Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union
رفتن به کانال در Telegram
This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.
نمایش بیشتر4 481
مشترکین
-124 ساعت
+147 روز
+3130 روز
آرشیو پست ها
"እስከዛሬ ስናናግረው የነበረ ግቢ የእስከዛሬው ተረስቷል ከአሁን ቡሃላ አንዳንድ እየሆናችሁ አናግሩን የሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የሚባል አናውቅም እያለ ነው።"
በዘመቻችን፦ https://vt.tiktok.com/ZSHcGsQTx/ በመግባት ኮሜንት ማድረግ እና ለሌሎች ማሰራጨት እንዳይዘነጋ።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
ጥያቄ፦ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚደርሰው የመብት ጥሰት መች ነው የሚያበቃው?
መልስ፦ አሁን ያብቃ!
@aaumsu
+1
"በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት ብቻ ሳይሆን ክብራቸውንም የሚነካ ድርጊት ስለሆነ በቶሎ እንዲቆም እንጠይቃለን።" - የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ
እየደረሰ ስላለው በደል ያወጣው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል። ጥያቄው የጥቂቶች ነው ላሉት አድርሱላቸው።ጥያቄው የሁሉም ሙስሊም ጥያቄ ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እንፈልጋለን ! ! !
@aaumsu
"ዩኒቨርሲቲው ጥቂት ስለሆኑ መመሪያውን አላሻሽልም ብሏል። የፌደራል መጅሊስን ሄደን ስንጠይቅ ደግሞ ኒቃብ ሱና ስለሆነ ተውት ብሎናል። እንደተባለውም እናንተ ጥቂቶች ናችሁና ዘገባ ልንሰራላችሁ አንችልም።" - ፋና
ሙስሊም ተማሪዎች አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እየፈፀመባቸው ስላለው የመብት ጥሰት ዘገባ ይሰራ ዘንድ ወደ ፋና ባመሩበት ወቅት ከተቋሙ የምርመራ ዘገባ ክፍል ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ጌታሁን ዳዲ ጋር ተወያይተው ነበር። በውይይቱ ወቅት የሚመለከታቸውን ሁሉ አናግረው ፍትሕ እስኪመጣ ድረስ ከጎናቸው በመቆም ሀላፊነታቸውን እንደሚወጡም አፅንዖት በመስጠት ገልፀው ነበር።
ሆኖም ግን ውጤት ለመጠየቅ ዳግም ሲሄዱ የሙያ ስነ-ምግባርን ባልተላበሰ እና ከፍትሕ ፅንሰ ሀሳብ በራቀ መልኩ ምላሽ ሰጥተዋል። በምላሻቸው የፌደራል መጅሊስ ሄደው ሲጠይቁ ኒቃብ ለትርፍ ፅድቅ የሚሰራ እንደሆነ እንደገለፁላቸው፤ ዩኒቨርስቲውም ይህንን እየጠየቁ ያሉት ተማሪዎች ጥቂቶች ስለሆነ መመሪያውን ሊያሻሽል እንደማይችል እንደገለፀላቸው፤ እርሳቸውም ጠያቂዎቹ ጥቂት ስለሆኑና ከመጅሊስ እና ከዩኒቨርስቲው የተሰጣቸው መልስ አመርቂ ስለሆነ ዘገባውን ሊሰሩ እንደማይችሉ ገልፀዋል።
ጥያቄው ዩኒቨርስቲውን የገነባው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደሆነ ሊሰመርበት ይገባል። መጅሊስ ያነሳነውን የመብት ጥያቄ ሱና ነውና ተውት ብሎ ከሆነም ይፋዊ ማብራሪያ እንዲሰጠን እንፈልጋለን። የሙስሊም ተማሪዎችን ጥያቄ ጥቂቶች ስለሆናችሁ አንዘግብም ስላለው ጋዜጠኛ ጌታሁን ዳዲ ሚዲያው አቋሙ ምን እንደሆነ ይፋ ሊያደርግ ግድ ነው።
ጥያቄያችን ፍትሕ ተነፍጎ እየደረሰብን ያለው በደል ይቆም ዘንድ የወጣው ጨቋኝ መመሪያ ይቁም ነው። ጥያቄው የሕዝበ ሙስሊሙ ነው።
መልስ እንፈልጋለን!
@aaumsu
ዶክተር ሽብሩ ተመስገን (የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ዲን) ሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄያቸውን ለማቅረብ ይምጡ ማለታቸውን ተከትሎ ቅሬታቸውን ለማቅረብ የሄዱ ተማሪዎች እሳቸው ስለሌሉ ተመለሱ ተባሉ ! ! !
------------------------------------------
ሚያዚያ 07 / 2018 ዓ.ል
------------------------------------------
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎቹን ሰብዓዊ መብት የሚጥስ መመሪያን ካወጣበት 2017 ዓ.ል ጥቅምት ወር ጀምሮ ተማሪዎች ለተለያየ የመብት ጥሰት ተጋላጭ ስለሆኑ የመብት ጥሰቱ ቆሞ መብታቸውን የሚያከብር መመሪያ ይወጣ ዘንድ ሲጠይቁ እንደነበር ይታወቃል። ለ19 ወራት ያክል ባደረጉት እንቅስቃሴ ውስጥም የተማሪዎች ሕብረት ከአቅሜ በላይ ነው ስላለ ከተማሪዎች ዲን ጀምሮ እስከ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ድረስ ተደጋጋሚ ውይይቶችን እያደረጉ፤ ደብዳቤዎችን እያስገቡ፤ የሚመለከታቸውን አካላት ሁሉ እየጠየቁ ዘልቀዋል።
ሆኖም ግን መፍትሔ መስጠት ያልፈለጉት የዩኒቨርስቲው አመራሮች ተማሪዎቹን አናውቃችሁም በማለት ያስገቡት ደብዳቤ ላይ ጭምር ስርዝ ድልዝ አድርገው እየመለሱ፤ ውይይት አናደርግም እያሉም እየተናገሩ ዘልቀዋል። በዚህ መሐል ስለጉዳዩ ማብራሪያ የተጠየቁት የተማሪዎች ዲን ዶክተር ሽብሩ ተመስገን "እኛ ጀመዓ አናውቅም። ተማሪዎች ጥያቄ ካላቸው በተናጠል መጥተው ይጠይቁ።" - ማለታቸውን ተከትሎ ተማሪዎች ለመጠየቅ የሄዱ ቢሆንም "እርሳቸው ዛሬ ቢሮ አልገቡም። ነገ ኑ!" - ተብለው ተመልሰዋል።
ተማሪዎች ቅሬታቸውን በሰላማዊ መንገድ አቅርበው መፍትሔን በውይይት ለመሻት ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርጉም ዩኒቨርስቲው እየመለሰበት ያለው መንገድ ግን ትክክለኛ ያልሆነ ነው። ተማሪው እየጠየቀ ያለው የተጣሱት መብቶቹ ይከበሩ ዘንድ ነው። ተማሪን በመናቅ ጥያቄዎችን ችላ ብሎ በማድበስበስ ለማለፍ እየተደረገ ያለው አካሄድ ሊስተካከል ይገባል። ጥያቄያችንን ላለፉት 19 ወራት በሁሉም መንገድ አቅርበናል። ከዶክተር ሳሙኤል ጀምሮ ዶክተር ሽብሩንም ጨምሮ ጥያቄዎቻችንን አቅርበን በተገኙበት ውይይት ላይ መፍትሔ የማይሆኑ ምላሾች ተሰጥተው ነበር። አሁን እየተከሄደ ያለው አካሄድ ደግሞ የውይይትንም በር የዘጋ ነው።
ነገሮች መስመር ይዘው መፍትሔ በቶሎ ይመጣ ዘንድ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ እንዲረባረቡ ዳግም ጥሪያችን ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@MohammadamminKassaw
"እኛ የሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የሚባል ነገር አናውቅም። ተማሪዎች ተሰባስበው ሳይሆን በተናጠል ሆነው ተማሪዎች ሕብረት ቢሮ በመምጣት የደረሰባቸውን በደል ያስረዱ።" - ዶክተር ሽብሩ ተመስገን (የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ዲን) ለሚንበር ቲቪ
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እያደረሰ ያለውን በደል አስመልክቶ ሚንበር ቲቪ በሰራው ዘገባ ላይ ማብራሪያ ይሰጡ ዘንድ የተጠየቁት የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች ዲን ሀላፊ ዶክተር ሽብሩ "እኛ የሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የሚባል አናውቅም። ተማሪዎች የደረሰባቸው በደል ካለ ተሰባስበው ሳይሆን በግለሰብ ደረጃ ወደ ተማሪዎች ሕብረት በመሄድ ያመልክቱ።" - የሚልን የተድበሰበሰ ምላሽ ሰጥተዋል። ይህ መልስ የተቋሙን አንጋፋነት፤ ታማኝነት የማይመጥን እንዲሁም ከተማሪዎች ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያሻክር ምላሽ ነው።
መመሪያው ይሻሻል ዘንድ እና እየደረሰ ያለው በደል ለ18 ወራት ያክል ለተማሪዎች ሕብረት ሲቀርብለት እንደነበርና ሕብረቱም "ከአቅሜ በላይ ነው!" - በማለት ወደ ተማሪዎች ዲን መርቶ እርሳቸው ባሉበት ውይይት ከተደረገ ቡሃላ "ይህ ከእኔ አቅም በላይ ነው። ከፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ጋር ተመካክሬ ውጤቱን አሳውቃለሁ።" - የሚል ምላሽን በመስጠት በያዙት ቀጣይ ቀጠሮ ላይ ሳይገኙ ቀርተው ተማሪዎችን እንዳስቀየሙ የሚታወቅ ነው።
በደሉ የደረሰባቸው ሙስሊም ሴቶች እንደ ግል ስለሚመለከታቸው ደጋግመው ጠይቀዋል። በደሉ የተፈፀመው እንደ ወል በሙስሊሙ ላይ ስለሆነ እንደ ሙስሊም ጠይቀናል። በግልም በወልም ውይይት የጀመሩ ቢሆንም መፍትሔ ይሰጡ ዘንድ ጫና ሲደረግባቸው ጀመዓ የሚባልን ነገር አናውቅም ብለዋል። ሊስተካከል ይገባል።
በዘገባው እንደተጠቀሰውም በፌደራል መጅሊስ የማህበራዊ ጉዳይ ምክትል ፕሬዚዳንት የሆኑት አግባብነት የሌለው መልስ ስለሰጡ ቃላቸውን ማካተት አልተቻለም ብሏል። እንደ መጅሊስ በሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ የተያዘው አቋም ግልፅ እንዲሆንና መፍትሔ ይመጣ ዘንድ አስቸኳይ እንቅስቃሴ እንዲደረግ ጥሪያችን ነው።
@aaumsu
ፕሮፋይል ቻለንጅ ! ! !
መብታችንን የሚጥስ መመሪያ አውጥተው ነፃነታችንን በመግፈፍ እምነታችንን በማስተው የእነርሱ አስተሳሰብ እስረኛ ሊያደርጉ የሞከሩ አካላትን "ጥያቄ አለን!" በማለት እምቢ ለባርነት ማለት ከጀመርን አመት ከመንፈቅ አልፏል። አሁን "መመሪያውን ያወጣነው እነርሱን አስበን አይደለም። ለሁሉም ተማሪ ነው። እነርሱ ጥቂት ስለሆኑ ለጥቂቶች ብለን አንቀይርም።" - የሚልን ተስፋ የቆረጠ እና የሐሳባቸው ውጥን እየተበጣጠሰ መሆኑን የሚያሳይ ምላሽ እየሰጡ ነው። ስንጀምር እንዳልነው ድል ከእውነት እና ከፍትሕ ጎን ነው። ላንጨርስ አልጀመርንም። እምነታችን ተከብሮ፤ ነፃነታችን ፀንቶ መብቶቻችን እስኪረጋገጡ ድረስ ትግላችን ይቀጥላል። ጥቂቶች ናችሁ ለሚሉን "የአንድ ሙስሊም ተማሪ ዋጋ ስንት ነው?" - በሏቸው። ዋጋችንን ጠንቅቀን እናውቃለንና "ጥያቄ አለን!" - በሏቸውም።
አዲሱን ምስል ፕሮፋይላችሁ አድርጉት! ሌሎች ያደርጉት ዘንድም አሰራጩ!! በአላህ ፈቃድ የፍትሕ ቀን ቅርብ ነው!!!
ጥያቄ አለን!
Gaaffii Qabna!!
@aaumsu
Duula 2 _ Miidiyaa Abdii Sabaatiin!
Miidiyaan Abdii Sabaa dookumentarii qopheesseera. Dookumentarii kanaan, miidhaa dubartoota Muslimaa Yuunivarsiitii Finfinnee keessatti irra ga’aa jiru bal’inaan dhiheessaniiru. Akkasumas, tarkaanfii yuunivarsiitichi dhimma kana irratti fudhachaa jiru ibsuun, furmaanni ariifachiisaan akka dhufuu fi warren balleessaa hojjetan hundi itti gaafatamummaa akka fudhataniif ergaa cimaa dabarsaniiru.
Duula Keenyaan:
Viidiyoo ilaaluun: Ergaa isaa haa hubannu.
Baballisuun: Akka hunda bira ga’uuf karaa danda’amu hundaan haa tamsaasnu. Gidiraa yuunivarsiitichi raawwate hundi akka beekuuf.
Sagalee Ta’uun: Callisni dhaabbilee keenyaa akka ifa ta’uu fi furmaata dhimma kanaa irratti hundi akka mari’atuuf.
Kun itti gaafatamummaa keenya isa xiqqaadha! Kun ijoollee Umar (RA) biratti homaa miti. Kun warra Sumayyaa bakka bu’aniif salphaadha. Kun Ummaata Ashrafal-Khalq (SAW) biratti dhimma salphaadha.
Liinkiin isaa: https://youtu.be/-oev1Tkye8M
Gara hojiitti!
@aaumsu
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በመገኘት ዩኒቨርስቲው እየፈፀመባቸው ስላለው በደል አቤቱታ አቀረቡ !!!
----------------------------------
ሚያዚያ 1 / 2018 ዓ.ል
----------------------------------
በዳዮች የሕዝብን እንባ ማፍሰሳቸው በታሪክ የታዬ ዛሬም የቀጠለ ነው። ሆኖም ግን በዳይን በዳይ ሲወርሰው ስለመብቱ የሚሞግትንም ለነፃነቱ የሚታገል ትውልድ ይወርሰዋል። በዚህም ፍትሕ እየሰፈነ ሕይዎት ይቀጥላል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶችም በዩኒቨርስቲው ግፍ እየተፈፀመባቸው መሆኑ የአደባባይ ሐቅ ነው። የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በስሙ ልክ ሆኖ የፈሰሰው እንባቸው ይታበስ ዘንድ ሰበብ እንዲሆን በማለት ከቢሮው በመገኘት አቤቱታቸውን አቅርበዋል። እየደረሰባቸው ያለውን በደል አብራርተው፤ የሄዱበትን ርቀት አስረድተው፤ በዳዮች የመለሱበት መንገድ ገልፀው ስለፍትሕ ሲባል መደረግ ስላለበት አስቀምጠዋል።
ታሪክ እየፃፈ ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች መብት ማን እንደታገለ፤ ማን ከትክክለኛው ቦታ እንደቆመ ታሪክ እየመዘገበ ነው። ያለፈው ትውልድ ትግል እና መስዋዕትነት እንደተከተበ ሁሉ የአሁኑም ትውልድ ንቅንቄ እየተመዘገበ ነው።
በአላህ ፈቃድ ለጥያቄው ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ድረስ ጉዞው ይቀጥላል። ሳንደክም ሳናፍር ሳንፈራ በሁሉም ቦታ ለሁሉም ጥያቄያችንን እናነሳለን።
ጥያቄ አለን እንላለን __ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
ዘመቻ 1 _ በሙባረክ ፖድካስት !
"የአንድ ሙስሊም ተማሪ ዋጋ ስንት ነው?" - በሚል ሐሳብ ተነስቶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው በደል ይዳስሳል። ከዩኒቨርሲቲው ጀምሮ፤ መጅሊስን ጨምሮ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የሰጡትን ምላሽ በዝርዝር ያስቀምጣል። የመፍትሔ ሀሳቡንም በጥልቀት ይገልፃል።
ዘመቻችን፦ ቪድዮውን በመመልከት ሐሳቡን እንውሰድ። ከሁሉም ሰው ይደርስ ዘንድ። ዩኒቨርሲቲው እየፈፀመው ያለው በደል ይጋለጥ ዘንድ። ተቋማቶቻችን ሀላፊነታቸውን በኣግባቡ ይወጡ ዘንድ። ሁሉም ሰው ለፍትሕ ይተጋ ዘንድ።
ይህ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው። አይደለም ወይ ያኡመተ ሙሐመድ?! ወደ ተግባር።
ሊንኩ፦ https://youtu.be/kRqk0MXuXvc?si=EJxv8KNF0yb1aFyZ ነው።
ፍትህ እስኪሰፍን በሁሉም ቦታ ለሁሉም ጥያቄ አለን እንላለን።
@aaumsu
"ምግቡ ምንም ቢሆን እንችለዋለን። በመጀመሪያ በእህቶቻችን ላይ እየፈፀማችሁት ያለውን በደል አቁሙ።" - በAAU Main Campus ያለ ተማሪ
በዛሬው እለት የሆነ ነው። የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ እና ምክትል ፕሬዚዳንቱ ከተማሪዎች መመገቢያ አዳራሽ ተገኝተው "ምግቡ እንዴት ነው? ምን ይሻሻል?" - በማለት ይጠይቃሉ። በዚህም መሐል አንድ ተማሪ ምግብ ምንም ይሁን እንችለዋለን። በመጀመሪያ በኒቃቢስት እህቶቻችን ላይ እየፈፀማችሁት ያለውን በደል አቁሙ።" - በማለት ጠይቋል። እየፈፀሙት ያለውን በደል ሸፋፍነው ለማለፍ ቢሞክሩም እስከ ጥግ ሞግቷቸው አልፏል። "በሁሉም ቦታ በሁሉም መንገድ እንጠይቃለን።" - ስንል ለእስልምናው የሚቆምን ትውልድ ይዘን ነው። ከምግብ ይልቅ ስለዲኑ ለመጠየቅ የማያፍር የማይፈራ ትውልድ ይዘን ነው።
ፍትሐዊ መልስ እስኪጣም በሁሉም ቦታ በሁሉም መንገድ ጥያቄ አለን ማለታችንን እንቀጥላለን።
©️ aaumsu
https://t.me/EHEMSU
+1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በፌደራል መጅሊስ ቢሮ በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ያለው በደል ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኝ እንዲሰራ ጠየቁ ! ! !
-------------------------------------------
መጋቢት 30 / 2018 ዓ.ል
-------------------------------------------
መጅሊስ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በሀገራቸው መብታቸው ሲጓደል ሊጠይቅ፤ የመብት ጥሰት ሲፈፀምባቸው መብታቸውን ሊያስከብር፤ በሁሉም መስክ ያለልዩነት እንደ ሀገር ነፃነታቸው ተከብሮ በእኩልነት እንዲኖሩ ለማስቻል የተቋቋመ የሙስሊሞች አባት ተቋም ነው። ስለሆነም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ያለውን የመብት ጥሰት በመዘርዘር፤ መጅሊሱ እስካሁን ድረስ መፍትሔ ሊያመጣ ያልቻለበትን ምክንያት በመጠየቅ፤ አፋጣኝ ምላሽ እና መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ባለመሰራቱ የደረሰባቸውን ቅሬታ በጥልቀት በማስረዳት ከመጅሊሱ ጋር የነበራቸው ውይይት አጠናቀዋል።
በሂደቱም መጅሊሱ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት በጥልቀት እንዲያዳምጥ እና እንዲገመግም፤ የዩኒቨርስቲውን አመራሮች በሕግ አግባብ ተጠያቂ እንዲያደርግ እና ዘላቂ መፍትሔ እስኪመጣ ድረስ በቁርጠኝነት እንዲሰራ ጠይቀዋል።
የሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ የሙስሊሙ ተቋማት፤ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ብሎም የሁሉም ፍትሕ ፈላጊ ሰው ሁሉ ጥያቄ ነው። ዘላቂ መፍትሔ በማምጣት ሁሉም ተማሪ በተመቻቸ ከባቢ ውስጥ ተምሮ ለሀገር የሚኖረው አበርክቶ እንዲያይል በማድረግ ረግድ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ አስቸኳይ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ እንዲተጉ ጥሪያችን ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ _ የተበደሉት እስኪካሱ _ በዳዮች ተጠያቂ እስኪደረጉ ! ! !
@aaumsu
በሙባረክ ፖድካስት ሁሉም ተዳሷል _ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት መፍትሔ ለመፈለግ የሄዱበት ውጣ ውረድ _ የሚመለከታቸው አካላት የሰጡት ምላሽ ___ የመፍትሔ ሐሳቦችም ጭምር ተነስተዋል። ዛሬ ምሽት በቲክቶክ ይጠብቁ። ለሁሉም ይደርስ ዘንድ አሰራጩት። ሪፖስትም አድርጉ።
ሊንኩ https://vt.tiktok.com/ZSHmJbpLy/ ነው።
@aaumsu
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በኦሮምያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (OBN) ቢሮ በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት አቤቱታ አቀረቡ ! ! !
-------------------------------------------
መጋቢት 28 / 2018 ዓ.ል
-------------------------------------------
እንደ ኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓታችን ተዳክሞ ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገባው ተማሪ ቁጥር ተመናምኗል። በሺ የሚቆጠሩ ትምህርት ቤቶች አንድ ተማሪ እንኳ ለዩኒቨርስቲ ማሳለፍ ተስኗቸው እያየን ነው። ወዲህ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ወደ ዩኒቨርስቲው የገቡ ሙስሊም ተማሪዎችን እምነት እና ማንነት አክብሮ ከማስተማር ይልቅ ብዙ መስዋዕትነት ከፍለው ከደረሱበት ውጤት ለማውረድ በሚመስል መልኩ ማንነታቸውን የሚነካ እና እምነታቸውን የማይቀበል መመሪያ አውጥቶ ለተማሪዎቹ ከመማር ውጪ ተጨማሪ ሀላፊነትን ጨምሯል።
ይህንንም ተከትሎ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች እነተካሄደ ስላለው የሰብዓዊ እና ሐይማኖታዊ መብት ጥሰት አቤት ለማለት ከኦሮምያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (OBN) ቢሮ ተገኝተዋል። እየተካሄደ ስላለው በደል፤ እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት ማብራሪያ ከሰጡ ቡሃላ ስለፍትሕ ድምፅ ይሆናቸው ዘንድ ጠይቀዋል።
የመብት ጥሰታቸውን እስከቀጠሉ ድረስ ስለመብታችን በሁሉም ቦታ በሁሉም መንገድ እንጠይቅ ዘንድ ግድ ሆኗል። በደላቸውን እስከገፉበት ድረስ ስለፍትሕ በሁሉም ቦታ በሁሉም መንገድ እንጮኽ ዘንድ ግድ ሆኗል።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ _ የተበደሉት እስኪካሱ _ በዳዮች ተጠያቂ እስኪደረጉ ! ! !
@aaumsu
+1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በሪፖርተር ቢሮ በመገኘት ዩኒቨርስቲው እያደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት ድምፅ ይሆናቸው ዘንድ አቤቱታ አቀረቡ ! ! !
-------------------------------------------
መጋቢት 28 / 2018 ዓ.ል
-------------------------------------------
በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው በደል፤ ዩኒቨርስቲው እየመለሰ ያለበት መንገድ፤ መንግስት የወሰደው አቋም፤ መጅሊስ እያሳየ ያለው ዝምታ፤ ሚዲያዎች እየሰጡት ያለው ቦታ እንዲሁም ሙስሊሙ ተማሪ እየጠየቀበት ያለው ሁኔታ ሕዝበ ሙስሊም በየዘርፉ ያለውን ቦታ የመጅሊስን አቅም እና የመንግስትን አቋም የሚያንፀባርቅ ነው። ተቋማቱ እና መንግስት የሚሰጡት ምላሽ ትክክለኛ መልካቸውን ከማሳየቱ ባሻገር ያለንበትን ሁኔታ እና የሚጠብቀንን ነገር ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
በዚህ ጉዞ ውስጥ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች ዩኒቨርስቲው እያደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት ድምፅ ይሆናቸው ዘንድ በሪፖርተር ፅ/ቤት ተገኝተዋል። እየደረሰባቸው ያለውን የመብት ጥሰት በማብራራትም እንደ ሚዲያ ሊወጡ የሚገባቸውን ሀላፊነት ጠቁመዋል።
የተጀመረው እንቅስቃሴ ፍሬ አፍርቶ ፍትሕ እስኪሰፍን ድረስ በፅናት እና በቁርጠኝነት መጠየቅ ያሉብንን ሁሉ መጠየቅ ባለብን መንገዶች እንጠይቃለን። ከመጅሊስ ጀምሮ ዩኒቨርስቲውን ጨምሮ የሚመለከታቸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እና የመንግስት አካላት ሁሉ መመሪያው ተሻሽሎ ለፍትሕ መስፈን አስተዋፅዖ ያደርጉ ዘንድ ጥሪያችን ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ _ የተበደሉት እስኪካሱ _ በዳዮች ተጠያቂ እስኪደረጉ ! ! !
@aaumsu
+1
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች አዲስ አበባ በሚገኘው የአልጀዚራ ቢሮ በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው ግፍ ድምፅ ይሆናቸው ዘንድ አቤቱታ አቀረቡ ! ! !
-------------------------------------------
መጋቢት 28 / 2018 ዓ.ል
-------------------------------------------
በአንድ ቦታ የሚፈፀም በደል በሌላ ቦታ ላለ ነፃነት ጭምር ስጋት ነው። የሐይማኖት ነፃነት መብት እና የሰብዓዊ መብት ሲሆን ደግሞ በሁሉም ቦታ ያለ ፍትሕ ፈላጊ ሁሉ ካልታገለለት እንደ ወረርሽኝ የሚዛመት ክፉ አደጋ ነው። በዚህም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት አዲስ አበባ በሚገኘው አልጀዚራ ቢሮ በመገኘት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ ጠይቀዋል።
እየደረሰባቸው ስላለው በደል በማብራራት፤ እየተፈፀመ ያለው የሰብዓዊ መብት ይቆም ዘንድ ሁሉም በየዘርፉ ይሳተፍ ዘንድ ጥሪ በማቅረብ ከፍሬያማ ውይይት ጋር የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀው ተመልሰዋል። ጥያቄዎቻችን ፍትሐዊ መልስ እስኪያገኙ ድረስ መሠል እንቅስቃሴዎቻችን ሰፍተው እና ጨምረው የሚቀጥሉ ይሆናል። ጨቋኙ መመሪያ ተስተካክሎ ፍትሕ እስኪሰፍን ድረስ በሁሉም አማራጭ በሁሉም ቦታ እየደረሰ ስላለው ግፍ ጮክ ብለን እንናገራለን።
አሁንም ቢሆን ጥሪያችን ለሁሉም ነው። ከመጅሊስ ጀምሮ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችንም ጨምሮ የሚመለከታው አካል ሁሉ ዘላቂ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ በአስቸኳይ እንቅስቃሴ ያድርግ።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ _ የተበደሉት እስኪካሱ _ በዳዮች ተጠያቂ እስኪደረጉ ! ! !
@aaumsu
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዶክተር ሳሙኤል አመራር በወጣው መመሪያ ምክንያት እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በመገኘት ድምፃቸውን አሰሙ ! ! !
-------------------------------------------
መጋቢት 25 / 2018 ዓ.ል
-------------------------------------------
በአራዳ ክ/ከተማ ለሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት የብልፅግና እጩ ሆነው የቀረቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ሙስሊም ተማሪዎች እና ፍትሕ ፈላጊ ሁሉ ያወጡትን ጨቋኝ መመሪያ በማስተካከል የሰብዓዊ መብት ጥሰታቸውን እንዲያቆሙ ቢጠይቅም፤ ውይይት የጠየቀውን ተማሪያቸውን እንዲያወያይ ጥሪ ቢያቀርብም ምላሽ ሳይሰጥ እና መፍትሔ ሳይቀመጥ እስካሁን አለ።
ይህ በግልፅነት፣ ተጠያቂነት እና ፍትሐዊነት ሊመራ የሚገባውን ዩኒቨርስቲያችንን ስም የሚያጎድፍ ተግባር በመሆኑ ማስተካከያ ተደርጎ ሁሉም በመስመሩ ይሆን ዘንድ ለማስቻል ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በእንቅስቃሴ ላይ ናቸው። በዛሬው እለትም በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በመገኘት የእርሳቸው አመራር እየፈፀመ ስላለው የመብት ጥሰት ድምፅ ይሆን ዘንድ ጠይቀዋል።
ጥያቄ አለን __ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
