7 369
مشترکین
-524 ساعت
+267 روز
+35130 روز
آرشیو پست ها
7 371
በሽርካ ወረዳ ሁለት ወንድማማች አረጋውያን የሆኑ ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸው ተሰማ።
በዚህም እስከ አሁን በወረዳው ባለፉት ሦስት ቀናት ውስጥ ብቻ 31 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸው ተገልጿል።
EOTCMK TV የካቲት 23 2018 ዓ.ም
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት የኦርቶዶክሳውያን አሰቃቂ ግድያ መፍትሔ ሳይገኝለት አሁንም ተባብሶ ቀጥሏል።
ለማኅበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን ጣቢያ በደረሰው መረጃ በትናንትናው ዕለት ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ላይ ሀገረ ስብከቱ በሚገኘው በሽርካ ወረዳ ጢጆ ለቡ ቀበሌ የሚኖሩ ሁለት የ70ና 72 ዓመት ወንድማማች ኦርቶዶክሳውያን አረጋውያን መሳሪያ በታጠቁ ኃይሎች በተተኮሰባቸው ጥይት በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል።
የግድያው መነሻ ከሰሞኑ በወረዳው 21 የተገደሉት ኦርቶዶክሳውያን ጋር የተያያዘ ሲሆን ከበባ ተደርጎባቸው መገደላቸውን መረጃው አስነብቧል።
የተገዱሉት ምእመናን ሀብትና ንብረታቸው የተዘረፈባቸው ሲሆን በአሁኑ ሰዓትም በሀገረ ስብከቱ ከሚገኙ ገጠራማ አካባቢዎች ምእመናን ቀዬአቸውን ለቀው በመውጣት እየሸሹ እንደሚገኙም ተነግሯል።
በመረጃው እንደተገለጸው ባለፉት 3 ቀናት ማለትም በየካቲት 19፣20ና 22 በሀገረ ስብከቱ ውስጥ በተፈጸሙ የግድያ ተግባራት እስከ አሁን ከ30 በላይ ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል ተብሏል።
በተጨማሪም እስከ አሁን በሀገረ ስብከቱ ሥር ባለው የሽርካ ወረዳ ብቻ ከ164 በላይ ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸው የመረጃ ምንጫችን ነግረውናል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በተፈጸሙ ጥቃቶች በሕይወት ይኑሩ ወይም ይሙቱ የማይታወቁ በርካታ ምእመና እንዳሉም ተነስቷል።
የሁለቱ ወንድማማቾች ሥርዓተ ቀብር በዛሬው ዕለት በጋለማ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን መፈጸሙን በደረሰው መረጃ ለማወቅ ተችሏል።
በወረዳው እየተባባሰ የመጣው የኦርቶዶክሳውያን ግድያ ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኝ የሚመለከታቸው የመንግሥት የጸጥታ ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ መተላለፉን በመረጃው ላይ ተጠቅሷል።
7 371
ተባብሶ የቀጠለው ጭፍጨፋ
ሽርካ አሁንም በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመው የዘር ማጥፋት እንደ ቀጠለ ነው። በ 22/06/2018ዓ.ም በጢጆ ለቡ ቀበሌ ሌሊት ሁለት ወንድማማች አረጋውያን ኦርቶዶሳውያን በአክራሪዎቹ ታርደዋል።አቶ ታደሰ የ 72ዓመት እድሜ እና አቶ በለጠ የ70 እድሜ ።አክራሪዎቹ ካረዷቸው በኋላ ንብረታቸውን ሙሉ በሙሉ ዘርፈው ወስደዋል። ሥርዐተ ቀብራቸው ዛሬ በ23/06/2018ዓ.ም ከረፋ 3:00 ላይ በጋለማ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።የቀበሌ ባለሥልጣናት መረጃው እንዳይወጣ ሥርዐተ ቀብራቸው ስፈጸም ፎቶ ሲያነሱ የነበሩ ኦርቶዶክሳውያንን ስልኮቻቸውን በመንጠቅ ወደ እርስቤት አስገብቶአቸዋል።ካህናትን ሳይቀር ፎቶ ብታነሱ እና መረጃ ብታወጡ አንፋታችሁም እያሉ ሲያስፈራሩአቸው ነበር። ያለ አንዳች ከለካይ ሕዝባችን ዘሩ ከምድረ ገጽ እየተጸዳ ነው ።
ኢዮሳፍጥ ጌታቸው
7 371
አሁናዊ መረጃ
የአርሲ ሽርካ ኦርቶዶክሳውያን ሰቆቃ እንደ ቀጠለ ነው አሁን ከመሸ ከ3:00 በኋላ ጋለማ ገብረ ክርስቶስ አከባቢ ያለው ሕዝብ በአክራሪዎቹ በመከበቡ ቤቱን ጥሎ በየጫካውና ገደሉ እየተንከራተተ ይገኛል።
7 371
8 ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል
የኦርቶዶክውያን እልቂት ተባብሶ እንደ ቀጠለ ነው።በምሥራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ በ19/06/2018ዓ.ም በግፍ የተጨፈጨፉት በተጨማሪ ትናንት ምሽት (20/06/2018ዓ.ም)እዚያው የጃዊ ዋጩ ቀበሌ ላይ 7ኦርቶዶክሳውን በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ 1 አንድ አረጋዊ አባት በ ቤት ውስጥ ተቃጥለው ሞተዋል።የሰማዕታቱ ሥርዐተ ቀብራቸው በጃዊ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ/ክ ዛሬ በ21/6/2018 ተፈጽሞአል። እነዚህ የእስልምና አክራሪ ታጣቂዎች ቤተክርስቲያኑን በር ሰብረው በመግባት በቤተ ክርስቲያኑ ድምጽ ማጉያ በቤተክርስቲያን ውስጥ ሲጨፍሩ አመሽተው በዚህ የሚኖሩ ነዳይ አቃቢት እና መሸሽ የማይችሉ አይነ ስውራንን ገድለዋል ቤታቸው ውስጥ እንዳሉም እሳት ተለኩሶባቸው የ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል ከስፍራው የሚወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ። በተጨማሪም የቤተ ክርስቲያኑ የሰበካ ጉባኤ ጽቤት ከቤተ ክርስቲያኑ እርሻ መሬት የተገኘ ጤፍ እና በርበሬ ስንዴ ከነመጋዘኑ ተቃጥሎአል ቤተ ከርስቲያኑን በተደጋጋሚ ለማቃጠል ተሞክሮ መቃጠል ሳይችል ቀርቶአል የኦርቶዶክሳውያን ቤቶች በጠቅላላ ተመርጠው ከነሙሉ ንብረታቸው ተቃጥለዋል።በሌሎች ቀበሌዎችም ስጋቱ እንደቀጠለ ነው።
ኢዮሳፍጥ ጌታቸው
7 371
እጅግ አሳዛኝ ዜና #ሽርካ
በምሥራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ጃዊ ዋጬ ቀባሌ ትናንት 19/06/2018ዓ.ም ከቀኑ 10:00ጀምሮ በታጠቁ በአክራሪ ሙስሊሞች በተፈጸመ ጥቃት 21 ኦርቶዶክሳውያን የተገደሉ ሲሆን ሰባቱ 7 ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ቀጥራቸው በውል ያልታወቀ ደግሞ የት እንደደረሱ አልታወቀም።የሟቾቹ ቁጥር ከዚህ በላይ ሊጨምር ይችላል። በኦርቶዶክሳውያኑ ላይ ጭፍጨፋ የሚፈጽሙት አክራሪ የእስልምና ታጣቂዎች የ አማርኛም ኦሮሚኛ ቋንቋ ይናገር ከየትኛውም ብሔር ይሁን የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይን ከአርሲ ምድር እናጠፋለን የሚል አቋም ይዘው የሚንቀሳቀሱ ናቸው።እነዚህ ኀይሎች በከፌዴራል እስከ ቀበሌ ድረስ ባለው በመንግሥት መዋቅር የሚደገፉ ናቸው በሶሚሊያ ባለው የአይኤስ አይኤስና አልሸባብ ጋር በባሌ በኩል ቀጥታ ግኑኝነት ያላቸው ናቸው።ያልታወቁ ኀይሎች፣ያልታወቁ ታጣቂዎች ወዘተ...የሚለው ዲስኩር ተቀባይነት የለውም።በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያላችሁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮችና ሰብአዊነት የሚሰማችሁ ኢትዮጵያውን ሕዝባችን በሃይማኖቱና በማዕተቡ ምክንያት እየተጨፈጨፈ ዘሩም ከምድረ ገጽ እየጠፋ ነውና ሕዝባችን ከጥፋት ለመታደግ የበኩላችሁን እንድትወጡ እስካሁን ሲፈጸም ከነበረውና እየተፈጸመ ካለው ወደ ይጸም ዘንድ እጅጉን ይከብዳል። ሕዝባችን በሁሉም አቅጣጫ ተከቧል የጅሃድ ነጋሪት ተጎስሞበታል።
ኢዮሳፍጥ ጌታቸው
