ASTU Network ®️
رفتن به کانال در Telegram
🛜 ASTU Network ®️ ➲ Join us || @ASTU_Network || || @ASTU_Network_Group || 📚 Library: @ASTU_Network_Library 👁🗨 We are here to keep you updated! ➲ Admin 📩 👤 @NS_Nazu Ⓝ Ŋazarene Ŝon [🥷] |➲| @ASTU_Network
نمایش بیشتر4 765
مشترکین
+724 ساعت
+1307 روز
+25330 روز
آرشیو پست ها
4 765
#ምርጫ2018
#ማሳሰቢያ!
እንደሚታወቀው ነገ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም በሀገራችን ኢትዮጵያ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ይካሄዳል። በመሆኑም ለመምረጥ የተመዘገባችሁ ተማሪዎች ምርጫው ክፍት በሚሆንበት ሰዓት በምትመርጡበት የምርጫ ጣቢያ በመገኘት የምርጫው ተሳታፊ በመሆን ሀገራዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ ይሁን።
#ማስጠንቀቂያ!
ሀገራችን እንደምታውቁት ሰላም የላትም። እዚህም እዚያም የሚሰማው ነገር ለመስማት የሚከብድ እና የሚዘገንን ከሆነ ሰነባብቷል። በመሆኑም በየአካባቢው የጸጥታ ስጋት ሊኖር ስለሚችል ተማሪዎች በተቻላችሁ መጠን እራሳችሁን እንድትጠብቁ እንላለን። ስጋቱን ለመቀነስ እና ደህንነትን ለመጠበቅ ፣ ከተፈቀደው ስዓት ውጪ ባለመንቀሳቀስ እንዲሁም ቢቻል የነገን እና ከዚያ በኋላ ያለውን ቀን ከቤት ባለመውጣት ብታሳልፉ ይመረጣል።
Nobody cares!
Take care of your own self!
መልካም ምሽት!
|➲| @ASTU_Network
4 765
+1
" አንዱ ተማሪ ድንገተኛ ክፍል ላይ እንደደረሰ ህይወቱ አልፏል። ሁለቱ ደግሞ ኦፕራሲዮን ክፍል ከገቡ በኋላ ነው ህይወታቸው ያለፈው " - የጤና ባለሞያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
በጎንደር ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ ተማሪዎች ተሰብስበው የአርሰናል እና ፒኤስጂ የቻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ጨዋታ እያዩ በነበረበት ወቅት በተከሰተው ፍንዳታ የተጎዱ ተማሪዎች ለህክምና ወደ ዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል መምጣታቸውንና የሞቱ ተማሪዎች እንዳሉ አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ የጤና ባለሞያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
በዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል እንደሚሰሩ የገለጹልን እኚሁ የጤና ባለሞያ ፍዳታው የተከሰተው ትናንት ምሽት 2 ሰዓት ተኩል ገደማ መሆኑን ገልጸውልናል።
" ማን እንደጣለው አይታወቅም ቦምብ ፈንድቶ ነው በርከት ያሉ ተማሪዎች ተጎድተው የመጡት። የሞቱ አሉ መባሉም እውነት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" አንዱ ተማሪ ድንገተኛ ክፍል ላይ እንደደረሰ ህይወቱ አልፏል። ሁለቱ ደግሞ ኦፕራሲዮን ክፍል ከገቡ በኋላ ነው የሞቱት። ሦስት ተማሪዎች ናቸው የሞቱት " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
የተጎዱ ተማሪዎች ስንት ናቸው ? ያልናቸው ባለሙያው " የተጎዱት በርከት ያሉ ተማሪዎች ናቸው። ቁጥሩን በትክክል አላውቀውም ግን በርከት ያሉ ተጎጂ ተማሪዎች ናቸው የመጡት " ብለዋል።
ተማሪዎች የተግጂዎችን ቁጥር 20 አድርሰውታል፤ በርከት ያሉ ሲባል 20 ይሆናሉ ? ስንላቸው፣ " ይሆናሉ አዎ። እንደዛ ይሆናሉ " ሲሉ መልሰዋል።
ፍንዳታው የቦምብ መሆኑን እንዴት እንደታወቀ ሲገልጹ ፥ " ቦምብ መሆኑን ያወቅነው ከጉዳቱ አንፃር ፍንጥርጣሪዎቹ ቁስል ላይ ስለተገኙ ነው " ብለዋል።
የተግዱት የዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል ውስጥ ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 765
" በፍንዳታው የተማሪዎች ህይወት አልፏል ፤ ጉዳትም ደርሷል " - የጎንደር ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች
⚫️ " መጀመሪያ ላይ የሆነ የሮኬት አይነት ድምጽ ተሰማን፣ ከዛ ስንነሳ እንደመብረቅ ድፍን ነው ያደረገን ! "
በጎንደር ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ትላንት ምሽት የአርሴናል እና ፒኤስጂ የቻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ ጨዋታ በሚተላለፍበት ወቅት በተከሰተ "ፍንዳታ" የተማሪዎች ህይወት ማለፉና ጉዳት መድረሱን የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ተማሪዎቹ ፍንዳታው "ቦንብ" ነው ሲሉ የገለጹ ሲሆን "ዲ.ኤስ ቲቪ ውስጥ ጭንቅንቅ ብሎ ስለነበር ከቦንቡ በተጨማሪ ተረጋግጦ የተጎዳም አለ ትክክለኛው ጉዳት ምን ያህል እንደሆነ ማወቅ አልቻልንም" ብለዋል።
አደጋው ስለተከሰተበት ሰዓትም ሲያስረዱ ፥ "የአርሰናል ጨዋታ የመጀመሪያው 45 ደቂቃ ሊያልቅ ጥቂት ደቂቃ ሲቀረው ነው ፍንዳታውን የሰማነው" ሲሉ ለቲክቫህ ተናግረዋል።
አንድ ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ የጤና ሳይንስ ተማሪ ፤ " አሁን ላይ በካምፓሱ ፖሊሶች ገብተው የፍንዳታውን መንስኤ እያጣሩ ነው " ያለ ሲሆን " አሁን ካምፓሱ ሰላም ነው፣ ግን ከዚህ በፊት ከነበረው ሁኔታ የተወሰነ ነገር ተቀይሯል። ጠዋት ላይ የሞቱ ልጆችን አስክሬን ወደቤተሰቦቻቸው ሸኝተናል። አሁን የተወሰነ የሀዘን ድባብ አለ። ግን ተረጋግቷል " ብሏል።
" በትክክል የሟቾች ቁጥር ባይታወቅም በእርግጠኝነት ሁለት ተማሪዎች ሞተዋል። ጠዋት የአስክሬን ሽኝት አድርገናል። አሁንም ቢሆን ሌላ የሞተ ተማሪ ይኖራል። ማታ ጉዳት ከደረሰባቸው ውስጥ በርካቶች በአንቡላንስ ወደ ጤና ተቋማት ተወስደዋል። ፍንዳታው ያስከተለው ጉዳት ከባድ ነው " ሲል አክሏል።
አብዛኞቹ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች በካምፓሱ ውስጥ በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑንም ጠቁሟል።
በሰዓቱ ጨዋታውን ከፊት ወንበር ላይ ሁኜ እያየሁ ነበር ያለን አንድ ተማሪ ደግሞ " የመጀመሪያው የጨዋታ ስዓት አልቆ ለእረፍት ልንወጣ ስንል ነው ፍንዳታው የተከሰተው " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።
" በጣም ትልቅ አዳራሽ ነው ኳስ የምናይበት፣ ግን በጣም ሰው ሞልቶት ተጨናንቋል፣ መግቢያ መውጫ የለውም። እያየን የነበረው በፕሮጀክተር እና በቴሌቪዥን ነበር " ሲል ገልጿል።
" መጀመሪያ ላይ የሆነ የሮኬት አይነት ድምጽ ተሰማን፣ ከዛ ስንነሳ እንደመብረቅ ድፍን ነው ያደረገን። ከፊታችን ብረት ስለነበር በድንጋይ መተውት ነው ብለን ነበር ያሰብነው። ግን ጭሱ በጣም አፈነን፣ በጣም ብዙ ተማሪ ነበርን እየተረጋገጥን በድንጋጤ ወጣን " ሲል አስረድቷል።
" ውጪ ከወጣን በኋላ ብዙ ተማሪ መመታቱን አየን፣ እኔም መጀመሪያ ደህና ነበርኩ፣ ከወጣሁ በኋላ ሳይ እግሬን ተመትቻለሁ። ምን እንደፈነዳ እንኳ አላውቅም። እኔ ያየሁት የሞቱ ሁለት ናቸው። ሌላ አላየሁም። ግን ለሞት የሚያሰጋቸው አሉ " ሲል አክሏል።
" ሁለቱንም እግሬን ነው የተመታሁት፣ እስካሁን እግሬ ላይ የገባው የፍንዳታው ፍንጥርጣሪ አልወጣልኝም። ግንባሬንም ተመትቻለሁ" ሲል በስዓቱ የተፈጠረውን ገልጿል።
የትላንት ምሽቱን ፍንዳታ ለዩንቭርስቲው ቅርበት ያላቸው የከተማው ነዋሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያረጋገጡ ሲሆን ተማሪዎች መጎዳታቸውንና ህይወታቸው ያለፉ "ተማሪዎች" መኖራቸውንም ገልጸዋል።
የሞቱት ተማሪዎች ቁጥር 3 እንደሆነ፤ 3 ሌሎች ተማሪዎች ከባድ አደጋ እንደደረሰባቸውና ከ30 ያላነሱት ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን እኚሁ ቅርበት ያላቸው ሰው አረጋግጠዋል።
ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ሌላኛው የጎንደር ነዋሪም " በዩኒቨርሲቲ የምትማር አንድ ልጅ አለች ብዙ ተማሪ መጎዳቱን ገልጻልኛለች እኛም መረጃውን ሰምተናል። ምን ያህል ተማሪዎች እንደተጎዱ እና ስለፍንዳታው አይነት ግን አላውቅም " ሲሉ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን በተመለከተ የተማሪዎች ህብረት አመራሮችን አነጋግሯል ፤ የቦምብ ፍዳታ መከሰቱንና የተማሪ ህይወት ማለፉን አረጋግጠዋል።
" ፍንዳታው በቦምብ ነው የተከሰተው፤ ተማሪዎች የዲኤስቲቪ ኳስ ጨዋታ እየተከታተሉ ባሉበት ሰዓት ነው የተከሰተው " ሲሉ ነው የገለጹት።
የተጎዱ ተማሪዎችን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸው አመራሮቹ " የተጎዱ ተማሪዎች የህክምና ክትትል እያደረጉ ነው ያሉት፤ በርካታ ተማሪዎች ነበሩ የተጎዱት ግን የተወሰኑ ተማሪዎች ናቸው። ውስጡ ያሉ ተማሪዎች ሙሉ አልተጎዱም " ሲሉ አክለዋል።
ህይወታቸው ያለፉ ተማሪዎች ስለመኖራቸው ጥያቄ ያቀረብንላቸው የተማሪዎች ኅብረት አባላት " ሁለት ተማሪዎች ለህክምና ከገቡ በኋላ ህይወታቸው አልፏል። ሆስፒታል ከገቡ በኋላ ነው ህይወታቸው ያለፈው " ብለዋል።
የተማሪዎቹ አስክሬንም ለቤተሰቦቻቸው መላኩን አክለው ገልጸውልናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን ከዩኒቨርስቲው አመራሮች ተጨማሪ ቃል ለመቀበል ያደረገው ተደጋጋሚ ጥረት አልተሳካም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 765
+1
#ምርጫ2018
ምን ያህል የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በመራጭነት ተመዘገቡ ?
በዩኒቨርስቲዎች በተከናወነ የመራጮች ምዝገባ 20,122 ተማሪዎች የመራጭነት ምዝገባ ማከናወናቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ለሰጠው መግለጫ አስታውቋል።
ለመራጭነት የተመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር ማነሱን ተመልክቶ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለምን ? ሲል ለቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ ጥያቄ አቅርቧል።
ሰብሳቢዋ ቁጥሩ አነስተኛ መሆኑን ገልጸው ሆኖም በአከባቢያቸው ባለ ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ በርካታ ተማሪዎች በአከባቢያቸው ባለ የምርጫ ጣቢያ በመመዝገባቸው ቁጥሩ መቀነሱን በምክንያትነት ጠቅሰዋል።
ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የለማው የመመዝገቢያ ፕላትፎርም ዘግይቶ ወደ ተግባር መግባቱን የገለጹት ሰብሳቢዋ ጉዳዩ ምርመራ የሚጠይቅ ቢሆንም በአጭሩ ግን በመደበኛ መኖሪያ ቦታቸው በመደበኛው የምዝገባ ሁኔታ የተመዘገቡ ብዙ አሉ ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም
@tikvahethiopia
4 765
#ስፖርት : በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ፒኤስጂ አርሴናልን በፍጹም መለያ ምት በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት መሆን ቻለ።
ፒኤስጂ አርሰናልን በመለያ ምት 4 ለ 3 ማሸነፍ ችሏል።
ሁለቱ ክለቦች መደበኛውን የጨዋታ ክፍለጊዜ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀው ተጨማሪ ደቂቃ ቢሰጣቸውም ሊሸናነፉ አልቻሉም። ይህን ተከትሎ ወደ መለያ ምት አምርተው ፒኤስጂ ማሸነፍ ችሏል።
ፒኤስጂ ለተከታታይ አመት ነው ዋንጫውን ማንሳት የቻለው።
ቲክቫህ ስፖርት / @tikvahethsport
ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 765
🚀 Tech With Hos
Joke aside — This channel is about building skills that actually open doors in tech.
👉 What you’ll find here:
➲ Core 💻 Computer Science & programming fundamentals.
➲ Competitive programming insights (ICPC 🧠 mindset)
➲ Real-world 🌐 software development tools, workflows, and projects
➲ Practical data analysis 📊 concepts
➲ Lessons inspired by ICPC finalists and top 🏆 competitive programmers
➲ Career guidance from seniors working in big tech
➲ Essential tech news 📰 and trends for serious students
For students who think long-term, build leverage early, and aim high.
Maintained by -👨💻 Mr. Hosam Adem 🔰Software Engineering student at ASTU, 🔰Competitive Programmer & A2SVian 📥 Contact hos - TelegramJoin Channel |➲| Tech with hos #techwithhos #technews #hos
4 765
#Update #CBE
ውድ ደንበኛችን:
*
የተሻሻለውን የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ሲያዘምኑ 'Passphrase' ጠይቆዎት ከነበረ ወይም ማንኛውንም አይነት ድጋፍ ካስፈለገዎት ወደ አቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ በመሄድ አገልግሎቱን እንደገና በቀላሉ አስጀምረው መጠቀም የሚችሉ መሆኑን እያሳወቅን፤ መተግበሪያውን እስኪያስተካከሉ ድረስ አገልግሎቱን በ USSD *889# በኩል እንዲጠቀሙ በአክብሮት እንገልፃለን።
በዚህ አጋጣሚ ከሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ጋር በተያያዘ በስልክ ተደውሎ የሚሰጥ ምንም አይነት የአሰራር ሂደት የሌለ መሆኑን በመረዳት እራስዎን ከአጭበርባሪዎች ይጠብቁ።
ለማንኛውም አይነት መረጃ 951 በነፃ ይደውሉ!
*
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!!
©️ CBE
|➲| @ASTU_Network
4 765
#ENEC 🤝 #ASTU
Adama Science and Technology University Signs MoU with Ethiopian Nuclear Energy Commission
======================================
Adama Science and Technology University (ASTU) has signed a Memorandum of Understanding (MoU) with the Ethiopian Nuclear Energy Commission on May 29, 2026, at the Commission’s office in Addis Ababa.
The agreement aims to establish a strong and sustainable partnership between ASTU and ENEC in advancing national human capacity development, academic programs, research, and institutional collaboration in the peaceful application of nuclear science and technology, in line with Ethiopia’s national nuclear policy and International Atomic Energy Agency (IAEA) standards.
The collaboration will focus on curriculum design and academic development based on IAEA frameworks, education and training, research and development, practical training and internship opportunities, capacity building and knowledge management, as well as workshops and scientific events.
During the discussion, both institutions emphasized the importance of transforming the agreement into practical and impactful activities that contribute to national development and technological advancement.
The MoU was signed by Dr. Lemi Guta, President of ASTU, and Mr. Sandokan Debebe, Commissioner of ENEC.
ASTU, the very University for you!
We are dedicated to innovative knowledge!
|➲| @ASTU_Network
4 765
+9
#ENEC 🤝 #ASTU
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ኒውክሊየር ሀይል ኮሚሽን ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ
======================================
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (ASTU) ከኢትዮጵያ ኒውክሊየር ሀይል ኮሚሽን (ENEC) ጋር ግንቦት 21/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው በኮሚሽኑ ጽ/ ቤት የመግባቢያ ሰነድ (MoU) ተፈራርሟል።
ስምምነቱ በኢትዮጵያ ብሔራዊ የኒውክሊየር ፖሊሲ እና በዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ (IAEA) መስፈርቶች መሰረት በኒውክለር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሰላማዊ አጠቃቀም ዘርፍ የሰው ኃይል ልማት፣ የትምህርት ፕሮግራሞች፣ ምርምር እና ተቋማዊ ትብብርን ለማጠናከር የተዋቀረና ዘላቂ የትብብር ማዕቀፍ ለመፍጠር ያለመ ነው።
ትብብሩ በIAEA ማዕቀፎች መሰረት የሥርዓተ ትምህርት ንድፍና የአካዳሚክ ልማት፣ ትምህርትና ስልጠና፣ ምርምርና ልማት፣ ተግባራዊ ስልጠናና የልምምድ ዕድሎች፣ የአቅም ግንባታና የዕውቀት አስተዳደር፣ እንዲሁም ወርክሾፖችና ሳይንሳዊ ዝግጅቶች ላይ ያተኩራል።
በውይይቱ ወቅት ሁለቱም ተቋማት ስምምነቱን ለሀገራዊ ልማትና ቴክኖሎጂ ዕድገት የሚያበረክቱ ተግባራዊና ውጤታማ እንቅስቃሴዎች ለማድረግ ያለውን አስፈላጊነት አጽንኦት ሰጥተዋል።
የመግባቢያ ሰነዱን የአ.ሳ.ቴ.ዩ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ለሚ ጉታ እና የኢ.ኒ.ሀ.ኮ ኮሚሽነር አቶ ሳንዶካን ደበበ ተፈራርመዋል።
|➲| @ASTU_Network
4 765
#ENEC 🤝 #ASTU
የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን እና የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን (ENEC) ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (ASTU) ጋር ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በሚገኘው የኮሚሽኑ ዋና መስሪያ ቤት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።
ይህ ስምምነት በኢትዮጵያ ብሔራዊ የኒውክሊየር ፖሊሲ እና በዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ (IAEA) መስፈርቶች መሰረት በኒውክሊየር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሰላማዊ አጠቃቀም ዘርፍ የተቀናጀና ዘላቂ የትብብር ማዕቀፍ ለመፍጠር ያለመ ነው።
ትብብሩ በዋናነት በሰው ኃይል ልማት፣ በስርዓተ ትምህርት ንድፍና አካዳሚክ ልማት፣ በምርምርና ልማት፣ በተግባራዊ ስልጠና፣ በአቅም ግንባታ እንዲሁም በሳይንሳዊ ዝግጅቶች ላይ የሚያተኩር ሲሆን፤ የሁለቱ ተቋማት አመራሮች ስምምነቱ ለሀገራዊ ልማትና ዕድገት ፋይዳው የላቀ መሆኑን በመግለጽ ውጤታማ ስራዎችን ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የመግባቢያ ሰነዱን የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ለሚ ጉታ እና የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሳንዶካን ተፈራርመውበታል።
|➲| @ASTU_Network
4 765
YouTube trusted creators since 2024. Now it trusts machines.
For two years, creators were asked to label AI videos themselves.
Many simply did not do it.
So YouTube built a system that detects AI on its own.
Soon every AI video you watch will carry a visible label.
The marker now sits right below the video, not hidden away.
You will know what is real before you press play.
©️ The Next Web
|➲| @ASTU_Network
4 765
#ጥቆማ
የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን የነጻ ትምህርት ዕድል ጥሪ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ጠንካራ ሀገራዊ የኒውክሊየር መሰረተ ልማት ለመገንባት የሚያስችሉ ከፍተኛ ባለሙያዎችን ለማፍራት ለኢትዮጵያውያን ተማሪዎችና ሰልጣኞች በሩሲያ የነጻ ትምህርት ዕድል ማመቻቸቱን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ለ2026/27 የትምህርት ዘመን በሩሲያ በሚገኙ ስመጥር የሳይንስና የምህንድስና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ መማር የሚፈልጉ ብቁ አመልካቾች እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።
የሚሰጡ የትምህርት ዘርፎች በኒውክሊየር ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮሩ ሲሆን እነዚህን ዘርፎችንም ያካትታል ፡-
- Nuclear Power Engineering and Heat Physics (BSc & MSc)
- Nuclear Physics and Technology (BSc)
- Nuclear Power Plants Design, Operation and Engineering (BSc)
- Heat Power Engineering (BSc)
- Management in Technological Systems (MA)
የመወዳደሪያ መስፈርቶች ?
• ለመጀመሪያ ዲግሪ (BSc) ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት ያልበለጠ እና የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ አማካኝ ውጤታቸው 500 እና ከዚያ በላይ የሆነ።
• ለሁለተኛ ዲግሪ (MSc/MA) ዕድሜያቸው ከ30 ዓመት ያልበለጠ እና በሳይንስና ምህንድስና ዘርፍ በከፍተኛ ውጤት የተመረቁ።
ሴት አመልካቾች ለዘርፉ እንዲበረታቱ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል።
መስፈርቱን ምታሟሉ አመልካቾች ከዛሬ ጀምሮ ባሉት 5 የሥራ ቀናት ውስጥ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን እና ደጋፊ ሰነዶቻችሁን በPDF በማዘጋጀት በኮሚሽኑ የኢሜል አድራሻ enecinfo@enec.gov.et መላክ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።
ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 765
Repost from 𝐀𝐒𝐓𝐔 𝐄𝐧𝐭𝐞𝐫𝐭𝐚𝐢𝐧𝐦𝐞𝐧𝐭 ™️
When you finally reach home and find them watching TV 📺😁
You guys still watch TV? 😅
4 765
ለክቡራን የባንካችን ደንበኞች፡
**********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አገልግሎቱን ቀላል፣ ምቹ እና በማንኛውም ሰዓት ተደራሽ ለማድረግ ዲጂታል የአገልግሎት አማራጮችን በየጊዜው ለደንበኞቹ እንደሚያቀርብ ይታወቃል።
ከባንኩ ዲጂታል የአገልግሎት አማራጮች መካከል ደግሞ ደንበኞች ሂሳባቸውን በቀላሉ በማንኛውም ሰዓት እና ቦታ በስልካቸው እንዲያንቀሳቅሱ ያስቻለው የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ዋነኛው ነው።
ባንካችን የደንበኞችን የአገልግሎት እርካታ ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በየጊዜው አገልግሎቱን የሚያዘምን ሲሆን፣ በአሁኑ ጊዜም በርካታ አዳዲስ የአገልግሎት አማራጮችን በማካተት እና ለአጠቃቀም ምቹ እና ቀላል በማድረግ የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት መተግበሪያውን በአማራጭነት አሻሽሎ አቅርቧል።
በዚህ መሠረት የተሻሻለውን የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ በርካታ ደንበኞች እየተጠቀሙበት ሲሆን፣ አዲስ በመሆኑ ምክንያት በተወሰኑ ደንበኞች ላይ የአገልግሎት መስተጓጎል እንዳጋጠመ ተረድተናል። ባንካችን ለተፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎል ይቅርታ እየጠየቀ፣ ችግሩን በአፋጣኝ ለመፍታት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን እና ችግሩ እንደተፈታም ለደንበኞቻችን እንደምናሳውቅ ለመግለፅ እንወዳለን።
ከተሻሻለው መተግበሪያ ጋር በተገናኘ ችግር ያጋጠማችሁ ደንበኞቻችን ከታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ በመግባት፤ ወደ 951 ነፃ የደንበኞች የጥሪ ማዕከል በመደወል ወይም በባንካችን የማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ በመግባት ድጋፍ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡
https://chat.whatsapp.com/BFR1h7SrAti091qznFEP4u
4 765
#ጥቆማ
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በስሩ በሚገኙ የኢንጂነሪንግ፣ የጤና እና የቢዝነስና ማኅበራዊ ጥናት ኮሌጆች በ2019 ዓ.ም በተለያዩ የመጀመሪያ ዲግሪ መርሐግብሮች ተማሪዎችን ተቀብሎ በመደበኛ ፕሮግራም ለማስተማር ይፈልጋል።
የምዝገባ መስፈርቶች
➫ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና የወሰዱ
➫ በትምህርት ሚኒስቴር የተቀመጠውን የመግቢያ ነጥብ የሚያሟሉ
➫ ሙሉ ጤነኛና ለጤና ምርመራ ፈቃደኛ የሆኑ
➫ ወታደራዊ ስልጠና ለመውሰድ ፈቃደኛ የሆኑ
➫ የመከላከያ ምልመላ መስፈርቶችን የሚያሟሉ
በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች 1ኛ ዓመት ወይም ከዚያ በላይ የምትማሩ ተማሪዎች በዝውውር 2ኛ ዓመት መቀጠል ትችላላችሁ ተብሏል፡፡
የትምህርት መስኮች
➫ የኢንጂነሪንግ ኮሌጅ ፕሮግራሞች (Bachelor of Technology)
➫ የቢዝነስና ማኅበራዊ ጥናት ኮሌጅ ፕሮግራሞች (BA)
➫ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ፕሮግራሞች (BSc)
የምዝገባ ጊዜ የሚያበቃው 👇
ሰኔ 05/2018 ዓ.ም
የመመዝገቢያ አማራጮች
➫ በአካል በተቋሙ የምዝገባ ማዕከላት
➫ በኦንላይን ለመመዝገብ 👇
https://www.etdu.edu.et/admission/register
ለምዝገባ የሚያስፈልጉ ሰነዶች
➫ የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ውጤት
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት
➫ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት
➫ ኦርጂናል ሰነዶች ከሁለት ኮፒ ጋር
➫ ሁለት ጉርድ ፎቶግራፍ
ለበለጠ መረጃ 👇
ዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር፦ 0114308408
@tikvahuniverity
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
