fa
Feedback
የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት

የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት

رفتن به کانال در Telegram

ይህ ቻናል በኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ቻናል ነው

نمایش بیشتر
746
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-47 روز
-630 روز

در حال بارگیری داده...

کانال‌های مشابه
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
سپتامبر '25
سپتامبر '25
+4
در 0 کانال‌ها
اوت '25
+11
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+21
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+22
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+39
در 1 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+23
در 2 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+12
در 1 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+617
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '250
در 1 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+121
در 2 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
17 سپتامبر0
16 سپتامبر0
15 سپتامبر0
14 سپتامبر0
13 سپتامبر0
12 سپتامبر0
11 سپتامبر0
10 سپتامبر0
09 سپتامبر0
08 سپتامبر0
07 سپتامبر0
06 سپتامبر+1
05 سپتامبر0
04 سپتامبر+1
03 سپتامبر0
02 سپتامبر+1
01 سپتامبر+1
پست‌های کانال
2
+ ከታቦር ተራራ አትቅር + "አጣቢም በምድር ላይ እንደዚያ ሊያነጣው እስከማይችል በጣም ነጭ ሆነ። " ማር 9: 3 /ሽራፊ ሃሳቦች ከደብረ ታቦር ንባብ/ የወንጌላውያን ትሕትና ይደንቃል ፣ ማቴዎስ ማርቆስ ሉቃስ ስለ ደብረ ታቦር ሲጽፉ ዮሐንስ አልጻፈም። ዮሐንስ ተመርጦ የተገኘበትን ታሪክ "ተመርጬ" ብሎ አልጻፈም። የቀሩት ወንጌላውያን ደግሞ "እኛ የሌለንበትን ነገር አንጽፍም" አላሉም። አንድ ወንጌል እየሰበኩ የሚፎካከሩ ፣ የአንድ ቤት ጣሪያ እየሠሩ ቆርቆሮ የሚሻሙ የእኛ ዘመን አገልጋዮች አልነበሩምና እነርሱ ያልተመረጡበትን ታሪክ ለመናገር ተሯሯጡ። እኛን የማያካትት ክብር ፣ እኛን የማይጨምር ድግስ ጉዳይ ሲነሣ ለማይጥመን ፣ እኛ የሌለንበትን ፎቶ እንኳን ለማየት የማንፈልግ ፣ በእኛ በኩል ያለፈን ነገር ብቻ የምናራግብ ፣ የሌለንበትን ነገር ጥሩም ቢሆን እንኳን ለምናጣጥል "በእኔ በቀር ባዮች" ትምህርቱ ድንቅ ነው። ሌላ ማሳያም አለ ማቴዎስ ወንጌላዊው ስለ ራሱ ታሪክ ሲጽፍ "ማቴዎስ የተባለ ቀራጭ በመቅረጫው ተቀምጦ" ብሎ በኃጢአት ከተዘፈቀበት ሥራ ላይ ወደ ክርስትና እንደተጠራ በግልጽ ሲጽፍ ሌሎቹ ወንጌላውያን ግን በሐዋርያት ዝርዝር ላይ ማቴዎስ ያሉትን ሰው ስለ ቀድሞ የቀራጭነት ሥራው ሲጽፉ ግን ሌዊ የሚል ተለዋጭ ስሙን ተጠቅመዋል። ትሑቱ ማቴዎስ ግን በሌሎች ወንጌላውያን የተሸሸገ የቀድሞ የኃጢአት አኗኗሩን ለእግዚአብሔር ይቅር ባይነት ማሳያ እንዲሆን ስለፈለገ ጭራሽ በሐዋርያት የስም ዝርዝር ላይ "ቀራጩ ማቴዎስ" ብሎ ራሱን ጠርቷል። የሚገርመው ከቀራጭነት ከተጠራ በኋላ በቤቱ ታላቅ ድግስ ደግሶ ጌታችንን ከኃጢአተኞች ጓደኞቹ ጋር የተቀበለ መሆኑን በሌሎች ወንጌላውያን ሲጽፉ ማቴዎስ ግን ቀራጭነቱን አጉልቶ እንዳልጻፈ ሁሉ የግብዣው ነገር ደጋሹ እርሱ መሆኑን አድበስብሶ በመጻፍ አልፎታል። ★ ★ ★ ቅዱስ ጴጥሮስ "ጌታ ሆይ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው" አለ። "ለእኛ" መልካም ነው የሚለው ቃል ድንቅ ነው። በእግዚአብሔር ቤት መኖራችን መልካምነቱና ጥቅሙ ለእኛ ነው እንጂ ለእግዚአብሔር አይደለም። የማንጠቅም ባሪያዎቹ ስሙን በአሕዛብ ዘንድ ከማሰደብ በቀር ለእርሱ ምን እንጠቅመዋለን። ለዚህም ነው ቅዱስ ባስልዮስ "ጌታ ሆይ የአንተ አምላክነት ለእኔ ያስፈልገኛል እንጂ የእኔ ፍጡርነት ለአንተ አያስፈልግህም" ያለው። ስለዚህ ጴጥሮስ "ለእኛ መልካም ነው" አለ። "ብትወድስ ሦስት ዳስ እንሥራ" አለ ፣ ጌታ ካልወደደ እንኳን ሦስት አንድ ዳስ መሥራት አይቻልም ፣ እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ" ስለዚህ "ብትወድስ" አለ። የዋሁ ጴጥሮስ ለእኔ ልሥራ አላለም ፣ የሐዲስ ኪዳን ሐዋርያ ነኝ ብሎ የብሉይ ኪዳን ነቢያትን ከማክበር ወደ ኋላ አላለም። "አንተ ዓለት ነህ በዚህች ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራታለሁ" በተባለ ማግስት ለነቢያቱ ድንኳን ሊቀልስ የጠየቀ ከጴጥሮስ በቀር ማን አለ? ከእግዚአብሔር አብ ግን "አትሙት" እስከማለት ለደረሰው ለነጴጥሮስ ንግግር "የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት" የሚል ትእዛዝ መጣ። ሃሳቡ ድንቅ ቢሆንም ቃሉን ሳይሰሙ ዳስ መሥራት መጀመር አይቻልም። በዚያ ላይ ጌታ የመጣው በደብረ ታቦር ድንኳን አስጥሎ ሊኖር ሳይሆን በቀራንዮ በተሰቀለበት በመስቀሉ ካስማ በደሙ ድንኳን ተክሎ ሊያስጠልለን ነው። ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ "ጴጥሮስ ሆይ ለአንተ የፊቱን ብርሃን እያየህ በዚህ መኖር መልካም ነው ፣ እኛ ግን የምንድነው በተራራው ሲኖር ሳይሆን ወርዶ ፊቱን በጥፊ ሲመታ ነው" ብሎታል። ጴጥሮስ የዋሁ "በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ" ላለው ለክርስቶስ ድንኳን ሊቀልስ ጠየቀ። በሰማይ "በሰው ሳይሆን በጌታ የተተከለች ድንኳን" ላለችው ሊቀ ካህናት ድንኳን ሊሠራ ለመነ። እዚህ አለ ሲሉት እዚያ ለሚገኘው ፣ በመንፈስ እየተነጠቀ አድራሻውን ለመወሰን ያስቸግር ለነበረው ኤልያስ እንዲቀመጥ ተስፋ አድርጎ ድንኳን ልሥራ አለ። እጅግ የተዋበችና በወርቅ በሐር ያጌጠችን የኦሪት ድንኳን ለሠራው ሙሴ ዓሣ አጥማጁ ጴጥሮስ ድንኳን ልሥራለት አለ። ሐዋርያት ነቢያቱን ሊያስተናግዱ የለመኑባት ደብረ ታቦር ፣ ሐዋርያት ነቢያቱን ለጌታ ቀኝ አዝማች ግራዝማች አድርገው በድንኳን አስቀምጠው እነርሱ እንደ ሎሌ ከደጅ ሊኖሩ የጠየቁ እነ ጴጥሮስ እንደምን ይደንቃሉ? ጴጥሮስ ሆይ አሁን በሰማይ ድንኳኖች ውስጥ እያገለገልህ ይሆንን? ደብረ ታቦርን አይተህ በደስታ "እንኑር" ያልከው ጴጥሮስ ሆይ የገነት ደስታ ስታይ ምን ተሰምቶህ ይሆን? በእሳት ድንኳን ለመኖር ተስፋ የምናደርግ "በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል" የተባልን እኛስ ምንኛ የታደልን ነን? ★ ★ ★ በታቦር ተራራ ላይ የጌታችን ልብስ እንደ ፀሐይ አበራ ፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ "ከፀሐይም በላይ ነው ፣ ፀሐይ አይቶ የወደቀ የለም የጌታችንን ልብስ ሲያዩ ግን የወደቁት ያበራው ከዚያ በላይ ስለሆነ ነው" ይላል። ከጌታችን በዚያ ተራራ ከሙሴና ኤልያስ ጋር ነበረ። ሙሴ እንደምናውቀው ጽላቱን ተቀብሎ ሲወርድ ሕዝቡ "እባክህን ተሸፈንልን" ብለውት ፊቱን በመጎናጸፊያው ሸፍኖ ነበር። የሙሴ አምላክ ክርስቶስ ግን ደቀ መዛሙርቱ ሲወድቁ አይቶ በልብሱ እንዳይሸፈን ያበራው ፊቱ ብቻ ሳይሆን ልብሱም ነበር። " አጣቢም በምድር ላይ እንደዚያ ሊያነጣው እስከማይችል በጣም ነጭ ሆነ" ማር 9: 3 የሚለው ቃል ምንኛ የሚደንቅ ነው። በምድር ላይ ያለ አጣቢ ቢፈትግ ቢታገል የዚያን ያህል ሊያነጻው የማይችለው ነጭ እንዴት ያለ ነው? መቼም ሁላችን የምናውቀው ነጭ ነገር ሁሉ በምድር ላይ ባለ አጣቢ የታጠበ ስለሆነ እንዲህ ነው ማለት አንችልም። ብቻ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በምድር ያሉ አጣቢዎች ከሚያነጡት በላይ ልብስን ማንጣት ይችላል። ይህ ቃል በኃጢአት እድፍ ልብሳችን ላደፈ ሁሉ መጽናኛችን ነው። መቼም የምድር አጣቢዎች አቅማቸው ውስን ነው። ቆሽሸን ያዩን ሰዎች ብንታጠብም አያምኑንም፣ ቢያጥቡልንም በኅሊናቸው የሚያስቀሩብን ቆሻሻ አለ። በሰው ዓይን አንዴ ቆሽሸህ አትገኝ እንጂ ከተገኘህ መቼም ነጭ አትሆንም። አንተ ግን የደብረ ታቦሩ ብርሃን መድኃኔ ዓለምን ብቻ "እጠበኝ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ" በለው "ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች። " ብሎ በገባው ቃል መሠረት ነጭ ያደርግሃል። እርሱ ወዳለባት የቅድስት ቤተክርስቲያን ተራራ በንስሓ ከደረስክና በታቦር ያበራውን ብርሃኑን ካበራልህ ነጭ ትሆናለህ። ከዚያ "አጣቢ የማያነጻውን ያህል ትነጻለህ" ከአብ የባሕርይ ልጅ ከብርሃኑ ፀዳል ስትቀርብ አንተም በጥምቀት ያገኘኸው የጸጋ ልጅነትህ ያንጸባርቃል። ነጭ በሆንህ ጊዜ የሚያዩህ ሁሉ "በበጉ ደም ልብስህ መታጠቡን"ና ነጭ መሆኑን አይተው ይደነግጣሉ ፣ ሊሰሙህ ያልወደዱ ሁሉ ለባሕርይ ልጁ "የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት" ብሎ እንዳዘዘለት ለአንተም ጆሮ እንዲሠጡህ ያደርግልሃል። አንተ ብቻ ከደብረ ታቦር አትቅር ፣ ካልሞትህ እንደ ኤልያስ ፈጥነህ ና ፣በበደል ከሞትክም እንደሙሴ ተነሥተህ ና። ብቻ ወደ ደብረ ታቦር ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለመምጣት ተስፋ አትቁረጥ ፣እንደ ሙሴ ትሞታለህ እንጂ ምድረ ርስትን አታይም ብትባል፣እንደ ኤልያስ ትኖራለህ እንጂ ሞትን አታይም ብትባል ብቻ አንተ ከደብረ ታቦር አትቅር። ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ደብረ ታቦር 2010 ለንደን ፣ ብሪታንያ https://t.me/ardssu
562
3
بدون متن...
843
4
#EOTC የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውሳኔ አሳልፋ እስኪተገበር ድረስ በሁሉም ሰንበት ትምህርት ቤት በአጫበር ስም የሚደረግ ዝማሬ እንዲቆም ተወሰነ። ውሳኔውን ያሳለፈው የአዲስ አበባ+2
#EOTC የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውሳኔ አሳልፋ እስኪተገበር ድረስ በሁሉም ሰንበት ትምህርት ቤት በአጫበር ስም የሚደረግ ዝማሬ እንዲቆም ተወሰነ። ውሳኔውን ያሳለፈው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ነው። ጠቅላላ ጉባኤው " የአጫበር ስም እየተተገበረ ያለ አዘማመርን በተመለከተ የዘርፉ ሊቃውንትን ጨምሮ ብዙ አባቶችን እና ምዕመናንን ያሳዘነ ጉዳይ በመሆኑ በሊቃውንት ተጠንቶ በቅድስት ቤተክርስቲያን ውሳኔ ተላልፎ እስኪተገበር ድረስ ሁሉም ሰንበት ትምህርት ቤት የአጫበር ስም የሚደረግ ዝማሬን እንዲያቆሙ " ብሏል። ጉባኤው የሰ/ት/ቤትን ዝማሬን በተመለከተም " ሁሉም ሰ/ት/ቤት የሚጠቀምበትን ልብሰ ስብሀት የካህናት በተለይም የዲያቆናት  አክሊል የሆነና ተመሳሳይ የሆነ ከዚህ በኋላ የትኛውም ሰ/ት/ቤት እንዳይጠቀም " ያለ ሲሆን " የልብሰ ስብሐትና የአክሊል ዓይነት ተወስኖ በመመሪያ እስኪወርድ ድረስ ከካህናትና ከዲያቆናት አልባሳትና አክሊል ውጪ ሰ/ት/ቤቶች ባላቸው ልብሰ ስብሐት እየተጠቀሙ እንዲቆዩ " ወስኗል። አዘማመርን በተመለከተ  ያሬዳዊ ዜማን የጣሰ ወደ ጭፈራ ያደላ አዘማመር እንዲቆም ይህንንም ለማስፈፀም ከክፍለ ከተማ አንድነት ክትትል እንዲያደርግ ስምምነት ላይ መደረሱን አሳውቋል። ከላይ በተጠቀሱት የአለባበስና አዘማመር ጉዳይ በሀገረ ስብከት መመሪያ እንዲተላለፍ እና ሰበካ ጉባኤያት ቁጥጥር እንዲያደርግ ስምምነት ላይ መደረሱንም ገልጿል። መረጃው ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተላከ ነው። @tikvahethiopia
277
5
ሦስተኛው የአህጉረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር ተከናወነ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 21 / 11 / 2017 ዓ.ም ሦስተኛው የአህጉረ ስብከቶች የሰ/ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ተከናውኗል። በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅና የሸገር ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የምስካየ ኅዙናን ገዳም የበላይ ጠባቂ እና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤጲፋኒዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ ፣ ዲ.ን ስንታየሁ ምስጋናው የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሓላፊዎች ፣ መምህራነ ወንጌል ፣ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሥራ አመራር አባላት ተገኝተዋል። ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ባስተላለፉት መልእክት "ጌታችን በመዋዕለ ሥጋዌው ለ3 ዓመት ከ3 ወር ሐዋርያትን ከተለያየ ግብርና ክፍል መርጦ ካስተማራቸው በኋላ ሂዱና አስተምሩ በሀገር ሁሉ ቋንቋ አስተምሩ ብሎ እንዳዘዛቸውና አልጫ የሆነውን ዓለም በማስተማር እንዳጣፈጡ ሁሉ እናንተም በተማራችሁት ትምህርት ሄዳችሁ እንድታስተምሩ ፣ እንድታሰለጥኑ ፣ ፍሬ እንድታፈሩ" በማለት አባታዊ ምክርና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል። ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም እንዲሁ "ከእግዚአብሔር የተላከ ከእግዚአብሔር የተመረጠ የአምላኩ የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራል" በሚል ኃይለ ቃል ተነስተው እርሱን ለማገልገል የሚጠራ ማንኛውም አገልጋይ የእግዚአብሔርን ዓላማ ፣ ሐሳብ የእርሱን ዕቅድና እርሱ ለሰው ያለውን አምላካዊ ጥበብ ፣ መግቦት በፍጥረቱም ላይ እንዴት እንደሚሠራና ጥልቅ የሆነውን ፍቅሩን ሁሉ ይናገራል። ብለው ወደ መጣችሁበት ስንቃችሁን ያዛችሁ በመሄድ በሚገባ አገልግሎታችሁን እንድትፈጽሙ ይሁን በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈው ቋጭተዋል። በዕለቱ ሌላኛውን አባታዊ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም እንዲሁ "በአባቶች ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ" የሚለውን የልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ቃል መነሻ አድርገው እናንተም በአባቶቻችሁ ፈንታ የተተካችሁ እንደመሆናችሁ አባቶቻችሁን መስላችሁ ቤተ ክርስቲያንን ልታገለግሉ ይገባል በማለት ለተመራቂ መምህራን የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ "መጻሕፍት እግዚአብሔርን ወደ ማድነቅ ልብህን ይመሩታልና" በሚል ኃይለ ቃል በመነሣት የማደራጃ መምሪያውን መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ዲያቆን ስንታየሁ ምስጋናው በሥልጠናው ጊዜ አጠቃላይ የተከወኑ ተግባራትና በቀጣይ እንዲሠሩ የሚፈለጉ ጉዳዮች ላይ ገለጻ አድርገዋል። ሠልጣኝ መምህራኑም የነበራቸውን የ15 ቀን ቆይታ የተመለከተ ዘገባ እና አቋማቸውንም እንዲሁ በተወካያቸው በኩል አቅርበው ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እጅ የዕውቅና የምስክር ወረቀታቸውን ተቀብለው የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል። ሥልጠናው ከሐምሌ 7 እስከ ሐምሌ 20 ቀን ድረስ በተከታታይ ለ15 ቀናት የተሰጠ ሲሆን በሥልጠናውም ላይ ከ30 አህጉረ ስብከት የተወጣጡ 209 መምህራን ተከታትለው አጠናቅቀዋል። ከነዚህም መካከል 106 ቀሳውስትና ዲያቆናት እንዲሁም 8 ሴቶች ይገኙበታል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website
751
6
+5
بدون متن...
541
7
+9
بدون متن...
536
8
ቅዱስ_ቂርቆስና_እናቱ_ቅድስት_ኢየሉጣ (#ሐምሌ_19) ሐምሌ ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ። ይህም ሕፃን ዕድሜው ሦስት ዓመት ሲሆነው ከሮሜ አገር ወደሌላ ሀገር እናቱ ይዛው ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኰንን አገኘችው።  ሰዎችም ነገር ሠሩባት ወደርሱ አስቀረባትና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኰንን ሆይ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነው ሕፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እርሱን ጠይቅ አለችው።  ሕፃኑም ወደአለበት ጭፍራውን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕፃኑም መልሶ አዎ ለእኔ ደስታ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ልቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስከ አስደነገጣቸው ድረስ ንጉሡን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሣ አደነቁ።  መኰንኑም በአፈረ ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ሥቃይን አሠቃየው እናቱንም ከርሱ ጋር እንደ እርሱ አሠቃያት እግዚአብሔርም ያለምንም ጉዳት ያነሣቸው ነበር። ብዙዎች አሕዛብም ይህን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበሉ።  በሕፃኑ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው። ከዚህም በኋላ መኰንኑ በታላቅ የናስ ጋን ውስጥ ውኃ ጨምረው በእሳት ያፈሉት ዘንድ አዘዘ የፍላቱም ድምጽ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ሆነ ያን ጊዜም ፍርሀትና የሃይማኖት ጉድለት በእናቱ ላይ ደረሰባት ሕፃኑም ስለ እናቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ።  ያን ጊዜ ጌታችን ልቧን ወደ ሰማይ አሳርጎ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁ የብርሃን ማደሪያዎችን አየች ከዚህም በኋላ ጸናች እግዚአብሔርንም አመሰገነችው ልጅዋንም ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አንተ አባቴ ነህ እኔም ልጅህ ነኝ አለችው።  ያቺ ከኔ የተወለድክባትም ቀን የተባረከች ናት አለች ወደዚያ ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና።  ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው እንዲጐትቷቸው አዘዘ ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ አዳናቸው መኰንኑም በታላቅ ሥቃይ ያሠቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው።  ያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕፃኑ ቂርቆስ ወርዶ አጽናናው አረጋጋውም። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጠው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። (#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሐምሌ)
444
9
"የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።" መዝ 33(34) ፡ 7 እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ! ሐምሌ 19 በዚህች ዕለት ቅዱስ ገብርኤል
"የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።" መዝ 33(34) ፡ 7 እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ! ሐምሌ 19 በዚህች ዕለት ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስን እና እናቱን ቅድስት እየሉጣን ከእሳት ያደነበት ዕለት ነው! መልካም በዓል! (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website
336
10
ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የክረምት የመምህራን አሰልጣኞች ሥልጠና እየወሰዱ ያሉ መምህራንን ጎበኙ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 18/11/2017ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሰን+1
ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የክረምት የመምህራን አሰልጣኞች ሥልጠና እየወሰዱ ያሉ መምህራንን ጎበኙ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 18/11/2017ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩንቨርስቲ እየተሰጠ የሚገኘው የክረምት የመምህራን የአሰልጣኞች ስልጠና ላይ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ በመገኘት አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል። ብፁዕነታቸው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለልጁ ለጢሞቴዎስ የተናገረውን "ለወንድሞችህ ይህንን አስተምራቸው" የሚለውን ኃይለ ቃል መነሻ አድርገው አባታዊ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ልጄ ሆይ ጆሮህን ለመምህራን ስጥ እንደተባለ ከመምህራን እግር ስር ቁጭ ብለው የሚማሩት ቃለ እግዚአብሔር ለሕይወታች ስንቅ ነውና ቅዱስ ጢሞቴዎስን አብነት አድርጎ በሕይወት መተርጎም ይገባል የተማርነውንም ለወንድሞች ማስረዳት መንገር ይገባል ብለዋል። በመጨረሻም ሰልጣኞች በተከታታይ በቀንም በማታም እየተሰጣቸው ያለውን ሥልጠና በሚገባ ተከታትለው በየሀገረ ስብከታቸው ሲመለሱ በትኩረት ሊሰሩ ለሌሎችም ሊያጋሩ እንደሚገባ አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website
356
11
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የክረምት የመምህራን አሰልጣኞች ሥልጠና እየወሰዱ ያሉ መምህራንን ጎበኙ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 14/11/2017ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሰንበ
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የክረምት የመምህራን አሰልጣኞች ሥልጠና እየወሰዱ ያሉ መምህራንን ጎበኙ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 14/11/2017ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩንቨርስቲ እየተሰጠ 7ኛ ቀኑን በያዘው የክረምት የመምህራን የአሰልጣኞች ስልጠና ላይ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ በመገኘት አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል። ብፁዕነታቸው ለእናንተ የመንግስተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቷችኋል" ማቴ 13፥11 በሚል ርዕስ ቃለ እግዚአብሔርና አባታዊ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የመንግስተ ሰማያት ምሥጢር ለማወቅ ጾታና ማዕረግ ሳይለይ ለሁሉም የሰው ዘር የተሰጠ ጸጋ መሆኑንና ይህን ምስጢር አውቆ ማሳወቅ ከመምህራን የሚጠበቅ ተግባር ነው ብለዋል። አያይዘውም ለሰንበት ትምህርት ቤቶች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መሠራት እንዳለበት አሳስበው እንደ ሀገረ ስብከታቸው ሰሜን ወሎ ለሰንበት ትምህርት ቤት አገልግሎት ልዩ ትኩረት በመስጠት ሰልጣኞችን በመላክና በመማርያ መጻሕፍት ግዥ አስፈላጊውን በጀት በመመደብ እየሠሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። በመጨረሻም ሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ሥልጠና በሚገባ ተከታትለው በየሀገረ ስብከታቸው ሲመለሱ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website
749
12
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በአለፋት አራት ዓመታት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎችን የ2017 ዓ/ም የ4ተኛ እና የ8ተኛ ክፍል ብ+5
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በአለፋት አራት ዓመታት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎችን የ2017 ዓ/ም  የ4ተኛ እና የ8ተኛ ክፍል ብሔራዊ  ተፈታኞችን ምዘና ሐምሌ 13/2017 ዓ.ም  ለመጀመሪያ  ጊዜ በተለያዩ የምዘና ማዕከላት ተሰጠ። ምዘናው የተሰጠባቸው ማዕከላት ✅የቅዱስ ሉቃስ ምድብ አንድነት           አቡነ ቴዎፍሎስ አካዳሚ ✅በቅዱስ ማቴዎስ ምድብ አንድነት ማቴዎስ         ደብረ ዓባይ ቅዱስ ገብርኤል፣ ✅በቅዱስ ዮሃንስ ምድብ አንድነት           መካነ ሰላም ድባንቄ መዳኒዓለም፣ ✅በቅዱስ ማርቆስ ምድብ አንድነት        ደብረ ይባቤ ዘንዘልማ ሚካኤል ምዘናው በሦስቱ ማዕከላት በጥሩ ሁኔታ የተሰጠ መሆኑ ሲገለጽ አንድ ማዕከላት የምዘና ወረቀት ብዜት ችግር ገጥሞ የነበረ መሆኑ ተገልጾል። ዘገባው የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website
542
13
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ከ14,000 በላይ ለሚሆኑ የሰንበት ት/ ቤት ተማሪዎች በሀገረ ስብከት ደረጃ የብሔራዊ ፈተና ምዘና በዛሬው ዕለት አከናወነ። ብጹዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ፣ ሃድያ እና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም ወቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ካቴድራል ተገኝተው ምዘናውን በጸሎት አስጀምረዋል። በዛሬው የአራተኛ የስምንተኛ እና የአስረኛ ክፍል ተማሪዎች በአመቱ የተማሩትን ምን አውቀዋል ምን አላወቁም የሚለውን   በወረቀት የሚያሰፍሩበት የተማሩት ሚዛን ላይ ወጥቶ የሚመዘንበት እውቀታቸው የሚለካበት ማጠቃለያ ምዘና  መሆኑን ገልጸው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ  ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ሁሉም ከክፍል ወደ ክፍል በሚዛን የሚዘዋወሩበት  የሥርዓተ ትምህርት ሒደት መልካም ጅማሮ መሆኑን ገልጸዋል። በዕለቱም ከአራቱም አቅጣጫ  ከ168 ሰንበት ትቤቶች የተውጣጡ  ተማሪዎች እየተመዘኑ  መሆናቸውን አሳውቀው፤  በስተመጨረሻም  ለተፈታኞች መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።    በዕለቱ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ ፣ የሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም እና ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ካቴድራሉ ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ኃይል አባ ተክለ ብርሃን ደስታ  እና የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ  እና የቦሌ ክፍለ ከተማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አመራሮች በተገኙበት በሀገረ ስብከት ደረጃ  የመክፈቻ  መርሐግብር ተከናውኗል። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ   እንደተናገሩት የሰንበት ት/ቤት ታዳጊዎች እና ሕፃናት ላይ መሥራት የነገ ቤተክርስትያንን ዛሬ ላይ ሆኖ መገንባት ነው ትውልድ ላይ መሥራት ቤተክርስትያንን ለቀጣይ ዘመን ማሻገር መሆኑን ጠቅሰው በሰንበት ት/ቤት እየተተገበረ ያለውን የመማር ማስተማር ሂደት ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት በትኩረት ሊያግዙ እንደሚገባ በመግለጽ፤ በተለይም ሰበካ ጉባኤያት በየገዳማት እና አድባራቱ አስፈላጊውን ድጋፍ በመስጠት ታሪካዊ ሐላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ላእከ ኄራን መንክር ግርማ በበኩላቸው ተመዛኞች ዓመቱን ሙሉ በሰንበት ት/ቤቶች ሲማሩ መቆየታቸውን አስታውሰው  በዛሬው ዕለት ከ168 ሰንበት ት/ቤቶች የተውጣጡ 14,800 የሚሆኑ ተመዛኞች የተፈተኑ ሲሆን፤ በሁሉም የመፈተኛ ጣብያዎች ፈተናዎቹ መሰጠታቸውን እንዲሁም የቋንቋ እና ልዩ ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች አስተርጓሚ እና አንባቢ ተመድቦላቸው እንደተፈተኑ በተጨማሪም የሰባቱም ክፍለ ከተማ አንድነት ጽ/ቤት እና ትምህርት ክፍሎች በየክፍለ ከተሞቻቸው ያሉ ተፈታኞችን የክትትል ጣቢያዎች አዘጋጅተው በጥሩ መልኩ ያስተባበሩ መሆናቸውን የክፍለከተማ ቤተክህነት ሐላፊዎችም በተመደቡበት ጣቢያ በመገኘት በጸሎት በመክፈት እና ጉብኝት በማድረግ ፤ የገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎችም በጸሎት በመክፈት እና አስፈላጊ ድጋፍ በመስጠት ለመርሐ ግብሩ መሳካት ሁሉም የበኩላቸውን ተወጥተዋል። በመጨረሻም የክፍለ ከተማ አስተባባሪዎቹ  ከየፈተና ጣብያዎች የተሰበሰቡ የፈተና ወረቀቶችን  ከቀኑ 9:00 ጀምሮ ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከቱ አንድነት ትምህርት ክፍል አድርሰዋል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website
416
14
የ2017 ዓ.ም የክረምት የአሰልጣኞች መምህራን ሥልጠና ተጀመረ (ሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 07 2017 ዓ.ም የ2017 ዓ.ም የክረምት የአሰልጣኝ መምህራን ሥልጠና በዛሬው ዕለት በቅድስት ሥላሴ+9
የ2017 ዓ.ም የክረምት የአሰልጣኞች መምህራን ሥልጠና ተጀመረ (ሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 07 2017 ዓ.ም የ2017 ዓ.ም የክረምት የአሰልጣኝ መምህራን ሥልጠና በዛሬው ዕለት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ተጀመረ። በዛሬው የመክፈቻ መርሐ ግብር ላይም አረጋዊው አባት ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ ምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ የተገኙ ሲሆን ብፁዕነታቸው "እነሆ ጊዜው ደረሰ" በሚል መነሻ ቃለ ወንጌል ፣ አባታዊ ምክርና ቃለ ምዕዳን ለሰልጣኝ መምህራኑ አስተላልፈዋል። "እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤" የሚለውን የልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊትን ቃል መነሻ በማድረግ የማደራጃ መምሪያው ሐላፊ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። በዛሬው የመክፈቻው መርሐ ግብር ላይ ሰልጣኞች በሚኖራቸው ቆይታ ሊያውቋቸው የሚገቡ ጉዳዮችን በሚመለከት ገለጻ ተሰጥቶ የመክፈቻ መርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል። ሥልጠናው በዛሬው ዕለት በምሽት የሰንበት ት/ቤቶች መዋቅራዊ አደረጃጀትን በሚመለከት የሚቀጥል ሲሆን እስከ ሐምሌ 20 ድረስ በተከታታይ ለ15 ቀናት የሚቆይ ሲሆን የቅድስት ቤተ ክርስቲያን መሠረተ እምነትን ፣ የተለያዩ ክህሎትን የሚያዳብሩ እንዲሁም በሥርዓተ ትምህርቱ ላይ ትኩረት ያደረጉ ከ15 በላይ ሥልጠናዎችን የሚያገኙ ይሆናል። ሥልጠናውን ከ30 ሀገረ ስብከት የተወጣጡ 213 መምህራን የሚወስዱ ይሆናል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website
645
15
https://youtu.be/vS6_QuVSvLk?si=GihEQQEx9SxIiLAb
426
16
"እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ።" ማቴ 5:14 እንኳን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች
"እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ።" ማቴ 5:14 እንኳን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website
498
17
بدون متن...
455
18
+2
بدون متن...
402
19
+1
بدون متن...
430
20
+2
بدون متن...
431