ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
رفتن به کانال در Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
نمایش بیشتر672
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+37 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
+7
ፎቶ:- 1/05/2018 ዓ.ም
የቅዱስ እስጢፋኖስ በዓለ እረፍት በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል በታላቅ ድምቀት ተከበረ።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel
እንኳን ለንዑድ ክቡር ቀዳሜ ሰማዕት ወሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ። በነገው ዕለት በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል በታላቅ ድምቀት በዓለ ንግሱ ይከበራል።
እንዳትቀሩ!
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel
+4
ፎቶ :- 29/04/2018 ዓ.ም
በአሰላ ደብረ መ/መ/ዓ/ካቴድራል በፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት የተደረገ የልደት የነድያን በግቦት።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በመላው በፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አባላት ስም ከዝክረ ያሬድ ሰ/ት/ቤት በአንድነት ዝማሬው ላይ ስለተሰጠን ልዩ ስጦታ ከልብ እናመሰግናለን። የጠየቁትን የማይነሳ፣ የነገሩትን የማይረሳ ቸር እና መሀሪ አምላካችን መድኀኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ የአገልግሎት ዘመናችሁን ይባርክላቹ።
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
"የእግዚአብሔር ፈቃድ ምንም እንኳ መራራ ቢመስልም፣ መጨረሻው ግን የሕይወት መድኃኒት ነው። የእኛ ፈቃድ ደግሞ ምንም እንኳ ቢጣፍጥም፣ መጨረሻው የነፍስ በሽታ ሊሆን ይችላል።"
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ
✝ ቻይ እና ትዕግስተኛ የሆነ ሰው ይጸልያል ስለሚሰጠውም የእግዚአብሔር መልስ አይጨነቅም ። እግዚአብሔር ጸሎቱን እንደሚሰማው እርግጠኛ ነው ። ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ጥበብና ፈቃድ እንደሚሆን በተገቢው ጊዜና መንገድ መልስ እንደሚሰጠው በማመን ለእግዚአብሔር ፍቅር ይተዋል ። አንዳንድ ሰዎች ይህ መሰል ትዕግሥት የላቸውም ። እግዚአብሔርን መውቀስ እና ከእርሱ ስሕተት መፈለግ እንጂ መጠባበቅ አይችሉም ። እርሱን ይወነጅሉታል እርሱ ግን እጅግ ይታገሳቸዋል ወቀሳቸውንም ይሸከማል ። እነዚህ ሰዎች እግዚአብሔር ለእነርሱ እንደሚሰራ ማመን አለባቸው ።
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
“በቅዳሴ አፉን የፈታው ሕጻን”
በቅዳሴ አፉን የፈታ ሕጻን ይኼውላችሁ። ምስጋናን እየተመገበ ያደገውን ብላቴና ታዩት ዘንድ ኑ! በሕጻናት ልማድ አበ፣ እመ ብሎ አፍን መፍታት የተለመደ ነበር
“ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ” ብሎ ንግግሩን የጀመረ የዚህን ሕጻን ነገር ማሰብ ያስደንቃል።
ለጌታስ ሁሉ ይቻለዋል “ ከሕጻናትና ከሚጠቡት አፍ ምስጋናን ለራስህ አዘጋጀህ” ተብሎ ተጽፏልና።
ከታናሽነቱ ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ ያደረበትን ይህንን የጸጋ ዘአብን ፍሬ የእግዚእ ኃረያን በረከት ኑ እናመስግነው። በሆሣዕና ካመሰገኑ ሕጻናት እንደ አንዱ ሆኖ አገልግሏልና።
በረከቱን ታገኙ ዘንድ ኑ! የ እናቱን የእግዚእ ኀረያን ቤት በበረከት የሞላበት ቀን ነውና።
ጾምና ጸሎት ያጣፈጡት አገልግሎት፣ በምናኔ የበረታ ሕይወት በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘንድ እናገኛለን።
ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ከታናሽነታቸው ጀምሮ ራሳቸውን ለክርስቶስ ያላስገዙበት ጊዜ የለም። ስለዚህም የናቁት ዓለም ከእግራቸው ሥር ወድቆ ተገዛላቸው።
የክርስቶስ ፍቅር በልባቸው ስለሞላ ለዓለም የሚሰጡት ፍቅር የላቸውም። ነገር ግን ክርስቶስ ከዚህ ዓለም ያልሆኑ ቅዱሳንን ሊሰበስብ በዓለም እንደተመላለሰ ኢትዮጵያዊው ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ለክርስቶስ የተለዩ ምዕመናንን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመሰብሰብ በከተማና በገጠር ዞረው አገልግለዋል።
ዞሮ ከማገልገል የሚቀድመው አገልግሎት ዛሬ በእናቱ እቅፍ ያቀረበው ምስጋና ነው። ከተወለደ በሦስተኛው ቀን በ እግዚአብሔር ፊት ያቀረበው ምስጋና እስከ መጨረሻው የጸና ሆነ።
የሰውን ታናሽነት የማይንቅ እግዚአብሔር በሰማይ የመላእክት በምድር የቅዱሳን ምስጋና ይበቃኛል የማይል በየዘመኑ ለምስጋና ሰውን የሚያዘጋጅ በመሆኑ በሰውና በ እግዚአብሔር ፊት የተወደደ አገልጋይ አስነሣልን።
የጻድቁ በረከት ይደርብን!
✨️️️️✨️️️️✨️️️️ 🌸🌼🌺✨️️️️✨️️️️✨️️️️ 🌸🌼🌺✨️️️️✨️️️️
✨️️️️ 🌸🌼🌺
ሰላም ለፅንሰትከ ወለልደትከ እምከርሥ÷
አመ ዕሥራ ወረቡዑ ለወርኃ ታኅሣሥ÷|
ተክለ ሃይማኖት በኵሉ ወበ ውስተ ኵሉ ውዱስ÷
ናሁ ወጠንኩ ወዕቤ ለስብሐቲከ ሐዲስ÷
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ::
✨️️️️ 🌸🌼🌺
ከተቀደሰችው ማኅፀን ስለሆነው የመጸነስህና የመወለድህ ነገር ሰላምታ ይገባል፥
ይኸውም በታኅሣሥ ወር በሃያ አራተኛው ቀን ተፈጸመ፥
ተክለ ሃይማኖት ሆይ በሁሉ እና በሁሉም ውሥጥ የተመሰገንክ ነህ፥
✨️️️️ 🌸🌼🌺
አንተ ያቀረብከው የሆነውን አዲስ ምሥጋና አመሠግን ዘንድ እንዲህ ብዬ ጀመርኩ፥
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ በማለት።
✨️️️️ 🌸🌼🌺
መልክአ ተክለ ሃይማኖት
ለጽንሰትከ
✨️️️️✨️️️️✨️️️️ 🌸🌼🌺✨️️️️✨️️️️✨️️️️ 🌸🌼🌺✨️️️️✨️️️️
#ራኬብ
በእግዚአብሄር ማሉልኝ
ምልክትን ለግሱኝ
ቸርነትን እንዳረኩላቹ
እንፋትረሱኝ ከተማይቱን ሲሰጣቹ
ራኬብ ሆይ አረሳሽም በእውነት
ውለታሽን ያንቺን መልካምነት/2
እግዚአብሄር ምድሪቱን ሰጧችኋል
ስለእናንተ በፍራት ተውጠናል
እናውቃለን ከግብፅና ወታቹ
ያንን ባህር በሀይሉ ከፍሎላቹ/2*/
#አዝ
ንጉስ ሀገር የርስቱን የባሳንን
ንጉስ ሲሆን የዓሞራውያንን
ድል ተመተው ተሸንፈዋልና
አምላካችን ሀይለኛ ነው ገናና/2*/
#አዝ
ግንቡ ሲናድ ሲነፋ መለከት
ቀዩን ፈትል እሰቅላለው በመስኮት
እናት አባት ዘመዶቼን አደራ
ቀስት እና ጦር እናዳይወጋን መከራ/2*/
#አዝ
ሸፋፍኜ ሰገነት ላይ ወጥቼ
እንድትድኑ የሉም ብዬ ዋሽቼ
ስላወኩኝ ስለገባኝ ነው ክብሩ
የሚረዳን በሰማይ ነው ሀገሩ/2*/
ሰማይ ምድሩ ያንተ ነው
ማይታየው ሚታየው
በፍርድ ቀን በግርማህ ስትመጣ
እንዳትረሳን በቀኝ አቁመን የኛ ጌታ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በጎርጎርዮሳውያን /Gregorians/ የዘመን አቆጣጠር በነገው ዕለት የሚጀመረውን የ2026 አዲስ ዓመት በማስመልከት ለመላው የዓለም ማኅበረሰብእ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።
ታኅሣሥ 22 ቀን 2018 ዓመተ ምሕረት
ቅዱስነታቸው በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት የአማርኛ ትርጉም እንደሚከተለው ቀርቧል፦
ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ለመላው የዓለም ሕዝብ የተላለፈ
አባታዊ መልእክት
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
“እስመ ናሁ ተወልደ ለክሙ ዮም መድኅን ዘውእቱ ክርስቶስ እግዚእ ቡሩክ በሀገረ ዳዊት፡-
እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋል፤ ይኸውም ቡሩክ ጌታ ክርስቶስ ነው።”
(ሉቃ. 2፡11)
የጌታችን ልደት የሰው ልጆች ምኞት የተፈጸመበት ፣ ከሁሉ በላይ የእግዚአብሔር ፍቅርና ማዳን የተገለጠበት በመሆኑ ክርስቲያኖች ሁሉ ሲያስቡት ይኖራሉ፤ አዲስ ዘመንም ካለፈው ዓመት የቀጠለ የቍጥር ቀመር ሳይሆን እያንዳንዱ ቀን የእግዚአብሔር ስጦታ መሆኑን እናምናለን፤ በዘመን ላይ ዘመን ሲጨመር ገንዘብ ሊገዛው፣ ሥልጣን ሊያመጣው የማይቻለውን የዕድሜ ስጦታ አግኝተናልና የምስጋና ርእሳችን ነው ። እያንዳንዱ ዘመን ይዞት የሚመጣው በረከት፣ ትምህርትና ብስለት ያለው በመሆኑም በመላው ዓለም ሆናችሁ እንደየዘመን አቆጣጠራችሁ የጌታችን፣ የአምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ለምታከብሩ፤ እንዲሁም የ2026ን አዲስ ዓመት ለመቀበል ለተዘጋጃችሁ ወገኖቻችን እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እንወዳለን ።
በአዲስ ዘመን ተነፋፍቆ የቆየው ወዳጅ የሚገናኝበት ፣ ወደ ቤቱም የሚመለስበት እንደሆነ የሚታወቅ ሲሆን በዚህ ዘመን ብዙ ልዩነቶች ዓለምን እያወኩ ይገኛሉ፤ የበዓሉ ዓላማ ግን መገናኘት በመሆኑ ወደ አንድነት መምጣት አስፈላጊ ነው። ሁሉን የሚያስተባብር ደስታ በዓለም ላይ የለም ፣ የክርስቶስ መወለድ ግን ሰማይና ምድርን፣ ሰዎችና መላእክትን ለዝማሬ ያገናኘ፣ ሰላምን ዓላማ ያደረገ ታላቅ መገለጥ ነው ። ዛሬም የምንኖርባት ዓለም በዚህ የጌታችን ልደትና የ2026 አዲስ ዓመት ዋዜማ ላይ ስለ ሰላም ማሰብ ይጠበቅባታል፤ የእስራኤልና የፍልስጥኤም ሕዝቦች፣ የሩሲያና የዩክሬን ወገኖቻችንም ዘላቂ ሰላም ሊያገኙ ይገባቸዋል ። በየስፍራው የሚገደሉና የሚታገቱ፣ እግዚአብሔር በሰጣቸው ማንነትና ሃይማኖት ዋጋ እየከፈሉ ያሉ ተጠቂዎችን ለመታደግም ጊዜው አሁን ነው ። በስደት ዓለም ላይ ተጨማሪ ስደት የገጠማቸውን ወገኖች መጠጊያ መስጠት፣ ዓለም ጊዜያዊ ቤት መሆኗን አምኖ እርስ በእርስ መረዳዳት ይገባል ። በዚህ ወቅትም ከዘመድና ከወዳጅ ርቀው ያሉት የሰዎችን ፍቅር ስለሚፈልጉ በክርስቶስ የምታምኑ፣ በበጎነት የምትደሰቱ ሁሉ ወገን ለሌላቸው ወገን ትሆኑ ዘንድ እንመክራለን።
የተወደዳችሁ የዓለም ሕዝቦች!
ክርስትና ለዓለም ትልቅ ብርሃንን ያበሰረ ፣ የሞራል ልዕልናን የሰበከ ፣ ከሁሉ በላይ በማዳን እውነት የሚጀምር ሃይማኖት ነው ። አብዛኛው የዓለም ሕዝብ ክርስትናን የሚከተል ቢሆንም ይህ ክርስትና በዘመናችን በተለያዩ አካላት ሲገፋ እየተመለከትን ነው፡፡ ለአብነትም ክርስቲያኖች በየስፍራው ይታገታሉ፤ ይገደላሉ፤ ስልጣኔው ብዙ ምቹ ነገሮችን ያመጣ ቢሆንም ለክርስትናው ግን ምቹ ያልሆነ ይመስላል፡፡ ስለሆነም ባለማወቅም ሆነ በዓላማ ክርስትናን ለማዳከም እና ለማጥፋት የሚንቀሳቀሱ ሁሉ ከክፉ ድርጊታቸው እንዲመለሱ አበክረን እናሳስባለን፡፡
ዓለም አቀፍ ተቋማትና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትም የሰውን የሃይማኖት መብት ለማስከበር የበኩላቸውን ጥረት ያደርጉ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
በመጨረሻም መጪው ዘመን ችግረኞች የምግብና የደኅንነት ዋስትና የሚያገኙበት፣ የተለያዩት የሚገናኙበት፣ የጦርነት ቀጠሮዎች የሚሰረዙበት፣ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ወደ ቀያቸው የሚመለሱበት፣ የዓለም ኢኮኖሚ ከፍ የሚልበት፣ ክብር የሚመለስበት፣ መሪዎች በጥበብ የሚያስተዳድሩበት፣ ሕዝቦች በትሕትና የበላዮቻቸውን የሚያከብሩበት፣ ከሁሉ በላይ ፍቅር በእያንዳንዱ የዓለም ጎጆ ውስጥ የሚገባበት እንዲሆን አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን!
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን፤ እንዲሁም መላውን ዓለም ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ታኅሣሥ 22 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
