ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
رفتن به کانال در Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
نمایش بیشتر672
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+37 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
+9
ፎቶ :- 24/11//2017 ዓ.ም
ፍኖተ ወንጌል አረንጓዴ አሻራዋን አስቀምጣለች።
የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አባላት በዛሬው እለት በተከናወነው 700 ሚሊየን ችግኝ የመትከል ዘመቻ ላይ በንቃት ተሳትፈዋል።
+3
ፎቶ :- 24/11//2017 ዓ.ም
ፍኖተ ወንጌል አረንጓዴ አሻራዋን አስቀምጣለች።
የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አባላት በዛሬው እለት በተከናወነው 700 ሚሊየን ችግኝ የመትከል ዘመቻ ላይ በንቃት ተሳትፈዋል።
አረንጓዴ አሻራ ከፍኖተ ወንጌል ጋር
ነገ ማለትም ሀሙስ 24/11/2017 ዓ.ም ለሚከናወነው ሀገር አቀፍ ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ላይ እኛም እንደ ቤተ ክርስቲያን እና እንደ ደብራችን በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል የራሳችንን አሻራ ለማኖር ጥዋት 12 ሰዓት ላይ መገኛችንን በአሰላ መስቀል አደባባይ እንድታደርጉ ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት
እሳት የማያቃጥላት ዕፅ
እሳት ከነደደ የማያቃጥለው ዛፍ የለም።
ነቢዩ ሙሴ ግን እሳት እየነደደባት እሳት የማያቃጥላት ፅፀ ጳጦስ የተባለች ዛፍ በደብረ ሲና አይቶ ተደንቆ ነበር።
ያቺ ዕፀ ጳጦስ የድንግል ማርያም ምሳሌ ናት።
እሳቱ ከዛፏ ጋር እየነደደ ቢታይም እንዳላቃጠላት ሁሉ፥ ድንግል ማርያምም ጌታችን ክርስቶስን ጸንሳ በወለደች ጊዜ እሳተ መለኮቱ አላቃጠላትም። አንድም፥ እሳት የተባለ ሞት ነው። ሁሉንም ዛፎች ማውደም የሚችለው እሳት ዕፀ ጳጦሷን ማቃጠል እንዳልቻለ ሁሉ፥ የአዳምን ልጆች በሙሉ የሚበላውና የበላው ሞትም፥ በእርሷ በእመቤታችን ላይ በእሳት አምሳል ታይቷል፤ አፍርሶ አበስብሶ ያስቀራት ዘንድ ግን አልተቻለውም።
እሳተ መለኮት ያላቃጠላትን ጳጦስ፥ አዳም በዕፀ በለስ ያነደደው እሳት/ሞት እንዴት ያቃጥላት ዘንድ ይቻለዋል?
✍ሊቀ ሊቃውንት ስሙር አላምረው
"እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፡፡" (ሉቃ 1:19)
እንኳን አደረሳችሁ! ለቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት እየሉጣ ፈጥኖ የደረሰ መልአክ ለእኛም ይድረስልን፤አሜን!
ቅዱስ_ቂርቆስና_እናቱ_ቅድስት_ኢየሉጣ (#ሐምሌ_19)
ሐምሌ ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ። ይህም ሕፃን ዕድሜው ሦስት ዓመት ሲሆነው ከሮሜ አገር ወደሌላ ሀገር እናቱ ይዛው ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኰንን አገኘችው።
ሰዎችም ነገር ሠሩባት ወደርሱ አስቀረባትና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኰንን ሆይ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነው ሕፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እርሱን ጠይቅ አለችው።
ሕፃኑም ወደአለበት ጭፍራውን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕፃኑም መልሶ አዎ ለእኔ ደስታ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ልቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስከ አስደነገጣቸው ድረስ ንጉሡን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሣ አደነቁ።
መኰንኑም በአፈረ ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ሥቃይን አሠቃየው እናቱንም ከርሱ ጋር እንደ እርሱ አሠቃያት እግዚአብሔርም ያለምንም ጉዳት ያነሣቸው ነበር። ብዙዎች አሕዛብም ይህን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበሉ።
በሕፃኑ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ በታላቅ የናስ ጋን ውስጥ ውኃ ጨምረው በእሳት ያፈሉት ዘንድ አዘዘ የፍላቱም ድምጽ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ሆነ ያን ጊዜም ፍርሀትና የሃይማኖት ጉድለት በእናቱ ላይ ደረሰባት ሕፃኑም ስለ እናቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ።
ያን ጊዜ ጌታችን ልቧን ወደ ሰማይ አሳርጎ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁ የብርሃን ማደሪያዎችን አየች ከዚህም በኋላ ጸናች እግዚአብሔርንም አመሰገነችው ልጅዋንም ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አንተ አባቴ ነህ እኔም ልጅህ ነኝ አለችው።
ያቺ ከኔ የተወለድክባትም ቀን የተባረከች ናት አለች ወደዚያ ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው እንዲጐትቷቸው አዘዘ ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ አዳናቸው መኰንኑም በታላቅ ሥቃይ ያሠቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው።
ያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕፃኑ ቂርቆስ ወርዶ አጽናናው አረጋጋውም። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጠው።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሐምሌ ➛ ስንክሳር ዘተዋሕዶ ፌስቡክ ገጽ የተወሰደ)
" በሰዎች ዘንድ አጥብቀህ ብትፈልግና ብታንኳኳ ነዝናዛ ተደርገህ ትቆጠራለህ። በእግዚአብሔር ዘንድ ግን እርሱን ባለማስቸገርህና ባለመነዝነዝህ እጅግ ታሳዝነዋለህ።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
መዝሙረ ዳዊት 12
፩ አቤቱ፥ አድነኝ፤ ደግ ሰው አልቆአልና፥ ከሰው ልጆችም መተማመን ጐድሎአልና።
፪ እርስ በርሳቸው ከንቱ ነገርን ይናገራሉ፤ በሽንገላ ከንፈር ሁለት ልብ ሆነው ይናገራሉ።
፫ የሽንገላን ከንፈሮች ሁሉ እግዚአብሔር ያጠፋቸዋል፥ ታላቅ ነገርን የምትናገረውን ምላስ፤
፬ምላሳችንን እናበረታለን፤ ከንፈራችን የእኛ ነው፥ ጌታችን ማን ነው? የሚሉትን።
፭ ስለ ድሆች መከራ፥ ስለ ችግረኞች ጩኸት እግዚአብሔር። አሁን እነሣለሁ ይላል፤ መድኃኒትን አደርጋለሁ፥ በላዩም እገልጣለሁ።
፮ በምድር ላይ እንደ ተፈተነ ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ ብር። የእግዚአብሔር ቃላት የነጹ ቃላት ናቸው።
፯ አቤቱ፥ አንተ ጠብቀን፥ ከዚህችም ትውልድ ለዘላለም ታደገን።
፰ በሰው ልጆች ዘንድ ምናምንቴ ከፍ ከፍ ባለ ጊዜ ክፉዎች በዙሪያው ሁሉ ይመላለሳሉ።
"በጨነቀኝ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፥ ወደ አምላኬም ጮኽሁ፤ ከመቅደሱም ቃሌን ሰማኝ፥ ጩኸቴም በፊቱ ወደ ጆሮው ገባ።"
መዝ 18÷6
🌿🌷🌿🌷🌿🌷🌿🌷🌿🌷🌿🌷
"በስጋ ተዋህዶ በዚህ ዓለም ከመኖር በየክፍሉ ወደተዘጋጀው (ተሠራ) ተስፋ ህይወት ለነፍስሽ መውጣት ሰላም እላለሁ ።ቅድስት ሐና ሆይ ነፍስ ከስጋዬ በተለየች ጊዜ ማርታ ለክርስቶስ ማዕድን በቤቷ እንዳዘጋጀች ለእኔም በአማላጅነትሽ ዋጋዬን አዘጋጂልኝ።"
🌹 መልክዐ ሐና 🌹
"ለቅድስት ሥላሴ" - ዘማሪት ቤዛዊት ደርቤ | @-betaqene4118
https://youtube.com/watch?v=r-VXSbJgNoc&si=okkOZghldnLWnUGz
“ ሳናቋርጥ የሦስቱን ምስጋና አንድነት እንናገራለን ፥ ፍጹም አሸናፊ አንድ አምላክ እግዚአብሔር አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ኾይ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ተብለኽ የምትመሰገነው ምስጋናኽ በሰማይ በምድር ምሉዕ ነው ፡፡ "
ሃይማኖተ አበው ዘጎርጎርዮስ
በመዶሻ 'ጥፊ' ተመትቶ አለቱ፣
ምርጥ ዕቃ ተመርጦ ቤቱ መገንባቱ፣
ቢነፍስም ቢዘንብም ቢጎርፍም በብርቱ፣
ልክ እንደ ትላንቱ፣
ዛሬም ጽኑ ቤት ነው ውስጥ ለገቡቱ።
(መዶሻና ምርጥ ዕቃ የተባለ ቅ.ጳውሎስ በአንድ ወቅት አሕዛብን ለማስተማር አለት የተባለ ቅ. ጴጥሮስን በጥፊ መምታቱን ልብ ይሏል)
#እንኳን_አደረሳችሁ
ነገ ሐምሌ 5 የብርሃናተ ዓለም የሐዋርያው ቅድስ ጴጥሮስ እና የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለ
የእረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡፡
እንኳን አደረሳችሁ🙏❤
ለሰዎች የምትሰጡአቸው ምንም ነገር ከሌላችሁ፥ ሞቅ ያለ ልባዊ ፈገግታን ስጡአቸው፣ መልካም ቃልን ስጡአቸው፣ ፍቅርን ስጡአቸው፣ ርኅራኄን ስጡአቸው፣ የሚያበረታ ቃልን ስጡአቸው፤ ልባችሁን ስጡአቸው።
ቅዱስነታቸው አቡነ ሺኖዳ ሣልሣዊ
🌿🍁🌿
“ወዳጆች ሆይ፥ ፍቅር ከእግዚአብሔር ስለ ሆነ፥ የሚወደውም ሁሉ ከእግዚአብሔር ስለ ተወለደ እግዚአብሔርንም ስለሚያውቅ፥ እርስ በርሳችን እንዋደድ። ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፥ እግዚአብሔር ፍቅር ነውና።”
- 1ኛ ዮሐንስ 4፥7-8
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
"ወፈቀዱ ይሰይምዎ በስመ አቡሁ ዘካሪያስ፤ወትቤ እሙ ዮሐንስሃ ይሰመይ፤ወይቤልዎ አልቦ ዘሰማዕነ ዘከመዝ ስም እምአዝማድኪ፤ወዘካርያስ ሰአለ መጽሐፈ፤ወጸሐፈ እንዘ ይብል ዮሐንስ ስሙ፤እስመ ከማሁ ዮሐንስ ብሂል፤ፍሱሕ ወልድ ብሂል በትርጓሜሁ።"
ትርጉም
"በተወለደም ጊዜ በአባቱ ስም ዘካርያስ ይሉት ዘንድ ወደዱ፤ እናቱ ኤልሳቤጥ ግን ዮሐንስ ይባል አለች። እነሱም መልሰው "እንዲህ ያለ ስም ከዘመዶችሽ የሰማነው የለም" አሏት። ካህኑ ዘካርያስም ብራና ያመጡለት ዘንድ ለምኖ "ስሙ ዮሐንስ ይባል" ብሎ ጻፈ። ዮሐንስ ማለት ፍሥሓ ወኃሤት ርኅራኄ ወሣህል ማለት ነውና።"
መጽሐፈ ዚቅ (የሠኔ ዮሐንስ እስመ ለዓለም)
