cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Eyoha Tv

✨ለታማኝ፣ የተረጋገጡ እና ፈጣን መረጃዎች t.me/eyohatv - Facebook.com/eyohatv - youtube.com/@eyoha24

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
1 920
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+77 روز
+2230 روز
توزیع زمان ارسال

در حال بارگیری داده...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
تجزیه و تحلیل انتشار
پست هابازدید ها
به اشتراک گذاشته شده
ديناميک بازديد ها
01
በ4 ፖትሮሎች ከጣርማበር ወደ መዘዞ ያቀናው ሀይል የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ በወሰደው እርምጃ ከ17 በላይ የሚሆኑት ሰራዊቶች ሲማረኩ ሁሉም ፖትሮሎች ተማርከዋል፤ ቀሪዎቹ እጃቸውን ለመስጠት ፋቃደኛ ስላልሆኑ እርምጃ ተወስዶባቸዋል።
3450Loading...
02
ጃዋር ለአሜሪካ አምባሳደር የሰላም ጥሪ መንግስት የሰጠው ምላሽ እንዳስገረመው፣ መንግስት ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ ግጭቶችን በመነጋጋር እፈታለሁ ያለውን ቃል መቀልበሱ ልክ እንዳይደለ አምርሮ ወቀሰ። በማህበራዊ ሚዲያ ገፁ ለአሜሪካ አምባሳደር የሰላም ጥሪ አድናቆትን በመቸር፣ መንግሰት ጥሪውን ያልተቀበለበት ሁኔታ ኮንኗል። የፖለቲካ ምህዳሩ መጥበቡን፣ ብሄራዊ ምክክር በአሁኑ ወቅት ወደማይቻል ደረጃ መውረዱን፣ መንግስት የህዝብ ዝምታን እንደ ድጋፍ መመልከቱ ስህተት መሆኑ፣ ህዝብ ለፖለቲከኞች እድል በመስጠት ዝም ማለቱን በማስታወስ፣ እድሎች ከማምለጣቸው በፊት ወደ ንግግር መመለስ የሚሻል መሆኑን መክሯል።
3670Loading...
03
ይሄን ቪዲዮ ብዙ ነገር ይነግረናል‼️ አማራ ስለሆነች ፓስፓርቷን ወረወሩባት ይሄ አዲስ አበባ ላይ የሆነ እና አሁንም የቀጠለ ነወ። በሁሉም የመንግስት መዋቅር ውስጥ አማራ ላይ በስውር ይደረጉ የነበሩ መድሎዎች አሁን አይን አውጥተው በግልጽ ብሄር እየጠየቁ መሳደብ እና መሰል ነገር በcustomer service በሚሰጡ አካላት ጭምር እየተደረገ ነው።
3230Loading...
04
በሚሊዮን የሚቆጠር የራያና የወልቃይት መታወቂያ እየተሰራጨ ነው! ብልፅግና በአማራ ግዛቶች አስተዳደሮችን አፍርሶ "በፌደራል ስር ሆነው ሕዝበ ውሳኔ ይሰጥባቸዋል" ብሎ ነበር። እውነታው ግን ለትህነግ አሳልፎ ሰጥቶ  የትግራይ ወጣት ህገወጥ  የራያና ወልቃይት መታወቂያ በገፍ እየታተመ እየታደለው እንዲሰፍር እየተደረገ ነው። የፈለገ የትግራይ ስራ አጥ ወጣት የራያ ይሁን የወልቃይት መታወቂያ ይታደለዋል። ትህነግ በሀሰት በሚሊዮን የሚቆጠር ተፈናቃይ አለኝ ባለው መሰረት በአማራ ግዛቶች ህዝብ ለማስፈር በሚሊዮን የሚቆጠር መታወቂያ ተዘጋጅቶ እየተሰራጨ ነው። ብልፅግና በመከላከያ ስር ሆኖ ህዝበ ውሳኔ ይደረግበታል ቢልም አሳልፎ ሰጥቶ መታወቂያ እየታተመ የህዝብን አሰፋፈር ለመቀየር እየተሰራ ነው።  በግልፅ "መታወቂያ ውሰዱ" እየተባለ እየተሰጠ ነው። የፕሪቶሪያ ስምምነት ሆነ ብልፅግና በየዕለቱ መከርኩበት የሚለው ይህን አይልም። ይህ የጓዳ ውሉ ውጤት ነው! እርባና ቢሱ ብአዴን ደግሞ ዝምታን መርጧል። ©Getachew Shiferaw
3390Loading...
05
"መምራት አልቻልክም" አሜሪካ የአብይ መንግስት የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ "ውንጀላ አቅርበዋል"፤ "መንግሥት አገሪቱን እንዴት መምራት እንዳለበትም ያልተጠየቁትን ምክር ለግሰዋል" በማለት ወቅሷል። የአምባሳደሩ ንግግር "ትርጉም የማይሰጡ" እና "በበቂ ኹኔታ ያልተጤኑ" ሃሳቦችን ያካተተ ነው ያለው ሚንስቴሩ፣ አምባሳደሩ "በምርጫ የተመረጠውን መንግሥት በኃይል ለመጣል የሚሠሩ ቡድኖችንም በስም ጠቅሰዋል" በማለት ተችቷል። አምባሳደር ማሲንጋ ትናንት የመን የማኅበረሰብ ትምህርት ቤት ውስጥ ባደረጉት ንግግር፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄደው ጦርነት በሲቪሎች ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳይ በመጥቀስ "አገር ዓቀፍ የተኩስ አቁም" እንዲደረግ ጠይቀው ነበር።
3680Loading...
06
ሚሊሻው በገፍ ፋኖን ተቀላቅሏል! ዘር አጥፊው የብልፅግና ቡድን አሰልጥኖና አስታጥቆ ወገናቸውን እንዲወጉ አሠማርቷቸው የነበሩ ሚሊሻዎች ወደ ሕዝባዊ ሠራዊቱ እየተቀላቀሉ ነው። ጎንደር ላይ በቀረበው ጥሪ መሠረት እንደዚህ ወደ ሕዝባዊ ታጋዩ ተቀላቅለው ይመካከራሉ። ወደፋኖ ገብቶ መሰልጠን ተመራጭ ነው።
3770Loading...
07
ሚሊሻና ፖሊሶች የጉልበት ሰራተኛ በመቅጠርም ሆነ ለሌላ አርሶ አደር በማከራየት መሬታቸውን እያሳረሱ እነሱ የአማራ ህዝብ ጠላት የሆነ ስርዓት ጋር አብረው የሚንቀሳቀሱበትን እድል አንፈጥርም ያለው አርበኛው፡ ከዚህ በኋላ እጃቸውን ለፋኖ በመስጠት ወደ ሰላማዊ ህይወታቸው የማይመለሱ ከሆነ በመሬታቸውና በሌሎች ንብረቶቻቸው ላይ የማዘዝ መብት አይኖራቸውም ሲል ገልጿል። ስለሆነም ግፍን በመቃወም የቀረበውን ጥሪ ተቀብለው እጃቸውን ለፋኖ የሚሰጡ የሚልሻና ፖሊስ አባላት በሰላም ወደ ቤታቸው ገብተው መሬታቸውን ማረስ የሚችሉ ሲሆን ከፋኖ ጋር ተቀላቅለን እንታገላለን ካሉም በየሙያ ዘርፋቸው እድሉ ይመቻችላቸዋል ተብሏል። ነገር ግን ይሄን ፋኖ ያቀረበውን ጥሪ የማይቀበሉ የፖሊስና ሚሊሻ አባላት መሬታቸውን ማሳረስም ሆነ ለሌላ አርሶ አደር ማከራየት እንደማይችሉ የተገለፀ ሲሆን ለስራ አጥ ወጣቶች እንዲከፋፈልም ተወስኗል። ይህ መመሪያ ከዕዝና ከክፍለ ጦሮች የመጣ ነው ሲሉ ከአማራ ድምፅ ሚድያ ጋር ባደረጉት ቆይታ የተናገሩት የመካነሰላም አባይ ሸለቆ ብርጌድ አዛዡ አርበኛ አብነው ታደሰ፡ ዕዙ በሚንቀሳቀስባቸው በሁሉም ቀጠናዎች የሚተገበር መሆኑንም ጠቁመዋል። ይሄንን መመሪያ ተከትሎ የፖሊስና የሚልሻ ማሳዎችን ለማረስ ተከራይተው የነበሩ ሰዎች የኪራይ ውላቸውን እያቋረጡ መሆኑም ተሰምቷል። #የአማራ ድምፅ
4100Loading...
08
"በምሬና በዘመነ መካከል፣ #በመሳፍንትና በአሰግደው መካከል ያለው የስምና የአካል ልዩነት ብቻ ነው። የሀሳብና የአላማ ልዩነት የለም። አራቱም መሪወች ተነጋግረው በ30 ደቂቃ ውስጥ ባሕርዳር ላይ መገናኘትና መወሰን ይችላሉ። ክልላችንን ወራሪው ሀይል ይልቀቅ።" = ማርሸት ከተናገረው የተወሰደ =
4010Loading...
09
"ሰቅጣጭ" በሆነው አዋሽ አርባ የሚገኙ "የኅሊና" እስረኞች እንዲለቀቁ ሲል ኢሕአፓ ጠየቀ ሐሙስ ግንቦት 08 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሊቀ መንበሩን ጨምሮ ሌሎች በአዋሽ አርባ የሚገኙ "የግፍ" እስረኞች እንዲለቀቁ ጠየቀ። ፓርቲው ዛሬ ለአዲስ ማለዳ በላከው መግለጫ "ኢትዮጵያ እንደ አገር እንድትቀጥል የሕግ የበላይነት ሊኖር ይገባል" ሲል የገለጸ ሲሆን የፓርቲው ሊቀ መንበር ዝናቡ አበራ ሌሎችም "የህሊና" እስረኞች እንዲለቀቁ ተማጽኗል። የብልጽግና መንግስት በሕዝብ ላይ ጦር መስበቅ፣ ሰራዊት ማዝመት፣ በድሮንና በአየር ኃይል ሕዝብ መፍጀቱን በአስቸኳይ እንዲያቆም ሲል ኢሕአፓ አሳስቧል። ፓርቲው አክሎም "ብልጽግና ፖለቲከኞችን፣ ጋዜጠኞችን፣ ማህበራዊ አንቂዎችን፣ ሌሎችንም ዜጎች እያፈሰ በማሰር፣ በማሰቃየት የፖለቲካ ስልጣኑን የሚያቆይ ከመሰለው እጅጉን ተሳስቷል" ብሏል። ፓርቲው በህዳር 30 የጦርነት ይቁም ሰላማዊ ሰልፍ አዘጋጆች ሰላማዊ ታጋይ በመሆናቸው እንዲፈቱ እንዲሁም በዘርና በሌሎች ፍረጃዎች የታሰሩ የህሊና እስረኞች በሙሉ ይፈቱ ሲል አሳስቧል።
5000Loading...
10
"ውስጣዊ ችግሮቻችን ግዙፍ አላማዎቻችን በማስቀደም እየፈታን ወደፊት በድል እንገሰግሳለን" - አርበኛ ዘመነ ካሴ የአማራ ፋኖ በጎጃም ካሉት 9 ክፍለ ጦሮች ውስጥ አንዱ የሆነው የጃዊ ክፍለ ጦር ከሚያዚያ 8-12 ባደረገው ፍልሚያ እና በተገኘው አስደናቂ ድል፣ ቀጣይ መታረም ባለባቸው እንከኖች ዙሪያ በአማራ ፋኖ በጎጃም የአደረጃጀት መምሪያ ሀላፊ ፋኖ እሸቱ ጌትነት አወያይነት ለ2ቀን ከመከሩ በኋላ አሉ የሚሏቸው ውስጣዊና ውጫዊ፣ ግላዊና ተቋማዊ ችግሮችን አንስተው በመምሪያ ሀላፊው በኩል በቂ ማብራሪያ ተሰጥቶ ላስገኙት አስደናቂ ድልና ቀጣይ ለሚያደርጉት የተሻለ የግዳጅ አፈጻጸም የአማራ ፋኖ በጎጃም ሰብሳቢ አርበኛ ዘመነ ካሴ ባካል ተገኝቶ ምስጋና ተችሯቸው ቀጣዩን ድርጅታዊ የስራ መመሪያም በመሪው በኩል በመቀበል አጠናቀዋል።
4640Loading...
11
ኢሳያስ በላይ የአማራ ባንክ የማኔጅመንት ሰራተኛ ነበር ። ብልፅግና ሰሞኑን አፍሶ ካሰራቸው የአማራ ባንክ ሰራተኞች አንዱ ነው ። ዛሬ ፓሊስ ደውሎ ሬሳውን ለቤተሰብ እና ለስራ ባልደረቦቹ አስረክቧል ። © ኤልሻዳይ የግዮን ልጅ
4550Loading...
12
የጉራጌ ህዝባዊ ሰራዊት! ጉራጌ በልጆቹ አንገቱን ቀና ለማድረግ የድም ስርዔት ለመክፈል የመጀመሪያውን ምዕራፍ ከፍቷል። 🟢🟡🔴◈◈◈◈◈🟢🟡🔴
4362Loading...
13
በአምሐራ ህዝብ ላይ የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የጊዜ ገደብ ሊጠናቀቅ መቃረቡን ተከትሎ ከዚህ በኋላ ለሚመጣው ጊዜ ምን ብናደርግ ይሻለናል በሚል የብአዴን ካድሬዎች በሁለት ጎራ ተከፍለው እየተነታረኩ ነው ተብሏል። ፨ አንደኛው ጎራ የብርሃኑ ጁላ ጦር ክልሉን ለቆ እንዲወጣ ምክረ ሀሳብ አቅርቦ ተከራክሯል ተብሏል። ፨ ሁለተኛ ጎራ አረጋ እና ግብረ አበሮቹ ያሉበት) ሠራዊቱ በፍጹም ክልሉን ለቆ መውጣት የለበትም። እንዲያውም የድሮን እና ጄት ጥቃት እስካሁን ከተፈጸመው ጥቃት ሁሉ ከፍ ባለ ደረጃ ሊፈጸም ይገባል የሚል አቋም መያዛቸው ተሰምቷል።
4390Loading...
14
መረጃ..‼️ በጎንደር በለሳ ማክሰኝትና አይምባ አካባቢ እጅግ ብዙ የሚኒሻና የአድማ ብተና አባላት ፋኖን ተቀላቅለዋል።
4250Loading...
15
ሶሮቃ!! አዲስ የተመሰረተው የተከዜ ክፍለ*ጦር አንፀባራቂ ድ*ል አስመዝግቧል። በትናንትናው እለት ሶሮቃ ከተማን ተቆ*ጣጥሮ ድ*ል ያስመዘገበው የአ*ማራ ፋ*ኖ በጎንደር አዲስ የተቋቋመው ተከዜ ክፍለ*ጦር ነው። ሶሮቃ ከተማ ላይ ቀድሞ በተጠኑ እና በተለዩ ወታ*ደራዊ ጠቀሜታ ባላቸው ይዞታዎች ላይ ነው እር*ምጃ የተወሰደው። አንዱ እና ዋናው ስኬት እስር*ቤት ሰብ*ሮ ብዛት ያላቸውን የፖ*ለቲካ እስ*ረኞች ነፃ እውጥቷል። በዚሁ ሂደት ስምንት መሳ*ሪያ በወገን ኃ*ይል ተማ*ርኳል። የተከዜ ክፍለ*ጦር ምክትል አዛዥ እና የክፍለ*ጦሩ አካል የሆነችው "የብሶተኛው ብር*ጌድ" ዋና አዛ*ዥ የሆነችው ጀግኒት ሴት ፋ*ኒት መሆኗ ታውቋል። የሶሮቃው ኦፕ*ሬሽን ላይ አመራር የሰጠችው ይህች ጀ*ግና ስሟ ከፍ ብሎ እየተጠራ ነው! የመዳኛችን ብቸኛው መንገድ ማሸ*ነፍ ብቻ ነው!
4450Loading...
16
"ለጆሮ ትልቅ፤ ለዓይን ደግሞ ትንሽ አትሁኑ" ዋርካው ምሬ ወዳጆ የአማራ ፋኖ በወሎ ዋና አዛዥ
4330Loading...
17
አገዛዙ የአማራን ቀጣይ ትውልድ እያጠፋ ነው ስንል በምክንያት ነው!! አሁን ከሂሳብ ትምህርት ይልቅ ስለ ዲሽቃ(መገዳደያ ጦር መሳሪያ) በቂ እውቀት አለኝ!!
4420Loading...
18
#መራዊ ! የመራዊ ሚሊሻ ትናንት ድንገት መብርቅ ጥሎበት ጭዳ ሁኗል! ከየት መጡ ሳይባል ፋኖወቹ ገብተው አጭደውት ሂደዋል በዚህ ጥቃት 17 የመከለካያ እባል እና አንድ የደህንነት ሃአልፊ ሲገደሉ፣ 13 ክላሽንኮቭ መሳሪያም ገቢ ተደርጓል።
4430Loading...
19
የዋና ዋና ፋኖ መሪዎች የቅርብ ቤተሰቦች ስልክና የግንኙነት መስመሮች ተጠልፈዋል። ይህም የሆነው ፋኖዎች በተለዋጭ ቁጥሮችም ቢሆን ለቤተሰቦቻቸው መደወላቸው አይቀርም በሚል ነው። ባለፈው ለትንሳኤ በዓል በርካታ ፋኖዎች ለቤተሰቦቻቸው እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት የተወሰዱ ቁጥሮች አሁን GPS ንባብ ውስጥ ገብተው ለድሮን ጥቃት እየተጠኑ ነው። ስለሆነም የፋኖ መሪዎች ጥንቃቄ እንዲወስዱ በቶሎ መረጃው ይድረሳቸው! (ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት በውስጥ የመጣ)
4470Loading...
20
ሰበር ዜና‼️ የአማራ ፋኖ በጎጃም ደምበጫ ኢንጅነር ክበር ተመሰገን ብርጌድ ታሪክ ሰሩ። ሻለቃ 1 እና ሻለቃ 2 በጥምር ከአንጀኔ እሰከ ደምበጫ የጠላትን አሰከሬን ተከመረ። በዛሬው እለት ከ 80 በላይ የሚሆን የጠላት ሀይል ሙትና ቁሰለኛ አድርገናቸዋል።ጠላት በጣም ተማሯል መሄጃው ጠፋቶታል ጨልሞበታል። በከተማዋ 02 ቀበሌ ከ8 ሰዓት እሰከ 12 ሰዓት ተቆጣጥረን ኦፕሬሺን ሰርተን ጨርሰን ወጠናል። ያሰቆመንም ሆነ የታገለን የለም የሚጠብቁንም ከገደል አውጠን እሰከምንጨርሳቸው ነው። የሀይለ እየሱሰ ፋላቴ ልጆች የጥቁሩን ፋሺሰት ናዚወችን ከምድረገጥ እያጠፋቸው ይገኛል።
4860Loading...
21
"በተፈናቃዮች ብር የተሰራው ሆቴል" የዛሬ 7አመት አካባቢ ከሱማሌ ክልል የሃረርጌ ኦሮሞዎች ይፈናቀላሉ። በዚህ ምክንያትም ለወገን ደራሽ ወገን ነው በማለት የቶምቦላ ሎተሪ ተዘጋጅቶ በኦሮሚያ ከክልል እስከ ቀበሌ ተሸጠ። የዚህ ሎተሪ ኮሚቴዎች መሀከል ደሞ በምስሉ ላይ የሚታየው ሞቲ ሞረዳ ነው (ቀሲስ በላይም እንዳሉበት ተነግሯል)። ለማንኛውም ይሄ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ የተሸጠ ሎተሪ እጣው ሳይወጣ ደብዘው ከጠፋ 7አመት ሆነው። ቄሱም ዝም መፅሀፉም ዝም ሆኖ ሰንብቷል።ገንዘቡ የተሰበሰበው በክልሉ መንግስት መዋቅር እና አስተባባሪነት እንደሆነ ልብ ይሏል።ለማንኛውም ከኮሚቴዎቹ አንዱ የሆነው ጀለስ የግዜው ሰው ሞቲ በተፈናቃዮቹን ስም የተሰበሰበውንገንዘቡን አምስት ሳንቲም ሳያጠፋ ቦሌ ላይ ባለግዜነቱን ተጠቅሞ ባገኘው ቦታ ላይ ይሄን መሰል ቅንጡ ሆቴል ከፍቷል። እልልልልልልልልላልልልል በል የኦሮሞ ህዝብ ልጅህ ገንዘቡን አላጠፋም።
4630Loading...
22
እነሱም መማረካቸውን፣ አማራውም መማረኩን ቀጥሎበታል! የመቶ ሁለተኛ ኮር የ66ኛ ክፍለ ጦር አመራር ምርኮኛው ሻምበል ኤርሚያስ ኤራሞ ባቡሬና የአማራ ፋኖ በጎጃም በበላይ ብርጌድ የሳተናው ሻለቃ አዋጊውና ማራኪው ፋኖ ቃልኪዳን ሊቁ በቢቸና ሰማይ ስር ። ሰብሳቢ ለሌለው ሠራዊት ለማረክ ትልቅ ዕድል የሆነበት ሁኔታ ነው ያለው!
4440Loading...
23
አይ ብልጽግና¡ ይህ የምትመለከቱት ፎቶ ከምስራቅ ሀረርጌ የተገኘ ነው። ብልጽግና ለወታደራዊ ስልጠና ብሎ ወጣቶችን ያፍሳል። በኋላ ቤተሰብ መጥቶ ልጆቻችንን ልቀቁልን ይላል። የወረዳው አስተዳዳሪም ገንዘብ ክፈሉንና እንለቃለን ይላል። ይኼው officially በእያንዳንዱ ወጣት ከ7-10 ሺ ብር ገንዘብ እየተቀበለ እየለቀቀ ይገኛል። አንድ የአከባቢው ሽማግሌ ይህን ተመልክተው ስርዐቱን "ቶርቶሬራ " በማለት መግለጻቸውን ሰምተናል። በስብሷል እንደማለት ነው።
4670Loading...
24
ህርዳር!! === ባህርዳር ትናንት ከመሼ ከመኮድ ወደ ኤርፖርት ሲሄድ በነበረ አንድ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ በጫነ ፓትሮል ላይ በተወሰደ ደፈጣ ጥቃት ከእነ አጃቢዎቹ መደም'ሰሱ ተረጋግጧል።
4670Loading...
25
የስሎቫኪያው ጠቅላይ ሚኒስትር በጥይት ተመተው ሆስፒታል መግባታቸው ተሰማ የስሎቫኪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሮበርት ፊኮ በጥይት ተመተው ሆስፒታል መግባታቸው ተሰማ። የሃገሪቱን መገናኛ ብዙሃን ዋቢ ያደረገው የሬውተርስና ቢቢሲ ዘገባ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ሃንድሎቫ በተሰኘች አነስተኛ ከተማ ከከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ስብሰባ በኋላ በተተኮሰ ጥይት መመታታቸውን ያመላክታል። የመንግስት ባለስልጣናትም በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ የግድያ ሙከራ ተደርጓል ብለዋል። ፖሊስም ተጠርጣሪ ግለሰብን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህይወታቸው አስጊ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ነው የተባለው። ሮበርት ፊኮ በፈረንጆቹ 2018 ከጋዜጠኛ ግድያ ጋር በተያያዘ ከስልጣን ከለቀቁ በኋላ ባለፈው መስከረም ወር በተደረገ ምርጫ ወደ ስልጣን መምጣታቸውን ዘገባው አስታውሷል።
5370Loading...
26
የቦረናዉ ጉብል- ዝምተኛዉ ገዳይ፣ እፍን አርጎ ቃመዉ--አደሬ ቆቦ ላይ። ቦረኔዉ ቆርጦ በመነሳት የጠላትን የሴራ ገመድ እየቆራረጠ ተግባሩን ማጉላት ጀምሯል ! ዛሬ ማለትም በቀን 07/09/2016 ዓ. ም ወደ ቢሊ ሲገሰግስ የነበርን የአገዛዙ ሚኒሻና ፓሊስ መኪና ላይ እንዳለ  ዶግ አመድ አድርጎታል። ምንጭ ፦ ድምፃዊ ፋኖ ተመስገን በቀለ
5200Loading...
27
ባህር ዳር ባለፀጋ፣ ደፋር፣ በክብሩ የማይደራደር ሰው አጣች። ተፈሪ መኮንን ይባላል። የአሚኮ ፕሮሞሽን ሀላፊ ነበር። አንድ ለአምስት አልሰበሰብም በማለቱ ከደረጃ ዝቅ ሲል  በክብሬ እና በነፃነቴ ብሎ በ2008 ስራ ለቀቀ።  ከዚያም በባህርዳር ወጣቱን ማንቃት፣ ማደራጀት ጀመረ። የአብን ዋና አንቀሳቃሽ ሞተር፣ የንስር ሚዲያም መስራች፣ የህዝባዊ ግንባር መስራች፣ በሗላም ሁሉም የአማራ  ፋኖዎችን ወደ አንድ ሊያመጣ ወሎ በሄደበት  መስዋዕት ሆኗል። ትግሉ በእንቁ ወንድሞቻችን መስዋዕትነት ይቀጥላል።
5140Loading...
28
የአማራ ፋኖ በወሎ ! የአማራ ፋኖ በወሎ የስራ አስፈፃሚ አባላቱን ማደራጀቱን አዛዡ ዋርካው ምሬ ወዳጆ ገለፀ ከሳምንታት በፊት የምስራቅ አማራ ፋኖና የወሎ ዕዝን በማዋሀድ የአማራ ፋኖ በወሎ በሚል የተደራጀው ግዙፉ የፋኖ ኃይል ከጦር ሜዳ ታጋድሎው ጎን ለጎን የአደረጃጀት ስራውን ቀጥሏል። በውህደት ምስረታው ዋርካው ምሬ ወዳጆን ዋና አዛዥ፣ ኮረኔል ፋንታሁን ሙሀባን ደግሞ ምክትል አድርጎ መርጦ የነበረው የአማራ ፋኖ በወሎ ትናንት ደግሞ የስራ አስፈፃሚ አባላቱን አደራጅቶ መጨረሱን ሮሃ ሰምታለች። ዋና አዛዡ ምሬ ወዳጆ ለሮሃ በስልክ በሰጠው ቃል ላለፉት ጊዜያት ብዙ ሲለፋበት የነበረው የስራ አስፈፃሚ አደረጃጀት ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን አስረድቷል። ምሬ ወዳጆ "ብዙ ሲሰራበት የቆየውን የአደረጃጀት መዘርጋታና የአመራር መዋቅር ስብስብን የተመለከተው ስራችን መጠናቀቁን ለመላው የአማራ ህዝብ አበስራለሁ" ብሏል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በወሎ ግዛት የተለያዩ አካባቢዎች የፋኖ ወታደራዊ ተጋድሎ ቀጥሏል። ከውጊያው ጎን ለጎን አደረጃጀትና ተቋም እያሰለጠ ያለው ፋኖን ተግባር በተመለከተም ምሬ ወዳጆ ተከታዩን ብሏል።
4870Loading...
29
#ወረኢሉ..‼️ የወረኢሉ ወረዳ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅን ካምፕ አድርጎ ለወራት መሽጎ የነበረው የብልጽግና ሰራዊት ጀግናው የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ይኩኑከምላክ ክፍለጦር የፕሮፌሰር አስራት እና ራስ አባተ ቧያው ብርጌድ በከፈተው መብረቃዊ ጥቃት ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሶበት ተበትኗል፡፡ ትላንት ሌሊት ከምሽቱ 5 ሰዓት በካምፑ ላይ በደረሰ የደፈጣ ጥቃት 40 የሚሆኑት እጃቸውን ለፋኖ የሰጡ ሲሆን በካምፑ የነበሩ ሙሉ በሙሉ መደምሰሳቸውን ከአካባቢው ምንጮች ለጃንጥራር አምባሰል ተናግረዋል፡፡ ከጥቃቱ በኋላ ጫካ ለጫካ ህዝቡ አስክሬን እየፈለገ እየቀበረ ነው፤ የሚሉት እኝህ የአይን እማኝ የፋኖ ጦር ሰራዊቱ የምጠቀምባቸውን እጅግ ዘመናዊ የግል እና የቡድን መሳሪያዎችን ማርኳል በማለት ተናግረዋል፡፡
4390Loading...
30
ሰበር..‼️ የአማራ ፋኖ በጎጃም ጠቅላይ አዛዥ ጓድ አርበኛ ዘመነ ካሴ ከግዙፉ የጃዊ ክፍለጦር አመራሮች ጋር ውይይት አድርጓል። ውይይቱ ጠንካራ ጎንን ለማስቀጠል ድክመቶችን ነቅሶ ለማውጣት ያለመ ነው።
4770Loading...
31
ዳግማዊት ጣይቱ!! የአማራ ፋኖ በጎጃም የዮፍታሔ ንጉሴ ክ/ጦር ምክትል አዛዥ ምንትዋብ አስረስ!!
4600Loading...
32
የአማራ ፋኖ ጎንደር እዝም በደቡብ ጎንደርና አርማጭሆ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል። አርማጭሆና ቀራቀርን ጨምሮ በአካባቢው ያሉ ከተሞችን ተቆጣጥሮ የሚገኘው የአማራ ፋኖ ጎንደር እዝ በሚካኤል ደብር የመሸገውን 51ኛ ክፍለ ጦርን ሲመራ የነበረ አዋጊ ኮለኔል እስከወዲያኛው አሰናብቶ የክፍለ ጦሩን 3ኛና 4ኛው ሬጅመንት ሙሉ በሙሉ በሙሉ በማውደም ንብረቶቹም በእጁ አስገብቷል።
4770Loading...
33
ዜናቸው የቀደመ ጀልባዎች !! ጣና ነሽ ፪ የተሰኘችው ዘመናዊ የህዝብ ትራንስፖርት ጀልባና ሌላኛዋ መለስተኛ ፈጣን ቃኝ ጀልባ በአሶሳ መርከብ ላይ ተጭነው ይደርሳሉ ተብሎ ከተያዘላቸው አንድ ቀን ቀድመው መጋቢት ጅቡቲ ወደብ ደርሰዋል የተባሉት ጅቡቲ የወደብ ክራይ እየቆጠረባቸው ነው ተባለ። በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ Via Zehabesha
4960Loading...
34
የአማራ ፋኖ በጎጃም የዮፍታሔ ንጉሴ ክ/ጦር ምክትል አዛዥ  ምንትዋብ አስረስ ያስተላለፈችዉን መልዕክት በዩቱብ ቻናላችን ከቆይታ በኋላ የምናጋራ ይሆናል  subscribe በማድረግ ያግዙ። https://www.youtube.com/@eyoha24
4710Loading...
35
"ጎጃም ውስጥ 10 ክፍለጦሮች ካለው የአማራ ፋኖ በጎጃም ውጭ ሌላ ወታደራዊ አደረጃጀት አላውቅም" ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው
4770Loading...
36
ለአድማ ብተና፣ ሚሊሻ፣ ህዝባዊ ፖሊስ (አማራ ፖሊስ)፣ መከላከያ ሰራዊት፣ ፌዴራል ፖሊስ፣ መረጃና ደህንነት አባላት እንዲሁም የታችኛው መዋቅር የአገዛዙ አካላት ከግንቦት 6 ቀን እስከ ግንቦት 21 ቀን ለሁለት ሳምንታት ወይም ለ15 ቀናት የሚቆይ የምህረት አዋጅ አጽድቋል፡፡ የምህረት አዋጁም ይሄ አዋጅ ከወጣበት እለት ማለትም ከቀን 6/9/2016 ዓ.ም. ጀምሮ በሁሉም ክፍለጦሮች እና ብርጌዶች ሙሉ በሙሉ እንዲፈጸም ጥብቅ ወታደራዊ ትእዛዝ ተላልፏል፡፡ የምህረት አዋጁም የሚከተሉትን ዋና ዋና ጉዳዮች ይዟል፦
5250Loading...
37
ዛሬ የአማራ ፋኖ በወሎ ዕዝ ሙሉ በሙሉ ስራ አስፈጻሚውን መርጦ ጨርሷል!!
5880Loading...
በ4 ፖትሮሎች ከጣርማበር ወደ መዘዞ ያቀናው ሀይል የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ በወሰደው እርምጃ ከ17 በላይ የሚሆኑት ሰራዊቶች ሲማረኩ ሁሉም ፖትሮሎች ተማርከዋል፤ ቀሪዎቹ እጃቸውን ለመስጠት ፋቃደኛ ስላልሆኑ እርምጃ ተወስዶባቸዋል።
نمایش همه...
6👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
ጃዋር ለአሜሪካ አምባሳደር የሰላም ጥሪ መንግስት የሰጠው ምላሽ እንዳስገረመው፣ መንግስት ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ ግጭቶችን በመነጋጋር እፈታለሁ ያለውን ቃል መቀልበሱ ልክ እንዳይደለ አምርሮ ወቀሰ። በማህበራዊ ሚዲያ ገፁ ለአሜሪካ አምባሳደር የሰላም ጥሪ አድናቆትን በመቸር፣ መንግሰት ጥሪውን ያልተቀበለበት ሁኔታ ኮንኗል። የፖለቲካ ምህዳሩ መጥበቡን፣ ብሄራዊ ምክክር በአሁኑ ወቅት ወደማይቻል ደረጃ መውረዱን፣ መንግስት የህዝብ ዝምታን እንደ ድጋፍ መመልከቱ ስህተት መሆኑ፣ ህዝብ ለፖለቲከኞች እድል በመስጠት ዝም ማለቱን በማስታወስ፣ እድሎች ከማምለጣቸው በፊት ወደ ንግግር መመለስ የሚሻል መሆኑን መክሯል።
نمایش همه...
👍 3 2
02:45
Video unavailableShow in Telegram
ይሄን ቪዲዮ ብዙ ነገር ይነግረናል‼️ አማራ ስለሆነች ፓስፓርቷን ወረወሩባት ይሄ አዲስ አበባ ላይ የሆነ እና አሁንም የቀጠለ ነወ። በሁሉም የመንግስት መዋቅር ውስጥ አማራ ላይ በስውር ይደረጉ የነበሩ መድሎዎች አሁን አይን አውጥተው በግልጽ ብሄር እየጠየቁ መሳደብ እና መሰል ነገር በcustomer service በሚሰጡ አካላት ጭምር እየተደረገ ነው።
نمایش همه...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
በሚሊዮን የሚቆጠር የራያና የወልቃይት መታወቂያ እየተሰራጨ ነው! ብልፅግና በአማራ ግዛቶች አስተዳደሮችን አፍርሶ "በፌደራል ስር ሆነው ሕዝበ ውሳኔ ይሰጥባቸዋል" ብሎ ነበር። እውነታው ግን ለትህነግ አሳልፎ ሰጥቶ  የትግራይ ወጣት ህገወጥ  የራያና ወልቃይት መታወቂያ በገፍ እየታተመ እየታደለው እንዲሰፍር እየተደረገ ነው። የፈለገ የትግራይ ስራ አጥ ወጣት የራያ ይሁን የወልቃይት መታወቂያ ይታደለዋል። ትህነግ በሀሰት በሚሊዮን የሚቆጠር ተፈናቃይ አለኝ ባለው መሰረት በአማራ ግዛቶች ህዝብ ለማስፈር በሚሊዮን የሚቆጠር መታወቂያ ተዘጋጅቶ እየተሰራጨ ነው። ብልፅግና በመከላከያ ስር ሆኖ ህዝበ ውሳኔ ይደረግበታል ቢልም አሳልፎ ሰጥቶ መታወቂያ እየታተመ የህዝብን አሰፋፈር ለመቀየር እየተሰራ ነው።  በግልፅ "መታወቂያ ውሰዱ" እየተባለ እየተሰጠ ነው። የፕሪቶሪያ ስምምነት ሆነ ብልፅግና በየዕለቱ መከርኩበት የሚለው ይህን አይልም። ይህ የጓዳ ውሉ ውጤት ነው! እርባና ቢሱ ብአዴን ደግሞ ዝምታን መርጧል። ©Getachew Shiferaw
نمایش همه...
"መምራት አልቻልክም" አሜሪካ የአብይ መንግስት የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ "ውንጀላ አቅርበዋል"፤ "መንግሥት አገሪቱን እንዴት መምራት እንዳለበትም ያልተጠየቁትን ምክር ለግሰዋል" በማለት ወቅሷል። የአምባሳደሩ ንግግር "ትርጉም የማይሰጡ" እና "በበቂ ኹኔታ ያልተጤኑ" ሃሳቦችን ያካተተ ነው ያለው ሚንስቴሩ፣ አምባሳደሩ "በምርጫ የተመረጠውን መንግሥት በኃይል ለመጣል የሚሠሩ ቡድኖችንም በስም ጠቅሰዋል" በማለት ተችቷል። አምባሳደር ማሲንጋ ትናንት የመን የማኅበረሰብ ትምህርት ቤት ውስጥ ባደረጉት ንግግር፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄደው ጦርነት በሲቪሎች ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳይ በመጥቀስ "አገር ዓቀፍ የተኩስ አቁም" እንዲደረግ ጠይቀው ነበር።
نمایش همه...
👍 5
04:43
Video unavailableShow in Telegram
ሚሊሻው በገፍ ፋኖን ተቀላቅሏል! ዘር አጥፊው የብልፅግና ቡድን አሰልጥኖና አስታጥቆ ወገናቸውን እንዲወጉ አሠማርቷቸው የነበሩ ሚሊሻዎች ወደ ሕዝባዊ ሠራዊቱ እየተቀላቀሉ ነው። ጎንደር ላይ በቀረበው ጥሪ መሠረት እንደዚህ ወደ ሕዝባዊ ታጋዩ ተቀላቅለው ይመካከራሉ። ወደፋኖ ገብቶ መሰልጠን ተመራጭ ነው።
نمایش همه...
3
ሚሊሻና ፖሊሶች የጉልበት ሰራተኛ በመቅጠርም ሆነ ለሌላ አርሶ አደር በማከራየት መሬታቸውን እያሳረሱ እነሱ የአማራ ህዝብ ጠላት የሆነ ስርዓት ጋር አብረው የሚንቀሳቀሱበትን እድል አንፈጥርም ያለው አርበኛው፡ ከዚህ በኋላ እጃቸውን ለፋኖ በመስጠት ወደ ሰላማዊ ህይወታቸው የማይመለሱ ከሆነ በመሬታቸውና በሌሎች ንብረቶቻቸው ላይ የማዘዝ መብት አይኖራቸውም ሲል ገልጿል። ስለሆነም ግፍን በመቃወም የቀረበውን ጥሪ ተቀብለው እጃቸውን ለፋኖ የሚሰጡ የሚልሻና ፖሊስ አባላት በሰላም ወደ ቤታቸው ገብተው መሬታቸውን ማረስ የሚችሉ ሲሆን ከፋኖ ጋር ተቀላቅለን እንታገላለን ካሉም በየሙያ ዘርፋቸው እድሉ ይመቻችላቸዋል ተብሏል። ነገር ግን ይሄን ፋኖ ያቀረበውን ጥሪ የማይቀበሉ የፖሊስና ሚሊሻ አባላት መሬታቸውን ማሳረስም ሆነ ለሌላ አርሶ አደር ማከራየት እንደማይችሉ የተገለፀ ሲሆን ለስራ አጥ ወጣቶች እንዲከፋፈልም ተወስኗል። ይህ መመሪያ ከዕዝና ከክፍለ ጦሮች የመጣ ነው ሲሉ ከአማራ ድምፅ ሚድያ ጋር ባደረጉት ቆይታ የተናገሩት የመካነሰላም አባይ ሸለቆ ብርጌድ አዛዡ አርበኛ አብነው ታደሰ፡ ዕዙ በሚንቀሳቀስባቸው በሁሉም ቀጠናዎች የሚተገበር መሆኑንም ጠቁመዋል። ይሄንን መመሪያ ተከትሎ የፖሊስና የሚልሻ ማሳዎችን ለማረስ ተከራይተው የነበሩ ሰዎች የኪራይ ውላቸውን እያቋረጡ መሆኑም ተሰምቷል። #የአማራ ድምፅ
نمایش همه...
👍 1
"በምሬና በዘመነ መካከል፣ #በመሳፍንትና በአሰግደው መካከል ያለው የስምና የአካል ልዩነት ብቻ ነው። የሀሳብና የአላማ ልዩነት የለም። አራቱም መሪወች ተነጋግረው በ30 ደቂቃ ውስጥ ባሕርዳር ላይ መገናኘትና መወሰን ይችላሉ። ክልላችንን ወራሪው ሀይል ይልቀቅ።" = ማርሸት ከተናገረው የተወሰደ =
نمایش همه...
5
Photo unavailableShow in Telegram
"ሰቅጣጭ" በሆነው አዋሽ አርባ የሚገኙ "የኅሊና" እስረኞች እንዲለቀቁ ሲል ኢሕአፓ ጠየቀ ሐሙስ ግንቦት 08 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሊቀ መንበሩን ጨምሮ ሌሎች በአዋሽ አርባ የሚገኙ "የግፍ" እስረኞች እንዲለቀቁ ጠየቀ። ፓርቲው ዛሬ ለአዲስ ማለዳ በላከው መግለጫ "ኢትዮጵያ እንደ አገር እንድትቀጥል የሕግ የበላይነት ሊኖር ይገባል" ሲል የገለጸ ሲሆን የፓርቲው ሊቀ መንበር ዝናቡ አበራ ሌሎችም "የህሊና" እስረኞች እንዲለቀቁ ተማጽኗል። የብልጽግና መንግስት በሕዝብ ላይ ጦር መስበቅ፣ ሰራዊት ማዝመት፣ በድሮንና በአየር ኃይል ሕዝብ መፍጀቱን በአስቸኳይ እንዲያቆም ሲል ኢሕአፓ አሳስቧል። ፓርቲው አክሎም "ብልጽግና ፖለቲከኞችን፣ ጋዜጠኞችን፣ ማህበራዊ አንቂዎችን፣ ሌሎችንም ዜጎች እያፈሰ በማሰር፣ በማሰቃየት የፖለቲካ ስልጣኑን የሚያቆይ ከመሰለው እጅጉን ተሳስቷል" ብሏል። ፓርቲው በህዳር 30 የጦርነት ይቁም ሰላማዊ ሰልፍ አዘጋጆች ሰላማዊ ታጋይ በመሆናቸው እንዲፈቱ እንዲሁም በዘርና በሌሎች ፍረጃዎች የታሰሩ የህሊና እስረኞች በሙሉ ይፈቱ ሲል አሳስቧል።
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
"ውስጣዊ ችግሮቻችን ግዙፍ አላማዎቻችን በማስቀደም እየፈታን ወደፊት በድል እንገሰግሳለን" - አርበኛ ዘመነ ካሴ የአማራ ፋኖ በጎጃም ካሉት 9 ክፍለ ጦሮች ውስጥ አንዱ የሆነው የጃዊ ክፍለ ጦር ከሚያዚያ 8-12 ባደረገው ፍልሚያ እና በተገኘው አስደናቂ ድል፣ ቀጣይ መታረም ባለባቸው እንከኖች ዙሪያ በአማራ ፋኖ በጎጃም የአደረጃጀት መምሪያ ሀላፊ ፋኖ እሸቱ ጌትነት አወያይነት ለ2ቀን ከመከሩ በኋላ አሉ የሚሏቸው ውስጣዊና ውጫዊ፣ ግላዊና ተቋማዊ ችግሮችን አንስተው በመምሪያ ሀላፊው በኩል በቂ ማብራሪያ ተሰጥቶ ላስገኙት አስደናቂ ድልና ቀጣይ ለሚያደርጉት የተሻለ የግዳጅ አፈጻጸም የአማራ ፋኖ በጎጃም ሰብሳቢ አርበኛ ዘመነ ካሴ ባካል ተገኝቶ ምስጋና ተችሯቸው ቀጣዩን ድርጅታዊ የስራ መመሪያም በመሪው በኩል በመቀበል አጠናቀዋል።
نمایش همه...