ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
رفتن به کانال در Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
نمایش بیشتر672
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+37 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
እውነት እላችኋለሁ፥ከሁሉ ከሚያንሱ ከነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል። ማቴ 25:40
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን🙏
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ውድ የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አባላት እንዲሁም የሰንበት ት/ቤቱ የቴሌግራም ቻናል ተከታታዮች ከላይ በምስሉ ላይ የምትመለከቱዋት እህታችን በአሰላ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ፈለገ ሊቃውንት ሰ/ት/ቤት ለረጅም ጊዜያት ያገለገለች እና በማገልገል ላይ ያለች እንዲሁም ሰ/ት/ቤቱን ወክላ በሰበካ ጉባኤ ውስጥ የምትሳተፍ ብርቱ አገልጋይ ነች ። እናም ወዳጆቻችን በአሁኑ ሰዓት ይህች ትጉ እና ብርቱ እህታችን በከፍተኛ ልብ ህመም እየተሰቃየች ትገኛለች ። ለህክምናም ከአቅም በላይ የሆነ ገንዘብ ስለተጠየቀ ሁላችንም ያቅማችንን በማገዝ እህታችንን አለንልሽ እንድንላት እናም ድና ወደምትናፍቀው አገልግሎትዋ እንድትመለስ እና ቤተሰብዋን እንድትመራ እንድናግዛት ስንል በአምላካችን በመድኃኔዓለም ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
እህታችንን ለመርዳት ከላይ በምስሉ ላይ በተቀመጡት የባንክ አካውንቶች መጠቀም ትችላላችሁ።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ከምንም በላይ ግን ለጸሎት በቆማችሁ ጊዜ በጸሎታችሁ አስቡዋት 🙏
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨✨✨✨✨✨✨✨
ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት
✨✨✨✨✨✨✨✨
ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15 : 58
“በእኔም ሰላምን እንድታገኙ ይህን ነገርኋችሁ፤ በዓለም ግን መከራን ትቀበላላችሁ፤ ነገር ግን ጽኑ፤ እኔ ዓለሙን ድል ነሥቼዋለሁና።”
(ዮሐ.፲፮፥፴፫)
"
እነሆ በፊትህ የተከፈተች ደጅ ሰጥቼሀለሁ ሊዘጋት የሚችል የለም"ራዕ 3:7 "በእርግጥም እግዚአብሔር ለአንድ ሰው በርን በከፈተለት ጊዜ ሊዘጋበት የሚችል ማንም የለም።በመሆኑም እግዚአብሔር እንዲከፍትልህ ብትሻ የሚያስፈልግህ ነገር ቢኖር መጸለይ ነው። ስለዚህ ፕሮጀክትህን ሁሉ ዕቅድህንም ሁሉ ልትጀምር በፈለግህ ጊዜ ይህንን ጸሎት አድርስ።" አቡነ ሺኖዳኑ አብረን እናንግስ
‘’አልጋ መግዛት ለምትፈልጉ ኑ አልጋ ላሳያችሁ! ይህ አልጋ የተራ ሰው ወይም የወታደር አልጋ አይደለም፡፡ የንጉሥ አልጋ ነው፡፡ ንጉሥም ቢባል ተራ ንጉሥ ሳይሆን በዓለም ሁሉ የሚዘመርለት ታላቅ ንጉሥ አልጋ ነው፡፡ የንጉሥ ዳዊትን አልጋ ላሳያችሁ፡፡ ይህ አልጋ ከወርቅ ወይም ከአልማዝ ወይም ከከበሩ ድንጋዮች የተሠራ አይደለም፡፡ ይህ አልጋ ከዕንባ የተሠራ አልጋ ነው፡፡ እርሱ ‘ሌሊቱን ሁሉ አልጋዬን አጥባለሁ ፤ በዕንባዬም መኝታዬን አርሳለሁ’ ብሏልና’’
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
እንኳን ለ2018ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ!
"አንተ ግን በተማርበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር!" ፪ኛ ጢሞ ፫፥፲፬እነሆ ዘንድሮም እንደአምናው በሰ/ት/ቤቱ የሚሰጠው ተከታታይ መንፈሳዊ ትምርት ለመስጠት ዝግጅታችንን ጨርሰን ተማሪዎችን በመመዝገብ ላይ እንገኛል። በሁለቱም ቋንቋዎች በአፋን ኦሮሞና በአማርኛ ከ1-9ኛ ክፍል ነባርና አዲስ ተማሪዎችን ለማስተማር ዝግጅታችንን ጨርሰናል ይምጡና ይመዝገቡ ይማሩ! የመመዝገቢያ ቦታ 👉ዘወትር ቀን ከ10:00 ሰዓት ጀምሮ በአውደ ምህረት፣ በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽና ቤተ መጽሐፍት 👉ሁሌም በስራ ሰዓት በሰ/ት/ቤቱ ነዋየ ቅዱሳት መሸጫ 👉 በፈለጉት ሰዓት ባሉበት ሆነው በሚከተለው ሊንክ በመግባት በonline መመዝገብ ይችላሉ( https://forms.gle/9RDHjM9H9Ymy924R6 ) ለበለጠ መረጃ 👉0968903347 👉0998646565 👉0938117125
"በሥራና በእውነት እንጂ በቃልና በአንደበት እንዋደድ።"
1ኛ ዮሐ 3÷18
መንፈሳዊ ትምህርት መማር የምትፈልጉ:-በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ንዋያተ ቅድሳት በመገኘት መመዝገብ ትችላላችሁ።
ማስታወቂያ 📢
መንፈሳዊ የ9ኛ ክፍል(ሳልሳይ) ትምህርት መጀመሩን ሰምተዋል?
ከዚህ በፊት በየትኛውም ደብር መንፈሳዊ ኮርስ እስከ 8ኛ ክፍል( ካዕላይ) የተማራቹ 9ኛ ክፍል(ሣልሳይ) በመግባት ትምህርታቹን መከታተል ትችላላችሁ።መንፈሳዊ ትምህርቱን መከታተላችሁን ማስረጃ ማቅረብ ግዴታ ነው።
🕰 ትምህርቱ የሚሰጥበት ሰዓት አርብ ፣ ቅዳሜ እና እሁድ ከሰዓት 11:30- 1:00 ሰዓት ድረስ።
📍 ትምህርቱ የሚሰጥበት ቦታ በአሰላ ደብረ መ/መ/ዓ/ካቴድራል በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ
