Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union
رفتن به کانال در Telegram
This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.
نمایش بیشتر4 477
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+117 روز
+1030 روز
آرشیو پست ها
በሐጂ አደም ሳዶ ሀገር ባሌ የሚገኘው መዳ ወላቡ ዩኒቨርስቲ የሚማሩ ሙስሊም ተማሪዎች "Niqaaba ni uffanna barnootas ni baranna - ኒቃቧን እንደለበሰች ትማራለች።" - በማለት መልዕክታቸውን አድርሰዋል። "Justice for AAU Muslim Students!" - ሲሉም ድምፃቸውን አሰምተዋል።
ጥያቄው የሁሉም ሙስሊም ተማሪ ነው። ጥያቄው የሕዝበ ሙስሊሙ ነው። ጥያቄያችን በመመሪያ የተጣሰው መብታችን በመመሪ ይፅና ነው። ኒቃብ መልበስ መብት ነው። ኒቃብን መከልከል እስልምናን መንካት፤ ሙስሊሞችን ከትምህርት ማገድ ነው። ሙስሊም ደግሞ እስልምናው ሲነካ ዝም ብሎ አያይም። በሁሉም መንገድ ስለመብቶቻችን መጠየቃችን ግድ ነው። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!
@aaumsu
ስለ ኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች ፈተና እና መፍትሔ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፕሬዚዳንት ሙሐመድአሚን ካሳው በሁዳ መልቲሚዲያ ውይይት አድርጓል። ሊንኩ https://youtu.be/eM0omRXNjIM?si=lKtxA0iK3NW96kMO ነው። በደንብ ያዳምጡ። የቤት ስራዎንም ይውሰዱ። ለሌሎችም ያሰራጩ።
ባለፈው ሳምንት _ በወሎ ዩኒቨርስቲ ከተደረገ የጁምዓ ኹጥባ !
"የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ፕሮጀክት ተመልከቱ። መራቆትን ባህል አድርገው እንደ ምዕራባውያን ካልሆናችሁ እያሉ ነው። ጉዳዩ የባህል ከሆነ ለምን የአፋር እና ሶማሌን ባህል አያከብሩም? ኒቃብ ለአፋር ባህሉ ነው። ኒቃብ ለሶማሌ ባህሉ ነው።"
@aaumsu
ተለቋል!
እንደ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች እየደረሰብን ያለውን የመብት ጥሰት በመታገል ረገድ አሁናዊ ሁኔታን በደንብ የሚገልፀው ፖድካስት ተለቋል።
ሊንክ https://youtu.be/OLd-8QipP2k?si=JhpcMx-4MoqCpmnE ነው። ለሌሎችም ያድርሱ።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
+1
የመቱ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት ያወገዘ ሲሆን የሚከተሉትን መልዕክቶችንም አስተላልፏል።
ለAAU ሙስሊም ተማሪዎች፦ እየጠየቃችሁ ያላችሁት የእኛን፣ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን የጋራ ጥያቄ ነው። ሙስሊም እንደ አንድ አካል ነውና ወንድሞቻችሁ ባስፈለጉበት ጊዜ እና ቦታ ሁሉ ከጎናችሁ መሆናቸውን እወቁ።"
ለፌደራል መጅሊስ፦ ከ9 ቀናት በፊት የፌደራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም የዩኒቨርስቲውን ፕሬዚዳንት ጨምሮ የሚመለከታቸውን አካላት አናግረው መፍትሔ ለማምጣት እንደተስማሙ ቢገልፁም እስካሁን ድረስ መፍትሔ የሚሆን ነገር አላየንም። ስለሆነም መጅሊሱ ሀላፊነቱ እንደሆነ በቁርጠኝነት ወስዶ አስቸኳይ እና ፍትሐዊ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ እንዲሰራ ጥሪያችን ነው።
ለመንግስት፦ ሙስሊም ተማሪዎች በሰላማዊ መንገድ ለጠየቁት ጥያቄ ውይይትን መሠረት ያደረገ፤ ሕግ እና ስርዓትን የተከተለ እንዲሁም አጥፊዎችን ተጠያቂ የሚያደርግ መፍትሔ እንዲመጣ ይሰራ ዘንድ ጥሪያችን ነው።
ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
ጥያቄው የሕዝበ ሙስሊሙ ነው !
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! !
@aaumsu
Barattoonni Musliimaa Yuunivarsiitii Mattuu ibsa jabaa baasaniiru. Ibsa kanaan sarbiinsa mirgaa barattoota Musliimaa Yuunivarsiitii Finfinnee (AAU) irratti raawwatamaa jiru balaaleffachuun, ergaa armaan gadii dabarsaniiru:
Barattoota Musliimaa AAU’f: "Gaaffiin isin gaafachaa jirtan gaaffii waliinii keenya fi kan Musliimota Itiyoophiyaa hundaati. Musliimni akka qaama tokkooti, kanaafuu obboloonni keessan yeroo fi bakka isaan barbaachisetti isin cinaa akka jiran beekaa."
Majliisa Federaalaaf: "Guyyoota 9 dura Pirezidaantiin Majliisa Federaalaa Sheek Haajii Ibraahim, Pirezidaantii Yuunivarsiitii dabalatee qaamolee dhimmi ilaallatu waliin dubbatanii furmaata fiduuf akka walii galan ibsanis, hanga ammaatti furmaata tokkollee hin agarre. Kanaafuu, Majliisni kun itti gaafatamummaa isaa kutannoodhaan fudhatee, furmaatni ariifachiisaa fi haqni akka dhufu akka hojjetu waamicha keenya ni dhiyeessina."
Mootummaaf: "Barattoonni Musliimaa gaaffii karaa nagaatiin dhiyeessaniif, furmaata marii irratti hundaa'e, seeraa fi sirna kan hordofe, akkasumas warra balleessaa raawwatan itti gaafatamoo kan taasisu akka fidu waamicha keenya ni dhiyeessina."
Gaaffichi kan uummata Musliimaati!
Gaaffii qabna — Hanga furmaata haqaa argannutti!
@aaumsu
ጥያቄ አለን (ከኮሜንት ማህደር የተወሰደ) !
«ጥያቄ አለን!» ብለን ስንነሳ፥ ይህ ጥያቄ ለተተኪዎቻችን ጥያቄ እንዳይሆን በማሰብ ነው።... የሆነ ጊዜ ሙስሊም መሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ጥያቄ ሆኖ ያውቃል፥ ዛሬ ላይ እኛ ራሳችንን በሙስሊም ኢትዮጵያዊነት ስንገልጽ በኩራት ነው። ይህ የቀደምቶቻችን የትግል ውጤት ነው። «ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሙስሊሞች» የሚልን ስያሜ ባለመቀበል ታግለው፥ ኢትዮጵያዊ ያለመባልን ዕዳ ለኛ ባለማውረሳቸው ገና ሀገር ሲባል ልባቸው የሚመታ፣ ሰንደቋን ሲመለከቱ እንባ የሚቀድማቸው፣ ቀን ሌት ለእድገቷ የሚታትሩ፣ ከአንገታቸው ቀና ያሉ ኢትዮጵያውያን "እኛዎች" ተፈጥረናል። ዛሬም ተመሳሳይ ነው። መረገጥን፣ ባርነትን፣ ጎንበስ ማለትን ለልጆቻችን አናወርስም። ኒቃብ የቀጣዩ ትውልድ የቤት ሥራ አይሆንም። ተወደደም ተጠላ፥ ይህ ዕዳ የኛ ነው። ከጨቋኞች የተረፈውን እኛው ራሳችንም ቢሆን ከፍለነው ሂሳቡን መዝጋት የግድ ግድ ነው። ... ሌሎች የቀሩ ሥራዎቹን ከመስራት ይህ አጀንዳ የማያደናቅፈው «ነጻ» ትውልድ እንፈጥራለን።
©️ aaumsu
@EHEMSU
+1
በአባጅፋር ሀገር ጅማ የሚገኘው የጅማ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫው፦
"ይህ ጉዳይ መቆየቱ እና አለመፈታቱ በአስተዳደሩ ዘንድ መፍትሔ ለማበጀት ፍላጎት እና ቁርጠኝነት እንደሌለ የሚያመላክት ሲሆን፤ በሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ ያነጣጠረ ስልታዊ መድልዎ እንዳለ ያሳያል። በሀገሪቱ በተደረጉ ረጅም ጥረቶች ውስጥ ዋና ሚና የነበረው ይህ ዩኒቨርስቲ ፤ ለሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ ዘላቂ መፍትሔ ማግኘት ሳይችል መቆየቱ እና ከመፍትሔ ይልቅ መከልከልን እርምጃ አድርጎ መውሰዱ ከባድ ተቋማዊ ድክመትን ያሳያል።" - በማለት የተጠቀሰ ሲሆን መመሪያው ተሻሽሎ ዘላቂ መፍትሔ ይሰጥ ዘንድ ተጠይቋል።
ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል። ለሁሉም ይደርስ ዘንድም አሰራጩት። ከጀሰዲን ዋሂድ ሲኮን እንዲህ ነው። ቀጣይ እርምጃስ ምን ይሆን? ከየትስ ይሆን?
@aaumsu
+1
"Barataan tokkollee amantii isaa fi barnoota isaa gidduutti akka filatu dirqamsiifamuu hin qabu."
Jama'aan Barattoota Muslimaa Yuunivarsiitii Jimmaa (JUMJ) dhimma dhorkaa Niqabaa obboleettota keenya kan Yuunivarsiitii Finfinnee irra ka'e ilaalchisee ibsa baaseera.
Amantiin keenyaa fi barnoonni keenya gonkumaa wal-faalleessuu hin qaban.
Ibsichi guutuun isaa armaan olitti maxxanfameera.@aaumsu
+1
የመዳ ወላቡ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት አስመልክቶ የአቋም መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫው በሙስሊም ተማሪዎች ላይ አድልዎ የሚፈጥረው መመሪያ መውጣቱን ተከትሎ የደረሰው እንግልት አግባብነት እንደሌለው በመግለፅ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ትኩረት ሰጥቶ በማየት እና ጣልቃ በመግባት የሐይማኖት ነፃነት መብትን ያስከብር ዘንድ ጠይቋል።
፨ ጥያቄው የሁሉም ሙስሊም ተማሪዎች ነው። ጥያቄው የሕዝበ ሙስሊሙ ነው። ጥያቄው በሰብዓዊ መብቶች መረጋገጥ የሚያምን ሰብዓዊ ፍጡር ሁሉ ነው። ስለእስልምና ብዙ በተከፈለበት ባሌ ከሚገኘው መዳወላቡ ዩኒቨርስቲ ጀመዓ መግለጫም የተረዳነው ይህንን ነው። የአንድ ሙስሊም ጉዳይ የሁሉም ሙስሊም ነውና በዚህ ልክ እንድንቆም ሆነናል። አልሐምዱሊላህ!
ጥያቄያችን ጨቋኙ መማሪያ ይሻሻል ነው። ጥያቄያችን መመሪያው ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ለ19 ወራት ያክል በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እንግልት የፈፀመው በዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ፕሬዚዳንትነት የሚመራው የዩኒቨርስቲው አመራር በሕግ አግባብ ይጠየቅ ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
የፌደራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ በአዲስ አበባ ከተማ የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ያደረጉትን ንግግር አስመልክቶ የቀረበ ዝርዝር መግለጫ።
ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ከሆኑ ቡሃላ የሕዝበ ሙስሊሙ ማንነት እና ክብር መገለጫ የሆነውን ኒቃብ የሚከለክልን መመሪያ በማውጣት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ለ19 ወራት ያክል የመብት ጥሰት ሲፈፀም እንደቆየ የአደባባይ ሐቅ ነው። ክልከላው ከሴኩላሪዝም ጋር በተያያዘ ፤ ከደህንነት እና ፀጥታ ጋር በተገናኘ ፤ በመማር ማስተማር ወቅት በመምህር እና ተማሪ ጋር ሊኖር ከሚገባ ግንኙነት ጋር በተገናኘ ከመሆኑም ባሻገር ለዚህ ሲባል በሕገ- መንግስቱ የፀደቁ የነፃነት መብቶችን መገደብ እንደሚችሉ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ በተለያየ ጊዜ ራሳቸው ዶክተር ሳሙኤል እንደገለፁም እሙን ነው።
በመመሪያው የሰፈረው እና እርሳቸው በተናገሯቸው ንግግሮች ውስጥ የተቀመጡት ምክንያቶች የሌለን ነገር በመፍጠር ስጋት ለማድረግ ከመሞከራቸው ባሻገር ከሕግ፣ አመክንዮ፣ ኢትዮጵያዊ እሴቶች እና ተለምዷዊ አሰራሮች ያፈነገጡ መሆናቸውን በተደጋጋሚ እየገለፅን አስቸኳይ ማስተካከያዎች ተደርገው መመሪያው እንዲሻሻል እና በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው በደል ይቆም ዘንድ ስንጠይቅም ነበር። ጥያቄውን ባቀረብን ወቅት የተፈጠረውን ችግር በውይይት ለመፍታት እርሳቸው ባሉበት መንገድ የተጀመረ ቢሆንም መፍትሔ ሊመጣ በተቃረበበት ወቅት ግን እንደ ሙስሊም ተማሪ የውይይቱ አካል የነበሩትን ተወካዮች አናውቃችሁም በማለት የውይይቱ በር መዘጋቱ ይታወሳል። ከዚያም ቡሃላ ደብዳቤዎችን አንቀበልም ብሎ ከመመለስ ጀምሮ የተቀበሉት ደብዳቤ ላይ ስርዝ አድርጎ አናውቃችሁም የሚልን ፅሁፍ ፅፎ እስከመመለስ ተደርሶ ነበር።
በእነዚህ ሂደቶች ውስጥ የሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ በሕገ- መንግስቱ የፀደቁትን የሐይማኖት ነፃነት እና እኩልነት መብትን በመጣስ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት፣ ክብር፣ እምነት እና ማንነት የሚጣረስ እና የሚጎዳ መመሪያ ስለወጣ በውይይት ይሻሻል፤ በመመሪያው ምክንያት እንግልት ለደረሰባቸው ተማሪዎች ፍትሕ ይፅና ቢሆንም የውይይትን በር ዘግተው እስካሁን አሉ። በተለያዩ ጊዜያቶች በነበሩ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ከአዲስ አበባ የፀጥታ ክፍል እና የብልፅግና ሀላፊዎች ጋር በነበረን ውይይት እነርሱ ባሉበት ከዶክተር ሳሙኤል ጋር ውይይት እንደሚደረግ የገለፁልን ቢሆንም፤ በሰዓቱም እራሳቸው ዶክተር ሳሙኤል ለውይይት እንደሚቀርቡ እንደገለፁላቸው ቢያስቀምጡልንም ቀኑ ሲደርስ ግን እምቢ ብለዋል በሚል ምክንያት ውይይቱ ሳይደረግ ቀርቷል።
የፌደራል መጅሊስ ችግሩ ከተፈጠረ ከ19 ወራት ቡሃላ ከዶክተር ሳሙኤል እና ከሌሎች አመራሮች ጋር ተወያይቶ ችግር እንደማይፈጠር በቃል እንደተገለፀላቸው በፌደራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ በኩል የተገለፀ ቢሆንም እስካሁን ከነበሩት ሁኔታዎች፤ ከተፈጠሩ ችግሮች፤ የዩኒቨርስቲያችን ፕሬዚዳንት ብለውታል እየተባለ ካልተፈፀሙ ቃሎች አንፃር የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ልዑክም በዚያው ዕለት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም እና ከመጅሊሱ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ባደረገው ስብሰባ "ብቸኛው እና የመጨረሻው መፍትሔ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ አድልዎ የሚፈጽመው መመሪያ እንዲሻሻል ማድረግ ብቻ ነው" የሚለውን ጽኑ አቋሙን በግልጽ አስቀምጧል። በዚህም መሰረት በመጅሊሱ እና በህብረቱ ተወካዮች መካከል በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ስምምነት ተደርሷል፦
1ኛ፦ ዩኒቨርስቲው ያወጣው ጨቋኝ መመሪያ በቶሎ እንዲስተካከል መጅሊሱ በቁርጠኝነት እንዲሰራ
2ኛ፦ መመሪያው ከወጣበት ጊዜ አንስቶ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የመብት ጥሰት የፈፀሙ የዩኒቨርስቲው አካላት በሕግ አግባብ ይጠየቁ ዘንድ መጅሊስ እና ህብረቱ በቅንጅት እንዲሰሩ።
3ኛ፦ ከዩኒቨርስቲው ጋር ያለው ግንኙነት ይቀጥል ዘንድ ከመጅሊሱ የሚወከሉ ተወካዮች ከተማሪዎች ጋር በመሆን ከዩኒቨርስቲው ጋር እንደሚወያዩ
4ኛ፦ በሀገርአቀፍ ደረጃ ዘላቂ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ በመጅሊስ ከተቋቋመው 17 ኮሚቴ ጋር ተማሪዎች በቅርበት እንዲሰሩ
ይህ በእንዲህ እንዳለ እስካሁን ባለው ሂደት የተፈጠሩ ችግሮችን በማረም እና ማስተካከል ረገድ ከዩኒቨርስቲው አመራሮች በኩል ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳልተደረገ ለማሳወቅ እንወዳለን። በተቃራኒው ግን በሚያዚያ 12 / 2018 ዓ.ል ዩኒቨርስቲው ችግሮችን ለመፍታት ፍቃደኛ ነኝ ባለበት ቀን ችግራቸውን በማስረዳት መፍትሔ ፍለጋ ከተማሪዎች ዲን ጽ/ቤት የሄዱ 13 ሙስሊም ሴት ተማሪዎችን አግባብነት የሌለውን ምላሽ በመስጠት መልሷቸዋል። በዚህ ውስጥ ከዩኒቨርስቲው አመራሮች በኩል የተፈጠሩትን ችግሮች በውይይት እና ቁርጠኝነት ለመፍታት ቅንነት እንደሌለ መረዳት እንችላለን። ስለሆነም ለ19 ወራት ያክል ሕገ- መንግስታዊ መብቶችን በመጣስ በወጣ መመሪያ ምክንያት ሲፈፀሙ የነበሩ የመብት ጥሰቶች እንዳልተፈቱ እና መፍትሔ እንዳልመጣ ሁሉም አካል ሊያውቅ ይገባል። ዘላቂ መፍትሔ በአጭር ሰዓት መጥቶ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ ያበቃ ዘንድ ሁላችሁም በያላችሁበት በዱዓ ታስታውሱን ዘንድ አደራችን ነው። ስለሆነም፦
ለፌደራል መጅሊስ፦ የተጀመረውን ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ አጠናክሮ በመቀጠል በጥቂት ቀናት ውስጥ አስተማማኝ መቋጫ እንዲሰጠው ኃላፊነቱን እንዲወጣ በድጋሚ እንጠይቃለን።
ለመንግስት ተቋማት፦ ከዚህ በፊት የችግሩን ጥልቀት ገልፀን የመፍትሔ አካል ይሆኑ ዘንድ በደብዳቤ ያሳወቅናቸው የሰላም ሚኒስቴር፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዲሁም የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን እና ሌሎች ተቋማት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እናሳስባለን።
ለሚዲያ ተቋማት (EBC, Fana, AMN, NBC ወዘተ)፦ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች እየደረሰባቸው ስላለው በደል በመግለፅ ድምፃቸውን ለሕዝቡ በማድረስ የሚዲያ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ተሰባስበው በመሄድ የጠየቋችሁ የሚዲያ አካላት እስካሁን ላሳያችሁት ዳተኝነት ራሳችሁን እንድትፈትሹና ለፍትሕ እና ለእውነት ድምጽ እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ጥያቄው የሁላችንም ነው!
ጥያቄ አለን!!
ፍትሐዊ መልስም እንፈልጋለን !!!
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ! ! !
AAU፦ ኒቃብሽን አውልቂ
ተማሪዋ፦ አላወልቅም። ለምን አውልቂ እንዳልክ ግን ጥያቄ አለኝ!!
ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት መሆናቸውን ተከትሎ የሙስሊሞች ማንነት እና ክብር የሆነውን ኒቃብ ከመማር ማስተማር እና አገልግሎት ጋር ይጋጫል በማለት ይከለከል ዘንድ መመሪያ አውጥተው ላለፉት 19 ወራት ያክል በኒቃቢስት ተማሪዎች ላይ ግፍ እና በደል ተፈፅሟል።
ኒቃቢስት ተማሪዎችም ባለፉት 19 ወራት ውስጥ የደረሰባቸውን በደል በሙባረክ ፖድካስት በዝርዝር አቅርበዋል። ግቡና ተመልከቱት። ድምጿ ይሰማ ዘንድም ለሁሉም አሰራጩት።
ሊንኩ https://youtu.be/CuafDziz2ss?si=OIJeGNwIgQWhpxOW ነው።
ጥያቄያችን ለዚህች ልጅ እምባ መፍሰስ መሠረቱን የጣለው መመሪያ ይሻሻል ነው። ጥያቄያችን ለዚህች ተማሪ እምባ መፍሰስ ምክንያት የሆነው የዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ አመራር ተጠያቂ ይሁን ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ዩኒቨርስቲው በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እያደረሰ ባለው የመብት ጥሰት ዙሪያ የፍትሕ ሚኒስቴር አስቸኳይ የሕግ ጣልቃ ገብነት እንዲያደርግ ጠየቀ ! ! !
--------------------------------------
ሚያዚያ 12 / 2018 ዓ.ል
--------------------------------------
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፍትሕን የሚያጓድል መመሪያ አውጥቶ ለ19 ወራት ያክል በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የመብት ጥሰት ሲፈፅም እንደነበር ይታወቃል። ፍትሕ ይሟላ ዘንድም ሙስሊም ተማሪዎች ያለፉትን ጊዜያት በሰላማዊ መንገድ ደጋግመው ለመጠየቅ ቢሞክሩም በዶክተር ሳሙኤል ፕሬዚዳንትነት የሚመራው የዩኒቨርስቲው አመራር የውይይት በርን ዘግቶ በበደሉ ላይ ቀጥሏል። የፍትሕ ሚኒስቴር የሕግ የበላይነትን የማረጋገጥ እና የዜጎችን ሕገ-መንግስታዊ መብቶች የማስከበር ያለበት ተቋም እንደመሆኑ አስቸኳይ የሕግ ጣልቃ ገብነት አድርጎ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዲያስቆም እና ኢ- ሕግመንግስታዊው መመሪያ እንዲሻሻል አስተዋፅዖ እንዲያደርግ ተጠይቋል።
ጥያቄ አለን _ መልስም እንፈልጋለን !
@aaumsu
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ዩኒቨርስቲው በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እያደረሰ ባለው የመብት ጥሰት ዙሪያ የትምህርት ሚኒስቴር አስቸኳይ የሕግ ጣልቃ ገብነት እንዲያደርግ ጠየቀ ! ! !
--------------------------------------
ሚያዚያ 12 / 2018 ዓ.ል
--------------------------------------
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሙስሊም ተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት በመጋፋት የሐይማኖት ነፃነት መብታቸውን የሚጋፋ መመሪያ አውጥቶ ላለፉት 19 ወራት ተማሪዎችን ለእንግልት እና ለስነ-ልቦና ጫና ሲዳርግ እንደቆየ ይታወቃል። ይህንን ተከትሎም ሙስሊም ተማሪዎች የተፈፀመው የመብት ጥሰት ቆሞ ተማሪዎች ነፃነታቸው ተከብሮላቸው ይማሩ ዘንድ ተደጋጋሚ ጥሪዎችን ቢያደርጉም አሻፈረኝ በማለት ለተማሪዎቹ ቅሬታ ጆሮዳባ ልበስ ብሏል።
የውይይት በር መዘጋቱ የመብት ጥሰቶቹ ተደጋግመው እንዲፈፀሙ መደላድል ከመስጠቱ ባሻገር ተማሪዎችን አላስፈላጊ ለሆኑ ጫናዎች እየዳረገ ነው። ይህ በቶሎ ቆሞ ችግሮች በውይይት ይፈቱም ዘንድ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በዛሬው እለት ለትምህርት ሚኒስቴር ደብዳቤ አስገብቷል። በደብዳቤውም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፦
1ኛ፦ የዩኒቨርስቲው አድሏዊ መመሪያ የዜጎችን የመማር መብትና ሕገ- መንግስታዊ ነፃነት በሚፃረር መልኩ የወጣ በመሆኑ፤ በአስቸኳይ እንዲነሳና መመሪያው እንዲሻሻል ጥብቅ ትዕዛዝ እንዲሰጥ።
2ኛ፦ ዩኒቨርስቲው ለደህንነት ፍተሻ ያቀረብናቸውን ዘመናዊ እና ሐይማኖታዊ መብትን የማይጋፉ አማራጮች ተግባራዊ እንዲያደርግ ግፊት እንዲደረግ
3ኛ፦ ኒቃብ ለባሽ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ሳይሰተጓጎሉ እኩልነታቸው ተከብሮ እንዲማሩ ክትትል እንዲደረግ
ተጠይቋል።
ጥያቄ አለን _ መልስ እንፈልጋለን !
@aaumsu
ኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ ለሁሉም ኢማሞች፣ ዱዓቶች፣ ኡስታዞች እና መሻይኾች መልዕክቱን አድርሱልን _ የመጪውን ጁምዓ ኹጥባ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኒቃባቸው ምክንያት የመብት ጥሰት እየደረሰባቸው ስላሉ ሙስሊሞች እንዲያደርጉ ! ! !
የአንድ ሙስሊም ጉዳይ የሁሉም ሙስሊም ጉዳይ ነው። ሙስሊም እንደ አንድ አካል ነውና አንዱ ክፍል ሲታመም ሌላውም አካል ሕመሙን ያስተጋባል። ሙስሊም እንደ አንድ ግንብ ነውና እርስ በዕርሱ ይጠነካከራል። ለዚህም ሲባል በሁሉም መስጂዶች ኹጥባው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ይሆን ዘንድ ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በደብዳቤ ጠይቀናል።
ስለሆነም ኡስታዞች፣ መሻይኾች፣ ዱዓቶች እና ኢማሞች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መብታቸው ሙስሊም ስለሆኑ ብቻ መብታቸው እየተጣሰባቸው ስላሉ ተማሪዎች በማድረግ ሀላፊነታችሁን ትወጡ ዘንድ በአላህ ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
"የሙስሊም ምሳሌው ... ልክ እንደ አንድ አካል ነው። የሆነ ክፍሉ ሲታመም ሌላው ክፍል እንቅልፍ በማጣት እና በትኩሳት ይጣራል።" - ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም)
@aaumsu
+1
የወራቤ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት በማውገዝ መግለጫ ያወጣ ሲሆን "የሙስሊሙ መሪ ተቋም የሆነው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ዙሪያ ይፋዊ አቋሙን በማስቀመጥ፤ ዘላቂ መፍትሔ ይመጣ ዘንድም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር አስቸኳይ እልባት ያመጣ ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን።" - ሲል ጠይቋል።
ሙሉ መግለጫውን ከተያያዘው ምስል ያንብቡ። ለሌሎችም ሼር ያድርጉ።
"ሙስሊም ምንድን ነው ያደረጋችሁ? እዚሁ እኛው ከተማ አዲስ አበባ ውስጥ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሚማሩ ሙስሊም ሴቶች ኒቃባችሁን አውልቁ ተብለዋል። ፀጉሯን ለቃ በሱሪ ተወጣጥራ የምትሄድ ሴት መብቷ ተከብሮ ለአላህ ብላ ሰውነቷን የሸፈነች ሴት እንዴት ትከለከላለች? የተቀመጣችሁበት ወንበር ለፍትሕ ከሆነ ይሄንን ልብ ልትሉ ይገባል። ወደሗላ ዞር ብላችሁም ታሪክን ተመልከቱ። ሩቅ ሳትሄዱ ትላንት 2003 / 2004 ሲያስሩ ሲገድሉ ሒጃብ ሲገፉ የነበሩ ሰዎች የት ነው ያሉት? አያቶቻችሁ የት ነው ያሉት? መሪዎቻችሁ የት ነው ያሉት? ትላንት አንደፈርም ጉልበት አለን ሲሉ የነበሩ ሰዎች ዛሬ ስልጣናቸው አለ?" - ኡስታዝ ሙሐመድ ኸዲር
@aaumsu
"እስከዛሬ ስናናግረው የነበረ ግቢ የእስከዛሬው ተረስቷል ከአሁን ቡሃላ አንዳንድ እየሆናችሁ አናግሩን የሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የሚባል አናውቅም እያለ ነው።"
በዘመቻችን፦ https://vt.tiktok.com/ZSHcGsQTx/ በመግባት ኮሜንት ማድረግ እና ለሌሎች ማሰራጨት እንዳይዘነጋ።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
