ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
رفتن به کانال در Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
نمایش بیشتر669
مشترکین
+124 ساعت
+37 روز
-330 روز
آرشیو پست ها
✨✨✨በዓለ ጰራቅሊጦስ✨✨
✨✨የቤተክርስቲያን የልደት ቀን✨✨
"አቤቱ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ ከአንተ ዘንድ ከሰማይ የሚገኝ ሰላምን ሁሉ በሁላችን ልቡና አሳድርብን። በእርስዋም የሕይወትን ሰላም ስጠን።ለሀገራችን ኢትዮጵያም ሰላሟን አጽናላት።"
ሥርዓተ_ቅዳሴ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
"ነገ እግዚአብሔር በመካከላችሁ ድንቅ ነገር ያደርጋልና ተቀደሱ" መጽ ኢያሱ 3÷5✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
🍁🍁🍁🌿🌿🌿🍁🍁🍁🌿🌿🌿🍁🍁🍁🌿🌿🌿
"የሰው ልጆች ሁሉ አዋቂ ናቸው የሚባለው ስህተት ነው። አዋቂ ማለት መጽሐፍትን ጠንቅቆ ያወቀ ሳይሆን ከኃጢአት በመቆጠብ ነፍሱን የማይጎዳ፣ አምላክን በማመስገን በማያወላውል በቅድስና ሥራ መልካም በመሥራት ነፍሱን የሚመግብ ያ ሰው እሱ ብቻ አዋቂ ተብሎ ይጠራል።"
🍁🍁🌿ታላቁ ቅዱስ እንጦንስ
“ተአምራትን ማድረግ ትፈልጋላችሁን? እንኪያስ በዘፈን የደነቆረን ጀሮ መዝሙር እንዲሰማ አድርጉት፡፡ ሴትን በመመኘት የታወረው ዐይን ፈጣሪውን እንዲያይ አድርጉት፡፡ በስርቆት የሰለለ እጅ በምጽዋት እንዲዘረጋ አድርጉት፡፡ ወደ ኃጢአት ቤት በመሄድ ሽባ የሆነውን እግር ወደ እግዚአብሔር ቤት እንዲሮጥ አድርጉት፡፡ ሐሜትን በማውራት ዲዳ የሆነውን ከንፈር መልካም ንግግርን እንዲናገር አድርጉት፡፡ ከተአምራት ሁሉ የበለጠ ተአምር ይሄ ነው፡፡"
🍁🍁🌿 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"ጌታ ሆይ ዕውሩን ሂድ ብለህ ወደላክህበት ወደ ሰሊሆም መጠመቂያ አሁን ልንሔድ አንችልም። ነገር ግን ሕይወትንና ብርሃንን የተሞላው የከበረ ደምህ ያለበት ጽዋ በእኛ ዘንድ አለ። ከእርሱ በተቀበልን ቁጥር እንነጻለን"
🍁🍁🌿 ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
🍁🍁🍁🌿🌿🌿🍁🍁🍁🌿🌿🌿🍁🍁🍁🌿🌿🌿
✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹
እንኳን አምላክን ለወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ለታየበት ፤ የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም ታላቅ በዓልን ላደረጉበት ለተወደደች ዕለት በሰላም አደረሳችሁ🙏
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
"አመ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ኀምሰ ዕለታተ። ትእምርተ ገጽኪ ይርአይ እስከ ይትነሣእ ዘሞተ። ሚ መጠነ ማርያም ታሥተፌሥሒ ትፍሥሕተ። ኅድጊሰ ጽጌ ፍቅርኪ በጊዜ ንቃሑ መዓልተ። ብፁዕ ዘርእየኪ በሕልሙ ሌሊተ"።
ትርጉም፦
✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹
የፊትሽን መልክ ያይ ዘንድ የሞተ ሰው እስኪነሣ ድረስ በደብረ ምጥማቅ ለአምስት ቀናት ያኽል በተገለጽሽ ጊዜ ማርያም ምን ያኽል ደስ ታሰኚ ኖሯል! በቀን የታየው የፍቅርሽ አበባ ይቅርና ሌሊት በሕልሙ ያየሽ ምስጉን ነው።
አባ ጽጌ ድንግልና
አባ ገብረ ማርያም
በማኅሌተ ጽጌ።
✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🌹🌹🌹
"ወንድሜ ሆይ ይህን ቅዱስ ምግብና መጠጥ አስብ ይኸውም የክርስቶስ አካል እና ደም አባቶቻችን በሙሉ ከመጀመሪያው የተፈጠረው አዳም ነቢያትም ሁሉ አጥብቀው ተጠሙ ነገር ግን አልተቀበሉትም ፣ አንተ ግን ከክፋትህ ርቀህ ከዚህ መለኮታዊ ምግብ ተካፈልህ።"
አቡነ ናዛሪንስ
"ለዓይንህ እንቅልፍን ለሽፋሽፍቶችህም እንጕልቻን አትስጥ፥እንደ ሚዳቋ ከአዳኝ እጅ፥ እንደ ወፍም ከአጥማጅ እጅ ትድን ዘንድ።አንተ ታካች፥ ወደ ገብረ ጕንዳን ሂድ፥ መንገድዋንም ተመልክተህ ጠቢብ ሁን።አለቃና አዛዥ ገዢም ሳይኖራት መብልዋን በበጋ ታሰናዳለች፥ መኖዋንም በመከር ትሰበስባለች።አንተ ታካች፥ እስከ መቼ ትተኛለህ? ከእንቅልፍህስ መቼ ትነሣለህ?"
ምሳ 6÷4-9
ጸሎት
"እነሆ በፊትህ የተከፈተች ደጅ ሰጥቼሀለሁ ሊዘጋት የሚችል የለም"ራዕ 3:7
"በእርግጥም እግዚአብሔር ለአንድ ሰው በርን በከፈተለት ጊዜ ሊዘጋበት የሚችል ማንም የለም።በመሆኑም እግዚአብሔር እንዲከፍትልህ ብትሻ የሚያስፈልግህ ነገር ቢኖር መጸለይ ነው። ስለዚህ ፕሮጀክትህን ሁሉ ዕቅድህንም ሁሉ ልትጀምር በፈለግህ ጊዜ ይህንን ጸሎት አድርስ።"
አቡነ ሺኖዳ
"እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንሁት እርስዋንም እሻለሁ፤ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፥ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውንም አይ ዘንድ፥ መቅደሱንም እመለከት ዘንድ።"
መዝ 27÷4
"ሁላችንም በአንድ ጦር ሜዳ ነንና አንድ ዓይነት ውጊያም ይጠብቀናል ። ስለዚህ ከንቱና ግብዝ ሐሳቦችን ጥለን ለእኛ የተላለፈውን ክቡርና ቅዱስ ትውፊት እንከተል እንጠብቀውም።"
ቀለሜንጦስ ዘሮም
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✞ እንኩዋን ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ዕርገት በሰላም አደረሳችኹ!
ዕርገተ እግዚእ
+የክብር ባለቤት መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በኪነ ጥበቡ (በሕማሙ: በሞቱ) ዓለምን አድኖ: ፵ ቀን ለሐዋርያቱ መጽሐፈ ኪዳንን: ትምሕርተ ኅቡዓትን አስተምሯቸዋል::
+በ፵ኛው ቀን ፻፳ውን ቤተሰብ ይዟቸው ወደ ቢታንያ ወጣ:: በዚያም እስከ ሊቀ ዽዽስና ድረስ ሾሟቸው: ከኢየሩሳሌም እንዳይወጡም አዟቸው የመንፈስ ቅዱስን ተስፋ ጠብቁ ብሏቸዋል:: እየባረካቸው በተዋሐደው ሥጋ ወደ ሰማያዊ ዙፋኑ ዐርጓል::
+ሰማያት: ምድር: ደመናት: ነፋሳት: መባርቅትና መላእክት: ፍጥረት በሙሉ አመስግኗል:: አይሁድ መናፍቃን ዕርገቱን ምትሐት ነው እንዳይሉ: ጌታችን ትንሳኤውን አማናዊ እንደኾነ ለማስረዳት በ፵ኛው ቀን ዐረገ::
አንድም ራስ ባለበት ሌሎች የሰውነት ክፍሎች ሊኖሩ ይገባልና ጌታችን ዕርገቱን በገሃድ አደረገው:: "ዐርገ እግዚእ ከመ ያለቡ ዕርገተ ጻድቃን ንጹሐን" እንዲል::
"ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ::
ወእግዚእነ በቃለ ቀርን::
ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ"
(መዝ. ፵፮:፮)
"እስከ ቢታንያም አወጣቸው:: እጆቹንም አንስቶ ባረካቸው:: ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ:: ወደ ሰማይም ዐረገ:: እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ:: ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ::"
(ሉቃ. ፳፬:፶-፶፫)
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
"ወንድማችንን ገንዘብ ካደረግነው እግዚአብሔርን ገንዘብ እናደርጋለን ፤ ወንድማችንን ካስቀየምነው ግን በክርስቶስ ላይ ኃጢአትን እናመጣለን ።"
አባ እንጦስ
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿
ሰባኬ ወንጌል መጋቤ ሃይማኖት ለቤተ ክርስቲያን ዘይደምፅ ቀርን ነባቤ ለቤተ ክርስቲያን፡፡ ያሬድ ፀሐያ ለኢትዮዽያ ዓምደ ብርሃን ለቤተ ክርስቲያን መልአክ ዘበምድር፡፡✨🌿ትርጉም ቅዱስ ያሬድ ሰባኬ ወንጌል መጋቤ ሃይማኖት ለቤተ ክርስቲያንም የሚመሰክር መለከት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ፀሐይ የብርሃንም ምሰሶ በምድር ላይ ያለ መልአክ ነው፡፡ ✨🌿✨🌿 እንኳን ለኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሰን አደረሳችሁ ! ✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
"ወንድሞች ሆይ ሁላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ በአንድ ልብና በአንድ አሳብም የተባባራችሁ እንድትሆኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ ።"
1ኛ ቆሮ 1÷10
+1
የታላቁ አባታችን አንጋፋው የደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል አገልጋይ የአባ ገብረ ጻድቅ ስርዓተ ቀብር ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ካህናት አባቶች ፣ ዲያቆናት፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች እና የአርሲ ሀገረ ስብከት የየመምሪያው ሀላፊዎች በተገኙበት በዛሬው እለት ግንቦት 10/2018 ዓ.ም በካቴድራሉ ተፈጽሟል።
ለመላው የደብራችን አገልጋዮች፣ ቤተሰቦቻቸው፣ የንስሀ ልጆቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።
🕯🕯🕯🕯 ዜና እረፍት 🕯🕯🕯🕯
የደብራችን አንጋፋ አገልጋይ የሆኑት አባ ገብረ ጻዲቅ ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል። ለመላው የደብራችን አገልጋዮች መጽናናትን እንመኛለን።
ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት
"አንድ ሰው በጽኑ ሁኔታ ታሞ ሳለና መመገብ ሲያቆም ወዳጆቹ ለሞት እንደ ቀረበ ይረዳሉ ። እኛም ከጸሎትና ከቅዱስ ቁርባን ስንርቅ ነፍሳችን እየ ሞተች ነውና መላእክት ስለ እኛ ያዝናሉ "
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
