ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
رفتن به کانال در Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
نمایش بیشتر672
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+37 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
♡ ልቤ ያውቀዋል ♡ልቤ ያውቀዋል ያደረክልኝ ነገር የሰራህልኝን ስራ መድኃኔዓለም አወጣህኝ ከመከራ በቃል ጉልበት አይወራ (2)
አዝመስቀል ተሸክመህ በደም ርሰህ እኔን በመከራ ዳግም ወልደህ በክብር ተሻገርኩ ክሰህልኝ በህይወት አቆምከኝ ወድቀህልኝ
አዝየበደሌን ጋራ አቀበቱን የባርነት ሰነድ እዳ ክሱን አጥፍተህው ጌታ መድሀን ሆነ እርቃኔ በእርቃንህ ተሸፈነ
አዝበፍቅርህ መአዛ እርክቷል ልቤ በማይቆም መውደድህ ተከብቤ የህይወቴ ወደብ መስቀልህ ነው ወጀብ እና ንፍስ የማይነቅለው (2)
አዝየእሾህ አክሊል ደፍተህ ኤልሻዳይ እፎይ አለ ልቤ ከስቃይ ሆኖልኛል መዳን አንተ ተማህ ነፃ ወጣሁ ሸክሜን አንተ ተሸክመህ
አዝዙፍንህን አስተወህ የኔ ፍቅር ከሰማይ ሀገርህ መጣ በምድር ታየህ ስትፈልገኝ ልጄ ብለህ ፈራጅና አስዳቂ አምላኬ ነህ (2)
ይህን ያውቁ ኖሯል ?
ካቴድራል(የካቴድራል ቤተክርስትያን)
ካቴድራል ማለት ቃሉ ግዕዝ ወይም አማርኛ ሳይሆን ጥሬ ቃሉ ግሪክ ሲሆን ወደ ላቲን ሲተረጎም (cathedra) ካቴድራል ይላል፡፡ ይህም የጳጳስ መቀመጫ (ዙፋን) ማለት ሲሆን በጥንታዊያን ክርስቲያኖች አመለካከት ካቴድራል ማለት የሥልጣን ምልክት ማለት ነው፡፡ የካቴድራል ሕንጻዎች መሠራት ያለባቸው በትልልቅ ከተማዎች ነው እንጂ በአነስተኛ መንደር መሠራት የለበትም፡፡ የካቴድራል ቤተክርስቲያን በጣም ትልቅ ግዙፍ ሕንጻ ነው፡፡
ጥንታዊያን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ካቴድራል ተብሎ የተሰጣቸው ስያሜ የለም፡፡ ይህም ቃሉ ያልተለመደ የባዕድ ቃል በመሆኑ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1924 ዓ.ም የተሰራውን የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን እጅግ በሥፋቱ ትልቅ በመሆኑና ውበትን የተላበሰ ዘመናዊ ሕንጻ በመሆኑ ይህን በማየትና በማድነቅ በግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ቤተክርስቲያኑ ለመጀመሪያ ጊዜ የካቴድራል ስም ተሰጠው፡፡
ከላይ እንደተገለፀው ካቴድራል ሲባል ብዙ ምዕመናን የሚይዝ ትልቅና ውበት የተላበሰ በሕንጻ አሠራሩም ካሉት ሦስት ዓይነት የቤተክርስቲያን አሠራር ውስጥ ከምኩራብ (አራት መአዘን)፤ ከክብ ቤተንጉሥ ከዋሻ አሠራር ዓይነቶች ውስጥ ካቴድራል የምኩራብ ከኦሪቱ ትውፊት የተወሰደውን ዓይነት ቅርፅ የያዘ ነው፡፡ ካቴድራል ተብሎ የሚሰየመው ይህ ታላቅ ቤተክርስቲያን ብዙ ምዕመናንን አካቶ ከመያዙም በላይ ሦስት መንበር በቤተ መቅደሱ ወስጥ ሊኖረው ይገባል፡፡ ይህም በክብረ በዓል ጊዜ በሦስቱ መንበር የቅዳሴው ሥነ-ሥርዓት ተከናውኖ ምዕመናን በሥርዓት እንዲስተናገዱ ይረዳቸዋል፡
ምንጭ : በኢ/ኦ/ተ/ቤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ድህረገጽ
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel
+++ ጸልየህ ልታደርገው ትችላለህ? +++
ማልዶ ቤተ ክርስቲያን ተሳልሞ ወደ ሥራ የሚሄድ አንድ መንፈሳዊ ሰው በጉዞው ከሌላ መንገደኛ ሰው ጋር ይገናኛል። ጥቂት እንደ ተጨዋወቱ ይህ በመንገድ ያገኘው ሰው ከደረት ኪሱ የሲጋራ ፓኮ በማውጣት አንዱን መዝዞ እንዲወስድ ይጋብዘዋል። ያም መንፈሳዊ ሰው "አይ ይቅርብኝ" ሲል እምቢታውን ገለጸ። ባለ ሲጋራውም "ኃጢአት ነው ብለህ ስላሰብህ ነው እምቢ ያልከኝ? ማጨስ እኮ ከአስጨናቂዋ ሕይወት ፋታ ለመውሰድና ራስን ዘና ለማድረግ ይረዳል። ግድ የለህም አንዱን ሞክር" እያለ ሊያግባባው ጣረ። በመጨረሻም መንፈሳዊው ሰው "ግድ የለም ለእኔ ይቅርብኝ። ባይሆን አንተ ይጠቅመኛል ካልህ በቃ ሲጋራውን ከመለኮስህ በፊት አንድ "አባታችን ሆይ" ጸልይና ጀምር" አለው። በዚህ ጊዜ ያ መንገደኛ ደንግጦ እንዲህ ሲል መለሰ "ጸሎት ጸልዬማ እንዴት እንዲህ አደርጋለሁ?!"
በጸሎት ልትጀምር የማትችላቸው ማናቸውም ነገሮች ለአንተ መልካም አይደሉም። በልብህ ኃጢአት እንድታደርግ የሚገፉፉህ ክፉ ሐሳብ ሲመጣ "ይህን ጸልዬ ማድረግ እችላለሁ?" ብለህ ራስህን ጠይቅ። ከጸሎት ጋር የማይጣጣም ከመሰለህ እርሱ ኃጢአት ነውና ተወው። ጸልዮ የሚዘሙት፣ ጸልዮ የሚሰርቅ፣ ጸልዮ ባልንጀራውን የሚሳደብ፣ ጸልዮ በወንድሙ ላይ ክፉ የሚያደርግ ማን ነው?
"ዲያቆን አቤል ካሳሁን ከፃፈው የተወሰደ"
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel
ከሞተ በኋላ ስለሚኖረው ዕውቀት በመጨነቅ ራስህን አታታል። በዚህ ዓለም የዘራኸውን በሚቀጥለው ዓለም እንደምታጭድ እወቅ። ከዚህ ዓለም ሰው ከተወሰደ በኋላ ሥራ የሚሠራበት ሌላ ዓለም የለም ዋጋ የሚከፈልበት እንጂ። ሥራው ያለው እዚህ ነው፤ ሽልማት እዚያ ነው። ትግሉ እዚህ ነው የድል አክሊሉ እዚያ ነው።
✨ ቅዱስ ይስሐቅ ግብጻዊ✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel
✨🍂✨
ይሄ እንግዲህ በምናብ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያሉ ቅዱሳን እና ሐዋርያት በዛሬ ዘመን ቢኖሩ በማለት እና ለሰሯቸው ኃጢአቶች የኛ ግብረ መልስ ምን ሊሆን እንደሚችል በማሳየት የተጻፈ ነው።
ጥቂት ነገር ልጨምር። የቤተ ክርስቲያን ራስ ክርስቶስ ነው ፥ ከቶ የማይጥለን፣ ከቶ ታምነንበት አንገታችንን የማያስደፋን እርሱ ብቻ ነው። ወደ ቤተ ክርስቲያን የምትመጡ ሰዎች ሆይ ፈጥናችሁ ይሄን የቤተ ክርስቲያን ራስ ተመልከቱ።
✨🍂✨
ሁለተኛው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስት ጊዜ ለካደው ቅዱስ ጴጥሮስ የመንግስቱን ቁልፍ የሰጠ አምላክ ነው(ቁልፍ በጣም ለታማኝ ሰው፣ ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት የክህደት ታሪክ ለሌለው ሰው የሚሰጥ ነበር)። ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ ሰዎች አስመሳዮች ናቸው ካላችሁ በጣም ልክ ናችሁ ምክንያቱም እኔም ነኝ። የመጣነው ማስመስል ስለደከመን ነው። አንድ ቀን ፈጽሞ ከዚህ በሽታ ወደሚፈውሰን የቤተ ክርስቲያን ራስ ወደ ሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለመጣን ግን ፍጹም ደስተኞች ነን። በሽተኞች ሆይ ኑ ፥ እሱም በውጋት በሽታ የሚሰቃየውን፣ ለቤተ ክርስቲያን ያለውን ንዴት መቆጣጠር አቅጦት እስጢፋኖስ የሚባል ምስኪን ወጣትን በድንጋይ አሶግሮ ያስገደለውን ፥ በልብሱ ጥላ ግን በሽተኞችን የሚፈውሰውን የክርስቶስ አገልጋይ ቅዱስ ጳውሎስን በቤተ ክርስቲያን ታገኙታላችሁ።
📝ሙሉዓለም ጌታቸው እንደጻፈው
📚 ጃንደረባው ሚድያ
✨✨✨🍂✨🍂✨🍂
✨✨✨🍂✨🍂✨🍂
ከቤተ ክርስቲያን የሚያሸሹን ሰዎች
ብዙዎቻችን ከቤተክርስቲያን የምንርቅበትን ወይም ከክርስትና የወጣንበትን ምክንያት ስንገልጽ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ አገልጋዮችን እንደምክንያት እንጠቅሳለን። የእናንተን አላውቅም እኔ ግን እንደዛ እል ነበር። እንደሚመስለኝ ብዙ ሰዎች ከጳጳሳቱ ጀምሮ እስከታች እስካሉት ዲያቆናት ማንነት እየጠቀሱ ምን ያህል አስመሳዮች እና ኃጢአተኞች እንደሆኑ በመናገር፣ ሁሉም ውሸታሞች ስለሆኑ ከክርስትና እንደራቁ ይናገራሉ።
እንዲህ የሚሉ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጠቀሱ ቅዱሳንን ምን ያህል እንደሚያውቋቸው አላውቅም። ማወቅ ስል በእውነት ከምር ማወቅን ነው እንጂ በስም እና በታሪካቸው ማለቴ አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያሉ ቅዱሳንን እነሱ በነበሩበት ሰዓት አይቶ ወደ ቤተክርስቲያን የመጣ ክርስቲያን ፥ በርግጎ ነው ከቤተክርስቲያን የሚወጣው እና መቼም የማይመለሰው። ለምሳሌ እነዛ ቅዱሳን በዚህ ዘመን ያሉ ናቸው ብለን እንውሰድ።
✨✨🍂✨
ኖኅ የሚባል በዕድሜው ያረጀ ትሑት የእምነት ሰው እና ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የታወቀ አባት ነበር፤ ይሄ ሰው "ብዙ ሰዎችን አጥምቆ ክርስቲያን አድርጓል" ግን ምን ያደርጋል ጥቂት ሰዎች ደግሞ በወይን ጠጅ ሰክሮ ራቆቱን ሲንገዳገድ እና የሌሎች እምነት ተከታዮች አይተው ሲሳለቁ እና በክርስትናው ላይ ሲያሾፉ አየተው ፥ እርም ብለው ከቤተ ክርስቲያን ርቀዋል።
እና አንድ ሰው የአብርሃምን እምነት አይቶ ቤተ ክርስቲያን መጣ። ወዲያው ግን አብርሃም ምን ያህል ፈሪ እንደሆነ እና የራሱን ሕይወት ለማትረፍ ሚስቱን አሳልፎ እንደሰጠ ያያል። ከዛ ይሄ አስመሳይ ነው ብሎ፣ “እውነተኛ መስሎኝ እንጂ ሚስቱን እኅቴ እያለ የራሱን ሕይወት ለማትረፍ የሚሳሳ ፈሪ” ብሎ ከቤተ ክርስቲያን ይጠፋል።
✨✨🍂✨
አንዷ በቀደም መጥታ ደግሞ እንዲህ አለችኝ። "ይሄ ቤተ ክርስቲያን የጥቂት ብሔሮች ነው፣ የሰሜኖቹ ነው" አለችኝ። "ለምን?" ስላት ፥ ስለማርያም እየተንዘከዘከች ተናገረች። "ቆይ ፥ ቆይ ስለየትኛዋ ማርያም ነው የምትይው?" አልኳት ደንግጬ። "የታላቁ ነቢይ ሙሴ እህት ናታ፣ ከበሮ እያነሳች መዘመር የማይሰለቻት፣ እንደውም ባለፈው የመከራን ባሕር እግዚአብሔር ከፍሎ ሲያሻግረን የሷን መዝሙር አይደለ እንዴ የዘመርነው፤ ትዝ አይልህም ፥ 'በክብር ከፍ ከፍ ብሎአልና ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ ፈረሱንና ፈረሰኛውን በባሕር ጣለ' የሚለው መዝሙሯ" አለችኝ። "አዎ! አወኳት" ስላት ፥ "በማስረጃ እንዴት ዘረኛ እንደሆነች ፥ ወንድሟ ከሌላ ዘር በማግባቱ ቁም ስቅሉን እያሳየችው መሆኑን እና ሚስቱን ሲፓራን ማስለቅስ ልማዷ መሆኑን" ነገረችኝ። "እንደውም ወንድሟ ያ ካህኑ አሮንም የማርያምን ሀሳብ ደግፎ ቆሟል ነው የሚባለው" አለችኝ። እኔም ይሄን የጸና የዘር ደዌ ቤተክርስቲያን ላይ ያሉ አንዳንድ ሰዎች ላይ አይቼ ስለተከፋው ለዚች ልጅ ምን ብዬ እንደማጽናናት ግራ ገባኝ። ሌላ ጊዜ ተገናኝተን ለማውራት ቀጠሮ ይዘን ብንለያይም ፥ እሷ ግን "የሷ ዘር ሰዎች በቅርብ ያቋቋሙት ሲኖዶስን መቀላቀሏን እና ከኔ ጋር መነጋገር አስፈላጊ እንዳልሆነ" ቴክስት ላከችልኝ።
ሌላው ደግሞ ሳምሶንን ዓይቶ፣ በጸጉሩ ማማር ተማርኮ፣ በጀግንነቱ እና ስለቤተክርስቲያን (እስራኤል) ያለው ቅናት አስደምሞት ቤተ ክርስቲያን መምጣት ይጀምራል። ይሄ ሰው ለሚስቱ ታማኝ ስለሆነ የሚዘሙት ሰው ሁሉ ይጠየፋል። ከዛ ሳምሶንን ሲዘሙት እና ከብዙ ሴቶች ጋር ያልተገባ ድርጊት ሲሰራ ያየዋል፣ ይሄ ብቻ ሳይሆን ለሴት ሲል ያ አስደማሚ ጸጉሩን ተላጭቶ ይመለከተዋል። “ሁሉ ነገር ውሸት ነው፣ አታላዮች እና አስመሳዮች ናቸው፣ እዛ የተሰበሰቡት ሁሉ ሌቦች ናቸው!” እያለ ቤተክርስቲያን ካሉ ሰዎች ይልቅ በዓለም ያሉ ሰዎች መልካም እንደሆኑ እየተናገረ ከቤተክርስቲያን ይጠፋል።
የቅርብ ጓደኛዬ ደግሞ በድምጹ ማማር፣ በበገና አደራደሩ፣ በመዝሙሮቹ ግጥም ጥንካሬ እና ውበት፣ ለክብሩ ሳይጨነቅ እግዚአብሔርን ጨርቁን ጥሎ ያመለከውን ዳዊትን ዓይቶ ቤተክርስቲያን ይመጣል፣ ሰንበት ትምህርት ቤት እየመጣ የዳዊትን መዝሙሮች ይከታተላል፣ ዳዊት አለ በተባለበት ጉባኤ ሁሉ ይገኛል። ከዛ ከእለታት አንድ ቀን ዳዊትን ከኦርዮ ሚስት ቤርሳቤህ ጋር ሲማግጥ ያየዋል፤ የሚያየውን ማመን ተሳነው። ያ ዳዊት፣ ያ በበገናው አጋንንት ሲያሶጣ ያየው ዳዊት፣ ያ ጨርቁን ጥሎ እግዚአብሔርን የሚያመልከው ዳዊት፣ ያ ጀግናው ዳዊት ሲልከሰከስ ዓየው፤ ይሄን ለማስታረቅ ተቸግሮ እና በግራ መጋባት ውስጥ እያለ ከሁነኛ ወዳጁ “ዳዊት ቤርሳቤህን እንዳስረገዘ እና ኦርዮን ሰምቶ እንዳያዋርደው ኦርዮንን ማስገደሉን” ይሰማል። ክሩን በጠሰ። ጾሙን አቆመ። ነጠላውን ወረወረ። ድሮም ሲሉኝ አልሰማ ብዬ እንጂ ሁሉም አጭበርባሪ እና አታላይ ናቸው አለ። ሁለተኛ ቤተክርስቲያን ላይሄድ እና መስቀል ላይሳለም ማለ። “ክርስትና ከነበረም ድሮ ነው። ሁሉም ከክርስቶስ ጋር ወይም በዛ ዘመን አብቅቶለታል” ብሎ ደመደመ።
አንዲት ሴት ደግሞ አስቴርን ተመልክታ መጣች። ይሄን የመሰለ ውበት እና እውቀት ኖሯት ከቤተክርስቲያን አለመራቋ እና በኪነጥበብ ክፍል ውስጥ ያላትን አገልግሎት ተመልክታ እሷም ቤተክርስቲያን ለመቅረት ወሰነች። አስቴር በዘመኑ የነበረውን ኃያል ጄኔራል አገባች። ሰውዬው ክርስቲያን አልነበረም። በዛ ላይ ክርስቲያን የሚጠሉ ሰዎችን እንደ ሃማ ያሉትን ነው በዙሪያው የሰበሰበው። ይሄ ግራ ገባት። ድሮ የምታቃት አስቴር አልሆንልሽ አላት። ስለዚህ ቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ ሰዎች ሁሉ የስጋ ምኞታቸው እስከሚፈጸም እዛ ያሉ መስሎ ታያት። ቀስ እያለች ቤተክርስቲያን መምጣቷን ቀነሰች። ለሷም ለአስቴርም ወዳጅ የነበረች ልጅ “አስቴር ጄኔራሉ አብያተክርስቲያናት እንዲቃጠሉ ማዘዙን ሰምታ ምንም አለመናገሯ ሳያንስ ወንድሟ አስልኮባት ራሱ ጄኔራሉን ባሏን ተው ብላ ለመገሰጽ እያመነታች” መሆኑን ስተሰማ ፥ ከቤተክርስቲያን ቀረች ቀረች።
✨✨🍂✨
አሁን በቅርቡ ደግሞ ጴጥሮስ የተባለው የቤተክርስቲያን መሪ እና ቤተክርስቲያኒቷ አለኝ የምትለው ታማኝ፣ ፈጣን አቧቷ ባለፈው በሀገር ደረጃ በመንግስት አቀነባባሪነት ቤተክርስቲያንን ለማሳደድ፣ ከተቻለም ለማጥፋት በተነሳው መከራ ሰዓት እና ቤተክርስቲያኒቷን ቁም ስቅሏን መንግስት ሲያሳያት ፥ በአደባባይ “መንግስት ምንም ኣላደረገም፣ እኔ ምስክር ነኝ ፥ ችግሩ እንደውም ከቤተክርስቲያኒቱ ነው” ብሎ መናገሩ ቀላል የማይባሉ ክርስቲያኖችን አሳዝኗል። እሱ ብቻ ሳይሆን አንዳንዶች “አባ ጴጥሮስ እንደዛ እያሉ እኛ የማን ቤት ነን ቤተክርስቲያንን የምንጠብቀው እና መንግስት ጋር እሰጣ ገባ የምንገባው” ብለው ከቤተክርስቲያን ከቶውንም ርቀዋል። በርግጥ ጥቂት ሰዎች “አባ ጴጥሮስ በተናገሩት ነገር እጅጉን ተጸጽተው ማልቀሳቸውን አይተው” ተናግረው ነበር። ግን ሰው የተናገሩትን በአደባባይ ስላየ እና መጸጸታቸውን በይፋ ስላልተመለከተ ወሬውን አላመነውም። እኔም ራሱ አባ ጴጥሮስ እንደዛ ማድረጋቸው ደብሮኝ እርም ክርስቲያን ብያለው።
የሚገርመው እኮ ከአንዱ ጳጳስ ውጪ ሁሉም፣ በዛ መንግስት በቤተ ክርስቲያን ላይ ግፍ በሚፈጽምበት ወቅት ፥ ከክርስቲያኖች ጋር ተገኝቶ የቤተ ክርስቲያንን መከራ የተካፈለ የለም። አባ ናትናኤል ብትል፣ አባ ፊሊጶስ ብትል፣ አባ ያዕብቆ ብትል፣ በርተለሜዎስ፣ አባ እንድርያስ ሁሉም እኮ ነው ሸሽተው የተደበቁት። ያ ምስኪን ዝምተኛ አባት፣ አባ ዮሐንስ ብቻ ናቸው እስከመጨረሻው ከምዕመናን ጋር ጸንተው የታዩት።
✨✨✨🍂
+1
የኬኒያው ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ለገሱ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሀገረ ኬንያ የናይሮቢ እምብርት ላይ ዓመታትን ያስቆጠረ ቤተ ክርስቲያን አላት።
ሁለተኛውን ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ሰሞኑን ገንብታ ለአገልግሎት አብቅታለች::
ይህ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ኬንያ መርሳቤት ክፍለ ሀገር ለኢትዮጵያውያን ስደተኞች የተገነባ ነው።
ቤተ ክርስቲያኑን የምሥራቅ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ እና ሌሎች አባቶች በቦታው ድረስ በመሄድ ባለፈው ሳምንት ባርከው አገልግሎቱን አስጀምረዋል::
ይህንን የተመለከቱት ፕሬዝዳንት ሩቶ እና የአካባቢው አስተዳደር ደስታቸውን ገልጸዋል።
ቤተ ክርስቲያኑ ከኢትዮጵያውያን ባለፈ በአካባቢው ለሚኖሩ ኬንያውያንም ወደ እግዚአብሔር ቤት መሰባሰቢያ እንደሚሆን በመተማመን ለቤተ ክርስቲያኗ የገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል።
ፕሬዝዳንቱ እና የአካባቢው አስተዳደር ያሰባሰቡትን ግማሽ ሚሊዮን ሽልንግ [በአሁኑ ምንዛሬ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ] ዛሬ ለናይሮቢ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አስረክበዋል።
©አቡቀለምሲስ ሚዲያ
"በምትጾሙበት ጊዜ እንደ ግብዞች አትጠውልጉ እነርሱ እንደ ጾሙ ለሰው ይታዩ ዘንድ መልካቸውን ይለውጣሉና እውነት እላችኋለኹ ዋጋቸውን ተቀብለዋል እናንተስ በምትጾሙበት ጊዜ ራሳችኹን ቅቡ ፊታችኹንም ታጠቡ በስውር ለሚያይ ለአባታችኹ እንጂ ለሰዎች እንደ ጾማችኹ እንዳትታዩ በስውር የሚያያችኹ አባታችኹም ዋጋችኹን በግልጥ ይሰጣችኋል።"
🌹አንቀጸ ጾም🌹
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️
"እግዚአብሔርን ስለምትወድ ስለ አገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ይሰጣት ዘንድ ጸልዩ"🤲🤲🤲
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel2
ዐርባ አራት ንዑሰ ክርስቲያን ተጠመቁ::
* ኢጃት ከሆሊ ሶፊያ ዩኒቨርስቲ ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራረመ
* እስከ ኅዳር 2018 ዓ.ም. ድረስ አርባ አራት ንዑሰ ክርስቲያን ተጠምቀዋል::
* የንዑሰ ክርስቲያን መድበል (Catechetical Document) ለኅትመት ዝግጅት ላይ ነው::
* ታኅሣሥ አጋማሽ ላይ ልዩ የዕቅበተ እምነት ዐውደ ጥናት ሊካሔድ ነው::
ጃንደረባው ሚድያ | ኅዳር 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ | ኢትዮጵያ
ኢጃት ጃን ማዕተብ በተሰኘው ፕሮጀክት በ2017 ዓ.ም. ከሰባ በላይ ንዑሰ ክርስቲያንን አስተምሮ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ማስረከቡ "ወደ ኦርቶዶክስ መመለስ" ከሚል ዘጋቢ ፊልም ጋር መታየቱ ይታወቃል:: በ2018 ዓ.ም. ለመጠመቅ በትምህርት ላይ ያሉትን አራት ንዑሰ ክርስቲያንን ጨምሮ ከሰኔ ወር ጀምሮ የቅድመ ጥምቀት ትምህርት የተማሩ ተመላሾች በአዲስ አበባ ሃያ የደረሰ መሆኑን በኢጃት የጃን ማዕተብ ሰብሳቢ ዶ/ር ቤተልሔም ገልጻለች::
በኢጃት ሐረር የጃን ማዕተብ ደግሞ ባለፉት ስድስት ወራት ሃያ ሦስት ንዑሰ ክርስቲያን ተምረው እንደተጠመቁ የኢጃት ሐረር ጃን ማዕተብ ሰብሳቢ ዲያቆን ቢንያም ገርጂ ገልጸዋል:: በኢጃት ድሬ በምሥረታ ላይ የሚገኘው ጃን ማዕተብ ደግሞ አንድ ንዑሰ ክርስቲያን እያስተማረ መሆኑም ታውቆአል:: ንዑሰ ክርስቲያኑ ከእስልምና ፣ ከፕሮቴስታንት ፣ ከኤቲይዝምና ከተሐድሶ ፕሮቴስታንቲዝም የመጡ ሲሆን ከጥሙቃኑ ውስጥ በተሐድሶ እንቅስቃሴ መሪ የነበሩም ይገኙበታል:: በቅርቡም በጃንደረባው ሚድያ በራሳቸው አንደበት የመመለስ ጉዞአቸውን ለሌላው ትምህርት እንዲሆን እንደሚመሰክሩ ተገልጾአል::
በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ በአንድ ለአንድ (One to One) የዕቅበተ እምነት አገልግሎት ላይ የሚያገለግሉ አገልጋዮችን እጥረት ለመቅረፍና በትምህርት ዝግጅት ለማጎልበት በኦርየንታል አብያተ ክርስቲያናት ከሚገኙ ስመ ጥር ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ከሆነው ከሆሊ ሶፊያ ዩኒቨርስቲ ጋር የትብብር ስምምነትን ተፈራርሞአል::
ኢጃት ንዑሰ ክርስቲያንን የሚያስተምረው የአንድ ለአንድ (one to one) ሥልትን በመከተል እንደመሆኑ ከልዩ ልዩ እምነቶች ወደ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ተምረው መመለስ የሚሹና ሳይክዱ በፊት እንዲማሩ በቤተሰቦቻቸው ተጠቁመው የሚመጡት ተማሪዎች ቁጥር እጅግ ብዙ በመሆኑ በንዑሰ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ የሚያስተምሩ ወንድሞችና እኅቶችን በብዛት ማሠልጠን አስፈልጓል:: መምህራን ለዐውደ ምሕረትና ለመድረክ አገልግሎቶች ያላቸውን ፈቃደኝነት አንድን ሰው ለብቻው ቁጭ አድርጎ በማስተማር አገልግሎት ላይ አለማሳየታቸው ለዚህ አገልግሎት ፍላጎት ያላቸውን ወንድሞችና እኅቶች ማብዛትን የግድ አድርጎታል::
ኢጃት ለንዑሰ ክርስቲያን አገልግሎትና በአጠቃላይ የመምህራንን አቅም ለማጎልበት ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል የተመረጡ አባላትን በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ በሆሊ ሶፍያ ዩኒቨርሲቲ ነገረ መለኮትን እንዲማሩ ማድረግ ሲሆን በተለይም በአሕዛብ በመከበብዋ ምክንያት በዕቅበተ እምነት ሥራ የካበተ ልምድ ካላት ከግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጋር በንዑሰ ክርስቲያን ትምህርትና አቀባበል ላይ ሥልጠናዎችን መውሰድ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቶአል:: በዚህም መሠረት ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የማኅበራት ምዝገባና ክትትል መምሪያ በተጻፈ የድጋፍ ደብዳቤ መሠረት ንዑሰ ክርስቲያንን ለሚያስተምሩ ተተኪዎች የትምህርት ዕድል ስምምነትን ከዩኒቨርስቲው ጋር አድርጎአል::
ስምምነቱን የተፈራረሙት በሆሊ ሶፊያ ዩኒቨርስቲ በኩል ዲን ዶ/ር አብርሃም አዝሚ ሲሆኑ በኢጃት በኩል ደግሞ የሆሊ ሶፊያ ዩኒቨርስቲ የማስተርስ ዲግሪ ምሩቅ የሆኑት ዲ/ን ዶ/ር ቶማስ ሽመልስ ናቸው::
በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዋድሮስ ፓትርያርክ ፕሬዝዳንትነት የሚመራው የሆሊ ሶፊያ ዩኒቨርሲቲ መሥራችና ዲን የሆኑት ዶ/ር አብርሃም አዝሚ ሆሊ ሶፊያ ዩኒቨርሲቲ በአረቢኛ ፣ በጀርመንኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞችን እያስተማረ መሆኑን ገልጸው በኢጃት በኩል መሥፈርቱን አሟልተው ለሚማሩ የዕቅበተ እምነት አገልግሎት ላይ የሚያገለግሉ ወጣቶች የሚሠጠውን የትምህርት ዕድል የኢትዮጵያዊው ጃንደረባን ታሪክ በማሰብ "የቅዱስ ፊልጶስ የትምህርት ፕሮግራም" ብለው መሰየማቸውን ገልጸዋል::
ዲ/ን ዶ/ር ቶማስ በበኩላቸው "በኢጃት በኩል ከሌላ እምነት ለሚመለሱ ንዑሰ ክርስቲያን ማስተማሪያ የሚውል የንዑሰ ክርስቲያን መድበል (Catechetical Document) ዝግጅት እየተጠናቀቀ ነው:: በሆሊ ሶፊያ ዩኒቨርሲቲ የተገኘው የትምህርት ዕድል ደግሞ ከዕቅበተ እምነትም ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ነው:: ከዩኒቨርሲቲው ጋር በተዋዋልነው መሠረት አንዳንድ የትርጉም ሥራዎችን ካጠናቀቅን አስፈላጊ ኮርሶችን በሥልጠና መልክ በአማርኛ ቋንቋ ተደራሽ ለማድረግም ዕቅድ ይዘናል" ብለዋል:: በታኅሣሥ ወር አጋማሽ ላይ በዓይነቱ ልዩ የሆነ የዕቅበተ እምነት ዐውደ ጥናት እንደሚኖርም ገልጸዋል::
#ሠረገላው_ይቆም_ዘንድ_አዘዘ
#የሚከለክለኝ_ምንድን_ነው
✨️️️️✨️️️️🍂🌿🌿✨️️️️✨️️️️
ሰውን የሚጥለው መመካቱ ነው
ወንድሜ ሆይ በሥራህ ሁሉ የታመንህ ሁን አገልጋይ ባልንጅሮችህን ውደዳቸው። ንጹሑን አረጋዊ መቼም መች አክብረው።
ወንድሜ ሆይ በታላላቆች መሃል አትቀመጥ። ተቀመጥ እስኪሉህ ድረስ ቁም እንጅ በሽማግሌዎች መካከል አትቀመጥ፤ በዝቀተኛው ማዕርግ ተቀመጥ እንጅ።ወንድሜ ሆይ ቁጡ ወይም አንጎራጓሪ አትሁን፤ በጸሎት ጊዜ ሐኬተኛ አትሁን፤ በጸሎት ጊዜ ምንም ተግባር ለመፈጸም ወዲያና ወዲህ አትናወጽ። እንዳትዋረድ በሊቅ በአዋቂ መሃል አትናገር። ✨️️️️🍂✨️️️️ ልጄ ሆይ በጽድቅህ አትመካ፤ ራስህን አታመስግን፤ ሰይጣን ትምክሕትን እንዳያመጣብህ ራስህን በፈቃድህ አዋርድ እንጅ። በትዕቢትና ትምክሕት ሰዶምና ገሞራ ወደቁ። ከእግዚአብሔር መንገድም ተሰናከሉ። ትምክሕተኛውን መነኩሴ ፈተና ያገኘዋል፤ መንፈስ ቅዱስም ይለየዋል፤ የዲያብሎስ መንፈስም ያድርበታል። በሥራችሁ ሁሉ አትመኩ፤ ሁሉም ሰው እግዚአብሔር የሰጠውን ይሠራል እንጅ ከራሱ የሆነ ምንም የለምና። ነቢይ የተናገረውን አልሰማችሁምን? ፈጽማችሁ አትመኩ ታላላቅ ነገርንም አትናገሩ፤ ክፉ ነገርም ከአንደበታችሁ አይውጣ። 📚መጽሐፈ ወግሪስ - ገጽ 84-85 📝በአባ ገብረ ኪዳን ✨️️️️✨️️️️🍂🌿🌿✨️️️️✨️️️️ የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel2
"ጌታዬና ንጉሤ ሆይ የራሴን ኃጢአቶች እመለከት ዘንድ እና በወንድሜ ላይ እንዳልፈርድ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ድረስ አመሠግንህ ዘንድ ማስተዋሉን ስጠኝ።"
ቅዱስ ኤፍሬም
🌹ኅዳር 12🌹
🌹እንኳን አደረሳችሁ🌹
🌹ኅዳር ቅዱስ ሚካኤል🌹
ለሰው ወገን የሚያዝንና የሚራራ፥ በእግዚአብሔር የጌትነት ዙፋን ፊት ሁልጊዜ ለምስጋና የሚቆም፥ ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ፥ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሢመቱና እስራኤላውያንን በባሕረ ኤርትራ ያሸገረበት በዓል ነው፡፡
በዓለ ሢመቱ፤ ሚካኤል ማለት ማን እንደ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ በእለተ እሁድ ካለመኖር ወደ መኖር የመጣ ሲሆን እርሱም የነገደ ኃይላት አለቃቸው ነው በተጨማሪም ከሳጥናኤል ውድቀት በኋላ የአጋእዝትን ነገድም በአለቅነት ደርቦ የያዘ ሲኾን፤ ለ100ውም(99ኙም) ነገደ መላእክት አለቃቸውም ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 (በዓለ ሢመቱ) ጀምሮ እስከ 13 (የአእላፍ መላእክት) በዓል ድረስ ከአምላኩ ምሕረትን የሚለምንበት ነው፡፡
በዚህ ቀን የሚከበረው እስራኤልን ከግብጽ ባርነት እየመራቸው ማውጣቱን ለማዘከር ነው፡፡
ይህም የሆነው ያዕቆብ በረሃብ 70 ኹኖ ወደ ግብፅ ከወረደ በኋላ በ215 ዓመታት (አብርሃም ወደ ግብፅ በተሰደደ በ430 ዓመታት) በኋላ፤ የዮሴፍን ዝና ያልሰማ ፈርኦን በግብፅ ነገሠ፡፡ እስራኤል ከእኛ ይልቅ በዝተዋል ጠላቶቻችን ቢነሱብን ተደርበው ያጠፉናል በማለት አገዛዝ አጸናባቸው ፍርድ አጓደለባቸው፡፡ የእስራኤል ሴቶች ልጅ ሲወልዱ ወንድ ከሆነ እንዲገደል በማድረግ መከራ አጸናባቸው፡፡ 430 ዘመን በባርነት ከቆዩ በኋላ ከእብራውያን ወገን የሆነችው ራሔል ጭቃ እያቦካች ምጥ በያዛት ጊዜ እንዲያሳርፏት ጠየቀች ግብጻውያን ግን የሕፃናቱ ደም ጡቡን ያጠነክራል እርገጭ አሏት፡፡ ከመሐጸኗ የወጡ ሁለት መንትያ ልጆቿን እያየች ከጭቃ ጋር ረገጠች፡፡ ራሔልም አለቀሰች ስለ ልጆቿም መጽናናትን እንቢ አለች፡፡ የእስራኤል ንጉሥ ሆይ የሆነብንን እይ ስትል ራሷን ይዛ ታለቅስ ጀመር እንባዋንም ወደ ሰማይ ንጉሥ ወደ እግዚአብሔር ረጨች፡፡ የራሔል እንባ የሕዝበ እስራኤል ሁሉ ጩኸት እሮሮ ይዛ ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰች፡፡ “. . . ራሔል ስለ ልጆቿ አለቀሰች የሉምና ስለ ልጆቿ መጽናናት እንቢ አለች” /ኤር 31፥5፤ ማቴ 2፥17/ እንዲል፡፡
ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ሙሴን አስነሳና፤ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል መሪነት፤ 10 ተዓምራትን በምድረ ግብፅ በ11ኛ ተዓምር ደግሞ በኅዳር 12 (ፈርዖንን ከነሠራዊቱ በኤርትራ ባሕር አስጥሞ) ድል በማድርግ ወደ ተስፋይቱ ምድረ መራቸው፡፡
ባሕረ ኤርትራን እስራኤላውያን እንደተሻገሩም የእስራኤል ልጆች የሙሴ የአሮን እኅት ማርያም ከበሮ እየመታች ንሴብሆ ለእግዚአብሔር ስቡሐ ዘተሰብሐ እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው እያሉ ጠላታቸውን የመታላቸውን እነሱንም በተአምራቱ ያሻገራቸውን ከጠላታቸው እጅ ያዳናቸውን እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ከዚህ በኋላ መጋቢ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው መና ከሰማይ እያወረደላቸው ውሃ ከጭንጫ እያፈለቀላቸው ቀኑን በደመና ሌቱን በብርሃን መርቷቸው አርባ ዘመን ተጉዘው የቃል ኪዳን አገራቸው ምድረ ርስት ከነዓን ገብተዋል፡፡ /ዘጸ 15/
ከሙሴ በኋላ እስራኤልን የመራው ነቢዩ ኢያሱም እስራኤልን በሚመራበት ጊዜ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እስራኤልን ይረዳቸው ነበር፡፡ ከጠላቶቻቸው ጋር ሲዋጉም ሰልፉን ይመራ የነበረው ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ለምሳሌ እስራኤላውያን ከኢያሪኮ አጠገብ በነበሩበት ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ኢያሱን አነጋግሮታል፡፡
ኢያሱ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ቀና ብሎ ሲመለከት የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ አንድ ሰው ከፊቱ ቆሞ አየ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ “ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” ሲል ጠየቀው፡፡ እርሱም “አይደለሁም ነገር ግን የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ በመሆኔ መጥቻለሁ” ብሎታል /ኢያሱ 5፥13-15/፡፡ ይህ የተመዘዘ ሰይፍ ይዞ ከኢያሱ ፊት ለፊት የቆመው መልአክ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ ይህን ለአብነት አነሣን እጅ እስራኤል በሚበድሉበት ጊዜ ሁሉ ወደ እግዚአብሔር የሚማልድላቸው ይህ ታላቅ መልአክ መጋቢ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በእደ መልአኩ ይጠብቀን፤ ከበዓሉ በረከት ይክፈለን፡፡
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel2
"በችግር ጊዜ እግዚአብሔር የት አለ? አትበል እግዚአብሔር በመከራ ውስጥ ሆነህ እርሱን እንድትጠራው እየጠበቀህ ነው።"
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
