fa
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

رفتن به کانال در Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

نمایش بیشتر
669
مشترکین
-224 ساعت
+57 روز
+130 روز
آرشیو پست ها
✨✨✨🍂🌿🍂 ✨✨✨ የቀጠለ ... ✨ጾም በቅዱሳን አባቶች ትምህርት ✨ ስለ ጾም ጠቃሚነትና አስፈላጊነት፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ሰማያዊ ዋጋ ያለው ስለ መሆኑ፣ በጾም ጊዜ የእንስሳት ተዋጽኦዎች (ዓሣን ጨምሮ) እንደማይበሉ፣ እና በመሳሰሉት ጾምን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምረዋል፡፡
“በጾማችን የነፍሳችንን ክፉ ልማዶች ካላስወገድን ከሥጋ መከልከላችን ብቻውን ምን ይጠቅመናል? ስንጾም ውለን ጾም ከመግባቱ በፊት እንመገበው የነበረውን ምግብ ለውጠን መናኛ የሆነ የጾም ምግብ በማዕዳችን አቀረብን፡ ሆኖም ግን በጸሙ የምንመገበውን ምግብ እንደ ለወጥን ክፉ ግብራችንን እና ሕይወታችንንስ አብረን ለውጠናል ይሆን? በእውነት እኔ ግን እንዲህ ያደረጋችሁ አልመሰለኝም፡፡ እንዲህ ከሆነ መጾማችሁ ጥቅሙ ምንድን ነው? ስለዚህ ከጾማችሁ ጋር ልማዳችሁንና ሕይወታችሁን ወደ መልካምነት ትቀይሩ ዘንድ በተከታታይ እንድታስቡበት አደርጋችሁ ዘንድ ስለዚህ ነገር እናንተን ማስተማርንና መገሠጽን አላቋርጥም፡፡ በጾማቸው መንፈሳዊ ፉክክር የሚፎካከሩ እንዳሉ ሁሉ በዚህም አስደናቂ የሆነ ተጋድሎን የሚጋደሉ እንዳሉ ሁሉ፡ ሁለት ሙሉ ቀናትን በተከታታይ ምንም ነገር ሳይቀምሱ የሚጾሙ አንዳንዶች አሉና፡፡ ሌሎች ደግሞ በጾም ጊዜ ወይን እና ዘይትን መተው ብቻ ሳይሆን ሌላውን ነገር ሁሉ ትተው መላውን ዐቢይ ጾም በደረቅ ዳቦና በውኃ ብቻ የሚጸ አሉና፡ . . .
📝ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ 📚ትምህርት በእንተ ምክንያተ ሐውልታት 4 ቁ 12 ✨✨✨🍂🌿🍂

✨✨✨🍂🌿🍂 ✨ጾም በቅዱሳን አባቶች ትምህርት ✨ ስለ ጾም ጠቃሚነትና አስፈላጊነት፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ሰማያዊ ዋጋ ያለው ስለ መሆኑ፣ በጾም ጊዜ የእንስሳት ተዋጽኦዎች (ዓሣን ጨምሮ) እንደማይበሉ፣ እና በመሳሰሉት ጾምን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምረዋል፡፡
“. . . ትምህርታችንን እንደሚከተለው ማጠቃለል ተገቢ ነው፤ የተፈጠርነው በሐሤትና በደስታ እንድንኖር ነበር፡፡ ስንፈጠር ደስተኞች ተደርገን ነበር የተፈጠርነው፡፡ ገነትን የተሰጠነው በሕይወት እየኖርን ሐሤትን እንድናደርግ ነበር፡፡ ሕግን የተሰጠነውም እርሱን በመጠበቅ መልካም ስምና ክብር ይሆንልን ዘንድ ነበር፣ እግዚአብሔር ምን እንደሚሆን (ሕጉን እንደምናፈርስ) ስለማያውቅ ሳይሆን የነጻ ፈቃድን ሕግ ያስቀመጠ ስለሆነ ነበር፡፡ ከገነት የተባረርነውም ሕጉን ስላፈረስን ነበር፡፡ የእውቀት ዛፍ በተባለችው ተሸንፈን መጾምን እምቢ በማለታችንና ጾምን በማፍረሳችን ከዚያ በኋላ በደረሰብን መከራ በግድ ጾምን፡፡ የጾም ሕግ ጥንታዊና ቀዳማዊ ነውና፣ ከእኛ መፈጠር ጋርም አብሮን የነበረ ሕግ ነውና፡፡ የጾም ሕግ አስቀድሞ የተሰጠንም ለነፍሳችን ትምህርት፡ ለድሎትና እርሱ ለሚያመጣው ዕዳ አርቆ ማጠሪያና መጠበቂያ እንዲሆነን ነበር፡፡ ስለዚህም ዛሬ ከጥንቱ ከመጀመሪያው የጾምን ሕግ ባለመጠበቃችን ምክንያት ያጣነውን ነገር መልሰን እናገኝ ዘንድ ጾምን እንድንጾምና ለጾም እንድንገዛ አደረገን፡፡ "
📝ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ፣ 📚ትምህርት ካልአይ በእንተ ትንሣኤ፡ ቁ. 28 ✨✨✨🍂🌿🍂

ጾመ ነቢያት ኅዳር 15 ይጀምራል። ጾመ ነቢያት (የገና ጾም) ከሰባቱ የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ሲሆን "ጾመ ነቢያት" የተባለበት ምክንያት ነቢያት ለአዳም የተሰጠውን "አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለው" የሚለውን የተስፋ ቃል በማሰብ ከሰማየ ሰማያት ይወርዳል ፤ ከድንግል ማርያም ይወለዳል ፤ በሞቱም ሞት የተፈረደበትን የሰው ልጅ ነጻ ያወጣዋል ብለው ስለጾሙት ነው። እኛም በልባችን ውስጥ እንዲወለድ ፣ ከእርሱም በረከት እንዲያሳትፈን እንጾማለን።

⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️ "የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ሆይ፤ የተቸገሩትን የተጨነቁትን ዘወትር እንደምትረዳቸው ሁሉ እኔንም ለመርዳት ክንፍህን ዘርግተህ ፈጥነህ ድረስልኝ ።" �
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️ "የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ሆይ፤ የተቸገሩትን የተጨነቁትን ዘወትር እንደምትረዳቸው ሁሉ እኔንም ለመርዳት ክንፍህን ዘርግተህ ፈጥነህ ድረስልኝ ።"   🌹    መልክዐ ሚካኤል     🌹

እንኳን አደረሳችሁ!!! #ሕዳር_ሚካኤል_12 ህዳር ሚካኤል ለምን ይከበራል? በዋነኝነት ሕዳር ሚካኤል ስለሁለት ነገር ይከበራል። 1/የመላዕክት አለቃ ሁኖ የተሾመበት (ዘንዶውንና ሰራዊቱን ድል አድርጎ
እንኳን አደረሳችሁ!!!
#ሕዳር_ሚካኤል_12 ህዳር ሚካኤል ለምን ይከበራል?
በዋነኝነት ሕዳር ሚካኤል ስለሁለት ነገር ይከበራል። 1/የመላዕክት አለቃ ሁኖ የተሾመበት (ዘንዶውንና ሰራዊቱን ድል አድርጎ መልአከ ኃይል የተሰኘበት ዕለት) 2/እስራዔላውያንን ከግብፃውያን ባርነት ነፃ ያወጣበትና ባሕረ-ኤርትራን ያሻገረበት ቀን ስለሆነ ነው። #ሚካኤል_ማለት   መኑ ከመ አምላክ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው  ማለት ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ገናንነትና እሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ የሚያመለክት ነው እንደ እግዚአብሔር ያለ ቅዱስ፣ ንጹሕ፣ ርህሩህ፣ ኃያል፣ ረቂቅ ማነው  መልሱ የለም ነው፡፡ #ቅዱስ_ሚካኤል የስሙ ዘርፍ ሆነው የሚጨመሩ መጠሪያዎች አሉት። እነዚህም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠውን የባለሟልነት ክብር የሚገልጹ ናቸው፡፡ ይኸውም መልአከ ኃይል፣ መጋቤ ብሉይ፣ መልአከ ምክሩ፣…ናቸው፡፡ #መልአከ_ኃይል የተባለው እግዚአብሔር በሱ አማካይነት ታላላቅ ሥራዎችን በመሥራት ኃይሉን ስለገለጸ - ዲያብሎስን ከነሠራዊቱ ስላሸነፈ ነው፡፡ #መጋቤ_ብሉይ የተባለበት ምክንያት በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከእግዚአብሔር እየተላከ ብዙ ታላላቅ ሥራዎችን የሠራ በመሆኑ ነው፡፡ #መልአከ_ምክሩ ወይም የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ የተባለበት ምክንያት እግዚአብሔርን በምክሩ ይረዳዋል ለማለት ሳይሆን እግዚአብሔር የሚሠራውን ሥራ ለወዳጁ ለቅዱስ ሚካኤል ይገልጽለታል በሱም አማካኝነት ይሠራል ለማለት ነው፡፡ የታላቁ መልአክ የቅዱስ ሚካኤል ምልጃውና ጸሎቱ በሁላችን ላይ ይሁን። # የቅዱስ ሚካኤል ፈጣን ተራዳኝነት እና አመላጅነት አይለየን ።

✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟ " ሰውን አትበለው አወቀ ረቀቀ ሞትን አያውቅም ወይ ችሎማ ካወቀ " ጣፋጭ ጥበብ ገጽ ፻፸፬ ቁጥር  ፩ሽ ፪፻፹፮ ✣✣✣✣✣✣✣✣✣✣✣✣✣✣✣✣✣✣✣✣ " የሰው ልጆች ሁሉ አዋቂ ናቸው የሚባለው ስህተት ነው ። አዋቂ ማለት መጽሐፍትን ጠንቅቆ ያወቀ ሳይሆን ከኃጢአት በመቆጠብ ነፍሱን የማይጎዳ ፣ አምላክን በማመስገን በማያወላውል በቅድስና ሥራ መልካም በመሥራት ነፍሱን የሚመግብ ያ ሰው እሱ ብቻ አዋቂ ተብሎ ይጠራል።"       ታላቁ ቅዱስ እንጦንስ ✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥ የአባቶቻችን ጸጋና በረከት ትደርብን 🙏

🎲 Quiz 'ፍኖተ ወንጌል ልዩ መንፈሳዊ የጥያቄና መልስ መርሐግብር "start the quiz"የሚለውን ይጫኑ "i am ready" ሲጫኑ ይጀምራል። መልካም ዕድል🛎🛎🛎' 🖊 7 questions · ⏱ 30 sec

ድንግል ሆይ ከልጅሽ ጋር በተሰደድሽ ጊዜ ካንቺ ጋር መሰደዱን አሳስቢ፤ ረሃቡን እና ጥሙን ችግሩና ሀዘኑን ከእርሱ ጋር የደረሰብሽን ሁሉ አሳቢ፤ለፃድቃን ያይደለ ለሀጥዓን አሳስቢ፤ ለንፁሃን ያይደለ ለ
ድንግል ሆይ ከልጅሽ ጋር በተሰደድሽ ጊዜ ካንቺ ጋር መሰደዱን አሳስቢ፤ ረሃቡን እና ጥሙን ችግሩና ሀዘኑን ከእርሱ ጋር የደረሰብሽን ሁሉ አሳቢ፤ለፃድቃን ያይደለ ለሀጥዓን አሳስቢ፤ ለንፁሃን ያይደለ ለተዳዳፉት አሳስቢ፤ ከሁሉ በላይ ስለበደልኩ ስለእኔም አሳስቢ እመቤቴ በደብረ ቁስቋም በመልዓኩ መሪነት ካረፍሽ በኃላ አዳም ስደቱ ተሻረለት የግብፅ ጣኦታት ተዋረዱ አምልኮተ እግዚአብሔር ነገሰ። ይኸው እስካሁን አንቺ እና ልጅሽ የተቀመታቹበትን አለት መንበር አድርገው ይቀድሱበታል፤  ደብረ ቁስቋምን ለመሳለም ያብቃን   እንኳን ለደብረ ቁስቋም አደረሳችሁ

ናሁ ተፈጸመ ማህሌተ ጽጌ ማህሌተ ጽጌ ኢየኃፍር ቀዊመ ቅድመ ስእልኪ ወርኃ ጽጌረዳ አመ ኃልቀ፤ዘኢየኃልቅ ስብሐተኪ እንዘ እሴብሐኪ ጥቀ፤ተአምርኪ ማርያም ከመ አጠየቀ፤ጸውዖ ስምኪ ያነሥእ ዘወድቀ፤ኃጥአኒ ይሬሲ ጻድቀ፡፡ 👉ትርጉም እጅግ ብዙ የማያልቅ ምስጋናሽን እያመሰገንኩኝ : የጽጌረዳ ወራት ባለቀ ጊዜ በስዕልሽ ፊት መቆምን አላፍርም : ማርያም ተዓምርሽ እንዳስረዳ ስምሽን መጥራት የወደቀን ያነሳል : ኃጥኡንም ጻድቅ ያደርጋል ። 👉ምስጢር የጽጌረዳ ወራት ባለቀ ጊዜ በሥዕልሽ ፊት መቆምን አላፍርም ማለቱ ከመስከረም 26 - ኅዳር 6 የቆየው የጽጌ ወቅት ቢያልፍም እኔ ግን ምስጋናሽን አላቋርጥም ይላል የዚህ ክፍል ጥንተ ነገሩ ዘካርያስ የሚባል ሰው የእመቤታችንን ሥዕል ያገኛል ፤ በጣም ተደሰተ ፤ የእመቤታችን ፍቅር አደረበትና ምን ላድርግላት ብሎ ተጨነቀ ። ወቅቱ የጽጌ ነበርና እለት እለት 50 አበባ ለሥዕሏ አደርጋለሁ አለ ። እንዳለውም በየቀኑ ሀምሳ ጽጌሬዳ እየቆረጠ ለሥዕሏ ያደርግ ነበር ። በኋላ የአበባ ጊዜ ሲያልፍ አበቦችን ማግኘት ስለማይችል ምን ላድርግ ብሎ አሰበ ፤ በአበቦቹ ፈንታ ሀምሳ ጊዜ በሰላመ ቅዱስን አደርሳለሁ ብሎ ማድረስ ጀመረ ። ከእለታት በአንዱ ቀን ወደ ሌላ ሀገር ሲሄድ መንገድ ላይ ሽፍታዎቹ አግኝተውት እርሱ በሰላመ ቅዱስ ገብርኤል መልአክ እያለ ይጸልያል ፤ እመቤታችን ለሽፍቶች ተገልጣ አንድ በሰላመ ቅዱስ ሲል አንድ አበባ ስትቀበል ይመለከታሉ ፤ ሀምሳውን ሲጨርስ ሀምሳ አበባ ። የዚህን ጊዜ ሽፍታዎቹ በግንባራቸው ተደፍተው ሰገዱለት ፤ በኋላም አምነው መነኮሳት ሆነዋል ። እናም ይህ የጽጌ ምሥጋና ቢያልቅም የእመቤታችን ምሥጋና እንደማይቋረጥ ሲገልጽ ነው ፤ በውዳሴ ማርያም ፣ አርጋኖን ፣ ማኅሌት ፣ ሰዓታቱ ትመሰገናለችና ። ስምሽን መጥራት የወደቀን ያነሣል ማለቱ አንድ እመቤታችን የሚወድ ሰው ነበር ፤ ከተወደደ ልጇ ጋር ሥዕሏን ስሎ በመሰላል ወጥቶ ዲያቢሎስ በሲኦል ነፍሳትን መከራ ሲያጸናባቸው እየሣለ እያለ ዲያቢሎስ ተናድዶ መሰላሉን መትቶ ሊጥለው ወደ ታች ሊወድቅ ሲሄድ ከሳላት ሥዕል የእመቤታችን እጅ ወጥቶ ይዞ አድኖታል ። ኃጥኡንም ጻድቅ ያደርጋል ሲል በቃልኪዳኗ ልጄ ወዳጄ ማርልኝ ብላ ስትለምን ስለ እናትነቷ ይምራልና ኃጥኡንም ጻድቅ ያደርጋል ብሏል ። ማህሌተ ጽጌ ለንጉሠ ነገሥት ሰሎሞን ከመ ተፈሥሐ ልቡ፤በዕለተ ወፃእኪ መርዓት ለአንበሳ ትንቢት እምግቡ፤ማዕከለ ማኅበር ፍሡሓን ተአምረኪ ዘይነቡ፤እዜምር ለኪ ጽጌ ሐና ወፍኖተ ነፈርዓፅ እሌቡ፤ከመ ጣዕዋ ሐሊበ ዘይጠቡ። ትርጉም የሀና አበባ  ሆይ!ሐሴትን በተመሉ ( ማኅበረ ጻድቃን)ማኅበር መካከል ተአምርሽን የሚናገር የነገሥታት ንጉሥ ሰሎሞን ሙሽሪት  ከአንበሳዉ ትንቢት ዋሻ በወጣሽ ጊዜ ልቡ ሐሴት እንዳደረገ  እንደ ሚጠባ እንቦሳ የመፈርጠጫ ቦታየን አስተውላለሁ፤ እዘምርልሽም አለሁ። ማኅሌተ ጽጌ ኅብረ ሐመልሚል ቀይሕ ወፀዓድዒድ አርአያ ኰሰኰስ ዘብሩር ተአምርኪ ንጹሕ በአምሳለ ወርቅ ግቡር ተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌ ሥሙር አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማይ ወምድር ከመ በሕፅንኪ ያስምክ ፍቁር ። ትርጉም የሚያብረቀርቅ ቀይነ ነጭ ቀለም ያለው አርአያው የብር ዝንጉርጉር የሆነ ንጹሕ ተዓምርሽ በወርቅ አምሳል የተሰራ ነው ፤ እነሆ የተወደደ መልካም ማኅሌተ ጽጌ ተፈጸመ ፤ የሰማይና የምድር ንግሥት ማርያም ሆይ የተወደደ ልጅሽ በእቅፍሽ እንዲጠጋ (እንዲንተራስ ) በእርሱ አማጽኝ ። ምስጢር ቀይና ነጭ ቀለም ያለው ማለቱ ቀይ በትስብእቱ ነጭ በመለኮቱ ማለትም ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ ዝንጉርጉርም ያለው ሰው እና አምላክነቱን ነው  ( እንዘ ተኃቅፊዮ ላይ በሰፊው አይተናል ) ተአምርሽ በወርቅ አምሳል የተሰራ ነው ሲል ወርቅ የንጽሕና ምሳሌ ነውና እመቤታችንም ንጽሕተ ንጹሐን ናትና ። |  ኵለንታሃ ወርቅ | ወርኀ ጽጌ አልቋል ሲል ተፈጸመ ማኅሌተ ጽጌ ስሙር አለ የሰማይና የምድር ንግሥት ( መዝ 44 ) ስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ... አሜን !

🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️✨✨✨🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️✨✨✨🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️ የሰማይና የምድር ንግሥት ድንግል ማርያም ✨ማኅሌተ ጽጌ ተፈፀመ። 🌹ኅብረ ሐመልሚል ቀይሕ ወፀዓድዒድ
🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️✨✨✨🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️✨✨✨🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️ የሰማይና የምድር ንግሥት ድንግል ማርያም                       ✨ማኅሌተ ጽጌ ተፈፀመ። 🌹ኅብረ ሐመልሚል ቀይሕ ወፀዓድዒድ አርአያ ኰሰኰስ ዘብሩር፤ተአምርኪ ንጹሕ በአምሳለ ወርቅ ግቡር፤ተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌ ሥሙር፤አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማያት ወምድር፤ከመ በሕጽንኪ ያሰምክ ፍቁር🌹 ✨✨✨ ናሁ ተፈፀመ ማህሌተ ፅጌ ስሙር አስምኪ ቦቱ ንግስተ ሰማያት ወምድር ከመ በህፅንኪ ያሰምክ ፍቁር። ንግስተ ሠማያት ወምድር ማርያም ድንግል { ፪ } ተፈፀመ { ፬ } ማህሌተ ፅጌ ይህ መልካም፣ ያማረ፣ የተወደደ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመስከረም 26 ጀምሮ እስከ ኅዳር 6 መድረሻ የመጨረሻዋ ሰንበት የሚደረሰው ይህ ድንቅ ማሕሌተ ጽጌ “እነሆ የተወደደ (መልካም) ማሕሌተ ፅጌ ደረሰ ተፈጸመ” የእመቤታችን ፍቅሯና አማላጅነቷ በረከቷም አይለየን           ✨🙏✨የዓመት ሰዉ ይበለን ✨🙏✨ 🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️✨✨✨🌹️️️️🌹️️️️🌹️️️️✨✨✨

ለመንፈሳዊ ትምሕርት ፈላጊዎች በሙሉ!!! ሼር በማድረግ ለወንድም እሕቶቻችን እናድርስ።
ለመንፈሳዊ ትምሕርት ፈላጊዎች በሙሉ!!! ሼር በማድረግ ለወንድም እሕቶቻችን እናድርስ።

ቃልኪዳንህን_ፈጽምልኝ🙏 እግዚአብሔር ብዙ ቃል ገብቷል፣ እርሱ ታማኝ ነውና ቃሉን አያጥፍም እናም ቃሉን ይዛችሁ 'ቃልኪዳንህን ፈጽምልኝ!' ስትሉ ቅዱስ ዳዊትን አብነት አድርጋችሁ ከእርሱ ጋር ተወያዩ
ቃልኪዳንህን_ፈጽምልኝ🙏 እግዚአብሔር ብዙ ቃል ገብቷል፣ እርሱ ታማኝ ነውና ቃሉን አያጥፍም እናም ቃሉን ይዛችሁ 'ቃልኪዳንህን ፈጽምልኝ!' ስትሉ ቅዱስ ዳዊትን አብነት አድርጋችሁ ከእርሱ ጋር ተወያዩ፣ ተከራከሩም። እርሱ እንዲሰራብን እኛ ልባችንን አንሰጠውም እንጂ እርሱ ቃሉን አያጥፍም። ጥሩ ሰው ስላልሆንኩ ጥሩ ሰው ሆኜ እመለሳለሁ አትበሉ። እርሱ እንዲህ ይላችኋል 'ራሳችሁን ጥሩ አድርጋችሁ ወደ እኔ ከምትመጡ ይልቅ ወደ እኔ ኑና እኔ ጥሩ አደርጋችኋለሁ።' በመፅሐፍ ከደዌ እንደፈወሳቸው ድውያን እንደቆሸሸ ወደ አባቱ ቤት እንደተመለሰውም የጠፋው ልጅ ከነድካማችን እንዲሰራብን በፊቱ እንቅረብ። ✨✨🌿✨✨ ከእግዚአብሔር ርቃችሁ ለመስተካከል ብትሞክሩ በፍጹም ልትስተካከሉ አትችሉም÷ ይልቁንም በርሱ ፊት ራሳችሁን ስትጥሉና ወደ ሕይወታችሁ ስትጠሩት ብቻ እንጂ! ከእግዚአብሔር ጎን ሆናችሁ ተፋለሙ ታሸንፉማላችሁ! 'ጌታ ሆይ ተመልከተኝ  ካልተስተካከልኩ ከደጅህ ከቤተክርስቲያን ዐውደምሕረት ተደፍቼ ወዴትም አልወጣም! የሚሳንህ የለምና እኔንም አስተካክለኝ  አልለቅህም! የበጎ ነገር ፈጣሪ ነህና በእኔም ውስጥ በጎን ነገር ስራብኝ' በሉት።
'ኑና እንዋቀስ! ይላል እግዚአብሔር። ኀጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች ÷ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች።' (ትን. ኢሣ 1÷18)
       አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ 🌿🌿🌿🌿🌿🍁🍁🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

እርዱኝ እረዳችኋለሁ አንድ ትልቅ አረጋዊ በረጅም የሽምግልና ዘመናቸው ጆሯቸው ሳይደነግዝ ሁሉን ይሰማሉ፣ዓይናቸው ሳይፈዝ ሁሉን ያያሉ።አንድ ሰው ይጠይቃቸዋል እንዲህ ብሎ፦"አባ እግዚአብሔር ረድቶዎት
      እርዱኝ እረዳችኋለሁ      አንድ ትልቅ አረጋዊ በረጅም የሽምግልና ዘመናቸው ጆሯቸው ሳይደነግዝ ሁሉን ይሰማሉ፣ዓይናቸው ሳይፈዝ ሁሉን ያያሉ።አንድ ሰው ይጠይቃቸዋል እንዲህ ብሎ፦"አባ እግዚአብሔር ረድቶዎት ነው እንጂ በእርስዎ እድሜ ውስጥ ያሉት እኮ ዓይናቸው ዓያይም ጆሯቸው አይሰማም?" ይላቸዋል። እሳቸውም፦"ምን እግዚአብሔር ብቻ ይረዳኛል እኔም እግዚአብሔርን ረድቸው ነው እንጂ ወራት እየለየሁ ቅቤ እቀባለሁ፣በፀሐይ አላነብም፣ጨረር አላይም እና እኔስ እየረዳሁት አይደለምን? እግዚአብሔር የሚረዳን ስንረዳው ነው"ይሉታል። ታዲያ በሀገራችን ብሂልም "እርዱኝ እረዳችኋለሁ ብሏል" እየተባለ ይነገራል። ይሄንን ሀሳብ ወድጀዋለሁ እግዚአብሔር የነጻነት አምላክ ነው ወደን ፈቅደን የምናደርገውን መልካም ነገር ሁሉ ይባርክልናል።የድርሻችንን ሳንወጣ ግን እርዳን ማለት ትልቅ ስንፍና ነው። እግዚአብሔር አስገድዶ ምንም ነገር አድርጉ አይለንም። የሚጠቅመንን የሚያጸድቀንን እንድናደርግ ግን ይወዳል። ቁጭ ብለን እግዚአብሔር ይርዳን ብንል ግን ስንፍናን በሰማይ ሰሌዳ ላይ እንደመጻፍ ነው። "የተነቃነቀ ጥርስ ቢስቁበት አያደምቅ ቢበሉበት አያደምቅምና"ጠንክረን እንሥራ።