Mella Tutorials
رفتن به کانال در Telegram
A hub of wisdom. Subscribe on Youtube | www.youtube.com/@mella_tutorials Buy ads https://telega.io/c/mella_tutorials
نمایش بیشتر6 222
مشترکین
-924 ساعت
-437 روز
-8530 روز
آرشیو پست ها
6 224
6 224
Hello everyone,
Today’s lesson covers the Simplex method for Linear Programming (minimization problems) using the Big-M approach. It has been carefully explained through three clear and well-structured examples.
We encourage you to watch, share the link with others, and stay engaged as we continue completing the remaining chapters.
Please remember to use a VPN while watching.
Thank you 🙏
ሰላም እንዴት ናችሁ
ዛሬ በዚህ ቪድዮ simplex LPM for minimization case using Big-M method በቆንጆ ሁኔታ 3 ምሳሌዋችን በመጠቀም እንመለከታለን።
ሁላችሁም በማየት እና ለብዙዋች በማጋራት ቀጣይ የቀሩትን ምዕራፎች እንድንጨርስ አበርቱን።
በ VPN መመልከታችሁንም አትርሱ
እናመሰግናለን 🙏
https://youtu.be/SU2YXMqtLbo
6 224
ለማኔጅመንት፣ ቢዝነስ ማኔጅመንት እና አድሚንስትሬሽን ተማሪዎች በሙሉ
የካቲት 19 2018 ዓም የተሰጠውን የ2 session exit ጥያቄዎችን ጨምሮ ከ2015 ጀምሮ ሲሰጡ የነበሩትን Original Exit ጥያቄዎችን ከነማብራሪያ መልሳቸው የያዘ
በተጨማሪም
16ቱም ኮርስ ላይ የተዘጋጁ አጫጭር ኖቶችን እንዲሁም በየኮርሱ የተዘጋጁ model ጥያቄዎችን ከፈለጉ ሁሉንም በአንድ ላይ የያዘ documents መላ ቱቶሪይልስ አዘጋጅቶላችኋል።
በስልክ ቁጥር 0933025888/0710526605 ይደውሉልን።
6 224
ለማኔጅመንት፣ ቢዝነስ ማኔጅመንት እና አድሚንስትሬሽን ተማሪዎች በሙሉ
የካቲት 19 2018 ዓም የተሰጠውን የ2 session exit ጥያቄዎችን ጨምሮ ከ2015 ጀምሮ ሲሰጡ የነበሩትን Original Exit ጥያቄዎችን ከነማብራሪያ መልሳቸው የያዘ
በተጨማሪም
16ቱም ኮርስ ላይ የተዘጋጁ አጫጭር ኖቶችን እንዲሁም በየኮርሱ የተዘጋጁ model ጥያቄዎችን ከፈለጉ ሁሉንም በአንድ ላይ የያዘ documents መላ ቱቶሪይልስ አዘጋጅቶላችኋል።
በስልክ ቁጥር 0933025888/0710526605 ይደውሉልን። @melakubeshaw ያናግሩን
6 224
#AD
ሠላም AHADU(፩) WRITERS ነን
⚡️CV እና Application Letterዎን ለቀጣሪዎች እጅግ ሳቢ በሆነ መልኩ እና እርሶን በልዩ መልኩ የሚገልጽ ችሎታዎን እውቀቶን እና ልምዶን በአግባብ የሚያሳይ አጭር እና ግልጽ በሆነ መንገድ እንሠራሎታለን
በተጨማሪም CV እና Application Letterዎን ሲያፅፉ
🌟 አንድ ጊዜ በከፈሉት ክፍያ እስከ 3 ጊዜ የሚደርስ ነፃ የCV Editing
🌟 እዲሁም ስለCV እና በዛ ዙሪያ ነፃ የማማከር አገልግሎት ያገኛሉ
⭐️ https://t.me/AhaduCv16
ባስቀመጥንላችሁ Link ወደ አሀዱ Channel ተቀላቀሉ የተለያዩ በCV, Interview እና ስራን የሚመለከቱ ጠቃሚ Tipochun ታገኛላችሁ
🌟🌟🌟ከብዙሃኑ ተለይተው ወደ ቀጣዬ ደረጃ መሸጋገር ከፈለጉ🌟🌟🌟
⚡️በ0984749011 እና
⚡️0973068724
@Felishaa24
@Joocv07
በአሀዱ የስራ ጉዞውን ያቅልሉ
6 224
Operation Research lecture videos
Operation Research (OR): https://www.youtube.com/playlist?list=PL5SvRn1ByFvv7mEw-YtjBttPhx6HxCD_D
6 224
Eid Mubarak عيد مبارك ኢድ ሙባረክ
እንኳን ለ 1447ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
Wishing you all a joyous Eid-ul-Fitr filled with happiness and blessings.
@mella_tutorials
6 224
#ExitExam
" ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜው ነገ ዓርብ ነው የሚያልቀው። ላቀረቡት ለእያንዳንዱ ቅሬታ በቂ ምርመራ ተደርጎ፣ ተፈትሾ ምላሽ ይሰጣቸዋል " - አገልግሎቱ
የ2018 ዓ.ም አጋማሽ አመት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤት ለማየት እንደተቸገሩ ፤ ለትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ቅሬታ ቢያቀርቡም እስካሁን ምላሽ ያልተሰጣቸው እንዳሉ አሁንም እየገለጹ ናቸው።
የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት በበኩሉ፣ ፈተናቸውን ሪፖርት ያደረጉ ሰዎች ላይ " ቅሬታ አለኝ፣ ሪፖርት የተደረገብኝ ጉዳይ አግባብነት የለውም " የሚሉ ተፈታኞች ቅሬታ ማቅረብ መብታቸው መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ይህን ያሉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር)፣ " ገና ቅሬታ እየተቀበልን ነው ያለነው " ብለው፣ " ለቀረበው ቅሬታ ደግሞ ምላሽ እየሰጠን እንገኛለን " ብለዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ፣ ፈተና ወስደው ቅሬታ ላላቸው ተማሪዎች " ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜው ነገ ነው የሚያልቀው " ሲሉም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
" ከዓርብ በኋላ በአካል መጥተው አንድ በአንድ ሊያቀርቡ ይችሉ ይሆናል። ግን የቅሬታ ጊዜ ተብሎ የተሰጠው ከባለፈው ዓርብ እስከ ነገ ዓርብ ነው አንድ ሙሉ ሳምንት ነው የሰጠነው " ነው ያሉት።
ውጤቱ የተለቀቀው ሐሙስ ማታ መሆኑን አስታውሰው፣ " ስለዚህ እስከ ነገ ዓርብ 10 ሰዓት ድረስ ቅሬታቸውን ማቅረብ ይችላሉ። ላቀረቡት ደግሞ ለእያንዳንዱ ቅሬታ በቂ ምርመራ ተደርጎ፣ ተፈትሾ ምላሽ ይሰጣቸዋል " ብለዋል።
ተፈታኝ ተማሪዎች በበኩላቸው ቅሬታቸውን ቢያቀርቡም ወዲያው መልስ እንዳልተሰጣቸው፣ በተደጋጋሚ እየገለጹ ናቸው።
ለዚሁ ቅሬታ በሰጡት ምላሽ እሸቱ (ዶ/ር)፣ ወዲያውኑ ምላሽ የማግኘት ፍላጎት እንደሚኖር ገልጸው፣ " የቅሬታ አቅራቢዎቹ ቁጥር የራሱ ቅደም ተከትል ስላለው እየፈታን ነው ያለነው፤ በትዕግስት ቢጠብቁን ለሁላቸውም መልስ እንሰጣለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ነገር ግን ተማሪዎቹ በሚያውቁት ጉዳይ ቅሬታ ብለው የኛንም የራሳቸውንም ጊዜ አያጥፉ ሲሉ መክረው፣ " በተለያየ የዲስፕሊን ኬዝ እነርሱም የሚያውቁት እኛም የምናውቀው ጉዳይ ላይ ያሉ ልጆች ያንን መቀበል ነው " ያለባቸው ብለዋል።
በተያያዘ፣ ተፈታኝ ተማሪዎች ከሰሞኑ ቅሬታ ለማቅረብ ወደ ተቋሙ በአካል በቀረቡበት ወቅት በተቋሙ ሰዎች "የማመናጨቅ" ሁኔታ እንደገጠማቸው እና "ስማችህን እና ስልክ ሞልታችሁ" ሂዱ እንደተባሉ በመግለጽ፣ ለሁሉም ተማሪ እየደወሉ ሊነግሩ ነው ወይ? የሚል ስሞታ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ይህ ለምን እንደሆነ የተቋሙን ዋና ዳይሬክተር ምላሽ የጠየቃቸው ሲሆን፣ እሳቸውም ሰዎች በአንዳንድ ነገር ስሜታዊ ሊሆኑ እንደሚችሉ ገልጸዋል።
የስልኩን ጉዳይ በተመለከተ ደግሞ፣ "መረጃ የሚቀበል፤ ቁጭ ብሎ የሚመረምር፤ ምላሽ የሚሰጥ አለ። የተስተካከለ ውጤት ካለ በውጤት ማያው ላይ አይተህ ማረጋገጥ ትችላለህ በሚል በስልክ እንነግራለን ሲስተም ላይ ስልክ ስላለ። የተገልጋይ ቁጥሩ ትንሽ ሲሆን ደግሞ በሰውም እንነግራለን" ብለዋል።
"ከመሰለፍ" ይልቅ፣ ቅሬታቸውን በፅሑፍ ካስገቡ "በቂ" መሆኑን እና ምላሽ እንደሚሰጡ ገልጸው፣ በምላሹ ላይ ካልረኩ በድጋሚ ቅሬታ ማቅረብ መብታቸው መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
6 224
#ምላሽ
#ExitExam
" የ11 ሺሕ 785 ተማሪዎች የዲሲፕሊን ኬዝ አጋጥሟል። የ817 ተማሪዎች ውጤት ሙሉ በሙሉ ' Disqualified ' ነው። የፈተና ሰዓት ያልተገበሩ 2,076 ልጆችም Disqualified ነው " - እሸቱ ከበደ (ዶ/ር)
➡️ " አቴንዳሳቸው በአግባቡ ሪፖርት ሳይሆን ተፈትነናል ያሉ ወደ 9 ሺሕ 561 ተማሪዎች አሉ። የእነርሱም ለጊዜው ያዝ ተደርጓል። ህጋዊ ምክንያት ሲያቀርቡ ውጤታቸው ይለቀቃል! "
የ2018 ዓ/ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል፣ ከ11 ሺሕ 700 በላይ የሚሆኑት የዲሲፕሊን ችግር እንደተገኘባቸው የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
በርካታ ተፈታኝ ተማሪዎች ደግሞ፣ ውጤት ለማየት ሲሞክሩ "Disqualified" የሚል ምላሽ እያገኙ በመሆኑ የሚመለከተው ተቋም መፍትሄ እንዲሰጣቸው በቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሰሞኑ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታ አቅርበዋል።
ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በኦንላይን እና በአካል ቅሬታ ቢያቀርቡም መፍትሄ እንዳላገኙም የገለጹ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያም የተማሪዎቹን ቅሬታ ይዞ፣ ይህ የሆነው ሲስተሙ ምን ሆኖባችሁ ነው ? ሲል ተቋሙን ምላሽ ጠይቋል።
የትምህርት ምዘና እና የፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር)፣ " ምንም የሆነብን ነገር የለም። ' Disqualified ' የሆኑ ተፈታኞች ' Disqualified ' ናቸው። ቅሬታ ካላቸው ደግሞ በኦንላይን፣ በቅርብ ያሉ በአካልም ማቅረብ ይችላሉ። ባቀረቡት መሰረት ምላሽ እየሰጠን ነው" ብለዋል።
ታዲያ ተፈታኞቹ ውጤት ለማየት በሚሞክሩበት ጊዜ፣ "Disqulified" የሚላቸው ምን ስለሆነ ነው ? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ ደግሞ፣ በአጠቃላይ የ11 ሺሕ 785 ተማሪዎች የዲሲፕሊን ችግር ማጋጠሙን በመጥቀስ፣ ተከታዩን ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
" አንደኛ፥ በአጠቃላይ የዲሲፕሊን ኬዝ ያጋጠመን የ11 ሺሕ 785 ተማሪዎች ናቸው። ከእነዚህ ውስጥ በተለያዩ ጊዜ ሁለት ጊዜ ለመፈተን የሞከሩ 632 ተማሪዎች አሉ።
ሁለተኛ፥ 817 ተማሪዎች በፈተና ወቅት ያልተፈቀዱ እንደ ስልክ፣ ስማርት ሰዓት እና አጠሬራ በፈተና ወቅት ይዞ መግባት፣ ክፍል ውስጥ መረበሽ፣ ኮምፒዩተሮች ላይ ጉዳት ማድረስ፣ ሌላ ሰው እንዲፈተንላቸው ወይም ለሌላ ሰው ለመፈተን ሞክረው ፈተና ሲሰጡ የነበሩ ሰዎች ሪፖርት አቅርበዋል።
የእነዚህ (የ817 ተማሪዎች) ሙሉ በሙሉ Disqulified ነው። ልጆቹም ራሳቸውን ያውቃሉ።
ሦስተኛ፥ አንድን ፈተና የመጀመሪያ እና መጨረሻ ጊዜ አለ። ማንም ተማሪ የፈተናውን 25% Allowed time ተጠቅሞ ክፍል ውስጥ መገኘት አለበት። አለበለዚያ ውጭ ላይ ሌላ ኮሚዩኒኬሽን ይፈጠራል ተብሎ ኦረንቴሽን ተሰጥቷዋል።
ያንን (የፈተና ሰዓት) ያልተገበሩ 2 ሺሕ 76 ልጆች አሉ። የእነዚህም Disqalified ነው።
አራተኛው፥ የተፈታኞች በተመደቡበት የፈተና ክፍል አለመገኘት ነው። ክፍል ያለመገኘት፣ አቴንዳንስ በአግባቡ ያለመፈረም አለ። አቴንዳሳቸው በአግባቡ ሪፖርት ሳይሆን ተፈትነናል ያሉ ወደ 9 ሺሕ 561 አሉ። የእነርሱም ለጊዜው ያዝ (Hold) ተደርጓል።
ይህ ማለት አንዳንድ ተፈታኞች በጤና እክል ምክንያት ከተመደቡበት ቦታ ውጭ ሌላ ጋር ተፈትነው ይሆናል በልዩ ሁኔታ ተፈቅዶላቸው። የተዛወሩበትን ህጋዊ ምክንያት እና ያዛወራቸውን ሰው የፈቀደበትን ሲያቀርቡ ውጤታቸው ይለቀቃል።
ነገር ግን ክፍሉ ውስጥ ገብቶ አቴንዳንስ ሳይፈርም ' ተፈትኛለሁ ' ቢል ተቀባይነት ስለሌለው አቴንዳንስ ላይ የሌሉበትን ምክንያት እስካላቀረቡ እና እስካልተጠራ ድረስ ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ ይሰረዛል።
ይሄ ዘንድሮ የተደረገ አይደለም፤ አዲስ የወጣ ህግ አይደለም።
ነገር ግን ቅሬታ አለኝ የሚል አካል ቅሬታውን ማቅረብ ይችላል። " ብለዋክ።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለመፈተን ቢሞሉም " የመፈተኛ ቦታ እጥረት አለብን " ተብለው ከ5 ኪሎ ካምፓስ ወደ 6 ኪሎ፣ ከ6ኪሎ ደግሞ ወደ 5 ኪሎ መዘዋወረቻውን የጠቀሱ ተማሪዎች ደግሞ፣ ለገጠማቸው ችግር ምክንያቱ የመፈተኛ ቦታ መቀያየር መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወቃል።
ለዚሁ ቅሬታ ምላሽ የጠቅናቸው ዋና ዳይሬክተሩ፣ ተዘዋውረው ከሆነ ያዘዋወራቸው ሰው ስለሚኖር እና በተዘዋወሩበት የፈተና ቦታም አቴንዳንስ ሞልተው ከሆነ፣ ፊርማው ተጣርቶ ትክክል መሆኑ ሲረጋገጥ ውጤት እንደሚለቀቅላቸው ገልጸዋል።
5 ኪሎ እየተጠበቀ 6 ኪሎ ለፈተና የሄደ ተማሪ ካለ 5 ኪሎ ላይ ኃላፊነት የተሰጠው አካል ተፈታኙን ሲያጣ ቀሪ ብሎ ሪፖርት እንደሚያደርግ፣ " 6 ኪሎ ላይ ኃላፊነት የተሰጠው አካል ተፈታኙን ተቀብሎ ስለሚያስፈርም፣ የፈረሙበት ስላለን እናረጋግጣለን " ነው ያሉት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
መጋቢት 10 ቀን 2018 ዓ/ም
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
