cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

አቡደርዳእ/ኢብኑ ጀሚል 🌙Ibnu jemil channel

💫ሀቅ ከማንም ከመጣልህ ተቀበል!! 💫በምትዘው አቃም ላይ መረጃ ይኑርህ!! 💫ሰውን ተከትለህ ምንም መረጃ ሳይኖርህ አቃም አትመሰርት!! 💫ወደ ሀቅ ጎዳና ከመጣክ አትወዛወዝ፣ከሀቅ ጋር ተያይዞ የምመጣውንም ፈተና ለመቀበል ዝግጁ ሁን!! 💫👇👇ይህ የአቡደርዳእ /ኢብኑ ጀሚል የተሌግራም ቻናል ነው።በአላህ እገዛ የተለያዩ ት/ቶች ይለቀቁበታል። https://t.me/ibnujemilchannel

نمایش بیشتر
أثيوبيا11 929زبان مشخص نشده استدین و مذهبی98 131
پست‌های تبلیغاتی
508
مشترکین
+724 ساعت
+417 روز
+15230 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ማንነትሽን ለማስተዋወቅ ብዙም ሚድያውን ካላጨናነቅኩት አትበይ።ያንቺን ማንነት ማወቅ ቀላል ዘዴ ኣለው።በፃፍሺውና ሎሺን ባጨናነቄው ሰውነትሽ አይደለም።እንደረከሰች ላም ለዛሬ አንድ ገበያ አንድ ገፅታ ለነገ አንድ ገበያ አንድ ገፅታሽን እየቀያየርሽ አትውጪ።ይልቅ ያንቺ ያለው ሰባት ምድር ብኖር አንቺ ሸሪዓው ያዘዘውን ተከትለሽ ቤትሽ ውስጥ በር ዘግተሽ ብትቀመጪ ከየትም ብሎ አንቺን ፍለጋ ይመጣል።እራስሽን ከማራከስ ውጪ ምትጠቀሚበት ምንም ነገር አይኖርም።ትክክለኛ ሰዎች በአንቺ አይነቱ ቀበጥ  ከመመስጥ የጠሩ ናቸው ። ተራ ሰው ጧቱን ብያቀሳስርልሽ  ያዙኝ ልቀቁኝ ኣልሽ!ታዳ ቀበሮን ቀበሮ ብከተለው ምኑስ ይገርማል።እንዳንቺ ያለ ርካሽን የማግኘት እድልሽ እራሱ የጠበበ ነው። አላህ ቀልብ ይስጥሽ 💫https://t.me/ibnujemilchannel
نمایش همه...
አቡደርዳእ/ኢብኑ ጀሚል 🌙Ibnu jemil channel

💫ሀቅ ከማንም ከመጣልህ ተቀበል!! 💫በምትዘው አቃም ላይ መረጃ ይኑርህ!! 💫ሰውን ተከትለህ ምንም መረጃ ሳይኖርህ አቃም አትመሰርት!! 💫ወደ ሀቅ ጎዳና ከመጣክ አትወዛወዝ፣ከሀቅ ጋር ተያይዞ የምመጣውንም ፈተና ለመቀበል ዝግጁ ሁን!! 💫👇👇ይህ የአቡደርዳእ /ኢብኑ ጀሚል የተሌግራም ቻናል ነው።በአላህ እገዛ የተለያዩ ት/ቶች ይለቀቁበታል።

https://t.me/ibnujemilchannel

በአንድ ቀን ፆም የአመት ወንጀል… ——— የዓሹራ ቀን ፆም ትሩፋት! ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል:- قال النبي صلى الله عليه وسلم: "صِيَامُ يَوْمِ عَرَفَةَ أَحْتَسِبُ عَلَى اللَّهِ أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلَهُ وَالسَّنَةَ الَّتِي بَعْدَهُ وَصِيَامُ يَوْمِ عَاشُورَاءَ أَحْتَسِبُ عَلَى اللَّهِ أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلَهُ " رواه مسلم “የዐረፋ ቀን ፆም ከፊቱ ያለውን (አንድ) አመት እና ከኋላው ያለውን (አንድ) አመት ወንጀል ያስምራል (ያሰርዛል) ብዬ በአላህ ላይ እገምታለሁ። #የዓሹራ_ፆም_ከፊቱ_የነበረችውን_አመት_ወንጀል_ያስምራል (ያሰርዛል) ብዬ በአላህ ላይ እገምታለሁ።” ሙስሊም 1162 ዘግበውታል። عن أبي قتادة رضي الله عنه – في صفة صوم النبي صلى الله عليه وسلم وهو حديث طويل – قال : وسئل عن صوم يوم عاشوراء فقال : " يكفر السنة الماضية " أخرجه مسلم , والترمذي , وابن ماجه አቢ ቀታዳ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ስለ ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ፆም ሁኔታ በረጅም ሀዲስ የሚከተለውን ብሏል:- ነቢዩ ﷺ ስለ ዓሹራ ፆም ተጠይቀው ሲመልሱ “ያለፈውን አንድ አመት ወንጀል ያስምራል (ያሰርዛል)።” ብለዋል። [ሙስሊም፣ ትርሚዚይ፣ እና ኢብን ማጃ ዘግበውታል።] ይህ አላህ ለኛ የዋለው ትልቅ ውለታ ነው!። በአንድ ቀን ፆም ምክንያት የአመት ትናንሽ ወንጀሎች ይሰረዛሉ። በመሆኑ በአላህ ፈቃድ ይህን ፆም የወፈቀው ሰው 9ኛውን ቀን ሰኞ ሙሀረም 9/1446 ዓ.ሂ: እንዲሁም በኢትዮ ሐምሌ 8/2016: በፈረንጆች ደግሞ ጁለይ 15/2024 ስለሆነ ሰኞን ፆሞ ማክሰኞን 10ኛውን ቀን ለመፆም እንዲዘጋጅ ሁላችንም በተቻለን መጠን እናነቃቃ፣ (እናስተውስ)። በመልካም ነገር ላይ በማስታወስ ተጨማሪ አጅር ከአላህ ዘንድ ለማግኘት መሽቀዳደም ነው። ✍🏻ኢብን ሽፋ: ሙሀረም 8/1446 ዓ. ሂ #Join ⤵️ የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join ያድርጉና ይቀላቀሉ https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa
نمایش همه...
[ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa]

እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ! በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ! ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ! ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን

قال ابن تيمية رحمه الله : ندمت على تضييع أكثر أوقاتي في غير معاني القرآن ******* قال الحسن البصري رحمه الله يا بني، ماذا يصنع المؤمن إذا لم يبكِ؟ يا بني إن البكاء داع إلى الرحمة. فإن استطعت أن تكون عمرك باكياً فإفعل، لعله تعالى أن يرحمك ..
نمایش همه...
የዓሹራ ቀን አጿጿም እና በዕለቱ የሚከሰቱ ቢድዓዎች ————— እንደሚታወቀው የዓሹራ ቀን ፆም ማለትም ሙሀረም 10ኛውን ቀን መፆም ከታላላቅ ሶናዎች ነው። ነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል:- (أَفْضَلُ الصِّيَامِ بَعْدَ رَمَضَانَ شَهْرُ اللَّهِ الْمُحَرَّمُ) رواه مسلم “ከረመዷን በኋላ በላጩ ፆም የሙሀረም ወር ፆም ነው።” [ሙስሊም 1163 ዘግበውታል።] ይህ ፆም የረመዷን ወር ከመደንገጉ በፊት ግዴታ ነበርም ተብሏል። የሚፆምበትን ምክንያት:- በመሰረቱ እንደ ሙስሊም ማንኛውም በቁርኣን እና በሶሂህ ሀዲስ የመጣን መልካም ስራ፣ ትእዛዝም ይሁን ክልከላ ምክንያቱን አወቅነውም አላወቅነውም መተግበርና መቀበል ግዴታችን ነው። በግልፅ ማስረጃ የመጣ ነገር እስከሆነ ድረስ መተግበር ነው። የዓሹራ ፆም ምክንያት አለው። በሚከተለው ሀዲስም ተብራርቷል:- عن ابن عباس ((قَدِمَ النَّبِيُّ -صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ- المَدِينَةَ فَرَأَى الْيَهُودَ تَصُومُ يَوْمَ عَاشُورَاءَ فَقَالَ مَا هَذَا؟ قَالُوا: هَذَا يَوْمٌ صَالِحٌ، هَذَا يَوْمٌ نَجَّى اللَّهُ بَنِي إِسْرَائِيلَ مِنْ عَدُوِّهِمْ فَصَامَهُ مُوسَى، قَالَ فَأَنَا أَحَقُّ بِمُوسَى مِنْكُمْ فَصَامَهُ وَأَمَرَ بِصِيَامِهِ)).  في صحيح البخاري ከኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ:- “ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ወደ መዲና በገቡ ጊዜ አይሁዶች የዓሹራን ቀን (ሙሀረም 10ኛውን ቀን) ሲፆሙ አዩዋቸው፣ ነቢዩም ለአይሁዶች ይህ ምትፆሙት ምንድነው? አሉዋቸው፣ ይህ ምርጥ ቀን ነው፣ ይህ ቀን አላህ በኒ ኢስራኢሎችን ከጠላታቸው የገላገለበት ቀን ነው፣ ሙሳ ፆሞታል። አሉ፣ ነቢዩም እኔ ለሙሳ ከናንተ የበለጠ የቀረብኩኝ ነኝ ብለው ፆሙት፣ እንዲፆምም አዘዙ።” [ቡኻሪ ዘግበውታል።] አጿጿሙን በተመለከተ:- ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል:- (( لَئِنْ بَقِيتُ إِلَى قَابِلٍ لَأَصُومَنَّ التَّاسِعَ )) ، أخرجه مسلم “ወደፊት ከቆየሁ ዘጠነኛውንም (ቀን) እፆማለሁ።” [ሙስሊም ዘግበውታል።] በዚህ መሰረት ዘጠነኛውንና አስረኛውን ቀን እንፆማለን ማለት ነው። ይህም ከምንም አይነት ጭቅጭቅ ነፃ የሆነው አጿጿም ነው። 10ኛው እና 11ኛው??? ዘጠነኛው ቀን ያመለጠው 10ኛውን እና 11ኛውን መፆሙን በተመለከተ ግን የተወሰኑ ጭቅጭቆች አሉበት። እንደ ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁላህ) ያሉ ሊቃውንቶች 10 እና 11 መፆም ይቻላል ሲሉ የሚከተለውን ሀዲስ ማስረጃ ያደርጋሉ:- (صُومُوا يَوْمَ عَاشُورَاءَ ، وَخَالِفُوا فِيهِ الْيَهُودَ ، صُومُوا قَبْلَهُ يَوْمًا أَوْ بَعْدَهُ يَوْمًا). رواه أحمد في مسنده “የዓሹራን ቀን ፁሙ፣ አይሁዶችን በመቃራንም ከፊቱ ወይም ከኋላው አንድ ቀን ፁሙ።” ኢማሙ አሕመድ በሙስነዳቸው የዘገቡት ሲሆን አልባኒን ጨምሮ ሌሎችም በርካታ ዓሊሞች ዷዒፍ ነው ብለውታል። የዚህን ሀዲስ ዷዒፍነት ያመኑ ዑለማዎች ሆነው ዘጠነኛው ቀን ያመለጠው ሰው 11ኛውን ለመፆሙ ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) "በሚቀጥለው ካደረሰኝ 9ኛውን እፆማለሁ።” ማለታቸው፣ ምክንያቱ ለ11ኛው ቀንም ይሆናል። ይላሉ፣ 9ኛውን ቀን እፆም ነበር ያሉበት ምክንያቱ አይሁዶችን ለመቃረን ነውና። 9ኛውን እና 10ኛውን ቀን ብቻ መፆም ነው፣ 9ኛው ካመለጠ ደግሞ 10ኛውን ብቻ መፆም ነው እንጂ 11ኛው የለም የሚሉት ደግሞ፣ "9ኛውን ቀን እፆም ነበር" ያሉበት ምክንያት አይሁዶችን ለመቃረን ቢሆንም  11ኛውን ለመፆም ማስረጃ አይሆንም ብለዋል። 1ኛ, ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በወቅቱ 10ኛውን ፆመው ነው ያቆሙት እንጂ 11ኛውን አልፆሙም። 2ኛ, በሚቀጥለው ካደረሰኝ 9ኛውን ወይም 11ኛውን እፆማለሁ ሳይሆን ያሉት 9ኛውን ብቻ ነው ከ10ኛው ጨምረው እንደሚፆሙት የተናገሩት። በነዚህ ምክንያቶች አንድ ሰው 9ኛው ካመለጠው 10ኛውን ብቻ ነው የሚፆመው ይላሉ። እንደ ማስረጃው አመዛኝነት ግን ከጭቅጭቁ ለመውጣትም በተቻለ መጠን 9ኛው እንዳያመልጥ ጥረት አድርጎ 9 እና 10 መፆም፣ 9ኛው ካመለጠ ግን ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ንም 9ኛው አምልጧቸው 10ኛውን ብቻ ስለ ፆሙ 10ኛውን ብቻ መፆም ነው። ወላሁ አዕለም!! የዓሹራ ቀን ቢድዓዎች። ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁላህ) እንዲህ ብለዋል:- “መኳኳልን እና መጋጌጥን፣ በቀኑ ለየት ያለ ሶላትን መስገድም ሆነ ሌሎች ለየት ያሉ ተግባሮችን በላጭነት አስመልክተው የመጡ ሀዲሶች በጠቅላላ ዷዒፍ ናቸው። የዚያን ቀን ከመፆም ውጭ ሌሎችን ነገሮች የሚጠቁም አንድም ትክክለኛ ከነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የተረጋገጠ ሀዲስ የለም። "የዓሹራ ቀን ባለው አቅም ሰፋ አድርጎ ያመቻቸ ሰው፣ የሌሎችንም አመታት አላህ ሰፋ ያድርግለት።” የሚለው ሀዲስ ኢማሙ አሕመድ ሶሂህ አይደለም ብለውታል። የዚያን ቀን እለቱን አስመልክቶ መኳኳል፣ መቀባባት፣ ሽቶ መጠቀም፣ ውሸታሞች ያስቀመጡትና ሌላውም ተቀብሏቸው ከሀዘን ወደ ደስታ የሽግግር ቀን ብለው መጋጌጫ አድርገው የያዙት ነው። ይህን ያደረጉት ሙብተዲዕና ከአህሉ ሱንና ያፈነገጡ ጭፍሮች ናቸው። አህሉ ሱንናዎች ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ያዘዙበትን የሚፈፅሙና ሸይጧን ያዘዘበትን ቢድዐ የሚጠነቀቁ (የሚርቁ) ናቸው።” [አልመናር አልሙነይፍ ፊ ሶሂሂ ወዷዒፍ 89] የሳዑዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴም "ይህን ቀን በመጋጌጥም ሆነ በምግብ ለየት ማድረግ አይፈቀድም። እንዲሁም ሺዓዎች እንደሚያደርጉትም የሀዘን ቀን አድርጎ ራስን በስለት መሰል ነገር መጉዳት አይፈቀድም። በዚያን ቀንም ሆነ በሌሎች ቀኖች ፋጢማን መለመን አይፈቀድም፣ በተውበት እንጂ አላህ ከማይምረው ከትልቁ ሺርክም ነው። ” ብሏል። [ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ ቁ. 22177] ሸይኽ ረቢዕ ቢን ሃዲ ዑመይር አልመድኸሊ (ሀፊዘሁላህ) በዚያ ቀን ለዕለቱ ብሎ ለየት ያለ ምግብ አዘጋጅቶ መብላት ይፈቀዳል ወይ? ተብለው ተጠይቀው፣ ሲመልሱ:- "በዓሹራ ለየት ያለ ነገር መዘጋጀት አለበት፣ ወደ አላህ ያቃርባል የሚል እምነት ኖሯቸው ከሆነ የሰሩት ይህ ቢድዓ ነው። ባረከላሁ ፊኩም።” ብለዋል። በሀገራችን በዚህ ቀን የተለያዩ ቢድዐዎች በተለይ ሱፊዮች ዘንድ ይፈፀማልና በዚህ ቀን ከፆም ውጪ ምንም አይነት ለየት ያለ ተግባር እንደሌለ አውቀን ከተለያዩ ቢድዐዎች ተጠንቅቀን ልናስጠነቅቅ ይገባል!!። ✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa) #Join ⤵️  የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join በማድረግ ይቀላቀሉ https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa
نمایش همه...
[ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa]

እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ! በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ! ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ! ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን

የረሳናት ሱና ::::::::::::::::: عَنْ عَائِشَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهَا، قَالَتْ : كَانَ النَّبِيُّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ إِذَا صَلَّى رَكْعَتَيِ الْفَجْرِ اضْطَجَعَ عَلَى شِقِّهِ الْأَيْمَنِ. 📚أخرجه السبعة 📌ከዓኢሻ ተይዞ አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና እንዲህ ትላለች፦ የአላህ መልክተኛ —ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም— የሱብሒን ሁለቱን ረከዓ ከሰገዱ ቦኃላ በቀኝ በኩላቸው ይጋደሙ ነበር። 👌 ይህ ስባል ተኝተህ እዛው ሱብሒን ሳትሰግድ ጎሁ ይውጣብህ ማለት አይደለም ‼በትንሹ ቀብሊያ ከሰገድክ ቦኃላ ገደም በልና ተነስ።ተኝተህ ስታንኮራፋ ጸሃይ ይውጣብህና ሌላ ጣቢያ ውስጥ ትገባለህ። 💫
نمایش همه...
የረሳናት ሱና ::::::::::::::::: عَنْ عَائِشَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهَا، قَالَتْ : كَانَ النَّبِيُّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ إِذَا صَلَّى رَكْعَتَيِ الْفَجْرِ اضْطَجَعَ عَلَى شِقِّهِ الْأَيْمَنِ. 📚أخرجه السبعة 📌ከዓኢሻ ተይዞ አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና እንዲህ ትላለች፦ የአላህ መልክተኛ —ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም— የሱብሒን ሁለቱን ረከዓ ከሰገዱ ቦኃላ በቀኝ በኩላቸው ይጋደሙ ነበር። 👌 ይህ ስባል ተኝተህ እዛው ሱብሒን ሳትሰግድ ጎሁ ይውጣብህ ማለት አይደለም ‼በትንሹ ቀብሊያ ከሰገድክ ቦኃላ ገደም በልና ተነስ።ተኝተህ ስታንኮራፋ ጸሃይ ይውጣብህና ሌላ ጣቢያ ውስጥ ትገባለህ። 💫https://t.me/ibnujemilchannel
نمایش همه...
አቡደርዳእ/ኢብኑ ጀሚል 🌙Ibnu jemil channel

💫ሀቅ ከማንም ከመጣልህ ተቀበል!! 💫በምትዘው አቃም ላይ መረጃ ይኑርህ!! 💫ሰውን ተከትለህ ምንም መረጃ ሳይኖርህ አቃም አትመሰርት!! 💫ወደ ሀቅ ጎዳና ከመጣክ አትወዛወዝ፣ከሀቅ ጋር ተያይዞ የምመጣውንም ፈተና ለመቀበል ዝግጁ ሁን!! 💫👇👇ይህ የአቡደርዳእ /ኢብኑ ጀሚል የተሌግራም ቻናል ነው።በአላህ እገዛ የተለያዩ ት/ቶች ይለቀቁበታል።

https://t.me/ibnujemilchannel

👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
نبدأ من هنا
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
قال الشيخ الوالد المحدث ربيع بن هادي المدخلي حفظه الله تعالى
من عنده عقل وإيمان صادق لا يُخالف سنة الرسولﷺ، ولا يخالفها إلا سخيف العقل أو مجنون - والعياذ بالله - لأنه إذا خالف الحديث الصحيح يكون قد اتبع هواه : ومن أضل ممن اتبع هواه بغير هدىً من الله.
https://t.me/DrRabeeM/1311 المجموع 2/ 108
نمایش همه...
🏝የዛሬ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ የቁርኣን ተፍሲር ፕሮግራማችን በአላህ ፍቃድ እንደተጠበቀ ነው ። 🕌ደቡብ ኣሪ ጂንካ መስጂደ–ረህማን ቀጥታ መከታተል ለምትሹ በዚህ ሊንክ መከታተል ትችላላችሁ👇 🚧https://t.me/ibnujemilchannel
نمایش همه...
አቡደርዳእ/ኢብኑ ጀሚል 🌙Ibnu jemil channel

💫ሀቅ ከማንም ከመጣልህ ተቀበል!! 💫በምትዘው አቃም ላይ መረጃ ይኑርህ!! 💫ሰውን ተከትለህ ምንም መረጃ ሳይኖርህ አቃም አትመሰርት!! 💫ወደ ሀቅ ጎዳና ከመጣክ አትወዛወዝ፣ከሀቅ ጋር ተያይዞ የምመጣውንም ፈተና ለመቀበል ዝግጁ ሁን!! 💫👇👇ይህ የአቡደርዳእ /ኢብኑ ጀሚል የተሌግራም ቻናል ነው።በአላህ እገዛ የተለያዩ ት/ቶች ይለቀቁበታል።

https://t.me/ibnujemilchannel

كتابة الحديث عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ دِينَارٍ قَالَ : كَتَبَ عُمَرُ بْنُ عَبْدِ الْعَزِيزِ إِلَى أَهْلِ الْمَدِينَةِ : أَنِ انْظُرُوا حَدِيثَ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فَاكْتُبُوهُ ؛ فَإِنِّي قَدْ خِفْتُ دُرُوسَ الْعِلْمِ وَذَهَابَ أَهْلِهِ. أخرجه الدارمي لم أقف لصحته ولا لضعفه
نمایش همه...
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.