጠፋም ከመንጋህ መካከል
ይመሻል ይነጋል እኔን ስትከተል
እንደወጣ ይቅር ብለህ መቼ ተውከኝ
ሴኬም ድረስ ወርደህ ልጅህን ፈለከኝ
አዝ
በዝናዬም ዘመን ባለጸጋ እያለሁ
ቤቴ በወዳጆች ቀን በቀን ሙሉ ነው
እንደ ጤዛ ሲረግፍ ሃብትና ንብረቴ
ያላንተ ማን ነበር በፈርሰው ቤቴ
አዝ
የታመንኩባቸው ወዳጆች ሲከዱኝ
ሕመሜ ስር ሆነው ደጋግመው ሲወጉኝ
ላንተ ጊዜ ባጣም ለኔ ጊዜ አለህ
ገፋህ ክፉ ቀኔን ከኔ ጋራ አብረህ
ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች
•➢ ሼር // SHARE
👇👇👇
https://t.me/Qmamaaa
♡ ቅዱስ ሚካኤል ወዳጅ ነህ ♡
ቅዱስ ሚካኤል ወዳጅ ነህ ለሁሉ
ዛሬም ቆመሀል በኪዳንህ ላሉ
ክንፍህን ዘርጋ ሚካኤል ቅደም ከፊቴ
ምራኝ መንገዱን እንዳይመሽ ልድረስ ካባቴ
እንዴት ይገፋል ጎዳናው ካላንተ እርዳታ
ጥሜን ቁረጠው በበትርህ ጭንጫውን ምታው
አዝ= = = = =
ተጠመጠመ ጠላቴ በእሳት ሰንሰለት
የጌታ መልአክ ሚካኤል በሰይፍ ወድቆበት
የለም ከቦታው ስመለስ አጥቼዋለው
የሚረዳኝን ተሹሞ አይቼዋለው
አዝ= = = = =
ከመቃብሩ ድንጋዩን አንከባለሀል
ስለረዳኸዉ ዳንኤል እጅግ ወዶሀል
ይነዋወፃል ባህሩ አንተ ስትመጣ
እግዚአብሄር ይንገስ ዳቢሎስ መድረሻ ይጣ
አዝ= = = = =
አለኝ ትዝታ በቤትህ ከልጅነቴ
ስትሳሳልኝ እያየው ፀንቷል ጉልበቴ
ልዘምር እንጂ ላመስግን ታላቁን ጌታ
አንተን የሰጠኝ ጠባቂ በቀን በማታ
ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች
•➢ ሼር // SHARE
👇👇👇
https://t.me/Qmamaaa
https://t.me/Qmamaaa
https://t.me/Qmamaaa
📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ፲፪/12
🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
በዚች ዕለት የተባረከና የተመሰገነ በሰማያት ያለ ምሥጢርን ያየ የኢትዮጵያ ንጉሥ ላሊበላ የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ።
ይህንንም ቅዱስ ወላጆቹ በወለዱት ጊዜ እግዚአብሔርን በመፍራትና በበጎ ሥራ ሁሉ አሳደጉት ። አድጎ አካለ መጠን በአደረሰ ጊዜ ታላቅ ወንድሙ ንጉሥ ቀናበት መልእክተኞችንም ልኮ ወደርሱ አስመጣው ምክንያትም ሽቶ ከሦስት ሰዓት እስከ ሰባት ሰዓት እንዲገርፉት አዘዘ ።ከዚህም በኋላ በፊቱ እንዲአቆሙት አዘዘ በአቆሙትም ጊዜ የደረሰበት ጉዳት እንደሌለ አይተው ንጉሡና መኳንንቶቹ ሁሉ አደነቁ የእግዚአብሔር መልአክ ከግርፋት ሠውሮታልና ። ከዚህ በኋላም ወንድሙ ንጉሥ በአንተ ላይ ስለአደረግሁት ክፉ ሥራ ወንድሜ ሆይ ይቅር በለኝ ብሎ ለመነውና እርስ በርሳቸው ታረቁ ።
ከዚህ በኋላም እግዚአብሔር መንግሥትን አወረሰው ። ክብር ይግባውና ጌታችንም የፍቅሩን ጽናት በአየ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለት ወደ እርሱም ወደ ሰማያት አወጣው ዐሥሩን አብያተ ክርስቲያንም እንዴት እንደሚሠራቸው አሳየው እነርሱም ሥራቸው የየራሳቸው የሆነ ልዩ ነው ተመልሶም መንፈስ ቅዱስ እንደአራቀቀው በአስደናቂ ጥበብ አነፃቸው ። እሊህንም አብያተ ክርስቲያናት አንፆ በፈጸመ ጊዜ መንግሥቱን ለወንድሙ ልጅ አወረሰ ። ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መቶ ብዙ ቃልኪዳን ገባለት ቅዱስ ላሊበላም ጌታችንን እያመሰገነ በምድርላይ ወድቆ ሰገደ ። ጌታችንም ሰላምታ ሰጥቶት በክብርና በምስጋና ወደ ሰማያት ዐረገ ። ከዚህም በኋላ ጥቂት ሕማም ታሞ በሰላም አረፈ። ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል)
ሚካኤል ወረደ
ሚካኤል ወረደ እኛም ከቤት ወጣን
በአውደ ምህረቱ ቆሟል ሊባርከን
በፊቱ ተቀኘን ቅኔን ስለክብሩ
ወጣት አዛውንቱ ህጻናት ዘምሩ
አዝሚካኤል ደምቀን እየኖርን በግብጽ አሸንክታብ ሚካኤል ሞልቶልን አያውቅም የልባችን ሀሳብ ሚካኤል ያስጎነበሰንን ነውር አንከባሎ ሚካኤል ጠራን ለዝማሬ ከተኩላው አስጥሎ
አዝሚካኤል እጃችን ተባርኮ ለምለም ጎዘጎዘ ሚካኤል ልባችን ለፍቅር ለሰላም ታዘዘ ሚካኤል የድሃ አደጉን ልጅ በፍቅር የሚያሳድግ ሚካኤል ከክፉ መከራ ከሞት የሚታደግ
አዝሚካኤል ከፊታችን የለም ጥቁር መጋረጃ ሚካኤል ጎዳናው ቀናልን ቀድሞ የርሱ ምልጃ ሚካኤል በኃጢያት ተይዘን ከደጁ ብንመጣ ሚካኤል ኑ ልጆቼ ብሎ ሊቀበለን ወጣ
አዝሚካኤል ተግተን ስንጠብቀው ዘርግተን ምንጣፉን ሚካኤል ወደኛ ፈጠነ ሊመራልን ሰልፉን ሚካኤል ኃይልን አልብሶናል ከእግዚአብሔር ተልኮ ሚካኤል በአናብስቱ ጉድጓድ መጽናናትን ሰብኮ
አዝሚካኤል ምልጃው ስለረዳን ነጋልን ሌሊቱ ሚካኤል በረሃ አልቀረንም ተጠምተን በከንቱ ሚካኤል አዲስ ሰው ሆነናል ዘንዶው ተሸንፎ ሚካኤል የእግዚአብሔርን ፍቅር በልባችን ጽ
ምስጋናዬን ላምላክ አቀርባለሁ
ምስጋናዬ ለአምላኬ አቀርባለሁ
በማደርያው ገብቼ እስግድለታለሁ
ኤልሻዳይ ነው ጌታ ሁሉን ቻይ
ይፈፀማል አምናለሁ የልቤ ጉዳይ{፪}
ዘንባባዬን ይዤ እንደ ህፃናቱ
ሆሳዕና ልበለው ሰግጄ በፊቱ
ምንም ባዶ ብሆን እውቀት ቢጎለኝ
ለስሙ ልዘምር ከልካይም የለኝ{፪}
አምላኬ በፌትህ ቃል አለብኝ እኔ
ቋንቋዬ መዝሙር ነው ያንተ እንደመሆኔ
በአሚናዳብ ደጃፍ በቅድመ ታቦቱ
ያየክብርህ ሁደት ጠራኝ ማህሌቱ{፪}
የህይወት ትርጉሜ አንተ ነህ ደስታዬ
ስምህን ማገልገል ክብሬ ነው ስራዬ
ለታመነው ጌታ ምስክር የሆኑ
ከብረው ተመለሱ ለበረከት ሆኑ{፪}
መነሻዬ አንተ ነህ ጉልበቴና ክብሬ
መድረሻዬም አንተ መደምደሚያ ቅጥሬ
በፅዮን ተራራ ስትገለጥ ያኔ
ነጩን ልብስ አልብሰህ አስነሳኝ ለቅኔ{፪}
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች
•➢ ሼር //
