ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
رفتن به کانال در Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
نمایش بیشتر670
مشترکین
-224 ساعت
+57 روز
+130 روز
آرشیو پست ها
ሐሙስ፦ እለተ ምሥጢር
➠ ምሥጢረ ጥምቀት ፦ ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ,ታጠቀ፤
በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ።
ወደ ስምዖን ጴጥሮስም መጣ፤ እርሱም፦ “ጌታ ሆይ፥ አንተ የእኔን እግር ታጥባለህን?” አለው።
ኢየሱስም መልሶ፦ “እኔ የማደርገውን አንተ አሁን አታውቅም፥ በኋላ ግን ታስተውለዋለህ፡” አለው።
ጴጥሮስም፦ “የእኔን እግር ለዘላለም አታጥብም፡” አለው። ኢየሱስም፦ “ካላጠብሁህ፥ ከእኔ ጋር ዕድል የለህም፡” ብሎ መለሰለት። ዮሐ ፲፫ ÷ ፬~፲
➠ ምሥጢረ ቁርባን ፦ ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና፦ “እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው፡” አለ።
ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ፦ ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።
ነገር ግን እላችኋለሁ፥ በአባቴ መንግሥት ከእናንተ ጋር ከዚህ ከወይን ፍሬ አዲሱን እስከምጠጣበት እስከዚያ ቀን ድረስ ከዛሬ ጀምሬ አልጠጣውም። ማቴ ፳፮ ÷ ፳፮~፴
➠ ሐዲስ ኪዳን ፦ ዓመተ ምህረት ብለን መቁጠር የጀመርን ክርስቶስ ከተወለደበት እለት ጀምሮ ቢሆንም ክርስቶስ ግን ያደገ ሕገ ኦሪትን እየፈጸመ ነው
ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤
እንደ ልጆች እንሆን ዘንድ፥ ከሕግ በታች ያሉትን ይዋጅ ዘንድ ገላ ፬÷፬
የበጉ የፈየሉ የላሙ የበሬው መሥዋዕት የስንዴው የወይኑ ቁርባን አለፈ ሁሉም በእርሱ መስዋዕትነት ተተካ
ከዚህ በፊት የነበረው መሥዋዕት መሥዋዕቱ ሌላ የሚሰዋው ሌላ የሚሰዋለት (ባለ ኃጢአቱ ) ሌላ የሚያስተሰርየው ኃጢአት ውጫዊ ለአባር ለቸነፈር ለመቅሰፍት ለመዓት እንጂ የነዘፍስን ኃጢአት አያስተሰርይም ከሲኦል አያላቅቅም ወደገነት አይመልስም ከውርስ ኃጢአት ከፍዳ ከመርገም አያድንም ነበር ።
ይህ ግን መሥዋዕቱ እራሱ የሚሰዋው ካህን እራሱ መሥዋዕቱን የሚቀበል እራሱ የሚሰዋበት ክህነቱ ባህርያዊ የሚያስተሰርየው ኃጢአት ውሳጣዊ በባህርይ ዘልቆ የገባ ነው ።
የሚሠዋ በግ እርሱ ነው (ሠን አጥብቅ) የሚሠዋ ካህን እርሱ ነው ከባህርይ አባቱ ከአብ ከባህርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ መሥዋዕቱን የሚቀበል እርሱ ነው ሃይ አበ ጎርጎ ፴፮ ÷ ፳፮
➠ ዕለተ ትሕትና ፦ የክርስቶስ ሰው መሆን ጠቅላላው ፍቅር ፈቃድ ትሕትና ነው ።
በአባቱ በእርሱ በመንፈስቅዱስ ፈቃድ ሰው ሆነ ውዳ ማር
ኃያል ወልድን ፍቅር ከዙፋኑ አወረደው ቅዳ ማር
እንደዚህ ያለ ትሕትና እንደምን ያለ ትሕትና ነው ዮሐ አፈ ቅዳ
በዚህ ምድር ሲመላለስ ግን በተለየ መልኩ በዚህ እለት መምህራቸውና ጌታቸው ሲሆን የደቀመዛሙርቱን እግር ዝቅ ብሎ ወገቡን አደግድጎ (ታጥቆ) አጥቧል
እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ፥ እንዲህም አላቸው፦ “ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም ይህን ብታውቁ፥ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ ዮሐ ፲፫ ÷ ፲፪~፲፰
➠ ዕለተ ጸሎት (ቤዛ አዳም) ፦ ክርስቶስ ዳግም አዳም ነው ቤዛ አዳም ነው ዳግም አዳምነቱ ንጹሐ ባህርይ ነው
ዳግማዊ አዳም ሆኜ ሞትሁ ሃይ አበ ቄር ፸፫ ÷ ፲፫
ቤዛ አዳምነቱ አዳም ሊያደርግ የሚገባውን አድርጓል
መጸለይ ነበረበት ጸልዮአል ደክሞ ነበር ደክሟል.....
ጠቅላላ ክስስቶስ ህየንተ አዳም ሆኖ የሰራው ስራ ሁሉ የቤዛነት ስራ ነው ማለደም ጮኸም አንቀላፋም .....ቢል የቤዛነት ስራ ነው ።
ጴጥሮስንም ሁለቱንም የዘብዴዎስን ልጆች ወስዶ ሊያዝን ሊተክዝም ጀመር ነፍሴ እስከ ሞት ድረስ እጅግ አዘነች፤ በዚህ ቆዩ ከእኔም ጋር ትጉ፡” አላቸው ጥቂትም ወደ ፊት እልፍ ብሎ በፊቱ ወደቀና ሲጸልይ፦ “አባቴ፥ ቢቻልስ፥ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ፤ ነገር ግን አንተ እንደምትወድ ይሁን እንጂ እኔ እንደምወድ አይሁን፡” አለ ማቴ ፳፮ ÷ ፴፯~፵
ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ወደ ሰማይ ዓይኖቹን አነሣና እንዲህ አለ፦ “አባት ሆይ፥ ሰዓቱ ደርሶአል፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ፥ በሥጋም ሁሉ ላይ ሥልጣን እንደ ሰጠኸው፥ ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ልጅህን አክብረው።
እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።
እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤John 17 አማ - ዮሐንስ
አሁንም፥ አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ።
ከዓለም ለሰጠኸኝ ሰዎች ስምህን ገለጥሁላቸው። የአንተ ነበሩ ለእኔም ሰጠሃቸው፤
ቃልህንም ጠብቀዋል። የሰጠኸኝ ሁሉ ከአንተ እንደ ሆነ አሁን ያውቃሉ የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና፤ እነርሱም ተቀበሉት፥ ከአንተም ዘንድ እንደ ወጣሁ በእውነት አወቁ፥ አንተም እንደ ላክኸኝ አመኑ።
እኔ ስለ እነዚህ እለምናለሁ፤ ስለ ዓለም አልለምንም ስለ ሰጠኸኝ እንጂ፤ የአንተ ናቸውና፤
የእኔም የሆነ ሁሉ የአንተ ነው የአንተውም የእኔ ነው፤ እኔም ስለ እነርሱ ከብሬአለሁ።
ከዚህም በኋላ በዓለም አይደለሁም፥ እነርሱም በዓለም ናቸው፥ እኔም ወደ አንተ እመጣለሁ። ቅዱስ አባት ሆይ፥ እነዚህን የሰጠኸኝን እንደ እኛ አንድ እንዲሆኑ በስምህ ጠብቃቸው።
ከእነርሱ ጋር በዓለም ሳለሁ የሰጠኸኝን በስምህ እኔ እጠብቃቸው ነበር፤ ጠበቅኋቸውም መጽሐፉም እንዲፈጸም ከጥፋት ልጅ በቀር ከእነርሱ ማንም አልጠፋም
አሁንም ወደ አንተ እመጣለሁ፤ በእነርሱም ዘንድ ደስታዬ የተፈጸመ እንዲሆንላቸው ይህን በዓለም እናገራለሁ።
እኔ ቃልህን ሰጥቻቸዋለሁ፤ እኔም ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉምና ዓለም ጠላቸው።
ከክፉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ከዓለም እንድታወጣቸው አልለምንም።እኔ ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉም።
በእውነትህ ቀድሳቸው፤ ቃልህ እውነት ነው ወደ ዓለም እንደ ላክኸኝ እንዲሁ እኔ ወደ ዓለም ላክኋቸው እነርሱም ደግሞ በእውነት የተቀደሱ እንዲሆኑ እኔ ራሴን ስለ እነርሱ እቀድሳለሁ ዮሐ ፲፯ ÷ ፩~፲፱
🌒 ዘመልአክ ዳግም 🌗
ረቡዕ
፩, ዕለተ ምክር
🔀 አይሁድ ሠላሳ ሦስት አመት ከሦስት ወር መክረው
በተለይም ሦስት አመት ከሦስት ወር ከፍ ሲል ሁለት ቀን ማለትም ሰኞና ማግስተ ሰኞ መክረው ምክራቸው ሳይጸና ቀርቷል በዚህ በዕለተ ረቡዕ ግን ይሙት በቃ ወሥነው ምክራቸውን አጽንተው ተለያይተዋል ።
በዚያን ጊዜ የካህናት አለቆች የሕዝብም ሽማግሎች ቀያፋ በሚባለው በሊቀ ካህናቱ ግቢ ተሰበሰቡ፥
ኢየሱስንም በተንኰል ሊያስይዙት ሊገድሉትም ተማከሩ፤
ነገር ግን፦ “በሕዝቡ ዘንድ ሁከት እንዳይነሣ በበዓል አይሁን አሉ ማቴ ፳፮÷፫
፪, ዕለተ ድኅነት
🔀 ክርስቶስ ፦ አዳምን በኀሙስ ዕለት ወበመንፈቃ ለዕለት እትወለድ እምወለተ ወለትከ ወእድህክ ውስተ መርህብከ ወእትቤዘወከ በመስቀልየ ወበሞትየ
ትርጕም፦ አምስት ሺኽ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ከልጅ ልጅህ ተወልጄ በግዕዘ ሕጻናት አድጌ በመስቀል ተሰቅየ ሙቼ አድንሃለሁ መጽ ቀሌ ፫
ብሎ ቃል ኪዳን በገባለት መሠረት ጊዜ ሲደርስ አምባ ይፈርስ እንዲሉ ዘመኑ ሲደርስ ይህን ፈጽሞለታል የድኅነት ፍጻሜውም በሞት ነውና እርሱ ካልሞተ አዳም ስለማይድን ይሙት በቃ ፍርድ ከተፈጸመ ድኅነት ስለሚደረግ ዕለተ ድኅነት ተብሏል ፆመ ድኅነትም የተጀመረው ከዚህ አንጻር ነው ።
ወኢትትዐደው ፆመ ዘእግዚአብሔር ዘውእቶሙ ረቡዕ ወዓርብ ዘእንበለ ይርከብከ ደዌ ክቡድ ወዘእንበለ መዋዕለ ጰንጠቆስጤ ወበዓለ ልደት ወበመዋዕለ አስተርዕዮ ዘውእቱ ኤጲፋንያ
ትርጕም፦ ጌታ ያዘዘውን ፆም አትሻሩ እነዚህም ረቡና ዓርብ ናቸው ጽኑ ደዌ ካላገኘህ በቀር በበዓለ ሃምሳ በበዓለ ጥምቀት ይኸውም ኤጲፋንያ ነው ቢውሉ ነው እንጅ ሃይ አ ፳÷ ፲፰
፫, ፍጻሜ ምክረ አይሁድ ወአጋንንት
አይሁድ ሰኞና ማግስተ ሰኞ መክረው ያልተፈጸመላቸው ምክረ ኃሳብ በዚህ ዕለት ፍጻሜ አግኝቷል
ዲያብሎስ በአዳም ክፉ ምክር መክሮ አምስት ሺኽ ከአምስት መቶ ዘመን በሲኦል ወድቆ በእግረ አጋንንት በምክረ አጋንንት ዘባነ ልቡናውን ሲቀጠቀጥ ኖሮ በዚህ ዕለት ፍጻሜውን አግኝቷል ።
፬, ኪዳነ ይሁዳ ፦
አይሁድ ምክራቸውን ካጠቃለሉ በኋላ ማን ያሳይናል ማንስ ያሲዘናል ሲሉ ይሁዳ እኔ ባሲዛችሁ ምን ትሰጡኛላችሁ ብሎ ከአይሁድ ጋራ ቃል ኪዳን የተጋባ በዚህ እለት ነው
በዚያን ጊዜ የአስቆሮቱ ይሁዳ የሚባለው ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ወደ ካህናት አለቆች ሄዶ፦
ምን ልትሰጡኝ ትወዳላችሁ እኔም አሳልፌ እሰጣችኋለሁ?” እነርሱም ሠላሳ ብር መዘኑለት።
ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ አሳልፎ ሊሰጠው ምቹ ጊዜ ይሻ ነበር ማቴ ፳፮ ÷ ፲፬~፲፮
🌗 ዘመልአክ ዳግም 🌒
የመስቀል ብድራት፦
መድኅን ክርስቶስ ስለ ወደደን ፈጽሞ ሞተልን እኛም ስለወደድነው ፈጽመን መስቀሉን ተሸክመን እንሞትለታለን።
የመስቀል ብድራትን በሕይወታችን ዘመን ሁሉ ተሸክመን ፍሬ ትሩፋትን እናበቅል ዘንድ በልቡናችን የመስቀል እርፍን አሸክሞናል።
በክርስቲያናዊ ሕይወታችን በሙሉ የሚገጥሙን ነገሮች ትናንሽ መስቀሎች ናቸው።
+2
ዜና ቤተክርስቲያን
ከበሮ፣ ጸናጽል፣ መቋሚያና ከ፲ በላይ ቅዱሳት መጻሕፍት የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን በቅጂና ተዛማች መብቶች ሥራ ተመዝግበው ከሚያዝያ ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ጀምሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አእምሯዊ ንብረት መሆናቸው ተረጋግጧል።
ከዚህ ቀደምም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅርስ ጥበቃ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ በአእምሯዊ ንብረት ዐቢይ ኮሚቴ አማካኝነት በርካታ የቤተክርስቲያን ንብረቶች ተመዝግበው እውቅና አግኝተው ነበር።
መረጃው፦የኢ.ኦ.ተ.ቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።
ዕለተ ሠሉስ (ማግሥተ ሰኞ)
➠ እለተ ጉባኤ ፦
አይሁድ ሠላሳ ሦስት አመት ከሦስት ወር በኢየሱስ ክርስቶስ በሚያደርገው ስራ ሁሉ ሲበሳጩና ሲቀኑ ኖረው በተለይ የሆሳዕና ቤተመቅደስ ከገባና ወግዱ ካላቸው በኋላ ምን እናድርግ ብለው መሰብሰብ ጀምረዋል
➠ ዕለተ ምስጢትር ፦
ከዚህ በፊት በዓደባባይ ሲያስተምር ይውላል ማታ ማታ ደቀመዛሙርቱ ያልገባቸውን ቀርበው ተርጉምልን ይሉታል ይተረጉምላቸዋል ማግስተሰኞ ግን ሁሉም (ክፉዎቹም ደጎችም ) ቀርበው ሲጠይቁ ውለዋል ለክፉዎች እንደክፋታቸው ለደጎች እንደደግነታቸው ሲመልስላቸው ምሥጢር ሲገልጥላቸው ውሏል ።
➠ ዕለተ ተስዕሎት ፦
፩, አይሁድ፦ በመባህተ መኑ ትገብር ዘንተ፦ ይህንን በመን ስልጣን ታደርጋለህ ? (ሙት ማንሳቱን ድውይ መፈወሱን ከቤተመቅደስ ጠራርጎ ማስወጣቱን )
ክርስቶስ፦ የዮሐንስ የማጥመቅ ስልጣኑ ከሰመይ ነው ከምድር ብሎ ጠየቃቸው ከምድር እንዳይሉ ሕዝቡን ፈሩ ከሰማይ እንዳይሉ ለምን አላመናችሁበትም ሊላቸው እንደሆነ አውቀው ዝም ብለዋል ማቴ ፳፩÷፳፫~፳፯
፪, ሰዱቃውያን ፦ ሙሴ በጻፈው በኦሪት አንዲት ሴት ባሏ ቢሞት የባሏ ወንድም እርሷን አግብቶ ልጅ ይውለድ የልጁ መጠሪያም በሟቹ ይሁን ይላል ለአንድ ሰው ሰባት ወንዶች ቢኖሩት ሰባቱም እያገቧት ቢሞቱ በትንሳኤ ሙታን ጊዜ ለማን ትሆናለች ?
ክርስቶስ ፦ ሰው ሙቶ ከተነሳ በኋላ አያገባም አይጋባም እንደ እግዚአብሔር መላዕክት ሆኖ ይኖራል ማቴ ፳፪ ÷፳፫
፫, ክርስቶስ ፦ ለአንድ ሰው ሁለት ልጆች አሉት አንዱን ልጁን ዓጸደወይን ጠብቅ ብሎ አዘዘው እሺ ብሎ ሳይሄድ ቀረ ሁለተኛ ልጁን ዓፀደ ወይኑን ጠብቅ አለው መጀመሪያ እንቢ አለ ኋላ ሂዶ ሲጠብቅ ዋለ ያባቱን ፈቃድ የፈጸመ ማን ነው ?
አይሁድ ፦ ሁለተኛው ልጅ ነው
ክርስቶስ፦ እናንተንም ዘማውያን ነፍሰ ገዳዮች አህዛብ ቀድመዋችሁ መንግሥተ ሰማያት ይገባሉ ማቴ ፳፩÷፳፰
፬, አይሁድ ፦ አንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ ያለው በአንዱ ገጽታ የቄሳር ስም የተጻፈበት በአንዱ ገጽታ የእግዚአብሔር ስም የተጻፈበት ይዘው መጥተው ይህ ሳንቲም የማን ነው ብለው ጠየቁት ? የቄሳሩን ጽሑፍ ብቻ አይቶ የቄሳር ነው ቢል የእግዚአብሔርን ገንዘብ ለቄሳር ነው ይላል ብለው ከሕዝቡ ጋራ ሊያጣሉት የእግዚአብሔርን ጽሑፍ ብቻ አይቶ የእግዚአብሔር ነው ቢል ለቄሳር አትገብሩ ይላል ብለው ከቄሳር ጋራ ሊያጣሉት ነበር ፧
ክርስቶስ ፦ ተንኮላቸውን ያውቅባቸዋልና የቄሳረን ለቄሳር የእግዘብሔርን ለእግዚአብሔር ስጡ ብሎ ምላሽ አሳጥቷቸዋል ምክንያቱም እንዳይሰነጥቁት አንድ ሳንቲም ነውና ፣
፭, ሐዋርያት ፦ ሐዋርያትም ይህች ዕፀ በለስ በምትለመልምበት ጊዜ እንዴት ፈጥና ደረቀች ?
ክርስቶስ ፦ እምነት ካላችሁ ተራራውን ከዚህ ተነቅለህ ከዚያ ተተከል ብትሉት ይሆንላችኋል ማቴ ፳፩ ÷ ፳
፮, ፈሪሳውያንም ሰዱቃውያንን ዝም እንዳሰኛቸው በሰሙ ጊዜ አብረው ተሰበሰቡ።
ከእነርሱም አንድ ሕግ አዋቂ ሊፈትነው፦
መምህር ሆይ፥ ከሕግ ማናቸይቱ ትእዛዝ ታላቅ ናት?” ብሎ ጠየቀው።
ኢየሱስም እንዲህ አለው፦ “ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም ውደድ።
ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።
ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች፥ እርስዋም፦ ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ፡ የምትለው ናት።
በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል። ማቴ ፳፪ ÷ ፴፬ ~፵
🌗 ዘመልአክ ዳግም 🌒
ረቡዕ ..................ይቀጥ..........
የመስቀል ብድራት
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ የመስቀል የፍቅር መከራን አበድሮናል፡፡ በዚህ የመከራ ብድራትም መከራ ተቀብሎ አደራውን ብድሩን በፍቅር እንደ አቅሙ ያልተወጣ ቅዱስ፣ ሐዋርያ ሰማዕት የለም፡፡ የመከራ መስቀል ዓይነታቸውም ልዩ ልዩ ነው። በሁሉም የመከራ ዓይነት ግን የክርስቶስ መስቀል ዕለተ ዓርብነት አለ።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
ሰኞ(ሰኑይ)(ሁለተኛዋ ቀን)
መድኅን ክርስቶስ ሰባቱንም ዕለታት የድኅነት ሥራውን ገልጦባቸዋል።በዕለታት በደል የገባባቸው ስለሆኑ የካሽ መላሽ ያስፈልጋቸው ነበርና።
አንደኛ ሰባቱ ዕለታት በደለኞች ባይሆኑም በደል ተሠርቶባቸው ነበር።
ሁለተኛ፦ሰባቱ ዕለታት እና ሰባቱ ከዋክብት ሀያ ሁለቱን ሥነ ፍጥረት ፈጠሩ እያሉ የሚያመልኳቸው ነበሩና መመለካቸውን አስቀርቶባቸዋል።
ልዑለ ቃል ነቢዩ ኢሳይያስ ስለ ሰባቱ ዕለታት በተነበየበት በቃለ-ትንቢቱ፦
"በዚያም ቀን ሰባት ሴቶች የገዛ እንጀራችንን እንበላለን የገዛ ልብሳችንንም እንለብሳለን፤ ስምህ ብቻ በእኛ ላይ ይጠራ፥ መሰደባችንንም አርቅ ብለው አንዱን ወንድ ይይዙታል።"ኢሳ.፬፥፩ ብሏል።
አንድ ወንድ የተባለ ክርስቶስ ነው።ሰባቱ ሴቶች የተባሉ ሰባቱ ዕለታት ናቸው።
ፈጣሪ መባልን አስቀርልን አምላክ የላቸውም ከመባል አድነን ብለውታል።
በዕለታቱ የሰዎቹን መናገር ነው።
ሥራ ከሠራባቸው ዕለታቶች አንዷ ዕለተ ሰኑይ ናት፦
የሕማማቷ ሰኞ ርግመተ በለስ ትባላለች።
መድኅን ክርስቶስ "ለዘለዓለሙ ፍሬ አይገኝብሽ"ብሎ በበለስ አንጻር ኀጢአትን የረገመበት እና በፍዳ እንዳታስይዝ ያደረገበት ዕለት ስለሆነ ርግመተ በለስ ተብላለች።፡ማቴ.፳፩፥፲፰(በምሥጢር ርግመተ ኃጢአት ማለት ነው።)በዚህም ቀን በመድኅን ክርስቶስ ተመክሮበታል፦ምሳሌው በዘመነ ሕገ ልቡላ የተከናወነው ምክር ምሳሌ ነው። ፪.ይህች ዕለት አንጽሖተ ቤተ መቅደስ ትባላለች፦መድኅን ክርስቶስ ቤተ መቅደሱን፦"ቤቴ የጸሎት ይባላል"ብሎ ማጽዳቱ የሚታሰብበት ዕለት ስለሆነ ነው።በዕለተ ሰኑይ የሚነበበው ግብረ ሕማማት ይዘት፦ቅደም ተከተሉ ከብሉይ ጀምሮ ከላይ እንዳየነው ሲሆን፦
[ ] ስለ ዕፀ በለስና በለስ እና ስለ ኃጢአት።
[ ] ስለርግመት እና ርግመት ፍዳ መርገም።
[ ] ስለረሀብ እና ስለ ረሀበ ነፍስ
[ ] ስለ መቅደሰ ኦሪት እና የሐዲስ ኪዳን፣
[ ] ስለ ምእመነ እሥራኤልና ስለ እሥራኤል ዘሥጋ።ነበረች አለፈች ለማለት ነው
[ ] ስለ ዓመተ ኃጢአት እና ስለ መድኅን ቤዛነት። በተመለከ የሚያብራራ ክፍል ነው።
በሕማሙ አውቀን እንታመም።
ዛሬ ቀን ቅዳሜ (እምርት ዕለት)
ቅዳሜ የሆሣዕናም የትንሣኤም ዋዜማ ናት። ዋዜማ ደግሞ አይነታን የጠብቃል ወይም ይሰብካል….. እምርት ዕለት ትባላለች።
በዋሸ እና በፍረኩታ መዋዕለ ጾሙን ያሳለፉ አበው ግብረ ሕማማት ወደሚነበብበት ደብር የሚጠጉበት ዕለት ነው።
ዳግመኛም የፍጻሜ ጾሙን አዋጅ የሚሰሙበት ነው። እንደ ቅዱስ ዞሲማስ እንደ ሠለስቱ አሀው ያሉ ማለት ነው።
እምርት ዕለት ዋዜማ ጸዋኢ አስተጋባኢ በአለ እስራኤል እንዲህ ነበር.. ሕማማትን በደብር የሚወሰኑ አበው ከበአት የሚወጡባት እና ወደ ሕማማት በአት የሚገቡባት ዕለት ናት።
ከቅዳሜ ጀምሮ የግብረ ሕማማት ንባብ በዋዜማ ይጀምራል።
@ምሥራቀ ጸሐይ ጉባዔ ቤት
“ፍቅርህ ከዘባነ ኪሩብ አውርዶ በአህያ ጀርባ ላይ እንድትቀመጥ አስገደደህ፡፡ ብዙ ዐይንና ብዙ ገጽ ካላቸው ከሰራዊተ መላክእት ይልቅ በዲዳዋ አህያ ትመሰገን ዘንድ ወደድክ፡፡ በሰማይ ሰራዊት ሠረገላ ተቀምጠህ ክብርህን ማሳየት አልወደድክም፤ በውርንጭላይቱ ላይ ተቀምጠህ ወደ ሰማይ ሰራዊት መሄድን መረጥክ እንጂ፡፡ በአርያም እሳታውያን የሚሆኑ ኪሩቤል ያመሰግኑሃል፤ በምድርም ሕፃናት ይዘምሩልሃል፡፡ በአርያም ብርሃናውያን መላእክት በብርሃን ክንፋቸው መንገድህን ያነጥፉልሃል፤ በምድርም ደቀ መዛሙርትህ ልብሳቸውን አንጥፈው መንገድህን አስተካከሉ፡፡
ወዮ! አርያማዊ ሲሆን ምንም ሳይንቀን ይጐበኘን ዘንድ ከአባቱ መጣ፡፡ እርሱም በገዛ ፈቃዱ ሰው እስከመሆን ደርሶ መጣ፡፡ በአህያ ላይ ተጭኖም ይጐበኘን ዘንድ መጣ፡፡ ነቢዩ ዘካርያስ የመንፈስ ቅዱስን እንዚራ ይዞ በደስታ ትንቢትን ለመናገር ይቻኰላል፡፡ እየደረደረም የጽዮንን ልጅ ይጠራታል፡፡”
ሊቁ_ያዕቆብ_ዘሥሩግም
🌴ዐቢይ ጾም🌴
🌴ስምንተኛ ስምንት🌴
🌴ሆሣዕና🌴
እባክህ አሁን አድን🤲🌿ምንባባት🌿 ዕብ 9÷ 11-28 1ኛ ጴጥ 4÷1-11 ሐዋ 28÷11-31 🌿ምስባክ 🌿 ቡሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር ባረክናክሙ እምቤተ እግዚአብሔር እግዚአብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ 🌿🌿🌿 ትርጉም በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ እግዚአብሔር አምላክ ነው ለእኛም በራልን ወንጌል ሉቃ 19÷28-48 ቅዳሴ ዘጎርጎርዮስ 🕯🕯🕯🤲🤲🤲🕯🕯🕯 # እባክህ አሁን አድን🤲 #ዕለተ ሰንበት በማስቀድስ እናሳልፍ 🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴
+3
እንኳን ለሆሳዕና በዓል በሰላም አደረሳችሁ
እነሆ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት የፊታችን እሁድ ለሚከበረው የጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል ነድያንን ጾም ለማስፈታት ዝግጅቱን ከወዲሁ የጀመረ ሲሆን ለእዚህም ሁሉም ሰው የራሱ ድርሻ ስላለው በምትችሉት ሁሉ ከሰ/ት/ቤቱ ጎን በመቆም ነድያኑን በመመገብ የነፍስም የሥጋም በረከት ታገኙ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
✞ ምናለ ብታስተምረኝ ✞ በክብር በሞገስ በመወደስ ፈንታ መቀመጥ እንድችል ከመዋረድ ተርታ ስድብን እየሰማሁ ያለ አንዳች ሁካታ ለመቆም እንድችል ልቤ ሳይረታ ምናል ብታስተምረኝ /፪/ ብታስችለኝ ጌታ/፪/ ለእኔም አስተምረኝ ባላጠፉት ጥፋት በጸጋ መቀበል የአይሁድን ትፋት እንዴት እንደሚቻል ሳያጉረመርሙ ንገረኝ ጌታዬ ይረዳኝ ትርጉሙ ምናል ብታስተምረኝ /፪/ብታስችለኝ ጌታ/፪/ አዝ የመናቅን ጥበብ የውርደትን ዘዴ እባክህ አስረዳኝ አስተምረኝ አንዴ ብዔል ዜቡል ተብለህ ያልተበሳጨኸው የኃጢአተኞች ወዳጅ መባል ያልጠላኸው ጋኔን ይዞታልን የሰማህ በጸጋ ለእኔም አስተምረኝ/፪/ በቂም አልወጋ/፪/ አዝ አልወጋ እባክህ በመራርነት ጦር በቁጣ ጥላቻ ነፍሴ አትሰበር እንዴት ነበር ያኔ የይሁዳን እግር ዝቅ ብለህ ያጠብከው ስታውቅ ሁሉን ነገር ለእኔም አስተምረኝ/፪/ ብዙ ሳልናገር/፪/ አዝ በችንካር ተጣብቀህ ከመስቀሉ ጋራ የደምህ ነጠብጣብ ገና ሳያባራ አያውቁትምና የሚያደርጉትን ይቅርታን የለመንህ ላጠጡህ ሐሞትን ምናል ብታስተምረኝ/፪/ እንዲህ ያለ ሕይወትን/፪/ አዝ አሁን ምን ቸገረህ ብትሰጠኝ ለአንድ አፍታ የትሕትናን ቀሚስ የትዕግሥትን ኩታ እያየህም አይደል ወይ ነፍሴ እንዲህ ተራቁታ የመሰደብን ዘውድ የመናቅን ካባ ምናለ ብትኖር/፪/ ይህች ልቤ ደርባ/፪/ አዝ ትዕቢት ለተሞላው ለአትንኩኝ ባይ ልቤ ለክብሩ ለሚኖር ለኮርማው ሃሳቤ ምናለ ብትቀባው የትሕትናን ሽቶ እንደዚህ ከሚኖር ሸትቶ ተበላሽቶ ኸረ እኔ አልቻልኩም አቅቶኛል በጣም ስድብን መቀበል ሐሜትን ማጣጣም ስተርከው እንጂ ስኖረው አቃተኝ ይህን መራር ጉዞ አንተው ይዘህ ጋተኝ/፪/
