6 446
مشترکین
+424 ساعت
+427 روز
+36730 روز
آرشیو پست ها
6 610
ይህን አካውንቴ ለጊዜው እኔ አይደለሁም እየተጠቀምኩት ያለሁት…የአካውንትና የብር ዘረፋ እንዴትና በማን እንደተፈጸመብኝ በርዝር የምጽፍላችሁ ይሆናል። እስክዛው ግን አካውንቱን ቀጣይ ስለማልጠቀምበት…ሊጠቀምበት የሚችለውን ሰው እስክ ፎቶው፣ ማለትም ታውቁት ዘንድ እስክ ቤተሰቡ ፎቶ የማሳውቃችሁ ይሆናል።ከአሁኑ ይህን አውቃችሁ በአካውንቱ ላይ ምንም ነገር ቢፖሰት ወይም በውስጥ ቢጻፍላችሁ እኔን እንደማይወክል እንድታውቁት ለሌሎችም ከወዲሁ እንድታሳውቁልኝ ስል በትህትና ጠይቃለሁ።
6 610
ህጻናት በማግባት የማሜን ሱና የሚከተሉ ዲያቆናትን ልናስቆም ይገባል፣ ሁላችሁም እንዲህ አይነት ድርጊትን እንድናወግዝ ጥሪ አቀርባለሁ።
https://youtu.be/l2j1n3KGkqg?is=HudAx6y9x1cFd-jV
6 610
ውድ የቴሌግራም ተከታታዮቻችን ይህን ሊንክ በመጫን የቪኪን(Vikiን) የዩቱብ ቻናል ሰብስክራይብ በማድረግ አበረታቱት ጥሩ ጥሩ መረጃ እያስቀመጠላችሁ ስለሆነ።
https://youtube.com/@geez_church?si=WpgF0VqvFKeXA2QO
6 610
የቃል ሥጋ ሆነን አካውንት ፎሎ አድርጉት፣ ቀን ከለሊት እጅግ በትጋት የሚሰራ ወንድማችን ነው። አሁን ደግሞ ለየት ባለ መልኩ ሰሞኑን የሚጀምረው ፕሮግራም አለ። ስለዚህ ከአሁኑ በጉጉት ልትጠብቁት ይገባል። እኛ እንደ ኡስታዞች አካውንታችሁን ስጡን ወይም ትልልቅ አካውንት ግዙልን አንላችሁም...ግን ፎሎ ያላደረጋችሁ አድርጉ ትጠቀሙበታላችሁ።
https://vt.tiktok.com/ZSCEahk8q/
6 610
ተረት ተረት የበዛበት ማብራሪያ አያስፈልግም!!! በአጭሩ ለሥላሴ ጾታ ዬላቸውም ስለዚህ ዙሪያ ጥምጥም መሄድ አያስፈልግም። ታዲያ በወንድና በሴት ስም ለምን ተጠሩ ያልን እንደሆነ ከቋንቋ ውስንነት አንጻር ነው። ከዚህ የዘለለ ምዕምኑን ሊያወዛግቡ የሚችሉ እንቶ ፈንቶ ንግግሮች ወይም ትምህርቶች አስፈላጊ አይደሉም።
ለተራው ምዕምን ሲባል ግልፅ በሆነ መልኩ ማስረዳት ሲቻል ደጋ ቆላ እላይ እታች ነጭ ጥቁር ቀን ማታ እያሉ ሐተታ ማብዛት ለትውልዱ ምንም የሚፈይደው ነገር ዬለም።
6 610
ለሥላሴ የክፍል አካላት የሚሰጡ አንዳንድ መምህራን መኖራቸው ሲያስገርመን የነበር ቢሆንም ጭራሽ ጾታ አላቸው የሚሉ መምህር ሰሞኑን በመስማታችን አስደንግጦናል።
በአማን ነጸረ እሳቸው ራሱ ለሥላሴ ክፍለ አካላትን የሚያጸድቁ ቢሆንም ጾታ እንደማይነገርላቸው ግን በመጽሐፋቸው ላይም አስፍረዋል። በተለይም በዚህ ጉዳይ ላይ በእኛ ቤተክርስቲያን በሊቃውንቱና በቴዎለጂያኑ መካከል ልዩነት መኖሩን “ተኅሥሦ” በሚሰኝ መጽሐፋቸው ላይ አብራርተዋል።እሳቸው ግን የሊቃውንቱን አረዳድ እንደሚቀበሉም አስፍረዋል። የኢትዮጵያ ሊቃውንት ለሥላሴ የክፍል አካላትን ሲናገሩ ዝርው ብትን አይደለም ለማለት እንደሆነም ጠቁመዋል።
እንደ እኔ ዝርው ወይም ብትን አይደለም ለማለት ከሆነ ብዙም አይጎረብጠኝ….ነገር ግን እጅ ሲሉ ከእግር የተለዬ፣ ዓይን ሲሉም ለማዬት ብቻ የሚያገለግል፣ ጆሮ ሲሉ መስሚያ እንጂ መመልከቻ ያልሆነን እያሉ ከሆነ…ይህ ጤናማ ትምህርት ነው ብዬ አላምንም።
6 610
ለሥላሴ የክፍል አካላት የሚሰጡ አንዳንድ መምህራን መኖራቸው ሲያስገርመን የነበር ቢሆንም ጭራሽ ጾታ አላቸው የሚሉ መምህር ሰሞኑን በመስማታችን አስደንግጦናል።
ታዲያ በአማን ነጸረ እሳቸው ራሱ ለሥላሴ አካላትን የሚያጸድቁ ቢሆንም ጾታ እንደማይነገርላቸው ግን በመጽሐፋቸው ላይም አስፍረዋል። በተለይም በዚህ ጉዳይ ላይ በእኛ ቤተክርስቲያን በሊቃውንቱና በቴዎለጂያኑ መካከል ልዩነት መኖሩን “ተኅሥሦ” በሚሰኝ መጽሐፋቸው ላይ አብራርተዋል።እሳቸው ግን የሊቃውንቱን አረዳድ እንደሚቀበሉም አስፍረዋል። የኢትዮጵያ ሊቃውንት ለሥላሴ የክፍል አካላትን ሲናገሩ ዝርው ብትን አይደለም ለማለት እንደሆነም ጠቁመዋል።
እንደ እኔ ዝርው ወይም ብትን አይደለም ለማለት ከሆነ ብዙም አይጎረብጠኝ….ነገር ግን እጅ ሲሉ ከእግር የተለዬ፣ ዓይን ሲሉም ለማዬት ብቻ የሚያገለግል፣ ጆሮ ሲሉ መስሚያ እንጂ መመልከቻ ያልሆነን እያሉ ከሆነ…ይህ ጤናማ ትምህርት ነው ብዬ አላምንም።
