መጽሐፉ ይናገር | Official
Открыть в Telegram
መጽሐፉ ይናገር ክርስቲያናዊ አገልግሎት በወንጌላዊያን አማኞች የነገረ መለኮት ተማሪዎችና የቃሉ አገልጋዮች በ2013 ዓ.ም የተመሠረተ ተቋም ሲሆን አሁናዊ መስኮቹ፦ 🔘 የመጋቢያንና መሪዎች ስልጠና 🔘 የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ (Gateway) 🔘 የቲቪ ፕ/ም በተስፋ TV ቅዳሜ 9-10 🔘 መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኅብረቶች ሊንክ፦ @metsihafuyinager በውስጥ፦ @adfontess ☎️ +251947424046
Больше340
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
+1230 дней
Архив постов
ቃለ እግዚአብሔርን የንግግሮችህ ማጠናከሪያ አድርገህ ከመጠቀም ተቆጠብ። ይልቅ ገና ከመነሻው እንደ እግዚአብሔር ቃል ተናገር። "ማንም የሚናገር እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር" የተባለውን አትዘንጋ።
መጽሐፍ ቅዱስ አንተ ብዙ ካወራህ በኋላ ንግግሮችህ እግዚአብሔራዊ እንደሆኑ የምታስረዳበት ሰነድ ሳይሆን ምን፣ መቼና የት መናገር እንዳለብህ ታውቅ ዘንድ የተሰጠህ መመሪያ ነው። ስለዚህ ረጅም አውርተህ ይህ ንግግር እንደ እግዚአብሔር ቃል ነው? ከምትል ከቃሉ ጋር ረጅም ቆይተህ ጥቂት ብታወራ ይሻልሃል።
------------
Join & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
"ኢየሱስ ክርስቶስ ብሎ የተናገረው በዚህ ዓለም ስለ እኔ አባቱንና እናንቱን የሚተው በዚሁ ዓለም (በቤተ ክርስቲያን) ብዙ ወንድሞችና እህቶች ይኖሩታል ነው። በዚህ ዘመን ግን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንኳን እናትና አባት.... ወንድም እህት የለንም። ሁሉም fake ኅብረት ነው። ይህ ጅምላ ፍረጃ ሊሆን ይችላል ግን ይህ የዘመናችን ቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ ገጽታ ነው።"
ዶ/ር ተካልኝ ዱጉማ በመካር ወጎች ከተናገረው!
ነገሩ እንዲሁ ይሆንን?
------------
⏰11:30-1:30
📍Ayat Shopping Mall.
------------
Join & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
በውስጥ፦ @adfontess
ዛሬ በአያት ሴንተር!
የቆላስይስ ጥናት ከጀመርን አንድ ወር ሆኖናል። በእግዚአብሔር እርዳታ በቃሉ እየተሞገትን ነው። ባለፉት ሦስት ሳምንታት ቆላ 1:1-2 ላይ የተነጋገርን ሲሆን ዛሬ በሚኖረን ጊዜ በወንድማማች መዋደድ ጨዋታዎች እስካሁን ከሁለቱ ቁጥሮች በተነሱት ጥያቄዎች ላይ እንወያያለን።
የውይይት ጥያቄዎች!
➊ በቆላ 1:1 ጳውሎስ "የክርስቶስ ሐዋሪያ" ተብሏል፣ በዚህ ዘመን የክርስቶስ ሐዋሪያ (በቤተ ክርስቲያን የተሾመ) አይኖርም?
➋ በጥናት ጊዜያችን በቁ2 ላይ ስለሚገኙት ቁልፍ ቃሎች ስንነጋገር "ቅዱሳን" የሚለው የእግዚአብሔር ሕዝቡን የመለየት ሥራ (positional status) ሲሆን "የታመኑ" የሚለው ቃል ደግሞ የአማኙ የየእለት ሕይወት ጉዞ (sanctification) እንደሆነ ተነጋግረን ነበር። ይህን በሚመለከት ቀጣይ ጥያቄ ቀርቧል።
"ቅዱሳንና በክርስቶስ የታመኑ" የሚለው ሃሳብ የአንድ concept ተለዋዋጭ አገላለጽ እንደሆነ ብንረዳውስ? "እና" በሚለው አያያዥ ቃል መቅረቡ ተመሳሳይ ነገር እያወራ እንደሆነ ማሰብ አንችልም?
➌ "የታመኑ ወንድሞች" ከሚለው ሐረግ ተነስተን ጳውሎስ ነገ ድነትን ከነገረ ቤተ ክርስቲያን ነጥሎ አይረዳም! ያልነውን እናስታውሳለን። ይህ ሃሳብ ከቤተ ክርስቲያን ጋር በቀጥታ የተገናኘው እንዴት ነው? ክፍሉን መለጠጥ አይሆንብንም?
➍ ሲጀመር ቁ1 እና 2 ላይ ስለ ድነት እንዴት ልናወራ እንችላለን? ይህን (ገና በመግቢያ ክፍሉ) ማድረጋችን ዐውዳዊ ችግር አይፈጥርብንም?
------------
⏰11:30-1:30
📍Ayat Shopping Mall.
------------
Join & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
በውስጥ፦ @adfontess
"ፍቅር ምህረቱን የቀመሱቱ
ውበቱን ያዩ ሐዋሪያቱ
ለስሙ ኖረው መረጡ መሞት
የፍቅሩ ሆነው ሰማዕታት
ተነክተው በምህረቱ
ተነክተው በቸርነቱ....
ነክቷቸው ምህረቱ...
ነክቷቸው የዋህነቱ...
አቤት ትህትና አይ ቅንነት....
ሰው ያስተማረ ኖሮ በሕይወት"
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
ውድ ቤተሰቦቻችን ዛሬ ምሽት በቲክቶክ ላይ የሚኖረን የይሁዳ መልእክት ጥናታችን ከተለመደው ሰዓት 30 ደቂቃዎችን አርፍዶ (3:30) የሚጀምር ይሆናል።
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
ዛሬ ምሽት በTiktok ገጻችን!
-------🔥------------
የይሁዳ መልእክት ጥናት! 📖
እለቱ፦ ማክሰኞ ምሽት
ሰዓቱ⏰፦ 3:00-4:30
ቤቱ፦ መጽሐፉ ይናገር
የጥናቱ ክፍል፦ ቁ22-23
ሁላችንም በመገኘት እናትርፍ!!
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
ልዑሉ እግዚአብሔር ከድኩሙ የሰው ልጅ ጋር ያደረገው የቃል ኪዳን ስምምነት! ለዘላለም ታማኙ አምላክ ለማይታመነው ሰው ታማኝነቱን ሊገልጥ "ባልታመን በዚህ ፈትኑኝ" ብሎ በእነርሱ ጫማ ወርዶ መጣ!
እግረ መንገድ የቲክቶክ አካውንታችንን ተቀላቀሉ!!!!
👇
https://vt.tiktok.com/ZS4BUbKox/
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
እግዚአብሔር ወዶናል! 🔥
በሌሎች መወደድ ለእኛ መሠረታዊ ነገር አይደለም። እግዚአብሔር ወዶናልና። የውስጣችን (የነፍሳያችን) የፍቅር ጥያቄ ተመልሷል። ፍቅርን ከውጭ ስንፈልግ የእግዚአብሔርን ፍቅር አናቃልልም። ይልቅ ግኑኝነታችን ሁሉ ይህን የርሱን ፍቅር የምንገልጥባቸው እንጂ የፍቅር ጥያቄአችንን (ረሃባችንን) የሚመለሱ አይደሉም።
የነፍስያችን ፍቅር ፍለጋ ጩኸት ምላሽ በእግዚአብሔር ዘላለማዊ ፍቅር ምላሽ አግኝቷል።
እግዚአብሔር ወዶናል!!! 🔥
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
ዛሬ ከሰዓት በአያት ሴንተር
-----🎻---------
የቆላስይስ መልእክት ጥናት
(የሚያስመሰግን ሕይወት)
ጳውሎስ ስለ ቆላይስይ አማኞች ያመሰግናል። ይህንንም እንዲያውቁለት ይፈልጋል። የምስጋናውም ሰበብ ስለነርሱ የሰማው መልካም ዜና እንደሆነ ክፍሉ ያትታል። በዛሬው ጥናታችን የቆላስይስ አማኞች የተሰጣቸውን ምስክርነት መሠረትና ይዘት ከመጽሐፉ እንመረምራለን።
-----------
⏰ ከ11:30-1:30
📍አያት ባቡር ጣቢያ ጋር
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
መብዛት ከጥንትም የእግዚአብሔር ፕሮግራም ነበር። በዘፍ 1 "ብዙ ተባዙ" የተባለውና በዘፍ 12 ለአብርሃም "አበዛሃለሁ" የተባለው እንደሚገናኙ አስተውላችኋል?
ከቴሌቭዥን ፕሮግራማችን የተወሰደና በቲክቶክ አካውንታችን ከደቂቃዎች በፊት የተቀመጠ አጭር ቪዲዮ ይህን ይነግረናል። እግረ መንገድ ወደ ቲክቶካችንም ኑልን።
https://vt.tiktok.com/ZS4NWLgA5/
ስለ እግዚአበሔር ስንናገር በተምሳሌትና ተዛምዶ ማውራታችን እሙን ነው። ጸኑ የማይናወጥ መሠረት መኾኑን ለመግለጽ ዐለት ብለነዋል። እረኛም ኾኖ ተመስሏል። በንስር ክንፍ እንደ ተሸከመን ተነግሮናል። እንደ እናት ርኁሩኀ መኾኑንም ተጽፎልናል። ምሳሌና ንጽጽሮቻችን ኹሉ ግን ሙሉ አይደሉም። እንዲያውም የሚያጎድሉት ይበዛል። ይኼን እውነት አጽዖኖት ሰጥቶ የሚያብራራው የምስራቃዊያኑ Apophatic theology ነው። ተገልጦና ተዘርዝሮ የማይዘለቀውን መለኮታዊ ምሥጢር በተቃርኖ በኩል ለማሳየት ይደክማል።
የሰው ልጆች ቋንቋና ንድፋዊ ክፍሎች (conceptual categories) መለኮትን ለማስተንተን ሽባ ስለሆኑ ከእኛ እጅግ መለየቱን በማጽናት ድብቅነቱን ደግሞም ምጡቀነቱን ለማስጠበቅ ይሞክራል። እንደ ሰው አይደለም ብሎ ይጀምራል። ይዋሽ ዘንድም ሥጋ ለባሽ አይደለም። እሱ ብቻ የማይሞት ነው። እሱ ብቻም ማንም በማይቀርበው ብርሃን ውስጥ ይኖራል። ቸር ነው ስንል እንኳ ቸርነቱ በሰው መደብና ክበብ አይደለም። ይኼን መለኮታዊ ስውርነት Gregory of Nyassa "luminous darkness" በማለት ይጠራዋል። ቅዱስ አውግስጢኖስም "If you comprehend it, it is not God" በማለት አስረግጧል።
Cataphatic theology እግዚአብሔርን በመገለጡ በኩል ልናውቀው እንደምንችል ሲያጸና Apophatic theology ደግሞ ተገልጦም ጭምር ስውር መኾኑን እንዳንዘነጋ ያሳስበናል። የመለኮትን እውነት ለማስረዳት ስንባትል ተዛምዶአችን ውስንነት የሚያሰቃየው ድኩም መኾኑን መዘንጋት አይኖርብንም። ለክፉ መወራረስ የሚጋብዝ ተምሳሌት አለመጠቀማችንንም ማጤን ይኖርብናል።
(ወንድም ኢብሳ ቡርቃ እንዳሰፈረው)
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
ዛሬ ምሽት በTiktok ገጻችን!
-------🔥------------
የይሁዳ መልእክት ጥናት! 📖
እለቱ፦ ማክሰኞ ምሽት
ሰዓቱ⏰፦ 3:00-4:30
ቤቱ፦ መጽሐፉ ይናገር
የጥናቱ ክፍል፦ ቁ20-21
ሁላችሁም በመገኘት እናትርፍ!!
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
አንድ ነገር በጣም ገብቶኛል በሕይወት ዘመኔ፣
የዛለው በአንተ ሲበረታ አይቻለሁ በአይኔ፣
ተቆጥተህ በዚያው አትቀርም እስከ መጨረሻ፣
ጻዲቁ ቢወድቅም ይነሳል ስላለው መድረሻ...።
ስንት ጊዜ አነሳኸኝ!...🤲
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
ከነገ ተበድራችሁ አትጨነቁ።
ነገ የሚባለው ቀን የራሱ የጭንቀትና ጣጣ በጀት አለውና ስትደርሱበት ትጨነቃላችሁ፤ አሁን ላይ ስለ ዛሬያችሁን አመስግኑ። ዛሬም ግልጽ ካልሆነ ጸልዩ። ወደ ወንድሞች ኅብረት ሽሹ። ስለ ነገ አስባችሁ ጭንቀት አዕምሯችሁን አልለቅ ካላችሁ ስለትላንትናችሁ እያመሰግናችሁ ለአምላካችሁ ተቀኙለት።
ከዳኒ ጋር እንዲህ በሉ....
"የሚያስጨንቀኝን በርሱ ላይ ጣልኩና፣
ዝማሬ ዘመርኩኝ በገና ያዝኩና፣
አንተ አምላክ ነህ ብዬ የልቤን ብነግረው፣
እግዚአብሔር መንገዴን መልካም አደረገው!"
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
"በምህረትህ ብዛት ቤትህ አግብተኸኛል፣
ከፊትህ ጋር ደስታ ለእኔ ሰጥተኸኛል፣
ደግሜ ደግሜ የማመሰግንህ ምክንያቴ ብዙ ነው፣
ከዚያ ከጨካኙ ነፍሴን ከሚፈልግ ከአውሬው አስጥለኸኝ ነው።" 😍
አንተ እንደረዳኸኝ!
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
አንተ ከዘላለሙ እግዚአብሔር ነህ፤ እኛ የፈጠርኸን የኦጆችህ ሥራ ነን። ስለዚህም ይህን ቀንና በውስጡ ያሉ ሠራዊቶቹን ያለ እጅህ ግልጽ እርዳታ አንችልምና ትታደገን ዘንድ እንለምናለን።
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
ቅዱሳት መጻሕፍት የሚነገሩን እየከፋፈልን (Despense) እያደረግን በሚመቸን መንገድ ስለምንረዳቸው የተለያዩ ፕሮጀክቶች አይደለም። በመሠረቱ እግዚአብሔር አንድ እቅድ፣ አንድ ሃሳብ፣ አንድ ኪዳን፣ አንድ መንግሥት፣ አንድ ተስፋ፣ አንድ ክርስቶስ፣ አንድ ወንጌልና አንድ ሕዝብ ነው ያለው።
(በGateway Hermeneutics Class ወንድም Sol K. እንደተናገረው)
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
ስኬቴ በአንተ መታመኔ፣
ከፍታዬ እግርህ ስር መሆኔ፣
ውበቴ አንተን መጠጋቴ፣
ድምቀቴ ምህረትህ ነው ለእኔ።
ሀ..ሀ...ሀሌሉያ!
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
