የሕግ ነገር ⚖️
رفتن به کانال در Telegram
Well come to የሕግ ነገር channel. This channel aims to improve students skill and knowledge about law and raise puplic awareness in law cases 🔸legal Notes 🔸volumes 🔸proclamations 🔸Exit exams
نمایش بیشتر577
مشترکین
-124 ساعت
-17 روز
+1930 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
سپتامبر '26
سپتامبر '26
+7
در 0 کانالها
اوت '26
+19
در 1 کانالها
Get PRO
ژوئیه '26
+9
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '26
+10
در 0 کانالها
Get PRO
مه '26
+54
در 2 کانالها
Get PRO
آوریل '26
+46
در 2 کانالها
Get PRO
مارس '26
+177
در 3 کانالها
Get PRO
فوریه '26
+66
در 1 کانالها
Get PRO
ژانویه '26
+1
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '25
+11
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '25
+4
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '25
+19
در 2 کانالها
Get PRO
سپتامبر '25
+221
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 11 سپتامبر | +1 | |||
| 10 سپتامبر | 0 | |||
| 09 سپتامبر | +1 | |||
| 08 سپتامبر | 0 | |||
| 07 سپتامبر | 0 | |||
| 06 سپتامبر | 0 | |||
| 05 سپتامبر | 0 | |||
| 04 سپتامبر | 0 | |||
| 03 سپتامبر | +2 | |||
| 02 سپتامبر | +1 | |||
| 01 سپتامبر | +2 |
پستهای کانال
🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻
◇ Baga bara haaraa 2019 nagaan geessan!
◇ እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ!
◇ እንኳዕ ናብ ሓድሽ ዓመት 2019 ብሰላም ኣብጽሓኩም!
◇ Wishing you a peaceful and happy New Year 2019!
🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻
| 2 | 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻
◇ Baga bara haaraa 2019 nagaan geessan!
◇ እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ!
◇ እንኳዕ ናብ ሓድሽ ዓመት 2019 ብሰላም ኣብጽሓኩም!
◇ Wishing you a peaceful and happy New Year 2019!
🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 | 1 |
| 3 | 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻
◇ Baga bara haaraa 2019 nagaan geessan!
◇ እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ!
◇ እንኳዕ ናብ ሓድሽ ዓመት 2019 ብሰላም ኣብጽሓኩም!
◇ Wishing you a peaceful and happy New Year 2019!
🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 | 1 |
| 4 | ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ሊውሉ የሚችሉበት የህግ አግባብ !
⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️
🔑 ፖሊስ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ (Warrant) አንድን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ሊያውል የሚችልባቸው ልዩ ሁኔታዎች አሉ።
እነዚህም "እጅ ከፍንጅ" ወይም "አጣዳፊ ሁኔታዎች" ተብለው የሚታወቁ ሲሆን ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው ፦
1. ወንጀል ሲፈጸም እጅ ከፍንጅ ከተገኘ ✍️
አንድ ሰው ወንጀል ሲፈጽም ወይም ወንጀል ፈጽሞ ለማምለጥ ሲሞክር ከተገኘ ፖሊስ ያለ ትዕዛዝ ሊይዘው ይችላል።
ይህ የሚሆነው፦
ድርጊቱ እየተፈጸመ ሲታይ።
ወንጀሉ ከተፈጸመ በኋላ ወዲያውኑ በሕዝብ ጩኸት ወይም በፖሊስ ክትትል ሲደረግበት።
ተጠርጣሪው በወንጀል መፈጸሙን የሚያሳዩ መረጃዎች (ለምሳሌ የደም ነጠብጣብ፣ የጦር መሣሪያ ወይም የተሰረቀ ንብረት) ይዞ ሲገኝ።
2. ከባድ ወንጀል ተፈጽሟል ተብሎ ሲጠረጠር ✍️
ተፈጸመ የተባለው ወንጀል በሕጉ "ሊያስረው የሚችል ወንጀል" (Registrable/Cognizable offense) ተብሎ የተመደበ ሲሆንና የሚከተሉት ሁኔታዎች ሲሟሉ፦
ተጠርጣሪው ከአገር ሊወጣ ወይም ሊሰወር ይችላል ተብሎ በበቂ ሁኔታ ሲገመት።
ተጠርጣሪው የራሱ ቋሚ መኖሪያ የሌለውና ማንነቱ የማይታወቅ ሲሆን።
ተጠርጣሪው ምስክሮችን ሊያባብል ወይም ማስረጃ ሊያጠፋ ይችላል ተብሎ ሲሰጋ።
3. ከእስር ቤት ያመለጠ ሰው ✍️
ከዚህ ቀደም ተፈርዶበት ወይም በቁጥጥር ሥር ሆኖ እያለ ከእስር ቤት ወይም ከፖሊስ ቁጥጥር ያመለጠን ሰው ለማሰር ተጨማሪ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ አያስፈልግም ።
4. የጦር መሣሪያ ወይም የተከለከሉ ቁሶች ✍️
አንድ ሰው በሕገ-ወጥ መንገድ የጦር መሣሪያ፣ ፈንጂ ወይም ዕፅ ይዞ ሲገኝ ፖሊስ ወዲያውኑ በቁጥጥር ሥር የማዋል ሥልጣን አለው ።
🔑 በቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ ያለ መብት
ፖሊስ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰውን በቁጥጥር ሥር ካዋለ በኋላም ቢሆን የሚከተሉትን ግዴታዎች ማክበር አለበት፦
🔑 የ48 ሰዓት ገደብ፦ ተጠርጣሪው በቁጥጥር ሥር በዋለ በ 48 ሰዓታት ውስጥ ፍርድ ቤት መቅረብ አለበት (የመንገድ ርቀትን ሳይጨምር) ።
🔑 መንስኤውን የማወቅ መብት፦ የተያዘበት ምክንያት ወዲያውኑ ሊነገረው ይገባል።
🔑 የዝምታ መብት፦ "የምሰጠው ቃል ፍርድ ቤት በማስረጃነት ሊቀርብብኝ ይችላል" የሚለውን ማስጠንቀቂያ የማግኘትና የመዝጋት መብት አለው ።
,,,,,,,,✍️✍️✍️ | 74 |
| 5 | በወንጀል ሕጋችን፦ ስርቆት፣ ከባድ ስርቆት፣ ውንብድና፣ ዝርፊያ እና መሸሸግ ልዩነታቸው ምንድን ነው?
ብዙዎቻችን እነዚህን የንብረት ወንጀሎች በማደባለቅ እንጠቀማቸዋለን። ነገር ግን በኢትዮጵያ ወንጀል ሕግ መሠረት እያንዳንዳቸው የተለያየ የድርጊት ዓይነት፣ የቅጣት መጠን እና ሕጋዊ መለኪያ አላቸው።
ልዩነታቸውን በጥቅሉና በግልጽ እንደሚከተለው እንመልከት፦
1️⃣ ስርቆት (Simple Theft)
የሌላውን ሰው የሚንቀሳቀስ ንብረት ባለቤቱ ሳይያውቅ ወይም ሳይፈቅድ፣ ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ለማድረግ በማሰብ በደባ ወይም በስርቆት መውሰድ ነው።
ምንም ዓይነት ኃይል/ዛቻ (Violence) የሌለበት፣ በስውርና በደባ የሚፈጸም ነው።
2️⃣ ከባድ ስርቆት (Aggravated Theft)
ሕጋዊ ትርጉም፦ ስርቆቱ የተፈጸመበት ሁኔታ፣ ቦታ፣ ወይም መንገድ ወንጀሉን ከባድ የሚያደርገው ሲሆን ነው።
ዋና መለያዎች፦
# በሌሊት፣ በቡድን፣ ወይም መሣሪያ/መሳሪያ መሰል ነገሮችን በመያዝ ከተፈጸመ፤
# መቆለፊያ በመስበር፣ በር/መስኮት በመስበር ወይም የመግቢያ ቁልፍ አስመስሎ በመስራት ከተፈጸመ፤
# በእምነት ማጉደል ወይም በሥራ አጋጣሚ (ለምሳሌ፦ ዘበኛ፣ አጋዥ) ከተፈጸመ።
3️⃣ ዝርፊያ (Robbery)
የሌላውን ሰው ንብረት ለመውሰድ ሲባል ኃይልን (Force) መጠቀም ወይም በሕይወትና አካል ላይ አደጋ ለማድረስ ማስፈራራት/መዛተት ነው።
ከስርቆት የሚለየው ቀጥተኛ ኃይል፣ ጥቃት ወይም የዛቻ ድርጊት (Violence or Threat) የሚታከልበት በመሆኑ ነው።
4️⃣ ውንብድና (Brigandage / Banditry)
በቡድን በመደራጀት ወይም መሣሪያ በመታጠቅ መንገድ በመዝጋት፣ በሕዝብ ወይም በግል ንብረት ላይ ጥቃት በማድረስ የሚፈጸም እጅግ ከባድ የዝርፊያና የሽብር ድርጊት ነው።
በታጠቀ ቡድን የሚፈጸም፣ የህዝብን ሰላምና ጸጥታ በከፍተኛ ደረጃ የሚያናጋ እና ከግል ንብረት አልፎ የማኅበረሰብ ደህንነት ላይ አደጋ የሚደቅን ነው።
5️⃣ የስርቆት ዕቃ መሸሸግ (Receiving or Storing Stolen Property)
አንድ ንብረት በስርቆት፣ በዝርፊያ ወይም በወንጀል የተገኘ መሆኑን እያወቁ ወይም መጠራጠር ሲገባው ንብረቱን መግዛት፣ መረከብ፣ ማስቀመጥ ወይም መሸሸግ ነው።
ግለሰቡ በስርቆቱ ድርጊት ላይ ቀጥታ ባይሳተፍም፣ በወንጀል የተገኘውን ንብረት በስውር በመያዙ ወይም በመግዛቱ ተጠያቂ ይሆናል።
6️⃣ ከባድ መሸሸግ (Aggravated Storing/Concealment)
የሌላውን ሰው ወንጀል መሸሸግ ወይም የተሰረቀ ንብረት መረከብ በከባድ ሁኔታ ሲፈጸም ነው።
ዋና መለያዎች፦
#ድርጊቱን የተለመደ ሙያ ወይም ንግድ (Habitual Business) አድርጎ ሲይዘው፤
# በከባድ ወንጀል (ለምሳሌ፦ በዝርፊያ ወይም በውንብድና) የተገኘ ንብረት መሆኑን እያወቁ ሲሸሽጉ፤
# በስፋትና በከፍተኛ ደረጃ የተደራጀ የመሸሸግ ድርጊት ሲሆን።
“ህግን አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድንም!”
የወንጀል ሕጋችን የንብረት መብትን ለማስከበርና የዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ለእያንዳንዱ ድርጊት እንደ ከባድነቱ መጠን የተለያየ የሕግ ተጠያቂነትና የቅጣት እርከን አስቀምጧል። | 174 |
| 6 | በወንጀል ሕጋችን፦ ስርቆት፣ ከባድ ስርቆት፣ ውንብድና፣ ዝርፊያ እና መሸሸግ ልዩነታቸው ምንድን ነው?
ብዙዎቻችን እነዚህን የንብረት ወንጀሎች በማደባለቅ እንጠቀማቸዋለን። ነገር ግን በኢትዮጵያ ወንጀል ሕግ መሠረት እያንዳንዳቸው የተለያየ የድርጊት ዓይነት፣ የቅጣት መጠን እና ሕጋዊ መለኪያ አላቸው።
ልዩነታቸውን በጥቅሉና በግልጽ እንደሚከተለው እንመልከት፦
1️⃣ ስርቆት (Simple Theft)
የሌላውን ሰው የሚንቀሳቀስ ንብረት ባለቤቱ ሳይያውቅ ወይም ሳይፈቅድ፣ ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ለማድረግ በማሰብ በደባ ወይም በስርቆት መውሰድ ነው።
ምንም ዓይነት ኃይል/ዛቻ (Violence) የሌለበት፣ በስውርና በደባ የሚፈጸም ነው።
2️⃣ ከባድ ስርቆት (Aggravated Theft)
ሕጋዊ ትርጉም፦ ስርቆቱ የተፈጸመበት ሁኔታ፣ ቦታ፣ ወይም መንገድ ወንጀሉን ከባድ የሚያደርገው ሲሆን ነው።
ዋና መለያዎች፦
# በሌሊት፣ በቡድን፣ ወይም መሣሪያ/መሳሪያ መሰል ነገሮችን በመያዝ ከተፈጸመ፤
# መቆለፊያ በመስበር፣ በር/መስኮት በመስበር ወይም የመግቢያ ቁልፍ አስመስሎ በመስራት ከተፈጸመ፤
# በእምነት ማጉደል ወይም በሥራ አጋጣሚ (ለምሳሌ፦ ዘበኛ፣ አጋዥ) ከተፈጸመ።
3️⃣ ዝርፊያ (Robbery)
የሌላውን ሰው ንብረት ለመውሰድ ሲባል ኃይልን (Force) መጠቀም ወይም በሕይወትና አካል ላይ አደጋ ለማድረስ ማስፈራራት/መዛተት ነው።
ከስርቆት የሚለየው ቀጥተኛ ኃይል፣ ጥቃት ወይም የዛቻ ድርጊት (Violence or Threat) የሚታከልበት በመሆኑ ነው።
4️⃣ ውንብድና (Brigandage / Banditry)
በቡድን በመደራጀት ወይም መሣሪያ በመታጠቅ መንገድ በመዝጋት፣ በሕዝብ ወይም በግል ንብረት ላይ ጥቃት በማድረስ የሚፈጸም እጅግ ከባድ የዝርፊያና የሽብር ድርጊት ነው።
በታጠቀ ቡድን የሚፈጸም፣ የህዝብን ሰላምና ጸጥታ በከፍተኛ ደረጃ የሚያናጋ እና ከግል ንብረት አልፎ የማኅበረሰብ ደህንነት ላይ አደጋ የሚደቅን ነው።
5️⃣ የስርቆት ዕቃ መሸሸግ (Receiving or Storing Stolen Property)
አንድ ንብረት በስርቆት፣ በዝርፊያ ወይም በወንጀል የተገኘ መሆኑን እያወቁ ወይም መጠራጠር ሲገባው ንብረቱን መግዛት፣ መረከብ፣ ማስቀመጥ ወይም መሸሸግ ነው።
ግለሰቡ በስርቆቱ ድርጊት ላይ ቀጥታ ባይሳተፍም፣ በወንጀል የተገኘውን ንብረት በስውር በመያዙ ወይም በመግዛቱ ተጠያቂ ይሆናል።
6️⃣ ከባድ መሸሸግ (Aggravated Storing/Concealment)
የሌላውን ሰው ወንጀል መሸሸግ ወይም የተሰረቀ ንብረት መረከብ በከባድ ሁኔታ ሲፈጸም ነው።
ዋና መለያዎች፦
#ድርጊቱን የተለመደ ሙያ ወይም ንግድ (Habitual Business) አድርጎ ሲይዘው፤
# በከባድ ወንጀል (ለምሳሌ፦ በዝርፊያ ወይም በውንብድና) የተገኘ ንብረት መሆኑን እያወቁ ሲሸሽጉ፤
# በስፋትና በከፍተኛ ደረጃ የተደራጀ የመሸሸግ ድርጊት ሲሆን።
“ህግን አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድንም!”
የወንጀል ሕጋችን የንብረት መብትን ለማስከበርና የዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ለእያንዳንዱ ድርጊት እንደ ከባድነቱ መጠን የተለያየ የሕግ ተጠያቂነትና የቅጣት እርከን አስቀምጧል። | 1 |
| 7 | የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን በሽያጭ ወይም በስጦታ ማስተላለፍን በተመለከተ ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች
1) በስጦታ፣ በሽያጭ ወይም በሌላ መንገድ ተገልጋዮች ንብረት
ለማስተላለፍ ሲመጡ ካርታው ከጀርባው የተረጋገጠ መሆን አለበት፡፡ ካርታው ዲጂታል ከሆነ የጀርባ ማህተም አያስፈልገውም፡፡
2)በካርታው ከጀርባ ላይ ንብረቱ በውርስ የተገኘና የወራሾች ዝርዝር የተፃፈበት ከሆነ ተጨማሪ ማስረጃ ማየት ሳያስፈልግ መስተናገድ ይችላሉ፡፡ ሆኖም የንብረቱ መለያ ተጠቅሶ ወራሾች መሆናቸው በደብዳቤ ከተገለጸ አገልግሎቱን መስጠት ይቻላል፡፡
3)በውርስ ወይም በስጦታ የተገኘ ንብረትን ለማስተላለፍ ወይም ለማከራየት የጋብቻ ማስረጃ አይጠየቅም፡፡
4)ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውጭ የተመዘገቡ የሚንቀሳቀሱም ሆነ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን የማስተላለፍ ወይም የማከራየት አገልግሎት ማግኘት የሚቻለው ንብረቶቹ በሚገኙበት ክልል/ከተማ አስተዳደር ነው፡፡ ስለሆነም በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የተቋሙ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ሊስተናገዱ አይችሉም፡፡ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤትም የሚያስተናግደው በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሚመለከተው መ/ቤት የተመዘገቡ ንብረቶችን ብቻ ይሆናል፡፡
5)ከጋብቻ በፊት በተቋሙ ቀርበው የንብረት ማግለል ውል ያደረጉ ወይም በፍ/ቤት ያጸደቁ ተጋቢዎች ንብረታቸውን ለማስተላለፍ ወይም ለማከራየት ሲመጡ የትዳር አጋራቸው ስምምነት አያስፈልግም፡፡ ሆኖም የንብረት ማግለሉ ስምምነት አሁን ጸንቶ ካለው ጋብቻ የትዳር አጋር ጋር የተደረገ ሊሆን ይገባል፡፡
6)አካለ መጠን ላልደረሱ ልጆች ንብረት ለመግዛት የሚቻል ሲሆን ሁለቱም ወላጆች ሊገኙ ይገባል ፡፡ ካልሆነ አባት ወይም እናት ቀርበው መግዛት ይችላሉ፡፡ ሆኖም ከእናትና አባት ውጪ የሆነ ሞግዚት አካላመጠን ባልደረሰው ልጅ ስም ንብረት ለመግዛት በፍ/ቤት የተሰጠ ተጨማሪ ስልጣን ሊቀርብ ይገባል፡፡
7.)ለአካለ መጠን ባልደረሰው ልጅ ስም ተመዝግቦ የሚገኘውን የማይንቀሳቀስ ንብረት ለመሸጥ ሞግዚቱ እናትና አባትም ቢሆኑም በፍ/ቤት የተሰጠ ተጨማሪ ስልጣን ሊቀርብ ይገባል፡፡
8.)ያላገባ ማስረጃ ላይ ቀደም ሲል ጋብቻ ስለመኖሩ የሚጠቁም የጊዜ መረጃ ሲኖር ንብረቱ በጋብቻ ወቅት የተፈራ ሊሆን ስለሚችል ንብረቱ የተፈራበትን ጊዜ የሚያመለክት ከሚመለከተው አካል የተሰጠ ተጨማሪ ማስረጃ ሊቀርብ ይገባል፡፡
9.)ተነጻጻሪ ካርታ ማለት በአንድ የቦታ ስፋት ውስጥ የተለያዩ ቤቶችና ባለመብቶች ያሉበትና በተለያዩ ሰዎች ሊያዝ የሚችል ነው፡፡ ነገር ግን በዚህ ይዞታ ላይ የባለቤትነት መብት ያለው ሰው የራሱን ካርታ በመያዝ ድርሻውን ጠቅሶ መሸጥ ይችላል፡፡
10)ካርታ ላይ የሚጠቀሰው ቀን ካርታው የተሰጠበትን ቀን እንጂ ንብረቱ የተፈራበትን ቀን በቀጥታ ላያመለክት ይችላል፡፡ ስለሆነም ንብረቱ የተፈራበትን ቀን ለማወቅ አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ የንብረቱ ባለቤት ተጨማሪ ማስረጃ እንዲያቀርብ መደረግ አለበት፡፡ ለምሳሌ ከመሬት አስተዳደር ለገቢዎች እና ለካርታው ባለቤት የሚሰጡ ደብዳቤዎችን አያይዞ መስራት ይቻላል፡፡
11) የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረትን በሽያጭም ሆነ በስጦታ ለማስተላለፍ የፍቺ ውሳኔ ይዘው የሚቀርቡ ባለጉዳዮች ንብረቱ የጋራ ወይም የግል ስለመሆኑ በፍርድ ቤት የጸደቀ የንብረት ክፍፍል ስምምነት ወይም ውሳኔ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
12)ንብረት በስጦታ ለማስተላለፍ የተሠጠ የውክልና ሥልጣን ስጦታው ለማን እንደሚሰጥ እና ንብረቱ ምን አይነት እንደሆነ በውክልናው ላይ በግልፅ መቀመጥ አለበት፡፡ ነገር ግን በውክልና ስጦታ ለመቀበል ሲሆን ስጦታ ይቀበልልኝ የሚለው አገላለጽ በቂ ነው፡፡
13) የጋራ ንብረት በሽያጭ በሚተላለፍበት ጊዜ ገዢው ከንብረት ተጋሪው ውጪ የሆነ እንደሆነ የተጋሪው የቅድሚያ መግዛት መብት መጠበቁን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም የማይንቀሳቀስ ንብረት ሲሆን ተጋሪውን ምስክር በማድረግ፣ የሚንቀሳቀስ ንብረት ሲሆን ተጋሪው ማረጋገጫ እንዲሰጥ ማድረግ ይቻላል፡፡
14) የማይንቀሳቀስ ንብረት ገዢው የውጭ ሃገር ዜጋ ከሆነ የታደሰ በትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ወይም በኢንቨስትመንት አዋጁ መሠረት ቢያንስ አሥር ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ኢንቨስት በማድረግ በሥራ ላይ ማዋሉን የሚገልጽ ማስረጃ እና የኢንቨስትመንት ፈቃድ ሊቀርብ ይገባል፡፡
የማይንቀሳቀስ ንብረት ገዢው የውጭ ሃገር ዜጋ ሌላ የመኖሪያ ቤት በስሙ የሌለ ስለመሆኑ የሚገልጽ ከሚመለከተው የንብረት መዝጋቢ አካል ማስረጃ ማቅረቡን እንዲሁም ከተቋሙ የመረጃ ቋት ማጣራት ያስፈልጋል፡፡ | 210 |
| 8 | #NationalDialogue 🇪🇹
👉 ዓመተ ምህርት (ዓ.ም) የሚለው የዘመን አቆጣጠር የኢትዮጵያ አቆጣጠር (ኢ.አ) እንዲባል ስምምነት መደረሱ ተገለጸ።
ከ400 ምክረ ሀሳቦች አራቱ ብቻ በልዩነት ተይዘው የ38 ቀናት የምክክር ጉባዔ ትናንት ተቋጭቷል።
ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም በኮንቬንሽን ማዕከል በይፋ የተከፈተው በ8 ዋና አጀንዳዎች የተመከረበት የምክክር ጉባዔ በአጠቃላይ 400 ምክረ ሀሳቦች ከተመካካሪዎች ቀርበውለት አራቱ ሳያስማሙ ሌሎች አስማምተው፣ ጉባዔው ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ/ም ተቋጭቷል።
በልዩነት የተያዙ አራቱ ጉዳዮች ምንድን ናቸው ?
አንድ የጉባዔው ተመካካሪ፣ "የምክክር ኮሚሽኑ የትኛውን እንደሚያቀርብ አይታወቅም" ብለው፣ አራት ጉዳዮች በልዩነት መያዛቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ሌሎች ተመካሪዎችም ይህንኑ ሀሳብ ተጋርተዋል።
በልዩነት የተያዙት ምክረ ሀሳቦች፦
- የአዲስ አበባ ህጋዊ ጉዳይ፣
- የሰንደቅ አላማ ጉዳይ፣
- የመንግስት አደረጃጀት ጉዳይ
- የፌዴሬሽን ምክር ቤት ጉዳይ የተመለከቱ መሆናቸውን ተገልጿል። እነዚህ "በልዩነት ቀርበዋል። ሌሎቹ ግን ከስምምነት ተደርሶባቸዋል" ተብሏል።
1. የመንግስት ቅርጽን በተመለከተ፥ "'ፓርላሜንታዊ ሆኖ ፕሬዚዳንቱ ከፓርላማ ይመረጥ እና የፕሬዚዳንቱንም የጠቅላይ ሚኒስትሩንም ሥራ አንድ ላይ ይስራ'" እና "'ፕሬዚዳንታዊ ሆኖ ፕሬዚዳንቱ ከህዝብ ይመረጥ' የሚሉት በልዩነት ተይዘዋል።
2. የሰንደቅ አላማ ጉዳይ፥ አሁን ያለው አርማ ይቀጥል እና አካታች በሆነ መልኩ ይተካ የሚሉት ምክረ ሀሳቦች በልዩነት መያዙ ተመልክቷል።
3. የፌዴሬሽን ምክር ቤት በተመለከተ፥ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በቀጥታ በህዝ ተመርጠው ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ይቅረቡ፣ ክልሎች መርጠው ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ያቅርቧቸው የሚሉት ሀሳቦችም በልዩነት መያዛቸውን ተመካካሪው ተናግረዋል። የብሔረሰቦች አወካከልም በልዩነት መያዛቸው ተገልጿል።
4. የአዲስ አበባ ጉዳይ ሌላኛው በልዩነት የተያዘ መሆኑ ተገልጿል።
ከተማዋን በተመለከተ፣ ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ/ም በተነበበው 500 ሰዎች የመከሩበትና 120 አባላት ያሉት አዘጋጅ ቡድን ባዘጋጀው ቃለ ጉባዔ፥ ከተማዋ የፌዴራል መንግስት ተጠሪ እንድትሆን ስምምነት ሲደረስ፣ ከተማዋ "የኦሮሚያ መቀመጫ እንድትሆን ህገ መንግስቱ እውቅና ይስጥ" የሚለው ግን አማራጮች ቀርበውለት በልዩነት ተይዞ ነበር።
በልዩነት የቀረቡት ምክረ ሀሳቦች፥ ክልሎች ርዕሰ ከተማቸውን መምረጥ እንዲችሉ በሕግ ይደንገግ እና "አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ ከመሆኗ ጋር በተያያዘ" በከተማዋና በክልሉ መካከል ያለው ግንኙነት በሕግ ይደንገግ የሚሉ ናቸው።
ይሁን እንጅ የኦሮሚያ ተወካዮች በልዩነት የተያዙ ሁለቱ ምክረ ሀሳቦችን አስመልክተው ለኮሚሽኑ ቅሬታ በማቅረባቸው፣ ኮሚሽኑ ጉዳዩን የክልል ም/ቤት ጉባዔ (አሸማጋይ ቡድን) እንዲመክርበት አሳስቦ ነበር።
የአሸማጋዮች ቡድኑም፣ "አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ ከተማ ናት" የሚል ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌ እንዲኖር እና ከተማዋ የፌዴራል ተጠሪ እንድትሆን ምክረ ሀሳብ ማቅረቡን ኮሚሽኑ በመጨረሻው ቀን ለ4ሺሕው ለጉባያተኞች አንብቧል።
በዚህ መልኩ ስለአዲስ አበባ ጉዳይ ሁለት ሰነዶች የተነበቡ ሲሆን፣ ኮሚሽኑ የትኛውን ሰነድ ተቀብሎ በምክረ ሀሳቡን ለሚመለከታቸው ተቋማት እንደሚያሳልፍ እስካሁን አልታወቀም።
በልዩነት የተያዙት አራቱ ምክረ ሀሳቦች ምን ሊሆኑ ነው ?
በልዩነት የተያዙት ሀሳቦች ምን እንደሚሆኑ የጠየቅናቸው አንድ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ከሰሞኑ በሰጡን ቃል፣ "ኮሚሽኑ ሰነድ ተረክቦ የሚሰራው ስራ አለ። በአዋጅ ስልጣን አለው። በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 አንቀጽ 9 መሰረት። እነዚህን የተሰበሰቡትን አጀንዳዎች ዝም ብሎ አይለቃቸውም፤ ያደራጃቸዋል" ብለዋል።
የተመካካሪዎች የሚቀበሏቸው ምክረ ሀሳቦችን የያዘውን ሰነድ "የኛ ሰነድ ነው። ሰነዱን ወስደን ለሀገር በሚጠቅም መልኩ ተዘጋጅቶ ለሚመለከተው ወሳኝ አካል ይላካል" ሲሉም ተናግረዋል።
በሌላ በኩል ፦
ሲያከራክሩ ከቆዩት ምክረ ሀሳቦች መካከል የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር፣ "የውህድ ማንነት"፣ ብሔራዊ ቋንቋ፣ የሥራ ቋንቋ ጉዳዮች ተጠቃሽ ናቸው።
ዓመት ምሕረት (ዓ.ም) የሚለው የዘመን አቆጣጠር እንዲቀር የተለያዩ ምክረ ሀሳቦች ሲቀርቡ የነበረ ሲሆን፣ ለ4ሺሕ ጉባያተኞች ተነቦ ኮሚሽኑ በተረከበው ሰነድ፣ ዓ.ም የሚለው ቀርቶ የኢትዮጵያ አቆጣጠር (ኢ.አ) እንዲባል ስምምነት መደረሱን ተመካካሪዎች ገልጸዋል። ሒጅራ እንደ ካላንደር ይካተት ተብሎ መያዙም ተገልጿል።
ከሁለት በላይ ብሔሮች የተወለዱ ዜጎች አገልግሎት ለማግኘት ብሔር በሚጠየቁበት ወቅት "በውህድ ማንነት" እንዲጠሩ ተጠይቆ ጉዳዩ አከራክሮ የነበረ ሲሆን፣ "ከኢትዮጵያ ባህል ጋር የሚጋጭ ነገር እንዳይኖርበት ሆኖ፥ በውህድ ማንነት" እውቅና እንዲሰጣቸው ስምምነት መደረሱ ተመልክቷል።
በተያያዘ፣ በአንቀጽ 39 "እስከ መገንጠል" የሚለው እንዲሰረዝ ተመካካሪዎችን አስማምቷል። የመንግስት አወቃቀርን በተመለከተ ደግሞ ፌዴራላዊ ይሁን በሚል ምክረ ሀሳብ መያዙ ተነግሯል።
" ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቋንቋ ይኑራት፣ አይኑራት፤ ከኖራት አማርኛ ይሁን፤ አፋን ኦሮሞ ይሁን " በሚል ሲያከራክር የቆየው ጉዳይ "ለጊዜው ብሔራዊ ቋንቋ አይስፈልግም" በሚል ተይዟል። በሚያስፈልግበት ወቅት፥ የሥራ ቋንቋ ይሁኑ ተብሎ ያስማሙት አምስቱ ቋንቋዎች እንዲታዩ፣ ለሌሎች ቋንቋዎችም ክፍት እንዲደረግ መባሉን የዚሁ አጀንዳ ተመካካሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
"አማርኛ፣ ኦፋን ኦሮሞ ፣ ትግርኛ፣ ሶማሊኛ፣ አፋርኛ በቀጥታ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ ሆነው ተግባራዊ ይደረጉ"፥ ሲዳምኛ፣ ከምባትኛ፣ አገውኛ፣ ወላይትኛ፣ ከፍቾ፣ ጋሞኛ፣ ጉራግኛ እና ሌሎች የተናጋሪያቸው ብዛት መስፈርት ወጥቶና በጥናት ታይቶ ለወደፊት የፌዴራል የሥራ ቋንቋ የሚሆኑበት ሁኔታ ይኑር በሚል ማስማማቱ ተገልጿል።
@LawStudentsUnion | 229 |
| 9 | بدون متن... | 273 |
| 10 | ⚖️ በወንጀል ሕግ የምክንያትና የውጤት ግንኙነት መርህ (Causation) 🔗
በወንጀል ሕግ መሠረት፣ የአንድ ሰው ድርጊት የወንጀል ተጠያቂነትን 🧑⚖️ ሊያስከትል የሚችለው በድርጊቱና በተከሰተው ውጤት መካከል የምክንያትና የውጤት ግንኙነት (Causal Link) 🔗 መኖሩ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።
ይህ ግንኙነት አለ የሚባለውም፣ በነገሮች የታወቀ ወይም የተለመደ ሂደት የተከሳሹ ድርጊት የተከሰተውን ውጤት ለማስገኘት የሚችል ሆኖ ሲገኝ ስለመሆኑ በኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 24 (1) 📖 ላይ ተደንግጓል።
ድርጊቱ በተፈጥሮ ሕግ 🌱፣ በሳይንስ 🔬 ወይም በተለመደው የሰዎች የሕይወት ተሞክሮ (Ordinary course of nature/things) ሊተነበይና ሊታወቅ በሚችል መደበኛ ሂደት ውጤቱን የማስገኘት ብቃት ሊኖረው ይገባል።
ለምሳሌ በሰዎች ዘንድ በታወቀና በተለመደው የሕይወት ሂደት፣ የአንድን ሰው ራስ ቅል በኃይል በዱላ ደጋግሞ መምታት 🏏 ለሞት የሚያበቃ ከባድ ጉዳት 💀 ሊያስከትል እንደሚችል የታወቀ ነው። እዚህ ላይ በድርጊቱ (በዱላ መምታት) እና በውጤቱ (በሞቱ) መካከል ቀጥተኛና ምክንያታዊ ትስስር አለ።
በሌላ በኩል፣ የተሰነዘረው የዱላ ምት እጅግ ተራና ቀላል ሆኖ የተመታው እግሩ ላይ ቢሆን 🦵፣ በተለመደው የሕይወት ሂደት ለሞት ቀርቶ ለከባድ አካል ጉዳት እንኳ የማይዳርግ በመሆኑ የምክንያትና ውጤት ግንኙነቱ ይቋረጣል ❌።
በነገራችን ላይ፣ ሁሉም የወንጀል ዓይነቶች ውጤት መከሰትን ግዴታ አያደርጉም 🚫። ለምሳሌ በሐሰት መመስከር 🤥 ወይም የሐሰት ሰነድ ማዘጋጀት 📄 ያሉ ወንጀሎች፣ የተፈለገው ውጤት ባይገኝና በሌላ አካል ላይ ጉዳት ባይደርስ እንኳ ድርጊቱ በራሱ ተፈጽሞ በመገኘቱ ብቻ የወንጀል ተጠያቂነትን ⛓️ ያስከትላሉ።
ውጤት በሚያስፈልጋቸው ወንጀሎች ውስጥ ጉዳቱ እንዲከሰት ከአንድ በላይ የሆኑና የተሳሰሩ ልዩ ልዩ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ። ከእነዚህም መካከል አስቀድሞ የደረሰ ምክንያት፣ ጣልቃ የገባ ምክንያት (Intervening Cause) 🚧 ወይም የተደረበ ምክንያት ሊያጋጥም ይችላል።
ይህን በተመለከተ ሕጉ ሁለት ዋና ዋና መርሆችን ያስቀምጣል። ለተከሳሹ እንግዳ የሆነው አስቀድሞ የነበረው፣ የተደረበው ወይም ጣልቃ የገባው ምክንያት ራሱን ችሎ ውጤቱን (ሞቱን ወይም ጉዳቱን) ማስከተሉ ከተረጋገጠ፣ በተከሳሹ ድርጊትና በውጤቱ መካከል ሊኖር ይችል የነበረው ግንኙነት ይቋረጣል ✂️። ነገር ግን፣ የተቋረጠው የተከሳሹ ድርጊት በራሱ ራሱን የቻለ ሌላ ወንጀል ሆኖ በሚገኝበት ጊዜ ተከሳሹ ለዚያ ድርጊቱ ተጠያቂ ይሆናል 🚨። ይህም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 24 (2) 📜 ላይ ተደንግጎ ይገኛል።
በአንጻሩ፣ ልዩ ልዩ ምክንያቶቹ እያንዳንዳቸው ራሳቸውን ችለው አንድን ውጤት ማምጣት ባይችሉም፣ ተጣምረው (ተደራርበው) 🤝 አንድን ውጤት በሚያስከትሉበት ጊዜ ግን በእያንዳንዱ ምክንያት እና በተገኘው ውጤት መካከል የምክንያትና ውጤት ግንኙነት እንዳለ ይቆጠራል። ስለዚህ እያንዳንዱ ድርጊት ፈጻሚ በውጤቱ ተጠያቂ ይሆናል ⚖️። ይህም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 24 (3) 📌 ላይ ተመላክቶ ይገኛል። | 236 |
| 11 | ⚖️ በወንጀል ሕግ የምክንያትና የውጤት ግንኙነት መርህ (Causation) 🔗
በወንጀል ሕግ መሠረት፣ የአንድ ሰው ድርጊት የወንጀል ተጠያቂነትን 🧑⚖️ ሊያስከትል የሚችለው በድርጊቱና በተከሰተው ውጤት መካከል የምክንያትና የውጤት ግንኙነት (Causal Link) 🔗 መኖሩ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።
ይህ ግንኙነት አለ የሚባለውም፣ በነገሮች የታወቀ ወይም የተለመደ ሂደት የተከሳሹ ድርጊት የተከሰተውን ውጤት ለማስገኘት የሚችል ሆኖ ሲገኝ ስለመሆኑ በኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 24 (1) 📖 ላይ ተደንግጓል።
ድርጊቱ በተፈጥሮ ሕግ 🌱፣ በሳይንስ 🔬 ወይም በተለመደው የሰዎች የሕይወት ተሞክሮ (Ordinary course of nature/things) ሊተነበይና ሊታወቅ በሚችል መደበኛ ሂደት ውጤቱን የማስገኘት ብቃት ሊኖረው ይገባል።
ለምሳሌ በሰዎች ዘንድ በታወቀና በተለመደው የሕይወት ሂደት፣ የአንድን ሰው ራስ ቅል በኃይል በዱላ ደጋግሞ መምታት 🏏 ለሞት የሚያበቃ ከባድ ጉዳት 💀 ሊያስከትል እንደሚችል የታወቀ ነው። እዚህ ላይ በድርጊቱ (በዱላ መምታት) እና በውጤቱ (በሞቱ) መካከል ቀጥተኛና ምክንያታዊ ትስስር አለ።
በሌላ በኩል፣ የተሰነዘረው የዱላ ምት እጅግ ተራና ቀላል ሆኖ የተመታው እግሩ ላይ ቢሆን 🦵፣ በተለመደው የሕይወት ሂደት ለሞት ቀርቶ ለከባድ አካል ጉዳት እንኳ የማይዳርግ በመሆኑ የምክንያትና ውጤት ግንኙነቱ ይቋረጣል ❌።
በነገራችን ላይ፣ ሁሉም የወንጀል ዓይነቶች ውጤት መከሰትን ግዴታ አያደርጉም 🚫። ለምሳሌ በሐሰት መመስከር 🤥 ወይም የሐሰት ሰነድ ማዘጋጀት 📄 ያሉ ወንጀሎች፣ የተፈለገው ውጤት ባይገኝና በሌላ አካል ላይ ጉዳት ባይደርስ እንኳ ድርጊቱ በራሱ ተፈጽሞ በመገኘቱ ብቻ የወንጀል ተጠያቂነትን ⛓️ ያስከትላሉ።
ውጤት በሚያስፈልጋቸው ወንጀሎች ውስጥ ጉዳቱ እንዲከሰት ከአንድ በላይ የሆኑና የተሳሰሩ ልዩ ልዩ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ። ከእነዚህም መካከል አስቀድሞ የደረሰ ምክንያት፣ ጣልቃ የገባ ምክንያት (Intervening Cause) 🚧 ወይም የተደረበ ምክንያት ሊያጋጥም ይችላል።
ይህን በተመለከተ ሕጉ ሁለት ዋና ዋና መርሆችን ያስቀምጣል። ለተከሳሹ እንግዳ የሆነው አስቀድሞ የነበረው፣ የተደረበው ወይም ጣልቃ የገባው ምክንያት ራሱን ችሎ ውጤቱን (ሞቱን ወይም ጉዳቱን) ማስከተሉ ከተረጋገጠ፣ በተከሳሹ ድርጊትና በውጤቱ መካከል ሊኖር ይችል የነበረው ግንኙነት ይቋረጣል ✂️። ነገር ግን፣ የተቋረጠው የተከሳሹ ድርጊት በራሱ ራሱን የቻለ ሌላ ወንጀል ሆኖ በሚገኝበት ጊዜ ተከሳሹ ለዚያ ድርጊቱ ተጠያቂ ይሆናል 🚨። ይህም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 24 (2) 📜 ላይ ተደንግጎ ይገኛል።
በአንጻሩ፣ ልዩ ልዩ ምክንያቶቹ እያንዳንዳቸው ራሳቸውን ችለው አንድን ውጤት ማምጣት ባይችሉም፣ ተጣምረው (ተደራርበው) 🤝 አንድን ውጤት በሚያስከትሉበት ጊዜ ግን በእያንዳንዱ ምክንያት እና በተገኘው ውጤት መካከል የምክንያትና ውጤት ግንኙነት እንዳለ ይቆጠራል። ስለዚህ እያንዳንዱ ድርጊት ፈጻሚ በውጤቱ ተጠያቂ ይሆናል ⚖️። ይህም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 24 (3) 📌 ላይ ተመላክቶ ይገኛል። | 1 |
| 12 | ⚖️ በወንጀል ሕግ የምክንያትና የውጤት ግንኙነት መርህ (Causation) 🔗
በወንጀል ሕግ መሠረት፣ የአንድ ሰው ድርጊት የወንጀል ተጠያቂነትን 🧑⚖️ ሊያስከትል የሚችለው በድርጊቱና በተከሰተው ውጤት መካከል የምክንያትና የውጤት ግንኙነት (Causal Link) 🔗 መኖሩ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።
ይህ ግንኙነት አለ የሚባለውም፣ በነገሮች የታወቀ ወይም የተለመደ ሂደት የተከሳሹ ድርጊት የተከሰተውን ውጤት ለማስገኘት የሚችል ሆኖ ሲገኝ ስለመሆኑ በኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 24 (1) 📖 ላይ ተደንግጓል።
ድርጊቱ በተፈጥሮ ሕግ 🌱፣ በሳይንስ 🔬 ወይም በተለመደው የሰዎች የሕይወት ተሞክሮ (Ordinary course of nature/things) ሊተነበይና ሊታወቅ በሚችል መደበኛ ሂደት ውጤቱን የማስገኘት ብቃት ሊኖረው ይገባል።
ለምሳሌ በሰዎች ዘንድ በታወቀና በተለመደው የሕይወት ሂደት፣ የአንድን ሰው ራስ ቅል በኃይል በዱላ ደጋግሞ መምታት 🏏 ለሞት የሚያበቃ ከባድ ጉዳት 💀 ሊያስከትል እንደሚችል የታወቀ ነው። እዚህ ላይ በድርጊቱ (በዱላ መምታት) እና በውጤቱ (በሞቱ) መካከል ቀጥተኛና ምክንያታዊ ትስስር አለ።
በሌላ በኩል፣ የተሰነዘረው የዱላ ምት እጅግ ተራና ቀላል ሆኖ የተመታው እግሩ ላይ ቢሆን 🦵፣ በተለመደው የሕይወት ሂደት ለሞት ቀርቶ ለከባድ አካል ጉዳት እንኳ የማይዳርግ በመሆኑ የምክንያትና ውጤት ግንኙነቱ ይቋረጣል ❌።
በነገራችን ላይ፣ ሁሉም የወንጀል ዓይነቶች ውጤት መከሰትን ግዴታ አያደርጉም 🚫። ለምሳሌ በሐሰት መመስከር 🤥 ወይም የሐሰት ሰነድ ማዘጋጀት 📄 ያሉ ወንጀሎች፣ የተፈለገው ውጤት ባይገኝና በሌላ አካል ላይ ጉዳት ባይደርስ እንኳ ድርጊቱ በራሱ ተፈጽሞ በመገኘቱ ብቻ የወንጀል ተጠያቂነትን ⛓️ ያስከትላሉ።
ውጤት በሚያስፈልጋቸው ወንጀሎች ውስጥ ጉዳቱ እንዲከሰት ከአንድ በላይ የሆኑና የተሳሰሩ ልዩ ልዩ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ። ከእነዚህም መካከል አስቀድሞ የደረሰ ምክንያት፣ ጣልቃ የገባ ምክንያት (Intervening Cause) 🚧 ወይም የተደረበ ምክንያት ሊያጋጥም ይችላል።
ይህን በተመለከተ ሕጉ ሁለት ዋና ዋና መርሆችን ያስቀምጣል። ለተከሳሹ እንግዳ የሆነው አስቀድሞ የነበረው፣ የተደረበው ወይም ጣልቃ የገባው ምክንያት ራሱን ችሎ ውጤቱን (ሞቱን ወይም ጉዳቱን) ማስከተሉ ከተረጋገጠ፣ በተከሳሹ ድርጊትና በውጤቱ መካከል ሊኖር ይችል የነበረው ግንኙነት ይቋረጣል ✂️። ነገር ግን፣ የተቋረጠው የተከሳሹ ድርጊት በራሱ ራሱን የቻለ ሌላ ወንጀል ሆኖ በሚገኝበት ጊዜ ተከሳሹ ለዚያ ድርጊቱ ተጠያቂ ይሆናል 🚨። ይህም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 24 (2) 📜 ላይ ተደንግጎ ይገኛል።
በአንጻሩ፣ ልዩ ልዩ ምክንያቶቹ እያንዳንዳቸው ራሳቸውን ችለው አንድን ውጤት ማምጣት ባይችሉም፣ ተጣምረው (ተደራርበው) 🤝 አንድን ውጤት በሚያስከትሉበት ጊዜ ግን በእያንዳንዱ ምክንያት እና በተገኘው ውጤት መካከል የምክንያትና ውጤት ግንኙነት እንዳለ ይቆጠራል። ስለዚህ እያንዳንዱ ድርጊት ፈጻሚ በውጤቱ ተጠያቂ ይሆናል ⚖️። ይህም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 24 (3) 📌 ላይ ተመላክቶ ይገኛል። | 1 |
| 13 | የሰውን ፎቶ ወይም ቪዲዮ ያለፍቃድ ሶሻል ሚዲያ ላይ መፖሰት የሚያስከትለው የወንጀል ተጠያቂነት
⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️
የሰውን ፎቶ ወይም ቪዲዮ ያለባለቤቱ ፈቃድ በማህበራዊ ሚዲያ (Social Media) ላይ መፖሰት በኢትዮጵያ ህግ መሰረት ከባድ የወንጀልና የፍትሐብሔር (የካሳ) ተጠያቂነት ያመጣል።
ድርጊቱ የሚዳኘው በዋነኝነት በ2008 ዓ.ም በወጣው የሳይበር ወንጀል አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 958/2008)፣ በወንጀል ሕግ (2004) እና በፍትሐብሔር ሕግ ነው፡፡
1. በወንጀል ሕግ የሚያስከትለው ተጠያቂነት
🔹 የሳይበር ወንጀል አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 958/2008)፦
ስም ማጥፋትና ክብርን መንካት (አንቀጽ 13)፦ የሰውን ምስል ወይም ቪዲዮ በመጠቀም የሰውን ስምና ክብር የሚነካ ወይም የሚያዋርድ መረጃ ማሰራጨት እስከ 3 ዓመት በሚደርስ እስራት ወይም በመቀጮ ያስቀጣል።
የግል ሕይወት ምስጢርነትን መጣስ (አንቀጽ 14)፦ የአንድን ሰው የግል ሕይወት የሚያሳይ ምስል ወይም ቪዲዮ ያለ ፈቃድ ማሰራጨት ከ 1 ዓመት እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ያስቀጣል።
ምስልን በማቀናበር (Edit/AI) ማሰራጨት፦ የሰውን ፎቶ በመቀየር ወይም በማካበብ ሰውን ለመጉዳት ከተለጠፈ ቅጣቱ የበለጠ የከበደ ይሆናል።
🔹 የኢፌዴሪ ወንጀል ሕግ (2004)፦
ስም ማጥፋት (አንቀጽ 613)፦ በማንኛውም መንገድ የሰውን መልካም ስም የሚያጎድፍ ነገር ማሰራጨት በጥፋተኝነት ያስጠይቃል።
እፍረተ-ከንቱ ምስሎችን ማሰራጨት (አንቀጽ 640/641)፦ የሰውን ነውረኛ ፎቶ ወይም ቪዲዮ ያለፍቃድ ማሰራጨት (Revenge Porn) እስከ 5 ዓመት ወይም ከዚያ በላይ ጽኑ እስራት ያስቀጣል።
2. በፍትሐብሔር ሕግ የሚያስከትለው ተጠያቂነት (የካሳ ጥያቄ)
ተጎጂው ግለሰብ በፍትሐብሔር ሕግ (አንቀጽ 2032) መሠረት፦
የሞራል ካሳ፦ ለደረሰበት የስነ-ልቦና ጉዳትና የእፍረት ስሜት የገንዘብ ካሳ መጠየቅ ይችላል።
የቁሳቁስ ካሳ፦ ፎቶው በመፖሰቱ ምክንያት ከስራ ቢሰናበት ወይም የገንዘብ ጉዳት ቢደርስበት ካሳ የማስከፈል መብት አለው።
ምስሉ እንዲወገድ የማድረግ መብት፦ ድርጊቱ እንዲቆም፣ ምስሉ እንዲሰረዝ እና ይቅርታ በይፋ እንዲጠየቅ ማድረግ ይቻላል።
3. ሕጋዊ ሊሆኑ የሚችሉ አጋጣሚዎች
ለሕዝብ ጥቅም ሲባል፦ ወንጀለኛን ለመያዝ ወይም የጠፋን ሰው ለመፈለግ በሕግ አስከባሪዎች የሚደረግ ከሆነ።
በሕዝባዊ መድረክ ላይ ያለ ምስል፦ በባህሪው ለሕዝብ ክፍት በሆነ ትልቅ ስብሰባ ላይ የተነሳ ፎቶ ሆኖ፣ የተወሰነን ግለሰብ ለማጥቃት ካልተፈለገ።
💡 ማጠቃለያ፦ የሰውን ምስል ያለባለቤቱ እውቅና ማህበራዊ ሚዲያ ላይ መፖሰት ከእስራት እስከ ከፍተኛ የገንዘብ ካሳ የሚያስከትል የሳይበር ወንጀል ነው። | 309 |
| 14 | 🔴25 የሙስና ወንጀሎች🔴
(አዋጅ ቁጥር 881/2007 )
1. በሥልጣን ያለአግባብ መገልገል (አንቀፅ 9)
2. ጉቦ መቀበል (አንቀፅ 10)
3. የማይገባ ጥቅም መቀበል (አንቀፅ 11)
4. አስታራቂ ሽማግሌዎችና ሌሎች ሰዎች የሚፈፅሙት ጉቦ የመቀበል ወንጀል (አንቀጽ 12)
5. የመንግስት ወይም የሕዝባዊ ድርጅት ስራን በማያመች አኳኋን መምራት (አንቀጽ 13)
6. አደራ በተሠጠው ዕቃ ያለአግባብ ማዘዝ (አንቀፅ 14)
7. በሥራ ተግባር የሚፈፀም የመውሰድና የመሰወር ወንጀል (አንቀፅ 15)
8. በሥልጣን ወይም በኃላፊነት መነገድ (አንቀፅ 16)
9. በህገወጥ መንገድ መሰብሳብ ወይም ማስረከብ (አንቀፅ 17)
10. ያለአግባብ ጉዳይን ማጓተት (አንቀፅ 18)
11. ዋጋ ያለውን ነገር ያለክፍያ ወይም ያለበቂ ክፍያ ማግኘት (አንቀፅ 19)
12. ያለአግባብ ፍቃድ መስጠት ወይም ማፅደቅ (አንቀፅ 20)
13. ምንጩ ያልታወቀ ንብረትና ገንዘብ (አንቀፅ 21)
14. የሥራ ሚስጥርን መግለፅ (አንቀፅ 22)
15. መንግሥታዊ ወይም የህዝባዊ ሰነዶችን አስመስሎ ማዘጋጀት፣ ወደ ሐሰት መለወጥ ወይም በሐሰተኛ ሰነድ መገልገል (አንቀፅ 23)
16. መንግስታዊ ወይም የህዝባዊ ድርጅት ስነዶችን ማጥፋት ወይም ጉዳት ማድረስ (አንቀ8 24)
17. ጉቦ ወይም ተገቢ ያልሆነ ጥቅም መስጠት (አንቀፅ 25)
18. ዋጋ ያለዉን ነገር ያለክፍያ ወይም ያለበቂ ክፍያ መስጠት (አንቀፅ 26)
19. ማቀባበል (አንቀፅ 27)
20. በሌለው ሥልጣን መጠቀም (አንቀፅ 28)
21. በግል ተሰሚነት መነገድ (አንቀፅ 29)
22. በምርጫ ላይ የሚሰጥ መደለያ (አንቀጽ 30)
23. ከባድ የእምነት ማጉደል (አንቀፅ 31)
24.ከባድ አታላይነት (አንቀፅ 32)
25. በሙስና ወንጀል የተገኘን ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብና በወንጀሉ ስለመርዳት (አንቀጽ 33) | 267 |
| 15 | ⚖️ አዲስ የሕግ መጽሐፍ አያምልጥዎ! ⚖️
በሕግ ሙያ ለምትገኙ ዳኞች፣ ዐቃብያነ ሕግ፣ ጠበቆች፣ የሕግ መምህራንና ተመራማሪዎች እና ተማሪዎች እጅግ ጠቃሚ የሆነ ልዩ መጽሐፍ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንካችሁ እያለ ነው!
የመጽሐፉ አጠቃላይ መረጃ፡
የመጽሐፉ ርዕስ፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የወንጀል ሕግ ትርጉም ውሳኔዎች ስብስብ (በየጉዳዮች የተደራጀ ልዩ እትም)
አሳታሚ፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት
የታተመበት ጊዜ፡ የካቲት 2018 ዓ.ም
ይህ መጽሐፍ በአገራችን የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ውስጥ ወጥ የሆነ የሕግ አተረጓጎም እንዲኖር ለማስቻል ታስቦ የተዘጋጀ ድንቅ ማጣቀሻ ነው። የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጣቸውን አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ውሳኔዎች በአንድ ላይ ሰብስቦና በየጉዳዮቻቸው አደራጅቶ ይዟል።
የመጽሐፉ ዋና ዋና ይዘቶች እና ጥቅሞች፡
👉መጽሐፉ በአራት ዋና ዋና ምዕራፎች እና በ45 ክፍሎች ተደራጅቶ የቀረበ ነው።
👉በወንጀል ሕግ ጠቅላላ ክፍል፣ ልዩ ክፍል፣ ልዩ ልዩ አዋጆች እና የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ-ሥርዓት ሕግ ላይ የተሰጡ ውሳኔዎችን በስፋት ያካትታል።
👉86 ገላጭ የሆኑ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔዎችን ከነሙሉ ይዘታቸው መርጦ አሳትሟል።
👉አንባቢዎች ተጨማሪ መረጃዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ ተመሳሳይ እና ተያያዥነት ያላቸውን ሌሎች ውሳኔዎች በግርጌ ማስታወሻ አደራጅቶ ጠቁሟል።
👉በቀላሉ ጉዳዮችን ለማግኘት የሚያስችል የቃላት መፈለጊያ ማውጫ አካትቷል።
ይህ ልዩ እትም በግል ቤተ-መጻሕፍትዎ ውስጥ ሊኖር የሚገባ ነው! 📚✨
አሁኑኑ ያውርዱት፤ ለሌሎች ባለሙያዎችም በማጋራት መረጃው እንዲደርሳቸው ያድርጉ!
🔗 ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡ https://t.me/abdurahmanlawinfocenter19792015 | 124 |
| 16 | የጠፋው ሰው በሕይወት መመለስ እና ውጤቱ
የመጥፋት ውሳኔ የተሰጠበት ሰው በሕይወት መመለስ የመጥፋት ውሳኔ ቀሪ ከሚሆንባቸው ምክንያቶች ውስጥ አንዱ እንደሆነ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 170 ሥር ተደንግጎ የምናገኘው ጉዳይ ነው። ጠፋ የተባለው ሰው መመለስ ደግሞ የራሱ ውጤቶችን እንደሚያስከትል በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 171 ሥር የተመለከተ ሲሆን እነዚህም፡-
• ጠፋ የተባለው ሰው የተወሰዱ ንብረቶችን በሚገኙበት አኳኋን ይወስዳል። ንብረቶቹ ተሽጠው ከሆነ ደግሞ የተሸጡበትን ዋጋ ይወስዳል፣ ስለሆነም ንብረቶቹን የያዙ ግለሰቦች በዚህ አግባብ ለተመለሰው ሰው የማስረከብ ግዴታ አለባቸው። (የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 171)። ንብረቱን የያዙ ግለሰቦች በተንኮል ወይም በመጥፎ አስተዳደር ላጠፉት ነገር ካሳ የመክፈል ኃላፊነት አለባቸው (የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 171(3))።
• ጋብቻን በተመለከተ ግን በመጥፋት ውሳኔው የፈረሰው ጋብቻ መመለሱ ሕይወት እንዲዘራ ወይም እንደገና እንዲጸና የማድረግ ውጤት የለውም (የፍትሐብሔር ሕግ ሰ/መ/ቁ. 74791 ቅጽ 14፣ ሰ/መ/ቁ. 213917 ቅጽ 27)።
ማጠቃለያ
የመጥፋት ውሳኔ በሕይወት መኖሩ ባልታወቀ ሰው ምክንያት በቤተሰብ እና በንብረት መብት ላይ የሚፈጠርን ክፍተት ለመሙላት የተቀረጸ ጠቃሚ የሕግ መሣሪያ ነው። ሕጉ በአንድ በኩል የጠፋውን ሰው በሕይወት የመመለስ ተስፋና ንብረት ለመጠበቅ የጊዜ ገደቦችንና የዋስትና ግዴታዎችን የሚያስቀምጥ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የቀሩት ቤተሰቦችና ወራሾች ሕይወታቸውን እንዲቀጥሉና ንብረቱን እንዲያስተዳድሩ መብት ይሰጣል። በመሆኑም ሕጉ እንደሚደነግገው ያለ ፍርድ ቤት መደበኛ የመጥፋት ውሳኔ ማስታወቂያና ማረጋገጫ በሰዎች ንብረትና መብት ላይ መወሰን በሕግ ፊት ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ ማኅበረሰቡ ይህንን ሥርዓት ተገንዝቦ በሕጋዊ መንገድ መብቱን ማስከበር ይኖርበታል።
#ንቃተ ሕግና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ | 152 |
| 17 | ዕለታዊ🛎
ጠቅላላ የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶች
⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖
✍ ጠቅላላ የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶች የምንላቸው በወንጀል ህጋችን በአንቀጽ 84 ስር የተዘረዘሩት ናቸው፡፡
ሀ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው በከሀዲነት ወይም በወስላታነት ወይም በወራዳነት ወይም መጥፎ አመልን በሚያሳይ ምቀኝነት፣ጥላቻ፣ ስግብግብነት፣ መጥፎ ነገርን ለመስራት ወይም ሰውን ለመጉዳት ፍጹም ፍቃደኛ በመሆን ወይም በተለየ ክፋት ወይም ጨካኝነት እንደሆነ ፡፡
በዚህ ድንጋጌ መሰረት ቅጣትን ለማክበድ ከመካከላቸው የአንዱ መሟላት በቂ ነው፡፡
ለ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው ስልጣኑን፣ ተግባሩን ወይም የተጣለበትን እምነት ወይም ሀላፊነት ያለአግባብ በመገልገል እንደሆነ
የመንግስትን ስራ ለመስራት ወይም ለመምራት ስልጣን የተጣለበት ሰው ስራውን በታማኝነት እና በቅንነት መፈጸም አለበት፡፡ በተጨማሪም ይህንኑ ስልጣን ተገን በማድረግ ለራሱም ሆነ ለሌላው ጥቅም ለማስገኘት ወይም በሌላ ሰው ጥቅም ወይም መብት ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ አንድን ወንጀል ከፈጸመ ቅጣት ሊከብድበት እንደሚገባ የወንጀል ህጉ ይደነግጋል፡፡
ሐ.ወንጀለኛው በቀድሞ ጥፋተኛነቱ ወይም ወንጀልን ማድረግ ሙያ ወይም ልማድ አድርጎ መያዙ፣ ወይም የወንጀሉ አፈጻጸም ዘዴ፣ ጊዜ፣ ቦታና የአፈጻጸም አኳሀን፣ በተለይም በሌሊት ወይም በሽብር ወይም በሁከት ለአደጋ ሽፋን ወይም በጦር መሳርያ ወይም በሌላ አደገኛ መሳርያ ወንጀሉን በማድረግ የተለየ አደገኝነቱን አሳይቶ እንደሆነ ::
በዚህ የቅጣት ማክበጃ ምክንያት ስር ሶስት ዋና ዋና ምክንያቶች አሉ እነኚህም፡-
1.ወንጀልን ማድረግ ሙያው ወይም ልማዱ አድርጎ መያዝ
2.የወ/ል አፈጻጸም ዘዴ፣ጊዜ፣ቦታ እና የአፈጻጸም አኳሀን
3.ወንጀልን በጦር መሳርያ ወይም በሌላ አደገኛ መሳርያ መፈጸም ናቸው፡፡
በተጨማሪም ሌሊት የሚለው ሀረግ ከስንት ሰዓት ጀምሮ እንደሆነ አሻሚ ቢሆንም በተለምዶ ፍርድ ቤቶች ከሌሊቱ 6፡00-12፡00 ድረስ ያለውን የጊዜ ገደብ በሌሊትነት ወስደው ቅጣት ያከብዱበታል፡፡
በእጅ ወይም በዱላ የውንብድና ወንጀልን የፈጸመ ሰው እና የስለት ወይም የጦር መሳርያዎችን ተጠቅሞ ይህንኑ ወንጀል የፈጸመ ሰው የወንጀል ማድረግ አደገኛነቱ እኩል ሊሆን አይችልም፡፡
መ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው ወንጀል ለመፈጸም በተደረገ ስምምነት መሰረት ወይም ከሌሎች ጋር በመሆን ወይም ወንጀል ለመፈጸም ከተቋቋመ ቡድን ጋር በመስማማት ወይም አባል በመሆን ይልቁንም እንደ ወንጀል ቡድን ሹም ወይም አደራጅ ወይም መሪ በመሆን እንደሆነ ::
ወንጀልን ለመፈጸም ከሌላው ጋር ወይም ለዚሁ አላማ ከተደራጀ ቡድን ጋር በአባልነት በመስማማት ወንጀልን ማድረግ ቅጣትን ሊያከብድ የሚችል በቂ ምክንያት ነው፡፡
ሠ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው በዕድሜው፣ በጤንነቱ፣ በኑሮው ወይም በስራው ሁኔታ ልዩ ጥበቃ በሚያሻው ሰው ላይ በተለይም ለመከላከል አቅም በሌለው፣ መንፈሰ ደካማ፣ በሽተኛ ወይም አካል ጉዳተኛ ፣ እስረኛ ወይም በቅርብ ዘመዱ ላይ ወይም የበላዩ ወይም የበታቹ በሆነ ሰው ላይ፣ በህግ በተቋቋመ ባለስልጣን ወይም የስራ ግዴታውን በማከናወን ላይ በሚገኝ በአንድ የህዝብ አገልጋይ በሆነ ሰራተኛ ላይ እንደሆነ ቅጣቱ ሊከብድበት ይችላል :: | 221 |
| 18 | ስለቀዳሚ ምርመራ (Preliminary Inquiry) ፌርድ ቤት ተልዕኮ፣ ሥልጣን እና ተግባር በዐስማን መሃመድ ሰይድ | 273 |
| 19 | በችሎት ውስጥ ዳኛዋንና ባለቤቱን የገደለው ግለሰብ ከሆስፒታል 3ኛ ፎቅ ላይ ራሱን ወርውሮ አጠፋ
ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በሆለታ ወልመራ ወረዳ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በችሎት አዳራሽ ውስጥ አሰቃቂ ግድያ ፈጽሞ የነበረው ግለሰብ ራሱን ማጥፋቱ ተነግሯል። ግለሰቡ በዕለቱ የቤተሰብ ክርክር መዝገብ እየተመለከቱ የነበሩትን ክብርት ዳኛ ወርቄ ፈካንሳን እና የቀድሞ ባለቤቱን ወይዘሮ አልማዝ መኮንን በሽጉጥ ተኩሶ መግደሉ ይታወሳል።
ጥቃቱን ካደረሰ በኋላ ራሱ ላይ ተኩሶ ቆስሎ የነበረው ይኸው አቅነው በቀለ የተባለው ተከሳሽ፣ በፖሊስ ጥበቃ ስር ሆኖ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሕክምናውን ሲከታተል ቆይቷል። ሆኖም በዛሬው ዕለት ሕክምናውን አጠናቆ ከሆስፒታሉ ለመውጣት ዝግጅት እየተደረገ ባለበት ወቅት፣ ከሕንጻው 3ኛ ፎቅ መስኮት ራሱን በመወርወር ሕይወቱ እንዲያልፍ ማድረጉ ተነግሯል። | 336 |
| 20 | የእናቱን አስክሬን ቤት አስቀምጦ የእናቱን ቃል ለማክበር የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ከቀብር በፊት እና በኃላ ለፈተና የተቀመጠው ካሊድ 🏠📝
ይሕ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ታዳጊ ካሊድ ይባላል 👦 ገና የአስራ አራት ዓመት ልጅ ነው🗓️።ከሑለት ታናናሽ ወንድሞቹ ጋር በሸገር ከተማ አስተዳደር ኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ ከእናቱ ጋር ይኖራል🏡።
ካሊድ ከእናቱ ጋር ሲኖር ወላጅ አባቱ ከእነርሱ ርቆ ሌላ ትዳር መስርቶ ጅጅጋ ከተማ ይኖራል🏙️። ካሊድ ሠሞኑን እናቱ ታምወው በነበረበት ወቅት እኔ አንድ ነገር ብሆን ምንም ቢፈጠር አመት የለፋሕበትን ፈተና እንዳታቋርጥ ብለው ቃል ያስገቡታል🤝📜።
እናትም በነጋታው የስምንተኛ ክፍል ፈተና ሊሲጥ ሠዓታት ሲቀረው ሕይወታቸው ያልፋል⚰️💔።ካሊድ በእናቱ ሞት ከፍተኛ ሐዘን ቢሰማውም ለእናቱ የገባው ቃል አክብሮ የእናቱን አስክሬን እቤት ጥሎ የጥዋት ፈተናውን ተፈተነ📝🕯️።
ካሊድ ከሠዓት እናቱን አልቅሶ ቀብሮ ተመልሶ የከሰዓት ፈተናውን ተፈተነ🙏📚።
https://t.me/LawStudentsUnion | 278 |
