የቀጠናው ተመልካች
Открыть в Telegram
በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።
БольшеСтрана не указанаКатегория не указана
4 317
Подписчики
-324 часа
-127 дней
-7530 дней
Архив постов
4 317
🇮🇷🇺🇸🇧🇭 በባሕሬን በአሜሪካ ጦር ሰፈሮች ላይ የተሰሙት የሚሳዬሎቹ ፍንዳታ ኃይል፣ በኳታር ነዋሪዎች የተሰሙ መርገብገቦችን ፈጥረው ነበር።
በጥቁሉ፣ 40 የሚሆኑ ሚሳዬሎች በቀጥታ ወድቀዋል።
የአሜሪካ የአየር መቃወሚያ ብቃትና አቅም፣ እንደ ዩክሬን ተሽመደመደ እንዴ? ይሄ ሁሉ መሬት ሲነካ … ከባድ ነው።
*-*-*
አንተ ቻይና! ምናባህ ትሰራለህ፣ ውጣ ከሀገሬ!
4 317
🇺🇸🇮🇷🇧🇭⚡️- ሰበር ዜና: ብዛት ያላቸው ቀጥታዊ የሚሳዬል ምቶች እና እነሱን ተከትሎ የተፈጠሩ ፍንዳታዎች፣ በባሕሬን 5ኛ የአሜሪካ ጦር ሰፈር የሚገኝበት የNSA ቅጥር ግቢ ውስጥ ተሰምተዋል።
4 317
🇺🇸🇮🇷🇧🇭 - ሰበር ዜና፡ የኢራን መገናኛ ብዙሃኖች ቢያንስ በትንሹ 40 ባለስቲክ ሚሳዬሎችን ባሕሬን ላይ አስወንጭፋለች፣ ብለዋል። በመቶዎች የሚቆጠሩ ፍንዳታዎች በባሕሬን ተሰምተዋል፣ እንደ አንዳንዶች ዘገባ ድሮኖችም ተደባልቀው በአሁኑ ሰዓት እያጠቁ ናቸው። አየር መቃወሚያዎች እና በአንዳንድ ቦታዎች መትረየሶች ለድሮኖቹ እየተንጣጡ አየሩን እንደሞሉት ነው፣ እየተሰማ ያለው።
4 317
❗️🇮🇱/🇺🇸/ 🇮🇷 ከኦፕሬሽን ግምገማ በኋላ፣ ከፍተኛ የIDF እና የፖለቲካ ትዕዛዞችን ተከትሎ፣ የእስራኤል የትራንስፖርት ሚኒስትር፣ የአሜሪካ ወታደራዊ አውሮፕላኖች በቤን ጉሪዮን አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ - እንዲያርፉ ፍቃዳቸው ሰርዘዋል። በዚህም የተነሳ በቴል አቪቩ ቤን ጉሪየን ዛሬ ሊያርፉ የነበሩ የአሜሪካ ነዳጅ ጫኝ ወታደራዊ አይሮፕላኖች፣ ወደ ነጌቭ ምድረ በዳ ሄደው ለማረፍ ተገድደዋል - Hebrew Media
4 317
🇷🇺❌🇺🇦 - የሩስያ ጄራን-4 ሰው አልባ አውሮፕላኖች፣ ዛሬ፣ ወደ ዩክሬን ኦዴሳ ወደብ የሚሄዱ ሁለት የጭነት መርከቦችን መትተዋል።
4 317
🛥❌🇷🇺 የዩክሬን ባሕር ኃይል፣ የሩሲያ FSB የድንበር ጠባቂ መርከብ "ኢዙምሩድ" ን አወደመ።
የዩክሬን የባህር ኃይል አባላት፣ በኖቮሮሲስክ አቅራቢያ የሚገኘውን ይህን መርከብ፣ ሳርጋን-3000 የተባለ የባሕር ላይ ድሮንን በመጠቀም አስምጠውታል።
የመርከቧ ሠራተኞች እና ባሕረኞች፣ ጉዳት ሳይደርስባቸው እና ሳይሞቱ እንዳልቀረም ተዘግቧል።
4 317
🇷🇺⚡️🇺🇦 ኪየቭ፣ ሌሊቱን ስታስተናግድ ባደረችው የሩሲያ ሚሳዬሎች ጥቃት፣ በጭስ ተውጣ ትታያለች።
እንደ ባለፈው ሳምንቱ፣ ዛሬም፣ አንድም የሩሲያ ሚሳዬል በዩክሬን አየር መቃወሚያዎች ተመትቶ አልወደቀም።
ይህም፣ ዩክሬን አየር መቃወሚያዎቿን፣ በተለይም ፔትርዮት ሚሳዬሎቿን፣ አሟጣ ሳትጨርስ አልቀረችም፣ የሚለውን ፍራቻ አባብሶታል።
በዚህም ምክኒያት ይመስላል፣ ሩሲያ ከሰሞኑ ክፍተቱን በስፋት እየተጠቀመች ኪየቭን በከፍተኛ ሁኔታ እየደበደበች ያለችው።
በአሁኑ ሰዓትም፣ ብዛት ያላቸው የሩሲያ ሚሳዬሎች፣ በሰዓት 880 ኪሜ የሚሄደውን እስክንድር ሚሳዬልን ጨምሮ፣ ወደ ኪየቭ የተተኮሱ ሲሆን፣ በጥቂት ሰዓታት ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
4 317
🇷🇺⚡️🇺🇦 የዩክሬን ቻናል "ማይኮላይቭካ ኦንላይን"፣ በዶኔትስክ ኦብላስት ማይኮላይቭካ ከተማ ያለውን የጥፋት መጠን የሚያሳይ ካርታ ለቅቋል።
በትንታኔው መሠረት፣ በከተማው ውስጥ 80% የሚሆኑት ሕንፃዎች ተጎድተዋል ወይም ወድመዋል። ሐምራዊ የተቦደሱ ጣሪያዎችን፣ ቢጫ፣ ከባድ ጉዳትን እና ቀይ፣ ሙሉ በሙሉ መጥፋትን ይወክላል።
ይህ ሁሉ ጥፋት የተከሰተው አንድም የሩሲያ ወታደር በከተማው ዳርቻ እንኳ ገና ሳይረግጥ ነው (በአየር እና በአርትላሪ ብቻ)። ወታደሮቹ ተጠግተው ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ጥፋቱ የበለጠ የከፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
4 317
🇺🇦 እራሳቸውን፣ Coalition of The Willing (የቆራጦቹ ማሕበር- የራሴው ትርጉም ናት) - ብለው የሚጠሩት የአውሮፓ ሕብረት ሀገራት፣ በዛሬው ዕለት ለዩክሬን ባዘጋጁት የጎፈንድሚ ዝግጅት ላይ ዘለንስኪን በየተራ እየተቀባበሉ ሲያቅፉት እና ሲስሙት ውለዋል።
የፈረንሳዩ ኢማኑኤል ማክሮን "አንቺ ጉደኛ፣ ነይ እስኪ ወደዚ" ብሎ ዘለንስኪን እንዳለውና በስስት እንዳቀፈው ተሰምቷል።
የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚንስቴር ስታርመርም፣ "እቺ ድንቡሽቡሽ አጭሬ ፑቲንን ሰራችለት"፣ ሲል ተደምጧል።
በስብሰባው የተሳተፉት ሁሉም አባላት ዘለንስኪን አድንቀው፣ የወደፊቱን የሩሲያ ውድቀትን እና ማዕድናቶቿን፣ ወርቆቿን፣ ግዛቶቿን እና ሴቶቿን መቀራመትን እያሰቡ በስሜት ተውጠው እንደነበር ለማየት ተችሏል። ደስም ብሏቸው ለጦርነቱ ድጋፍ ለዩክሬን $160 ቢሊዮን ዶላር በቅርቡ እንደሚሰጡ፣ የመሳሪያ ጭነታቸውን በሦስት እጥፍ እንደሚያሳድጉ፣ የሕብረቱ ሀገራት የሆኑት ፈረንሳይና ጀርመን በጋራ እየፈበረኩ ያሉትን ረጅም ርቀት ሚሳዬል በማፋጠን ለዩክሬን እንደሚያደርሱ እና ለዩክሬን መንግሥት ሠራተኞች የአራት ወር ደመወዛቸውን ለመክፈል እንደተስማሙ ተገልጧል።
4 317
🇸🇦💋🇺🇸 የሳውዲው MBS, ትራምፕን በየመን አንሳረ' ላህ በመምታት ላይ ድጋፍ እንዲያደርግለት ደውሎለት ነበር - ሳውዲ የሰነዓ አየር ማረፊያን ከመምታቷ በፊት።
4 317
❗️🇮🇷/ 🇧🇭 ባለፉት 2 ሰዓታት ውስጥ በባሕሬን ቢያንስ 30 ሚሳኤሎች እና ሰው አልባ አውሮፕላኖች ተወንጭፈዋል። ፍንዳታዎች፣ አሁንም በመሰማት ላይ እንዳሉ ነው የሚነገረው።
ባለፉት 48 ሰዓታት ውስጥ፣ ይህ የኢራን ወታደራዊ ዘመቻ ከተኩስ አቁም ስምምነቱ የፈፀመችው ትልቁና ሰፊው ጥቃት ነው።
4 317
🇮🇷⚡️🇺🇸 CENTCOM, በኢራን ላይ የቅርብ ጊዜውን ዙር ጥቃት ማጠናቀቁን ተናግሯል።
ኦፕሬሽኑ፣ የኢራንን ደቡባዊ የባህር ዳርቻ 'የንግድ መርከቦችን የማጥቃት አቅም ለማውረድ ያነጣጠረ ነው ብሏል።
በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ 50ሺህ + የአሜሪካ ወታደሮች 'ዝግጁ እና ንቁ' ሆነው እንደሚቀጥሉ አስጠንቅቋል።
4 317
🇾🇪⚡️🇸🇦ሳዑዲ ዓረቢያ ዛሬ ቀትር ላይ፣ በሰነዓ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ያደረሰችውን ጥቃት በመቃወም፣ በየመን ምሽቱን በተለያዩ ከተሞች ሰልፎች እየተደረጉ ናቸው። ሰልፈኞቹ፣ የታጠቁ ኃይሎችን እንደሚደግፉ እና ኢራን እገዳውን ለማፍረስ እያደረገች ያለውን ጥረት እንደሚያደንቁ በሰልፎቹ ላይ እያስተጋቡ ናቸው።
4 317
🇺🇸⚡️🇮🇷 ሰበር ዜና፡ ፕሬዝዳንት ትራምፕ አሜሪካ ከኢራን ጋር ጦርነት ላይ መሆኗንና ወደ ጦርነት መመለሷን ለአሜሪካ ኮንግረስ በይፋ አሳውቋል። Politico.
4 317
⚡️🇮🇷🇺🇸 ፕረስ ቲቪ፡ በሰሜን ምሥራቅ ኢራን፣ ማሽሃድ ክፍለ ሀገር፣ በሴፊድ ሳንግ አቅራቢያ፣ የ3.6 ሬክተር የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።
መንስኤው ግልጽ አይደለም፣ እና ይህ ክስተት በመካሄድ ላይ ካለው ጥቃት ጋር የተገናኘ ወይም ተፈጥሯዊ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተት ስለመሆኑ አልተረጋገጠም።
4 317
🇮🇷❌🇺🇸 - የኢራን ምድር ጦር፣ ባሕር ኃይል እና የIRGC አባላት፣ በሆርሙዝ ባሕር ወሽመጥ፣ 20 ኪሎ ሜትር አካባቢ፣ ከአሜሪካ የጦር መርከቦች ጋር እየተፋለሙ ነው። MEHIR
4 317
+1
🇮🇷⚡️🇺🇸 በኢራን፣ በቡሸር ክፍለ ሀገር፣ በጃም ከተማ፣ ከባሕሬን በመተኮስ ያሉ Himars የአሜሪካ ሚሳዬሎች፣ ከፍተኛ ድብደባ በመፈፀም ላይ ናቸው።
4 317
⚡️🇺🇸❌🇮🇷 - ከ30 ደቂቃ በፊት፣ የዩናይትድ ስቴትስ ጦር፣ በዋና አዛዥ ብራድ ኩፐር ትእዛዝ፣ ለሶስተኛ ተከታታይ ቀን በኢራን ኢላማዎችን መምታት መጀመሩን ሴንትኮም አስታውቋል።
