cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

የቅዱሳን ታሪክ

ሰማያት የእግዚአብሔር ክብር ይገልፃሉ

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
1 706
مشترکین
+624 ساعت
+567 روز
+14730 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

አንተ ሰው ቃለ እግዚአብሔር ስትማር  ባትለወጥም ዝም ብለህ ተማር  ሁልጊዜ ተማር  ላትስተካከል ትችላለህ ላትለወጥም ትችላለህ  ግን ተማር  ቢያንስ ቢያንስ ጥሩ ሰው ባትሆንም ራስህን ለመውቀስ የምትችልበት አቅም ታገኛለህ  ካልተማርክም ራስህን የመውቀስ አቅም አታገኘም።ስለዚህ ተማር ሀጢአት ስትሰራ ራስህን ትወቅሳለህ እቺ ደግሞ የንሰሀ በር ትሆንሃለች።እቺ ደግሞ ንስሀ እንድትገባ ትረዳሃለች። ቅዱስ የሕንስ አፈወርቅ
نمایش همه...
ብሂለ አበው

በዚሁ ቻናል የቤተ ክርስቲያን ብሂለ አበው መንፈሳዊ ጥያቄዎች ይቀርብበታል።

🙏 10
እጅህ ላይ ባለው ነገር ከታመንህ እግዚአብሔር አምላክ በእጁ ውስጥ ያለውን ነገር ይሰጥሃል። በውስጥህ ያለውን አቅም መጠቅም ከቻልህ እግዚአብሔር የአንተ ያልሆነ ተጨማሪ አቅም ይሰጥሃል። ከእግረኞች ጋር ሳትደክም እኩል መራመድና መቅደም ከቻልህ እግዚአብሔር ፈረስን ለውድድር ይሰጥሃል። ኤር 12፥5 የሚታዩ ኃጢአቶችን ለመዋጋት ታምነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር የተሸሸጉና የማይታዩ ኃጢአቶችን ድል እንድትነሣ ይሾምሃል። በሕፃንነትህ ፣ በልጅነትህ ለእግዚአብሔር የታመንህ ሆነህ ከተገኘህ እርሱ በወጣትነትህ በምታደርገው ውጊያ ውስጥ ታማኝነትን ያድልሃል። ልያን ለመቀበል ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር ራሔልን ሚስት አድርገህ ታገባት ዘንድ ይሰጥሃል። ዘፍ 29:27 በሲና ምድረ በዳ ለመቀመጥ ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር አምላክ የተስፋይቱን ምድር ከነዓንን ያወርስሃል። በዚህ በተወሰነና አጭር ሕይወት ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር መጨረሻ የሌለውን ዘላለማዊ ሕይወት ያድልሃል። ትልቁ ቁም ነገር በእጅህ ውስጥ የገባው ነገር ትንሽም ይሁን ጥቂት በእርሱ መታመን መቻልህ ነው። ስለሆነም ባለህ አንድ መክሊት ታምነህ ስትገኝ እግዚአብሔር አምስት መክሊቶችን በአደራ ይሰጥሃል። አንተ በሚታዩት ነገሮች ላይ ታማኝ ሆነህ ስትገኝ እርሱ በማይታዩት ነገሮች ላይ ይሾምሃል። በመሆኑም ዓይን ያላየችውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልብ ያልታሰበውን መንግሥቱን ያወርስሃል። 1ኛ ቆሮ 2፥9 መንፈሳዊው መንገድ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ እንደ ጻፉት አያሌው ዘኢየሱስ እንደተረጎመው። https://t.me/kidesthaymanot
نمایش همه...
6🙏 1
Photo unavailableShow in Telegram
🙏 11
#ሰኔ_24 #ኢትዮጵያዊው_ቅዱስ_አባ_ሙሴ_ጸሊም ሰኔ ሃያ አራት በዚች ቀን አባ ሙሴ ጸሊም በሰማዕትነት ሞተ። ሰዎች ከገድሉ የተነሣ ይህን ቅዱስ ያደንቁታል እርሱ አስቀድሞ መንግሥተ ሰማያትን ገፍቷት ነበረና እርሱ በሥጋው ጠንካራ በሥራውም ኃይለኛ ነበር ይበላና ይጠጣ ይቀማና ያመነዝር ነበር ይገድልም ነበር ማንም ሊቋቋመው አይችልም ነበር።  አንድ በግ በአንድ ጊዜ ጨርሶ እንደሚበላና አንድ ፊቀን ወይን ጠጅ እንደሚጠጣ ስለ እርሱ ተነግሮአል። እርሱም ፀሐይን ለሚያመልኩ ሰዎች አገልጋይ ነበረ ብዙ ጊዜም ወደ ፀሐይ እያንጋጠጠ ፀሐይ ሆይ አንተ አምላክ ከሆንክ አነጋግረኝ ይል ነበር ደግሞም በልቡ የማላውቅህ ሆይ ራስህን አሳውቀኝ ይል ነበር።  ከዚህም በኋላ በአስቄጥስ ገዳም ያሉ መነኰሳት እግዚአብሔርን ያውቁታል ያዩታልም እያሉ ሲነጋገሩ ሰዎችን ሰማቸው። ያን ጊዜም ተነሣ ሰይፉንም ታጥቆ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደ በደረሰም ጊዜ አባ ኤስድሮስን አገኘው። አባ ኤስድሮስም ፈራው ሙሴ ጸሊምም እውነተኛውን አምላክ ታሳውቁኝና ታስረዱኝ ዘንድ ወደ እናንተ መጣሁ አለው። አባ ኤስድሮስም ወደ አባ መቃርስ ወስዶ አገናኘው።  እርሱም ተቀብሎ ሃይማኖትን አስተማረው እንዲህም አለው ታግሠህ የማስተምርህን ከጠበቅህ እግዚአብሔርን ታየዋለህ። ከዚህም በኋላ የክርስትና ጥምቀትን አጥምቆ አመነኰሰው ከብዙዎች ገድለኞች ቅዱሳን ይልቅ ብዙና ጽኑዕ ገድልን መጋደል ጀመረ።  ሰይጣንም ቀድሞ ሲሠራው በነበረ በመብሉና በመጠጡ በዝሙቱም ይዋጋው ነበረ እርሱም በራሱ ላይ የሚደርስበትን ሁሉ ለአባ ኤስድሮስ ይነግረው ነበር እርሱም አጽናንቶ ሊሠራው የሚገባውን ያስተምረው ነበር።  ከገድሉ ብዛትም የተነሣ አረጋውያን መነኰሳት በሚተኙ ጊዜ ቤቶቻቸውን በመዞር ውኃ መቅጃዎችን ወስዶ ውኃ መልቶ በየቤታቸው ደጃፍ ያኖር ነበር። ውኃው ከእነርሱ ሩቅ ነበረና እንዲህም እያደረገ በመጋደል ለብዙ ዘመናት ኖረ።  ሰይጣንም በእርሱ ቀንቶ በእግሩ ውስጥ አስጨናቂ የሆነ አመታትን መታው ተኝቶም እየተጨነቀ ብዙ ቀን ታመመ። ከዚህም በኋላ የመታውና የሚፈታተነው ሰይጣን እንደሆነ ዐውቆ ሥጋው በእሳት ተለብልቦ እንደ ደረቀ ዕንጨት እስቲሆን ድረስ ተጋድሎውንና አገልግሎቱን አበዛ። እግዚአብሔርም ትዕግስቱን አይቶ ከደዌው ፈወሰው የሰይጣንንም ጦር ከእርሱ አራቀለት የመንፈስ ቅዱስም ጸጋ አደረበት ወደርሱም አምስት መቶ ወንድሞች መነኰሳት ተሰበሰቡ በእነርሱም ላይ አበ ምኔት ሆነ።  ከዚህ በኋላ ቅስና ሊሾሙት መረጡት በቤተ መቅደስም በሊቀ ጳጳሳቱ ዘንድ በአቆሙት ጊዜ ሊቀ ጳጳሳቱም አልፈቀደም ነበር አረጋውያኑንም ይህን ጠቋራ ለምን አመጣችሁት ከዚህ አውጡት አላቸው እርሱም መልክህ የከፋ ጠቋራ ሆይ መልካም አደረጉብህ በማለት ራሱን እየገሠጸ ወጣ ከዚህ በኋላ ዳግመኛ ሊቀ ጳጳሳቱ ጠራውና እጁን በላዩ ጭኖ ቅስና ሾመው እንዲህም አለው ሙሴ ሆይ እነሆ በውስጥም በውጭም ሁለመናህ ነጭ ሆነ።  በአንዲትም ዕለት ቅዱሳን አረጋውያን ወደርሱ መጡ በእርሱም ዘንድ ውኃ አልነበረም እርሱም ከበዓቱ ብዙ ጊዜ ወጣ ገባ ይል ነበር ከዚህ በኋላም ብዙ ዝናም ዘንሞ ጕድጓዶችን ሁሉ ሞላ። አረጋውያንም ለምን ብዙ ጊዜ ወጣ ገባ ትል ነበር ብለው ጠየቁት እርሱም እግዚአብሔርን ውኃ ካልሰጠኸኝ ቅዱሳን አገልጋዮችህን ምን አጠጣቸዋለሁ እለው ነበር በቸርነቱም ዝናምን ልኮልን ውኃን አገኘን አላቸው።  በአንዲትም ዕለት አባ ሙሴ ከአረጋውያን ጋራ ወደ አባ መቃርስ ሔደ አባ መቃርስም የሰማዕትነት አክሊል ያለው ከእናንተ ውስጥ አንዱን እነሆ አያለሁ አላቸው አባ ሙሴም አባቴ ሆይ ምናልባት እኔ እሆናለሁ በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደል ዘንድ አለው የሚል ጽሑፍ አለና ብሎ መለሰ።  ከዚህም በኋላ የበርበር ሰዎች መጡ አባ ሙሴም ከእርሱ ጋራ ያሉትን መነኰሳት እነሆ የበርበር ሰዎች ደረሱ መሸሽ የሚፈልግ ይሽሽ አላቸው እነርሱም አባታችን አንተስ አትሸሽምን አሉት እርሱም በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደላል ስለሚለው የእግዚአብሔር ቃል እነሆ ያቺን ቀን ለብዙ ዘመናት ስጠብቃት ኖሬአለሁ አላቸው።  ወዲያውኑም የበርበር ሰዎች ገብተው በሰይፍ ገደሉት መሸሽ ስለ አልፈለጉ ከእርሱ ጋራ ሰባት መነኰሳትም ተገደሉ አንዱ ግን ከምንጣፍ ውስጥ ተሠወረ የእግዚአብሔርንም መልአክ አየ በእጁም አክሊል ነበር እርሱም ቆሞ ይጠብቅ ነበር። ይህንንም በአየ ጊዜ ከተሠወረበት ወጣ የበርበር ሰዎችም ገደሉት የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበለ።  ወንድሞች ሆይ ከሀዲና ነፍሰ ገዳይ ቀማኛና ዘማዊ የነበረውን ለውጣ ደግ አባት መምህርና የሚያጽናና ለመነኰሳትም ሥርዓትን የሠራ ካህን እንዳደረገችው በሁሉም አብያተ ክርስቲያን ስሙ እንዲጠራ እንዳደረገችው የንስሐን ኃይሏን ተመልከቱ። ሥጋውም በአስቄጥስ ገዳም ደርምስ በተባለ ቦታ ለዘላለም ይኖራል ከእርሱም ብዙዎች ድንቆችና ተአምራት ይታያሉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። (#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሰኔ)
نمایش همه...
6👍 1
እንኳን ለልዳዉ ሰማእት ለቅዱስ ጊዮርጊስ ወርሀዊ በዓል አደረሳችሁ
نمایش همه...
🙏 30
ሰይጣን መንፈሳዊ ሕይወትን ለመኖር ወስነህ ስትጀምር በእነዚህ ሁለት ሐሳቦች ይዋጋሃል። 1. አንተ ለዚህ ሕይወት እንደማትሆን እና መቼም እንደማትለወጥ ሹክ ይልሃል። ይህን የሚያደርገው ተስፋ ቆርጠህ የያዝከውን ሩጫ እንድታቆም ነው። የሚገርመው ግን መለወጥ ባትጀምር ኖሮ ሰይጣን “አልተለወጥህም” አይልህም። 2. ገና ከመጀመርህ የደረስህ እና ለመፈጸም ጥቂት የቀረህ አስመስሎ ያሳይሃል። ብዙ ርቀህ እንደ ሄድህ አስበህ ልክ እንደ ጥንቸሏ ተዘናግተህ እንድትተኛ እና የጽድቅ ነገር ሁሉ ጠላት የሆነው ትዕቢት እስረኛ እንድትሆን ያደርግሃል። አሁንም ሰይጣን “ደርሰሃል” እያለ ሲክብህ ገና እግርህን ለማንሣት የምትጣጣር እንደ ሆንህ አቅምህን በደንብ ያውቀዋል። ጀማሪ ስትሆን ሰይጣን “አትችልም” ብሎ ተስፋ በማስቆረጥ ወይም “ደርሰሃል” እያለ ያለ ልክ በማመስገን ወጥመዱ ውስጥ ሊጥልህ ይሞክራል። “በሰይጣን እንዳንታለል፤ የእርሱን አሳብ አንስተውምና”  2ኛ ቆሮ 2:11 ዲያቆን አቤል ካሳሁን
نمایش همه...
9🙏 3👍 1
አቅራቢ ፦ ✞ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍት 👇🏾📽 ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና የየዕለቱን ስንክሳር የምንልበት ቻነል ነው🖥👇🏾 ➮ከወደዱት ያጋሩ share & join    🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻 @religious_books_lover    🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔺 https://t.me/religious_books_lover
نمایش همه...
ገድሊ_ቅ_እንጦንዮስ.pdf62.99 MB
ሰኔ 21 ሰኔ ጎለጎታ ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማሪያምን በዚህ ቀን (ሰኔ21) ልጇን ወዳጇን ጎለጎታ ላይ ለኅጥአን ምህረትን ለምነዋለች ።ጌታችንም "ስምሽን የጠራዉን ፣በቃል ኪዳንሽ ያመነዉን ሁሉ እምረልሻለዉ " ብሏታል ።     የድንግል እመቤታችን ልመናዋ ክብራ ጣዕመ ፍቅሯን በረከቷን በሁላችንም ላይ ይደርብን   ወሰብሐት ለእግዚአብሔር
نمایش همه...
🙏 29
ሰኔ 21 ሰኔ ጎለጎልታ ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማሪያምን በዚህ ቀን (ሰኔ21) ልጇን ወዳጇን ጎለጎልታ ላይ ለኅጥአን ምህረትን ለምነዋለች ።ጌታችንም "ስምሽን የጠራዉን ፣በቃል ኪዳንሽ ያመነዉን ሁሉ እምረልሻለዉ " ብሏታል ።     የድንግል እመቤታችን ልመናዋ ክብራ ጣዕመ ፍቅሯን በረከቷን በሁላችንም ላይ ይደርብን   ወሰብሐት ለእግዚአብሔር
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
“በዚያ በጽርሐ አርያም የሚደነቅ ከማይታይ አብ የመወለድ ምስጋና አለው ፤ በዚህም በቤተ ልሔም ከድንግል የመወለድ ምስጋና አለው። በዚያ ከሰማያውያን ካህናት በወርቅ ማዕጠንት የዕጣኑን መዐዛ ይቀበላል ፤ በዚህም ወርቅን፣ ከርቤንና ዕጣንንም ከሰብአ ሰገል ተቀበለ ፤”              ✍️  አባ ጊዮርጊስ
نمایش همه...
💯 7
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.