ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
رفتن به کانال در Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
نمایش بیشتر669
مشترکین
-124 ساعت
+37 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ
ወደ ታላቁ ደብር ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም
መነሻ ነሐሴ 22/2016 ዓ.ም
መመለሻ ነሐሴ 28/2016 ዓ.ም
መስተንግዶን ጨምሮ
እግረ መንገዳችንን እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት እንሳለማለን
ለበለጠ መረጃ:- 0943620923
:- 0955252034
ከታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
🕊
[ † እንኳን ለሰማዕታት አበው አቡነ ጴጥሮስ ኢትዮጵያዊ : ቅዱስ መቃርስ እና ቅዱስ ለውንትዮስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † ታላቁ ኢትዮጵያዊ ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ † 🕊
† ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ምንም እንኳ ለሃገራቸውና ሃይማኖታቸው ያን ያህል ዋጋ ቢከፍሉም ትውልዱም : መንግስቱም : ራሷ ቤተ ክርስቲያናችንም ተገቢውን ክብር ሰጥተው እያሰቧቸው አይደለም:: እስኪ እንዲያው ቢያንስ እንደ ክርስቲያን : አንድም እንደ ኢትዮጵያዊ እነዚህ ነገሮቻቸውን እናስብ::
ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ከልጅነታቸው ጀምረው ትምሕርት : ትሕርምትና ደግነት ወዳጅ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ወቅቱ ኢትዮጵያ የራሷን ጳጳሳት የምትሻበት ጊዜ ነበርና በፈቃደ እግዚአብሔር ለመጀመሪያ ጊዜ የሃገራችን አራት አባቶች ጵጵስናን ተሾሙ::
እነርሱም ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ እና አበው አባ ሚካኤል: አባ አብርሃም እና አባ ይስሐቅ ናቸው:: የተሾሙትም ግንቦት 18 ቀን 1921 ዓ/ም ነው:: አቡነ ጴጥሮስ ከተሾሙ በኋላ በሐዋርያዊ አገልግሎትና በጸሎት ተግተው ኑረዋል::
በ፲፱፻፳፰/1928 ዓ/ም ፋሺስት ጣልያን ሃገራችንን በወረረች ጊዜ ቆራጡ ጳጳስ በዱር በገደል ለመሔድ ተነሱ:: በየበርሃው እየሔዱ አርበኞችን ሲያጽናኑ : ሲናዝዙ : ሲባርኩም ቆይተዋል:: ለሃገራቸውና ለሃይማኖታቸው ረሃብ : ጥም : እንግልትን ታግሰዋል::
በተያዙባት በዚያች ሌሊትም በጣልያኖች ለሮም እምነትና ለአገዛዙ እንዲያጐበድዱ ተጠየቁ:: ቆራጡ ሰው ግን እንቢ ቢሉ የሚደርስባቸውን እያወቁ "አይደረግም" አሉ:: በማግስቱ በአደባባይ መትረየስ ተደግኖባቸው አሁንም ጥያቄ ቀረበላቸው::
አቡነ ጴጥሮስ አፋቸውን ከፍተው ሊናገሩ ጀመሩ:- "የሃገሬ ሕዝብ ሆይ! ለሃገርህ : ለሃይማኖትህ ባትጋደል ትውልድ ይፋረድህ:: ለጣልያን ግን እንኳን ሰው ዛፍ ቅጠሉ መሬቱ እንዳይገዛለት አውግዣለሁ" አሉ:: በደቂቃዎች ልዩነት በግራዚያኒ ትዕዛዝ የመትረየስ ጥይት ዘነበባቸው::
አካላቸው ተበሳስቶ በሰንሰለት እንደ ታሠሩ መሬት ላይ ወደቁ:: አንዱ ወታደር ቀርቦ ቢመለከት ትንሽ ትንፋሽ ነበረቻቸው:: "ይሔ ቄስ አልሞተም" ብሎ ጭንቅላታቸው ላይ ተኮሰባቸው::
አቡነ ጴጥሮስ ለሃገራቸውና ሃይማኖታቸው ተሠው:: ነገሩ በአርበኞች ዘንድ ሲሰማ ትግሉ ተቀጣጠለ:: ይሄ የተደረገው ሐምሌ ፳፪ [22] ቀን በ፲፱፻፳፰/1928 ዓ/ም ነው:: አቡነ ጴጥሮስም በተ/መ/ድ [UN] የሺህ ዓመቱ ምርጥ ሰማዕት [MARTYR OF THE MILLENIUM] በመባል ይታወቃሉ::
🕊 † ቅዱስ መቃርስ ሰማዕት † 🕊
† ሰማዕቱ ተወልዶ ያደገው በአንጾኪያ [ሶርያ] በ፫ [3] ኛው መቶ ክ/ዘመን ሲሆን የታላቁ ቅዱስ ፋሲለደስ እና የቅድስት ሶፍያ ልጅ ነው:: ምንም በቤተ መንግስት ውስጥ ቢያድግም ከወላጆቹ ፍቅረ ክርስቶስን : ንጽሕናንና ደግነትን ወርሷል::
በተለይ ነዳያንን ሰብስቦ ዕለት ዕለት ያበላ ነበር:: [መቃርስ ማለት በልሳነ ዮናኒ ብጹዕ : ንዑድ : ክቡር ማለት ነው::] ቅዱሱ ያ የመከራ ዘመን ሲመጣ ሁሉም ቤተሰብ ስለ ክርስቶስ መሞትን በመምረጡ እርሱም ደስ እያለው የመከራው ተካፋይ ሆኗል::
ያን የመሰለ የቤተ መንግስት ክብር ስለ ክርስትና ናቀው:: ተገረፈ:: ተሰቃየ:: በእሳትም ተቃጠለ:: አንድ ጊዜም በአደባባይ የሞተ ሰው በጸሎቱ አስነስቶ "መስክር" አለው:: ከሞት የተነሳውም የክርስቶስን አምላክነት በመመስከሩ በአደባባይ የነበሩ ብዙ አሕዛብ በክርስትና አምነው ተሰይፈዋል::
ቅዱስ መቃርስን ግን ብዙ አሰቃይተው በዚህች ቀን አንገቱን ቆርጠውታል:: ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ አጽሙን አፍልሶ በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በስሙ ቤተ ክርስቲያን አንጾለታል::
🕊 † ቅዱስ ለውንትዮስ ሰማዕት † 🕊
† ቅዱሱ የተወለደው በተመሳሳይ ዘመን [በቅዱስ መቃርስ] ሲሆን ሃገሩ ጠራብሎስ ትባላለች:: በወቅቱ በወታደርነት ነገሥታቱን ያገለግል ነበር:: ድንግል : ደም ግባት የሞላለት ወጣት ስለ ነበር በሰዎች ፊት ሞገስ ነበረው::
እርሱ ግን ምንም ወታደር ቢሆን ጾምና ጸሎትን ያዘወትር ነበር:: በተለይ ደግሞ የዳዊትን መዝሙር እየመላለሰ ይጸልየው : ይወደው ነበር:: ንግግሩ ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ ጨውነት የታሸ ነውና ብዙ ጓደኞቹን ከክህደት ወደ ሃይማኖት : ከክፋት ወደ ደግነት መልሷል::
የመከራ ዘመን በደረሰ ጊዜም በገሃድ ስመ ክርስቶስን ይሰብክ ነበር:: ክፉ ሰዎች ከሰውት በመኮንኑ ፊት በቀረበ ጊዜም አልፈራም:: ወታደሮቹ መሬት ላይ ጥለው እየደበደቡት : ደሙ እንደ ጐርፍ እየተቀዳ እርሱ ግን ይዘምር ነበር::
በመጨረሻም ስለ ክርስቶስ ፍቅር በዚህች ቀን አንገቱን ተሰይፏል:: ቅዱስ ለውንትዮስ እጅግ ተአምረኛ ሰማዕት ነውና በእምነት እንጥራው::
† እግዚአብሔር ዐጽመ ሰማዕታትን ይጠብቅልን:: ከሰማዕታቱ ጽናትን : ጸጋ በረከትን ይክፈለን::
🕊
[ † ሐምሌ ፳፪ [ 22 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕት [ ኢትዮጵያዊ ]
፪. ቅዱስ መቃርስ ሰማዕት [ የፋሲለደስ ልጅ ]
፫. ቅዱስ ለውንትዮስ [ ክቡር ሰማዕት ]
፬. አባ እንጦንስ አበ መነኮሳት [ ቅዳሴ ቤታቸው ]
፭. ቅዱስ መርካሎስ
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት
፪. ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ
፫. ቅዱስ ደቅስዮስ [ የእመቤታችን ወዳጅ ]
፬. አባ ጳውሊ የዋህ
† "እንግዲህ አትፍሯቸው:: የማይገለጥ የተከደነ: የማይታወቅም የተሠወረ ምንም የለምና:: በጨለማ የምነግራችሁን በብርሃን ተናገሩ:: በጆሮም የምትሰሙትን በሰገነት ላይ ስበኩ:: ሥጋንም የሚገድሉትን: ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ:: ይልቅስ ነፍስንም: ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ::" † [ማቴ. ፲፥፳፮]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
+4
መርሐ ግብራችንን መከታተል ያልቻልችሁ ምዕመናን ከታች ባሉት ሊንኮች በቀጥታ ስርጭት መከታተል ትችላላችሁ።
በቀጥታ ስርጭት በማሕበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉ።
http://tiktok.com/@finotewongel27
https://t.me/Finote_Wongel
https://t.me/FinoteWongel27
ዛሬ ሐምሌ 21 ከቀኑ 7:00 ሰዓት ጀምሮ ጉባኤ ዘጸዓት መንፈሳዊ ጉባኤ
በቀጥታ ስርጭት በማሕበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉ።
በቲክቶክ ለመከታተል:- tiktok.com/@finotewongel27
በቴሌግራም Live stream ለመከታተል:- T.me/Finote_Wongel
:- T.me/FinoteWongel27
✞ ሐምሌ ፳፩ ቀን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከ፴፫ቱ በዓላት አንዱ ሲሆን ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ዑራኤል በአካል ሥጋ እያለች እመቤታችን ወደ ሰማይ ነጥቆ ገነት እና ሲኦል ያሳየበት እንዲሁም ኢትዮጵያ አስራት አድርጎ የሰጠበት ዕለት ነው ✞
✥ ቅዱስ ዳዊት ✥
ብፁዕ ዘይሌቡ ላዕለ ነዳይ ወምስኪን
እምዕለት እኪት ያድኀኖ እግዚአብሔር
እግዚአብሔር የዐቅቦ ወያሐይዎ ወያበፅዖ ዲበ ምድር
✢ ቅዱስ ያሬድ ✢
ትምክህተ ዘመድነ እንተ ይእቲ እግዝእትነ ማርያም
የባሕርያችን መመኪያ እመቤታችን ማርያም ናት
✥ አባ ጊዮርጊስ ✥
ፍቅርኪ ሰንፔር ለዘይርኀቅ ይስሕቦ መንገለ አሚን ያቀርቦ መኑ ከማኪ ምክንያተ ድኂን ዘተውህቦ
✢ የመልክአ ኤዶም ደራሲ አፄ ልብነድንግል ✢
ጼነወኒ ጼና ፍቅርኪ ከመ ጼና ምዑዘ ዕጣን ወልብየ ሰክረ በፍቅርኪ
የፍቅርሽ መዓዛ እንደ ጣፈጠ ዕጣን አናወደኝ ልቤም በጣዕመ ፍቅርሽ ወይን ሰከረ
✟ የመልክአ ማርያም ደራሲ አፄ ናዖድ ✟
ሰላም ለመልክዕኪ ዘተሠርገወ አሜረ ዘያበርህ ወትረ ፍቅርትየ አንቲ እንተ ታበድሪ ፍቅረ አርእይኒ ገጸ ዚአኪ ማርያም ምዕረ ዘኢይሰምዕ ካልዕ እነግርኪ ነገረ
❖ አባ አርከሡሉስ ❖
ሰላም ለኪ ተረሳዪተ ክብር በ በዑጻፌ ወቀናቲተ ንጹሕ አምሳለ መክፌ እምባሕረ ጊጋይ ስፉሕ እንተ አልቦቱ ጸናፌ ማርያም እንበሌኪ ኀጣእኩ ኃዳፌ ሶበ ተመየጥኩ ለፌ ወለፌ
✥ አባ ጽጌድንግልም በማኀሌተ ጽጌ ✥
አኮ ለሰብእ ባሕቲቱ ማርያም ሠናይት እስመ ርኀርኂት ልብ አንቲ በኵሉ ፍጥረት
መልካሚቱ ርግብ እመቤታችን ማርያም ሆይ አንቺ እንኳንስ ለሰው ለፍጥረት ኹሉ ርኀርኂት ነሽ
✣ እመቤታችንም አለች ✣
ወትቤሎ ማርያም ቀትለኒ ለቤዛሆሙ
ማርያም አለችው እኔ ግደለኝና እነሱ ይዳኑ
❖ አባ ሕርያቆስም ❖
አዘክሪ ለኃጥአን ወአኮ ለጻድቃን አዘክሪ ለርሱሓን ወአኮ ንጹሐን
ለጻድቃን ያይደለ ለኃጥአን አሳስቢ ለንጹሐን ያይደለ ለተዳደፉት አሳስቢ
✝ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሊቁም ✝
ቃላ ለሔዋን ከሠተ ዕፅ ወበውእቱ ዕፅ ወቦቱ ወፅአ አዳም እምገነተ ተድላ ወለቃልሰ ዘተወልደ እምድንግል ከሠተ መስቀል ወቦቱ ቦአ ፈያቲዊ ውስተ ገነት ተድላ ዘምስለ አቡሁ አዳም ወኵሎሙ አበው ቀደምት
ጣዕሟን በአንደበታችን ፍቅሯን በልባችን ታሳድርብን ቸሪቱ እመ አምላክ
ሐምሌ ፳፩ በዓላ ለእግዝእትነ ማርያም
+4
ታላቁ መምህራችን መጋቤ ኃይማኖት መምህር ኢዮብ ይመኑን ጨምሮ ታላላቅ መምህራንና ዘማርያን የተገኙበት ጉባኤ ዘጸአት የተሰኘው መርሐ ግብራችን በልዩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል። እርሶም በደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል በመገኘት የዚህ ልዩ ጉባኤ ተሳታፊ ይሁኑ።
ጉባኤ ዘጸአት
ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ
እነሆ በአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
ለበለጠ መረጃ:- የሰንበት ትምህርት ቤቱን ድህረ ገፆች ይከታተሉ።
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
ጉባኤ ዘጸአት
ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ
እነሆ በአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት ሐምሌ 20 እና 21/2016 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ በአይነቱ ልዩ የሆነ መርሐ ግብር ተዘጋጅቷል። እርሶም ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመሆን በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ በመገኘት የዚህ ልዩ ጉባኤ ተሳታፊ ይሁኑ።
አድራሻ:- በአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ
ቀንና ሰዓት:- ቅዳሜ እና እሁድ ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ
ለበለጠ መረጃ:- የሰንበት ትምህርት ቤቱን ድህረ ገፆች ይከታተሉ።
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
እንኳን አደረሳችሁ!
ሐምሌ 19
+ በዚህ ዕለት ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት እየሉጣን
ከእሳት አድኗቸዋል::
+ ቅዱስ ቂርቆስ ሀገሩ ሮም/ጣሊያን/ አንጌቤን ሲሆን አባቱ ቆዝሞስ እናቱ ደግሞ ኢየሉጣ ትባላለች፡፡
በዘመነ ሰማዕታት በጨካኙና በአረመኔው በዲዮቅልጥያኖስ ዘመነ
መንግሰት በ ፫፻፫ /303/ ዓ.ም አብያተክርስቲያናት ይውደሙ አብያተ ጣዖታት ይስፋፉ የሚል አዋጅ ታወጀ፡፡ በዚህ ምክንያት ብዙ ክርስቲያኖች ተሰደዱ ቅድስት ኢየሉጣም የ ፫ /3/ ዓመት ሕጻን ልጇን ቂርቆስን ይዛ ወደ ኢቆንዩን የምትባል ከተማ ሸሸች፡፡
+ መስፍነ ብሔሩ እለእስክንድሮስ ክርሰቶስን ካጂ ለጣዖት ስገጂ ቢላት
"ዓይን እያለው ለማያይ ጆሮ እያለው ለማይሰማ በቃልህ አዘህ በእጅህ ሰርተህ ላቆምከው ምስል አልሰግድም" አለች::
አይሆንም ካልሽማ በሰይፍ ትቀጫለሽ ብሎ አስፈራራት እስኪ ይህን ሕፃን ጠይቀው አለችው አንተ ሕፃን ወርቅ እሰጥሀለሁ ለዚህ ጣዖት ስገድ አለው::
መንፈስ ቅዱስ አድሮበታልና "ራሳቸውን ማዳን ለማይችሉ ርኩሳን ጣዖታትህ አልሰግድም" አለው::
ተበሳጭቶም የብረት ጋን ውስጥ ውኃ አስፈላ የፍላቱም ድምፅ እንደ ክረምት ነጎድጓድ 24ምዕራፍ ድረስ ይሰማ ነበር::
ሊከቷቸው ሲወስዷቸው እየሉጣ ልቧ በፍርሀት ታወከ ሕፃኑ ቂርቆስም እናቴ ሆይ አትፍሪ አናንያን አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ እኛንስ ያድነን የለምን ? እያለ ልብሷን እየጎተተ ከእሳቱ ቀረቡ ወደ ጋን ውስጥም ከተቷቸው::
+ ያን ጊዜ ጌታ ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ በበትረ መስቀሉ ውኃውን አቀዝቅዞ አውጥቷቸዋል::በወጡም ጊዜ ልብሳቸው ሳይበሰብስ ሰውነታቸው ሳይሸበሸብ ቢያዩ ከአሕዛብ ብዙዋቹ አምነው ሰማዕትነት ተቀብለዋል::
+የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ፈጥኖ ተራዳኢነት የቅዱስ ቂርቆስና የቅድስት እየሉጣ ረድኤት በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን::
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለ ወላዲቱ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክቡር
ጉባኤ ዘጸአት
ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ
እነሆ በአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት ሐምሌ 20 እና 21/2016 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ በአይነቱ ልዩ የሆነ መርሐ ግብር ተዘጋጅቷል። እርሶም ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመሆን በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ በመገኘት የዚህ ልዩ ጉባኤ ተሳታፊ ይሁኑ።
አድራሻ:- በአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ
ቀንና ሰዓት:- ቅዳሜ እና እሁድ ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ
ለበለጠ መረጃ:- የሰንበት ትምህርት ቤቱን ድህረ ገፆች ይከታተሉ።
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ
ወደ ታላቁ ደብር ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም
መነሻ ነሐሴ 22/2016 ዓ.ም
መመለሻ ነሐሴ 28/2016 ዓ.ም
መስተንግዶን ጨምሮ
እግረ መንገዳችንን እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት እንሳለማለን
ለበለጠ መረጃ:- 0943620923
:- 0955252034
ከታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !
“እግዚኦ ሚ በዝኁ እለ ይሣቅዩኒ፦አቤቱ፥ የሚያስጨንቁኝ ምንኛ በዙ ! ”
(መዝ. 3፡1)
#አባታዊ_የማጽናኛ_መልእክት
በጎፋ ዞን፣ በገዜ ጎፋ ወረዳ፣ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት ናዳ እጅግ ብዙ የሚሆኑ ወገኖቻችን በመሞታቸው ታላቅ ኀዘን ተሰምቶናል ። ምንም እንኳ የመከራ ድሀ ባንሆንም ይህ መከራ ለነጋሪውም ለሰሚውም ከባድ መሆኑን እንገነዘባለን ።
ይሁን እንጂ ጭንቀታችን ብዙ ቢሆንም እግዚአብሔር መልካም የምንሰማበትን ዘመን እንደሚያመጣ ተስፋ እናደርጋለን ።
በተለይም ደግሞ እኛ ክርስቲያኖች በወገኖቻችን መጎዳት ብናዝንም በትንሣኤ ሙታን ስለምናምን የምንጽናና በመሆኑ የሞቱት ልጆቻችን ዕረፍተ ነፍስ እንዲያገኙ እየጸለይን፤ የመከራው ገፈት ቀማሽ ለሆኑት የአካባቢው ማኅበረሰብእ ሁለንተናዊ ድጋፍ በማድረግ ሁሉም አቅሙ በፈቀደው መጠን እንዲደርስላቸው ስንል አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።
እግዚአብሔር አምላክ ለቤተሰቦቻቸውና ለሕዝቡ መጽናናትን ይስጥልን፤ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም.
ዋሽንግተን ዲሲ~ አሜሪካ
የብፁዕ ወቅዱስነታቸው በረከት አይለየን!
ጉባኤ ዘጸአት
ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ
እነሆ በአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት ሐምሌ 20 እና 21/2016 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ በአይነቱ ልዩ የሆነ መርሐ ግብር ተዘጋጅቷል። እርሶም ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመሆን በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ በመገኘት የዚህ ልዩ ጉባኤ ተሳታፊ ይሁኑ።
አድራሻ:- በአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ
ቀንና ሰዓት:- ቅዳሜ እና እሁድ ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ
ለበለጠ መረጃ:- የሰንበት ትምህርት ቤቱን ድህረ ገፆች ይከታተሉ።
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
ጉባኤ ዘጸአት
ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ
እነሆ በአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት ሐምሌ 20 እና 21/2016 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ በአይነቱ ልዩ የሆነ መርሐ ግብር ተዘጋጅቷል። እርሶም ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመሆን በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ በመገኘት የዚህ ልዩ ጉባኤ ተሳታፊ ይሁኑ።
አድራሻ:- በአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ
ቀንና ሰዓት:- ቅዳሜ እና እሁድ ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ
ለበለጠ መረጃ:- የሰንበት ትምህርት ቤቱን ድህረ ገፆች ይከታተሉ።
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ
ወደ ታላቁ ደብር ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም
መነሻ ነሐሴ 22/2016 ዓ.ም
መመለሻ ነሐሴ 28/2016 ዓ.ም
መስተንግዶን ጨምሮ
እግረ መንገዳችንን እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት
ለበለጠ መረጃ:- 0943620923
:- 0955252034
ከታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
"ሰንበት ትምህርት ቤትን በመደገፍ ለነገው ኦርቶዶክሳዊ ትውልድ መሠረት እናስቀምጥ" !!
እንኳን ለፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት 52ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን።
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከጌታችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበለችውን ትምህርት በልዩ ልዩ መንገድ ወደ ትውልድ በማሻገር ወንጌል በዓለም ሁሉ እንዲሰበክ አድርጋለች አባቶች የተቀበሉትን ለልጆች ልጆች የተቀበሉትን ለልጅ ልጆች እያስተላለፉ ዛሬ ላይ ደርሰናል ። ተተኪ ትውልድ በየጊዜው እየተነሳ ትምህርቱን ባይቀባበለው ኖሮ ዛሬ ላይ ቤተ ክርስቲያንን በሁሉም ቦታ ለማግኘት አስቸጋሪ ባደረገው ነበር የሀገራችንን ምሳሌ እንኳን ብንወስድ በ34 ዓ/ም በጃንደረባው አማካኝነት የተቀበልነው ክርስትና ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ እና በእግዚአብሔር ፈቃድ ዛሬ ላይ እንዲደርስ ሆኗል፡፡
መጪው ትውልድ ቤተክርስቲያንን እና አምላኩን ለማወቅ እንዳይቸገር መሠረት ጥሎ ማለፍ ላይ ሥራዎች እንዲሠሩ ቤተ ክርስቲያን ከመሠረተቻቸው ተቋማት መካከል ሰንበት ትምህርት ቤቶች ተጠቃሽ ናቸው ። በቃለ አዋዲው ላይ የተቀመጠው የሰንበት ትምህርት ቤት ትርጉምም ይሄንን የሚያሳይ ነው "ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የጾታ ልዩነት ሳይደረግ መንፈሳዊ ወጣቶችን በዕለተ ሰንበት: በዓበይት በዓላትና አመቺ በሆነ ጊዜ ሁሉ በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን እየተገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት: ሥርዓትና ምግባር የሚያጠኑበት ትምህርት ቤት ነው"
በሀገራችን ካሉ ሰንበት ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ የሆነው የአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት ከተመሠረተ ከግማሽ ምዕት ዓመት በላይ ያስቆጠረ አንጋፋ ሰንበት ት/ቤት ነው። ላለፋት 52 ዓመታት ቤተ ክርስቲያን የሰጠችውን ተልዕኮ ለመወጣት በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ሕጻናት እና ወጣቶችን በማሰብሰብ የቤተ ክርስቲያናቸውን ዶግማ ቀኖና እንዲያውቁ በማስተማር ባላቸው አቅም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ውስጥ ሱታፌ እንዲኖራቸው በማስቻል ድርሻውን ሲወጣ ቆይቷል።
ሰንበት ትምህርት ቤቱ ዛሬም በስምንት ክፍላት (ትምህርት ክፍል፣ መዝሙር ክፍል፣ ሙያነ በጎ አድራጎት ክፍል፣ ኪነ ጥበብ ክፍል፣ ሕፃናት ክፍል፣ ንብረት ክፍል፣ ግንኙነት ክፍል፣ ሚዲያ ክፍል) በተዋቀረው ሰፊ አገልግሎቱ በዋነኝነት ቅዱስ ሲኖዶስ ባጸደቀው የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ሕጻናት እና ወጣቶችን በማስተማር፣ በአባላት እና በምእመናን መንፈሳዊ ሕይወት ላይ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ልዩ ልዩ የሥልጠና እና የትምሕርት መርሐ ግብራትን በመዘርጋት፣ የቤተ ክርስቲያንን የመዝሙር ሥርዓት የጠበቁ ትምህርቶችንና የዜማ ንዋያት ስልጠና መርሐ ግብራትን በማዘጋጀት፣ ዘመኑን በዋጀ የሚዲያ አገልግሎት የቤተ ክርስቲያን ትምህርቶች ከእውነተኛው ምንጭ እንዲተላለፉ በማድረግ ፣ የአድራጎት ድጋፎችን በመስጠት ፣ አባላት ባላቸው ሙያ ቤተ ክርስቲያናቸውን የሚያገለግሉበትን ዕድል በማመቻቸት ፣ በልዩ ልዩ ጉባኤያት ላይ ኪነ ጥበባዊ በሆነ መንገድ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በማስተላለፍ እና በመሳሰሉት ተግባራት አገልግሎቱን በመከወን ላይ ይገኛል።
ይህ ሰፊ አገልግሎት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ድክመታችንንም አርመን በተሻለ ሁኔታ ቤተ ክርስቲያናችን እናገልገልግ ዘንድ በየደረጃው ያላችሁ የቤተ ክርስቲያን አካላት ድጋፋችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ፣ ሰንበት ትምህርት ቤቱን በመደገፍ ለነገው ኦርቶዶክሳዊ ትውልድ መሠረት እናስቀምጥ ስንል እንጠይቃለን።
በአጥቢያችን የምትገኙ ውድ ኦርቶዶክሳዊያን በሙሉ እስከዛሬ ድረስ ወደ ሰንበት ትምህርት ቤት ያልመጣችሁ ወጣቶችም ቀርባችሁ የቤተ ክርስቲያንን መሠረታዊ ትምህርቶች በመማር አብራችሁን እንድታገለግሉ ወላጆችም ልጆቻችሁን ወደ ሰንበት ት/ቤት በመላክ መንፈሳዊውን ትምህርት እንዲማሩ፣ ቤተክርስቲያንንም እንዲያገለግሉ፣ በስነምግባር እንዲታነፁ እንድታደርጉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የደብራችን ማሕበረ ካህናት፣ የአስተዳደር ሠራተኞች፣ የአጥቢያው ምእመናን፣ የአካባቢው ወጣቶችና የአቻ ደብራት ሰንበት ት/ቤቶች አሁንም የጸሎት፣ የምክር እና ሌሎችም ድጋፎቻችሁ እንዳይለየን የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አደራ እንላለን።
በመጨረሻም ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን፣ ቤተ ክርስቲያናችንን ይጠብቅልን፣ የሰንበት ትምህርት ቤታችንን አገልግሎት ያስፋልን እያልን መልካም በዓል እንዲሆንልን እንመኛለን።
"የፈጠራችሁን እስከ ዛሬም ድረስ የጠበቃችሁን እግዚአብሔርን ፍሩት"። መቃብያን ካልዕ 10 ÷1
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
