ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
رفتن به کانال در Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
نمایش بیشتر670
مشترکین
-224 ساعت
+57 روز
+130 روز
آرشیو پست ها
"በፈቃደ አቡሁ ወረደ፣ ኀበ ማርያም ተአንገደ፤ በድንግልናሃ ንጹሕ እግዚአብሔር ተወልደ። በጎለ እንስሳ ተወድየ፣ አምኃ ንግሡ ተወፈየ፤ ወከመ ሕጻናት በከየ፣ እንዘ ይስእል እምአጥባተ እሙ ሲሳየ።
➦በአባቱ ፈቃድ ወረደ፣ በማርያም ዘንድ፣ እንግዳ ሆነ፣ እግዚአብሔር በንጹሕ ድንግልናዋ ተወለደ። በእንስሳት በረት ተጨመረ፣ የንግሡንም እጅ መንሻ ተቀበለ፣ ከእናቱ ጡቶች ምግብን እየለመነ እንደ ሕጻናት አለቀሰ።"
ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ
ነገ ቀጠረዎት የት ነው ?
ኑ በዓለ ልደቱን ከባለ ልደቱ ጋር እናክብር።
በአሰላ መስቀል አደባባይ ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ የአንድነት ዝማሬ ላይ ለመገኘት ሁላችንም እንገሰግሳለን።
ኑ የምስጋናን መስዋዕት እንሰዋ።
"የጠፋ በግ አዳምን የፈለገው ባገኘውም ጊዜ የተሸከመው እውነተኛ ቸር ጠባቂያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።" ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (ተአምረ ማርያም
❤#እንኳን_ለቸሩ_መድኃኔዓለም_መታሰቢያ_አደረሰን♥️
🙇ጸለየ፤ #ጸሎት’ንና ምልጃን የሚቀበል ግን እርሱ ነው፡፡ አለቀሰ፤ የሰዎችን እንባ የሚያብስ ግን እርሱ ነው፡፡ እጅግ ርካሽ በሆነ በሰላሳ ዲናር ተሸጠ፤ #ዓለም’ን እጅግ ውድ በሆነ ደሙ የገዛ ግን እርሱ ነው፡፡ እንደ በግ ለመታረድ ተነዳ፤ እውነተኛው የበጎች እረኛ ግን እርሱ ነው፡፡ በሸላቾቹ ፊት ዝም እንደሚል በግ አፉን አልከፈተም፤ ዓለምን በቃሉ የፈጠረ ግን እርሱ ነው፡፡ ወንጀለኞችን ይፈውስ ዘንድ ከወንጀለኞች ጋራ ተሰቀለ፡፡
💖ቸሩ መድኃኔዓለም በምህረቱ ይመልከተን🙏
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
ለእኔ ጊዜ አታጣም
ኃጢአት አስነውሮኝ ከሰው ተሸሽጌ
እንዳያየኝ በሚል መደበቅ ፈልጌ
ጊዜዬ ካለፈ ከመሸ ብመጣም
ታስገርመኛለህ ለኔ ጊዜ አታጣም።
አትልም "አረፈድሽ" አትልም "የት ነበርሽ?"
አትልም "ረፍዷል፤ በይ ሂጂ ተመለሽ!"
አትልም "ለሊት ነው" አትል" ጊዜ የለኝ"
አዝኜ እንደመጣሁ አየሁ ክንድህ ሲያቅፈኝ።
የከበደኝ ሸክም ያጎበጠኝ ቀንበር
የታቀፍኩት ኃጢአት የጸነስኩት ችግር
የሰጠምኩበት ወንዝ የራስኩበት ባሕር
ሲርቅ ይታየኛል፤ ሲቀርበኝ ያንተ ፍቅር።
መመለሴ እንጂ ማርፈዴ አይገድህም
ትቀበለኛለህ አምሽቼ ብመጣም
አፍሬ ካልቀረሁ አሰናክሎኝ ኃጢአት
እኔን ላትቀበል አንተ አትሻም ምክንያት።
ነገ ቸሩ መድኃኔዓለም ነው ።
በዕለቱ ቀኑ ሰናይ ዜና ያሰማችሁ🙏
ብርሃን ወደ ዓለም መጣ።
"
ብርሃንም ወደ ዓለም ስለ መጣ ሰዎችም ሥራቸው ክፉ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለ ወደዱ ፍርዱ ይህ ነው። ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም። እውነትን የሚያደርግ ግን ሥራው በእግዚአብሔር ተደርጎ እንደ ሆነ ይገለጥ ዘንድ ወደ ብርሃን ይመጣል።"ዮሐ.፫፥፲፱-፳፩ በብርሃን ክርስቶስ ብርሃነ ሃይማኖትን እንለብሳለን፣ ብርሃነ ህሊናን እናገኛለን፣ ብርሃነ ምግባርን እንለማመዳለን፣ በብርሃነ መስቀል እንኖራለን፣ ብርሃነ ሕይወትን እናገኛለን፣ ወደ ብርሃናውያን ዓለማት እንገባለን።ኑ በብርሐኑ ተመላለሱ!
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ሃያ አራት በዚህች ዕለት ጌታ ሐዲስ ሐዋርያ ብሎ የሾማቸው የኢትዮጵያ ብርሃኗ የሆኑ የደብረ ሊባኖሱ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ልደታቸው ነው ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
+1
እንኳን የጻድቁ አባት አቡነ ተክለ ሃይማኖት እና እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሣምራ አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
የጻድቁ አባታችንን ክብረ በዓል በደብር ቅዱስ ደብረ መዓዛ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም እና
የእናታችንን ቅድስት ክርስቶስ ሣምራን ክብረ በዓል በደነባ ክርስቶስ ሣምራ ቤተ ክርስቲያን በመገኘት እናክብር።
የሆነ ጊዜ አለመኖር አለ..ጊዜ መስጠት ላለብን ነገር ጊዜ እንስጥ ለሚወዱን ለምናስፈልጋቸው ሰዎች ይልቁንም ለዘለዓለሙ አምላክ ለፈጣሪያችን ለቅዱስ እግዚአብሔር በወጣትነታችን እናገልግለው ጊዜ ሰተን ከደጁ አንጥፋ ቸሩ መድኃኔዓለም ከደጁ አያርቀን ...❤
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
"ሶበ ጸሐፈ ደቅስዮስ ተአምረኪ ቅዱሰ። መንበረ ወዐጽፈ ዕሤተ ጻማሁ ወረሰ። ማርያም ድንግል ዘታብእሊ ፅኑሰ። ዐስበ ማሕሌትየ ዐቅመ ልብየ ኀሠሠ።ጸግውኒ አትሮንሰ ወጽጉየ ልብሰ"
ትርጉም፦ ቅዱስ ደቅስዮስ ልዩ የኾነ ተአምርሽን በጻፈ ጊዜ የድካሙን ዋጋ ልብስንና ወንበርን አገኘ፤ ድኻውን ባለጠጋ የምታደርጊ (ነዳየ አእምሮውን በቃል ኪዳንሽ ባለ አእምሮ የምታደርጊ) ድንግል ማርያም ልቡናዬ በፈለገ መጠን የምስጋናዬን ደሞዝ ወንበርንና የክብር ልብስን ስጪኝ።✨ሊቆቹ አባ ጽጌ ድንግልና አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታም በማሕሌተ_ጽጌ ✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
"ብስራተ ገብርኤል"ማርያም ሆይ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ፡፡እነሆም ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ፡፡”ሉቃ.፩፥፴-፴፩
"ተፈስሂ ደስ ይበልሽ ብለህ ለእመብረሃን ደስታን እንዳበሰርካት ለኛም በለተ ቀንህ ያልታሰበዉን ደስታን አብስረን ብስራተ ዜና ቅዱስ ገብረኤል ታህሳስ 22 እንኳን አደረሳችሁ።🌷መልካም ቀን 🙏
"መንገርስ ለአንቺ ነው መማፀን ወደ አንቺ ፤
ተስፍን ለምትቀጥይ ህልምን ለምትፈቺ።"
እመብርሃን እናቴ ጥላቻ ያቆሸሸውን ስግብግብነት የደፈነውን ኃጥአት ያጨለመውን ልባችንን አብሪልን።
🌹መልካምና ብሩህ ቀን❤️
⚜🌿⚜🌿⚜🌿⚜🌿⚜🌿⚜🌿
"ማሸነፍ ትችል ዘንድ በልብኽ ውስጥ ያለውን የእግዚአብሔር ፍቅር በማያቋርጥ የጸጋ
ስጦታ ልታጠናክረው ይገባኻል፡፡
ብዙዎች የወደቁት ከጸጋው፤ ከጸሎት፤ ከስግደት፤ ከንባብ፤ ከጾም፤ ከመንፈሳዊ ስብሰባዎችና ከቅዱስ ቁርባን ስለተለዩ ነው፡፡
ስለኾነም ጸጋውን ከምታገኝበት መንገድ አትራቅ፡፡"
"መንፈሣዊው መንገድ" በቅዱስነታቸው አቡነ ሺኖዳ ፫ኛ
✨✨✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨✨✨
ቅዱሳን መላእክት ያድኑናል። ነቢዩ ዳዊት "የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።" እንዳለ(መዝ 33(34):7)። ያዕቆብም "ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ እነዚህ ብላቴናዎችን ይባርክ" ሲል እንደመሰከረ(ዘፍ 48:16)።
✔ [ገብርኤል ሆይ! በእግዚአብሔር የታመኑ ሦስቱ ሕጻናትን ከእቶን እሣት እንዳዳንካቸው እኛንም ከክፉ አድነን! አሜን🥀🤲
+4
ጎንዴ መድኃኔዓለም
ይህ ከላይ የምትመለከቱት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያ በአርሲ ሀ/ስብከት በጎንዴ የሚገኝ የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ነው። ህንጻ ቤተ ክርስቲያኑን መስራት ከተጀመረ ረጅም ጊዜ ቢሆነውም እግዚአብሔር ወዶና ፈቅዶ በአካባቢው ምዕመናን ርብርብ እና በሰበካ ጉባኤው ጥረት የፊታችን ጥር 6 እንደሚመረቅ እየሰማን እንገኛለን። ስለሆነም በዕለቱ(ጥር 6/2017 ዓ.ም) ሁላችንም የአሰላ ምዕመናን ሌላ ቀጠሮ ሳንይዝ በስፍራው በመገኘት የአባታችን የመድኃኔዓለም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን እናስመርቃለን። ተዘጋጁ!!!
Share በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ እናርግ።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
‹‹ለእግዚአብሔር በፍርሀት ተገዙ፥ በረዓድም ደስ ይበላችኹ ። ተግሣጹን ተቀበሉ ጌታ እንዳይቈጣ እናንተም በመንገድ እንዳትጠፉ።››
መዝሙር ፪፡፲፩
መልካም አዳር
✝ በቤተ ከርስቲያን ውስጥ ስትቆም #ከቅዱሳን_መላእክት ጋር በገነት እንዳለህ ቁጠርና ከወንድሞቻችህ ጋር አብረህ መጸለይ የማይገባህ አድርገህ ራስህን አዋርድ። ወንድሞችህ እንዴት እንደ ቆሙ ወይም እንዴት እንደሚያዜሙ ለመመልከት ወደፊት እና ወደኋላ እንዳትገላመጥ በንቃት ቁም፡፡ ይልቁንም ራስህን፥ዜማህንና ኋጢአቶችህን ብቻ ተመልከት።
#የሥነ_መለኮት_ሊቅ_ቅዱስ_ስምዖን
