cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

የዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች

"ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን" 2ኛ ቆሮ. 2:14 This channel is not run by D/n Henok Haile. YouTube https://www.youtube.com/@Min22111 Telegram Group https://t.me/dn_henok

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
5 797
مشترکین
+1024 ساعت
+107 روز
+21730 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Photo unavailableShow in Telegram
የፊታችን ረቡዕ ሌሊት 11፡00 ሰዓት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ትምህርት ስለምንጀምር በየትኛውም ዓለም የምትኖሩ እና መማር ፈቃዳችሁ የሆነ ሁሉ ከታች የተቀመጠውን የZoom link በመጠቀም ልትቀላቀሉን ትችላላችሁ:: “ብዙ ምርኮ እንዳገኘ በቃልህ ደስ አለኝ” መዝ 119:162 https://us02web.zoom.us/j/81873667259?pwd=R2ZGVWVEamhLZU5aVk1PeXhxcGFrdz09
نمایش همه...
👍 15 9
መዝሙረ ዳዊት Psalms 105፡(106)። 1፤ሃሌ፡ሉያ፤ቸር፡ነውና፥ምሕረቱም፡ለዘለዓለም፡ነውና፥እግዚአብሔርን፡አመስግኑ። 2፤የእግዚአብሔርን፡ኀይል፡ሥራ፡ማን፡ይናገራል፧ምስጋናውንስ፡ዅሉ፡ማን፡ያሰማል፧ 3፤ፍርድን፡የሚጠብቁ፥ጽድቅንም፡ዅልጊዜ፡የሚያደርጉ፡ምስጉኖች፡ናቸው። 4፤አቤቱ፥በሕዝብኽ፡ሞገስ፡ዐስበን፥በመድኀኒትኽም፡ጐብኘን፤ 5፤የመረጥኻቸውን፡በጎነት፡እናይ፡ዘንድ፥በሕዝብኽም፡ደስታ፡ደስ፡ይለን፡ዘንድ፥ከርስትኽም፡ጋራ፡ እንጓደድ፡ዘንድ። 6፤ከአባቶቻችን፡ጋራ፡ኀጢአትን፡ሠራን፥ዐመፅንም፥በደልንም። 7፤አባቶቻችን፡በግብጽ፡ሳሉ፡ተኣምራትኽን፡አላስተዋሉም፥የምሕረትኽንም፡ብዛት፡አላሰቡም፤በቀይ፡ባሕር፡ ባለፉ፡ጊዜ፡ዐመፁብኽ። 8፤ኀይሉን፡ግን፡ለማስታወቅ፥ስለ፡ስሙ፡አዳናቸው። 9፤ቀይ፡ባሕርንም፡ገሠጸ፥ርሱም፡ደረቀ፤እንደ፡ምድረ፡በዳ፡በጥልቅ፡መራቸው። 10፤ከሚጠሏቸውም፡እጅ፡አዳናቸው፥ከጠላትም፡እጅ፡ተቤዣቸው። 11፤ያሳደዷቸውንም፡ውሃ፡ደፈናቸው፥ከነርሱም፡አንድ፡አልቀረም። 12፤በዚያን፡ጊዜ፡በቃሉ፡አመኑ፥ምስጋናውንም፡ዘመሩ። 13፤ፈጥነውም፡ሥራውን፡ረሱ፥በምክሩም፡አልታገሡም። 14፤በምድረ፡በዳም፡ምኞትን፡ተመኙ፥በበረሓም፡እግዚአብሔርን፡ተፈታተኑት። 15፤የለመኑትንም፡ሰጣቸው፤ለነፍሳቸው፡ግን፡ክሳትን፡ላከ። 16፤ሙሴንም፡እግዚአብሔር፡የቀደሰውንም፡አሮንን፡በሰፈር፡ተመቀኟቸው። 17፤ምድርም፡ተከፈተች፡ዳታንንም፡ዋጠችው፥የአቤሮንንም፡ወገን፡ደፈነች፤ 18፤በማኅበራቸውም፡እሳት፡ነደደች፥ነበልባልም፡ኃጥኣንን፡አቃጠላቸው። 19፤በኰሬብም፡ጥጃን፡ሠሩ፥ቀልጦ፡ለተሠራ፡ምስልም፡ሰገዱ። 20፤ሣርም፡በሚበላ፡በበሬ፡ምሳሌ፡ክብራቸውን፡ለወጡ። 21-22፤ታላቅ፡ነገርንም፡በግብጽ፥ድንቅንም፡በካራን፡ምድር፥ግሩም፡ነገርንም፡በቀይ፡ባሕር፡ያደረገውን፡ ያዳናቸውንም፡እግዚአብሔርን፡ረሱ። 23፤እንዳያጠፋቸው፡ቍጣውን፡ይመልስ፡ዘንድ፡የተመረጠው፡ሙሴ፡በመቅሠፍት፡ጊዜ፡በፊቱ፡ባይቆም፡ ኖሮ፥ያጠፋቸው፡ዘንድ፡ተናገረ። 24፤የተወደደችውን፡ምድር፡ናቁ፥በቃሉም፡አልታመኑም፥ 25፤በድንኳኖቻቸውም፡ውስጥ፡አንጐራጐሩ፤የእግዚአብሔርን፡ቃል፡አልሰሙም። 26-27፤በምድረ፡በዳም፡ይጥላቸው፡ዘንድ፥ዘራቸውንም፡በአሕዛብ፡መካከል፡ይጥል፡ዘንድ፥በያገሩም፡ ይበትናቸው፡ዘንድ፥እጁን፡አነሣባቸው። 28፤በብዔል፡ፌጎርም፡ተባበሩበት፥የሙታንንም፡መሥዋዕት፡በሉ። 29፤በሥራቸውም፡አስመረሩት፥ቸነፈርም፡በላያቸው፡በዛ። 30፤ፊንሐስም፡ተነሥቶ፡ፈረደባቸው፥ቸነፈሩም፡ተወ፤ 31፤ያም፡እስከ፡ዘለዓለም፡ለልጅ፡ልጅ፡ጽድቅ፡ኾኖ፡ተቈጠረለት። 32-33፤በክርክር፡ውሃ፡ዘንድም፡አስቈጡት፥መንፈሱን፡አስመርረዋታልና፤ስለ፡እነርሱም፡ሙሴ፡ ተበሳጨ፤በከንፈሮቹም፡በስንፍና፡ተናገረ። 34፤እግዚአብሔርም፡እንዳላቸው፡አሕዛብን፡አላጠፉም፤ 35፤ከአሕዛብም፡ጋራ፡ተደባለቁ፥ሥራቸውንም፡ተማሩ። 36፤ለጣዖቶቻቸውም፡ተገዙ፥ወጥመድም፡ኾኑባቸው። 37፤ወንዶች፡ልጆቻቸውንና፡ሴቶች፡ልጆቻቸውን፡ለአጋንንት፡ሠዉ፤ 38፤የወንዶች፡ልጆቻቸውንና፡የሴቶች፡ልጆቻችን፡ደም፥ለከነዓን፡ጣዖቶች፡የሠዉአቸውን፡ንጹሕ፡ደም፡ አፈሰሱ፥ምድርም፡በደም፡ረከሰች። 39፤በሥራቸው፡ረከሱ፥በማድረጋቸውም፡አመነዘሩ። 40፤የእግዚአብሔርም፡ቍጣ፡በሕዝቡ፡ላይ፡ነደደ፥ርስቱንም፡ተጸየፈ። 41፤ወደ፡አሕዛብም፡እጅ፡አሳለፋቸው፥የሚጠሏቸውም፡ገዟቸው። 42፤ጠላቶቻቸውም፡ግፍ፡አደረጉባቸው፥ከእጃቸውም፡በታች፡ተዋረዱ። 43፤ብዙ፡ጊዜ፡አዳናቸው፤ነገር፡ግን፥በምክራቸው፡አስመረሩት፥በኀጢአታቸውም፡ተዋረዱ። 44፤ርሱ፡ግን፡ጩኸታቸውን፡በሰማ፡ጊዜ፡ጭንቃቸውን፡ተመለከተ፤ 45፤ለእነርሱም፡ኪዳኑን፡ዐሰበ፥እንደ፡ምሕረቱም፡ብዛት፡ተጸጸተ። 46፤በማረኳቸውም፡ዅሉ፡ፊት፡ሞገስን፡ሰጣቸው። 47፤አምላካችን፡እግዚአብሔር፡ሆይ፥አድነን፤ቅዱስ፡ስምኽን፡እናመሰግን፡ዘንድ፥በምስጋናኽም፡እንመካ፡ ዘንድ፥ከአሕዛብ፡መካከል፡ሰብስበን። 48፤ከዘለዓለም፡እስከ፡ዘለዓለም፡የእስራኤል፡አምላክ፡እግዚአብሔር፡ይባረክ፡ሕዝብም፡ዅሉ፡አሜን፡ ይበል።ሃሌ፡ሉያ።
نمایش همه...
12👍 7🙏 2
መዝሙረ ዳዊት Psalms 104፡(105)። ሃሌ፡ሉያ። 1፤እግዚአብሔርን፡አመስግኑ፥ስሙንም፡ጥሩ፥ለአሕዛብም፡ሥራውን፡አውሩ። 2፤ተቀኙለት፥ዘምሩለት፥ተኣምራቱንም፡ዅሉ፡ተናገሩ። 3፤በቅዱስ፡ስሙ፡ተጓደዱ፤እግዚአብሔርን፡የሚፈልግ፡ልብ፡ደስ፡ይበለው። 4፤እግዚአብሔርን፡ፈልጉት፡ትጸናላችኹም፤ዅልጊዜ፡ፊቱን፡ፈልጉ። 5-6፤ባሪያዎቹ፡የአብርሃም፡ዘር፥ለርሱም፡የተመረጣችኹ፡የያዕቆብ፡ልጆች፡ሆይ፥የሠራትን፡ድንቅ፡ ዐስቡ፥ተኣምራቱን፡የአፉንም፡ፍርድ። 7፤ርሱ፡እግዚአብሔር፡አምላካችን፡ነው፤ፍርዱ፡በምድር፡ዅሉ፡ነው። 8፤ቃል፡ኪዳኑን፡ለዘለዓለም፥እስከ፡ሺሕ፡ትውልድ፡ያዘዘውን፡ቃሉን፡ዐሰበ፥ 9፤ለአብርሃም፡ያደረገውን፥ለይሥሐቅም፡የማለውን፤ 10፤ለያዕቆብ፡ሥርዐት፡እንዲኾን፡ለእስራኤልም፡የዘለዓለም፡ኪዳን፡እንዲኾን፡አጸና። 11፤እንዲህም፡አለ፦ለአንተ፡የከነዓንን፡ምድር፡የርስታችኹን፡ገመድ፡እሰጣለኹ፤ 12፤ይህም፡የኾነው፡እነርሱ፡በቍጥር፡ጥቂቶች፡ሰዎች፥እጅግ፡ጥቂቶችና፡ስደተኛዎች፡ሲኾኑ፡ነው። 13፤ከሕዝብ፡ወደ፡ሕዝብ፥ከመንግሥታትም፡ወደ፡ሌላ፡ሕዝብ፡ዐለፉ። 14-15፤የቀባዃቸውን፡አትዳስሱ፥በነቢያቴም፡ክፉ፡አታድርጉ፡ብሎ፥ሰው፡ግፍ፡ያደርግባቸው፡ዘንድ፡ አልፈቀደም፥ስለ፡እነርሱም፡ነገሥታትን፡ገሠጸ። 16፤በምድር፡ላይ፡ራብን፡ጠራ፥የእኽልን፡ኀይል፡ዅሉ፡ሰበረ። 17፤በፊታቸው፡ሰውን፡ላከ፤ዮሴፍ፡ለባርነት፡ተሸጠ። 18፤እግሮቹም፡በእግር፡ብረት፡ደከሙ፥ርሱም፡በብረት፡ውስጥ፡ገባ። 19፤ቃሉ፡እስኪመጣለት፡ድረስ፥የእግዚአብሔር፡ቃል፡ፈተነው። 20፤ንጉሥ፡ላከ፡ፈታውም፥የአሕዛብም፡አለቃ፡አስፈታው። 21፤የቤቱ፡ጌታ፥የጥሪቱ፡ዅሉ፡ገዢ፡አደረገው፥ 22፤አለቃዎቹን፡እንደ፡ፈቃዱ፡ይገሥጽ፡ዘንድ፥ሽማግሌዎቹንም፡ጥበበኛዎች፡ያደርጋቸው፡ዘንድ። 23፤እስራኤልም፡ወደ፡ግብጽ፡ገባ፥ያዕቆብም፡በካም፡አገር፡ተቀመጠ። 24፤ሕዝቡንም፡እጅግ፡አበዛ፥ከጠላቶቻቸውም፡ይልቅ፡አበረታቸው። 25፤ሕዝቡን፡ይጠሉ፡ዘንድ፡በባሪያዎቹም፡ላይ፡ይተ፟ነኰሉ፡ዘንድ፡ልባቸውን፡ለወጠ። 26፤ባሪያውን፡ሙሴን፡የመረጠውንም፡አሮንን፡ላከ። 27፤የተኣምራቱን፡ነገር፡በላያቸው፡ድንቁንም፡በካም፡አገር፡አደረገ። 28፤ጨለማን፡ላከ፡ጨለመባቸውም፤በቃሉም፡ዐመፁ። 29፤ውሃቸውን፡ወደ፡ደም፡ለወጠ፥ዓሣዎቻቸውንም፡ገደለ። 30፤ምድራቸው፡የንጉሦቻቸውም፡ቤቶች፡በጓጕንቸር፡ሞሉ። 31፤ተናገረ፥የውሻ፡ዝንብ፡ትንኝም፡በዳርቻቸው፡መጡ። 32፤ዝናባቸውን፡በረዶ፡አደረገው፥እሳትም፡በምድራቸው፡ተቃጠለች። 33፤ወይናቸውንና፡በለሳቸውን፡መታ፥የአገራቸውንም፡ዛፍ፡ዅሉ፡ሰበረ። 34፤ተናገረ፥አንበጣም፡ስፍር፡ቍጥር፡የሌለውም፡ኵብኵባ፡መጣ፥ 35፤የአገራቸውንም፡ለምለም፡ዅሉ፡በላ፥የምድራቸውንም፡ፍሬ፡በላ። 36፤የአገራቸውንም፡በኵር፡ዅሉ፥የጕልበታቸውን፡መዠመሪያ፡ዅሉ፡መታ። 37፤ከወርቅና፡ከብርም፡ጋራ፡አወጣቸው፥በወገናቸውም፡ውስጥ፡ደዌ፡አልነበረም። 38፤ፈርተዋቸው፡ነበርና፥ግብጽ፡በመውጣታቸው፡ደስ፡አላት። 39፤ደመናን፡ለመሸፈኛ፡ዘረጋባቸው፥እሳትንም፡በሌሊት፡ያበራላቸው፡ዘንድ፡ዘረጋ። 40፤ለመኑ፥ድርጭትንም፡አመጣላቸው፥የሰማይንም፡እንጀራ፡አጠገባቸው። 41፤አለቱን፡ሰነጠቀ፥ውሃውም፡ፈሰሰ፤ወንዞች፡በበረሓ፡ኼዱ፤ 42፤ለባሪያው፡ለአብርሃም፡የነገረውን፡ቅዱስ፡ቃሉን፡ዐስቧልና። 43፤ሕዝቡንም፡በደስታ፡የተመረጡትንም፡በእልልታ፡አወጣ። 44፤የአሕዛብንም፡አገሮች፡ሰጣቸው፥የወገኖችንም፡ድካም፡ወረሱ፥ 45፤ሕጉን፡ይጠብቁ፡ዘንድ፥ሥርዐቱንም፡ይፈልጉ፡ዘንድ።ሃሌ፡ሉያ፡ https://t.me/hinokhayla https://t.me/hinokhayla
نمایش همه...
የዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች

"ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን" 2ኛ ቆሮ. 2:14 This channel is not run by D/n Henok Haile. YouTube

https://www.youtube.com/@Min22111

Telegram Group

https://t.me/dn_henok

15👍 4🙏 1
እስኪ ንገሩኝ! ከእናንተ መካከል ከመዝሙረ ዳዊት ውስጥ አንዲትዋን ምዕራፍ ወይም ከሌላው የቅዱሳት መጻህፍት ክፍል ውስጥ ጥቂት በቃልህ ድገም ቢባል ይህን ማድረግ የሚችል ማን ነው? አንድ ሰውስ እንኳ አይገኝም። የሚያሳዝነው ነገር ግን ይኼ ብቻ አይደለም። ከመንፈሳዊ ነገሮች አንፃር እንደዚህ አእምሮ የጎደላችሁ ኾናችሁ ሳለ ዲያቢሎሳዊ በኾኑ ነገሮች ላይ ግን ከእሳት በላይ ኀያላን ናችሁ። እንዲህም በመኾናችሁ አንድ ሰው መጥቶ ዲያቢሎሳዊ ዘፈኖችንና የዝሙት ዜማዎችን ንገሩኝ ቢላችሁ ከእናንተ መካከል እነዚህን የሚያውቁና ደስ ተሰኝተው የሚደግሟቸው ብዙ ሰዎችን ያገኛል። ነገር ግን"ለምንድን ነው እንደዚህ የምትኾኑት?" ተብላችሁ ስትጠየቁ የምትመልሱትስ መልስ ምን የሚል ነው? "እኔ ከመነኮሳት አንዱ አይደለሁም። ሚስት አለቺኝ፣ልጆችም አሉኝ፣የቤተሰብ መሪ ነኝ" የሚል ምክንያት ታቀርባላችሁ። ለምን እንደዚህ ትላላችሁ? ከመነኮሳቱ ይልቅ ይበልጥ ማንበብ ያለባችሁ እናንተ ኾናችሁ ሳለ ብዙዎች እንዲጠፉ ያደረገው "ቅዱሳት መፃህፍትን ማንበብ ለመነኮሳት ብቻ ነው" የሚለው አመለካከታችሁ ነው። ይበልጥ ብዙ መድኃኒት የሚያስፈልጋቸው በማእከለ ዓለም የሚኖሩትና ዕለት ዕለትም መንፈሳዊ ቁስል የሚያገኛቸው ሰዎች ናቸውና። ስለዚህም ከለማንበባችሁም በላይ" የእኛ ማንበብ ትረፍ ነገር ነው" ብላችሁ ማሰባችሁ በራሱ የዲያብሎስ አሳብ ነው። ወይስ ንዑድ ክቡር የሚኾን ጳውሎስ "ዝንቱ ኵሉ ተጽሕፈ ለተግሣጸ ዚአነ - ይህም ኹሉ እኛን ሊገስጸን ተፃፈ"(1ኛ ቆሮ 10:11) ያለውን አላዳመጣችሁምን? ቅዱስ ዮሀንስ አፈወርቅ
نمایش همه...
24👍 12😁 1
መዝሙረ ዳዊት Psalms 103፡(104)። የዳዊት፡መዝሙር። 1፤ነፍሴ፡ሆይ፥እግዚአብሔርን፡ባርኪ፤አቤቱ፡አምላኬ፡ሆይ፥አንተ፡እጅግ፡ታላቅ፡ነኽ፤ክብርንና፡ግርማን፡ ለበስኽ። 2፤ብርሃንን፡እንደ፡ልብስ፡ለበስኽ፤ሰማይንም፡እንደ፡መጋረጃ፡ዘረጋኽ፤ 3፤ዕልፍኙን፡በውሃ፡የሚሠራ፥ሠረገላውን፡ደመና፡የሚያደርግ፥በነፋስ፡ክንፍም፡የሚኼድ፥ 4፤መላእክቱን፡መንፈስ፡የሚያደርግ፥አገልጋዮቹንም፡የእሳት፡ነበልባል። 5፤ለዘላለም፡እንዳትናወጥ፡ምድርን፡በመሠረቷ፡ላይ፡መሠረታት። 6፤በጥልቅ፡እንደ፡ልብስ፡ከደንኻት፥በተራራዎችም፡ላይ፡ውሃዎች፡ይቆማሉ። 7፤ከዘለፋኽም፡ይሸሻሉ፥ከነጐድጓድኽም፡ድምፅ፡ይደነግጣሉ፤ 8፤ወደ፡ተራራዎች፡ይወጣሉ፥ወደ፡ቈላዎች፡ወዳዘጋጀኽላቸው፡ስፍራ፡ይወርዳሉ፤ 9፤እንዳያልፉትም፡ድንበር፡አደረግኽላቸው፥ምድርን፡ይከድኑ፡ዘንድ፡እንዳይመለሱ። 10፤ምንጮችን፡ወደ፡ቈላዎች፡ይልካል፤በተራራዎች፡መካከል፡ውሃዎች፡ያልፋሉ፤ 11፤የዱር፡አራዊትን፡ዅሉ፡ያጠጣሉ፥የበረሓ፡አህያዎችም፡ጥማታቸውን፡ይረካሉ። 12፤የሰማይም፡ወፎች፡በእነርሱ፡ዘንድ፡ያድራሉ፥በድንጋዩ፡ስንጥቅ፡መካከልም፡ይጮኻሉ። 13፤ተራራዎችን፡ከላይ፡የሚያጠጣቸው፤ከሥራኽ፡ፍሬ፡ምድር፡ትጠግባለች። 14፤እንጀራን፡ከምድር፡ያወጣ፡ዘንድ፡ለምለሙን፡ለሰው፡ልጆች፡ጥቅም፥ሣርንም፡ለእንስሳ፡ያበቅላል። 15፤ወይን፡የሰውን፡ልብ፡ደስ፡ያሰኛል፥ዘይትም፡ፊትን፡ያበራል፥እኽልም፡የሰውን፡ጕልበት፡ያጠነክራል። 16፤የእግዚአብሔር፡ዛፎች፡ርሱም፡የተከላቸው፡የሊባኖስ፡ዝግባዎች፡ይጠግባሉ። 17፤በዚያም፡ወፎች፡ይዋለዳሉ፥የሽመላ፡ቤትም፡የእነርሱ፡ጎረቤት፡ነው። 18፤ረዣዥም፡ተራራዎች፡ለዋላዎች፥ድንጋዮችም፡ለሽኮኮዎች፡መሸሻ፡ናቸው። 19፤ጨረቃን፡ለጊዜዎች፡አደረገ፤ፀሓይም፡መግቢያውን፡ያውቃል። 20፤ጨለማ፡ታደርጋለኽ፥ሌሊትም፡ይሆናል፤በርሱም፡የዱር፡አራዊት፡ዅሉ፡ይወጡበታል። 21፤የአንበሳ፡ግልገሎች፡ለመንጠቅ፡ይጮኻሉ፥ከእግዚአብሔርም፡ምግባቸውን፡ይሻሉ። 22፤ፀሓይ፡ስትወጣ፡ይሰበሰባሉ፥በየዋሻቸውም፡ይተኛሉ። 23፤ሰው፡ወደ፡ተግባሩ፥እስኪመሽም፡ድረስ፡ወደ፡ሥራው፡ይወጣል። 24፤አቤቱ፥ሥራኽ፡እጅግ፡ብዙ፡ነው፤ዅሉን፡በጥበብ፡አደረግኽ፥ምድርም፡ከፍጥረትኽ፡ተሞላች። 25፤ይህች፡ባሕር፡ታላቅና፡ሰፊ፡ናት፤በዚያ፡ስፍራ፡ቍጥር፡የሌለው፡ተንቀሳቃሽ፥ታላላቆችና፡ታናናሾች፡ እንስሳዎች፡አሉ። 26፤በዚያ፡ጊዜ፡መርከቦች፡ይኼዳሉ፥በዚያም፡ላይ፡የፈጠርኸው፡ዘንዶ፡ይጫወትበታል። 27፤ምግባቸውን፡በየጊዜው፡ትሰጣቸው፡ዘንድ፡እነዚህ፡ዅሉ፡አንተን፡ተስፋ፡ያደርጋሉ። 28፤በሰጠኻቸውም፡ጊዜ፡ይሰበስባሉ፤እጅኽን፡ትከፍታለኽ፥ከመልካም፡ነገርም፡ይጠግባሉ። 29፤ፊትኽን፡ስትሰውር፡ይደነግጣሉ፤ነፍሳቸውን፡ታወጣለኽ፡ይሞታሉም፥ወደ፡ዐፈራቸውም፡ይመለሳሉ። 30፤መንፈስኽን፡ትልካለኽ፡ይፈጠራሉም፥የምድርንም፡ፊት፡ታድሳለኽ። 31፤የእግዚአብሔር፡ክብር፡ለዘላለም፡ይኹን፤እግዚአብሔር፡በሥራው፡ደስ፡ይለዋል። 32፤ምድርን፡ያያል፡እንድትንቀጠቀጥም፡ያደርጋል፤ተራራዎችን፡ይዳስሳል፡ይጤሳሉም። 33፤በሕይወቴ፡ሳለኹ፡ለእግዚአብሔር፡እቀኛለኹ፥ለአምላኬም፡በምኖርበት፡ዘመን፡ዅሉ፡እዘምራለኹ። 34፤ቃሌ፡ለርሱ፡ይጣፍጠው፥እኔም፡በእግዚአብሔር፡ደስ፡ይለኛል። 35፤ኃጥኣን፡ከምድር፡ይጥፉ፤ዐመፀኛዎች፡እንግዲህ፡አይገኙ።ነፍሴ፡ሆይ፥እግዚአብሔርን፡ባርኪ።ሃሌ፡ሉያ። https://t.me/hinokhayla https://t.me/hinokhayla
نمایش همه...
👍 20 3
نمایش همه...
"የሚሮጥ ዲያቆን" ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የዲያቆናት በዓለ ሲመት ላይ ነበር ይሄንን መግለጫ ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ የተናገረው።እውነት ነው ዲያቆን ጠፍቷል ለዛም ነው የዲያቆን ያለህ እያለ የሚጮህው።video በትግስት አድምጡት ትጠቀሙበታላቹ።"ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ...

መዝሙረ ዳዊት Psalms 102፡(103)። የዳዊት፡መዝሙር። 1፤ነፍሴ፡ሆይ፥እግዚአብሔርን፡ባርኪ፥ዐጥንቶቼም፡ዅሉ፥የተቀደሰ፡ስሙን። 2፤ነፍሴ፡ሆይ፥እግዚአብሔርን፡ባርኪ፥ምስጋናውንም፡ዅሉ፡አትርሺ፤ 3፤ኀጢአትሽን፡ዅሉ፡ይቅር፡የሚል፥ደዌሽንም፡ዅሉ፡የሚፈውስ፥ 4፤ሕይወትሽን፡ከጥፋት፡የሚያድናት፥በምሕረቱና፡በቸርነቱ፡የሚከልልሽ፥ 5፤ምኞትሽን፡ከበረከቱ፡የሚያጠግባት፥ጕልማሳነትሽን፡እንደ፡ንስር፡ያድሳል። 6፤እግዚአብሔር፡ይቅርታ፡አድራጊ፡ነው፤ለተበደሉ፡ዅሉ፡ይፈርዳል። 7፤ለሙሴ፡መንገዱን፡አስታወቀ፥ለእስራኤል፡ልጆችም፡አደራረጉን። 8፤እግዚአብሔር፡መሓሪና፡ይቅር፡ባይ፡ነው፥ከቍጣ፡የራቀ፡ምሕረቱም፡የበዛ። 9፤ዅልጊዜም፡አይቀሥፍም፥ለዘለዓለምም፡አይቈጣም። 10፤እንደ፡ኀጢአታችን፡አላደረገብንም፥እንደ፡በደላችንም፡አልከፈለንም። 11፤ሰማይ፡ከምድር፡ከፍ፡እንደሚል፥እንዲሁ፡እግዚአብሔር፡ምሕረቱን፡በሚፈሩት፡ላይ፡አጠነከረ። 12፤ምሥራቅ፡ከምዕራብ፡እንደሚርቅ፥እንዲሁ፡ኀጢአታችንን፡ከእኛ፡አራቀ። 13፤አባት፡ለልጆቹ፡እንደሚራራ፡እንዲሁ፡እግዚአብሔር፡ለሚፈሩት፡ይራራል፤ 14፤ፍጥረታችንን፡ርሱ፡ያውቃልና፤አቤቱ፥እኛ፡ዐፈር፡እንደ፡ኾን፟፡ዐስብ። 15፤ሰውስ፡ዘመኑ፡እንደ፡ሣር፡ነው፤እንደ፡ዱር፡አበባ፡እንዲሁ፡ያብባል፤ 16፤ነፋስ፡በነፈሰበት፡ጊዜ፡ያልፋልና፥ስፍራውንም፡ደግሞ፡አያውቀውምና። 17፤የእግዚአብሔር፡ምሕረት፡ግን፡ከዘለዓለም፡እስከ፡ዘለዓለም፡በሚፈሩት፡ላይ፥ጽድቁም፡በልጅ፡ልጆች፡ ላይ፡ነው፤ 18፤ቃል፡ኪዳኑን፡በሚጠብቁ፥ትእዛዙንም፡ያደርጓት፡ዘንድ፡በሚያስቡ፡ላይ፡ነው። 19፤እግዚአብሔር፡ዙፋኑን፡በሰማይ፡አዘጋጀ፥መንግሥቱም፡ዅሉን፡ትገዛለች። 20፤ቃሉን፡የምትፈጽሙ፥ብርቱዎችና፡ኀያላን፥የቃሉንም፡ድምፅ፡የምትሰሙ፡መላእክቱ፡ ዅሉ፥እግዚአብሔርን፡ባርኩ። 21፤ሰራዊቱ፡ዅሉ፥ፈቃዱን፡የምታደርጉ፡አገልጋዮቹ፥እግዚአብሔርን፡ባርኩ። 22፤ፍጥረቶቹ፡ዅሉ፡በግዛቱ፡ስፍራ፡ዅሉ፥እግዚአብሔርን፡ባርኩ።ነፍሴ፡ሆይ፥እግዚአብሔርን፡ባርኪ። https://t.me/hinokhayla https://t.me/hinokhayla
نمایش همه...
የዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች

"ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን" 2ኛ ቆሮ. 2:14 This channel is not run by D/n Henok Haile. YouTube

https://www.youtube.com/@Min22111

Telegram Group

https://t.me/dn_henok

15👍 2🙏 2
Photo unavailableShow in Telegram
በምጸልይበት ጊዜ ልቤ አይሰበሰብም። እንዲህ ከሆነ መጸለይ ቢቀርብኝስ ? ልቡናውን ሰብስቦ መጸለይ ያቃተው አንድ ደቀ መዝሙር አረጋዊውን አባት እንዲህ ሲል ይጠይቃቸዋል፦ "አባቴ የጸሎት መጽሐፍ ይዤ ስጸልይ ልቡናዬ አይሰበሰብልኝም፤ አፌ ቢያነበውም ልቡናዬ ግን ይበታተናል፡፡ እኔ ደግሞ ዝም ብዬ ሳስበው፦ ቅዱሳን በፍጹም ሐሳባቸው እያሰቡና እያራቀቁ እንባንና ጸጸትን እየጨመሩ የጻፉትን እኔ በልቤ ሌላ እያሰብኩ በአፌ ብቻ ባነበንበው እንደ ገደል ማሚቶ ፊደሉ አፌ ላይ እየነጠረ ይሄዳል እንጅ ጸሎትም አይሆንልኝም ስለዚህ አባቴ የአፍ ብቻ ጸሎቴ ቅድመ እግዚአብሔር የማይደርስ ከሆነ ጸሎቴን ብተወው ይሻላል ወይስ ባልተወው ይሻላል?'' ብሎ ጠየቃቸው። አረጋዊው አባትም እንዲህ ሲሉ አስረዱት፡- "አየህ ልጄ ዐይነ ስውር ሰው በዘንጉ ምድር እየመታ ሲሄድ ከመንገድ ላይ ያለ እባብ ለጊዜው የበትሩን ድምጽ ሰምቶ ይመታኛል ብሎ ይሸሻል እንጅ ዐይነ ስውር ነው አላየኝም ብሎ ባለበት አይጠብቀውም። ስለዚህ አንተም አስተውለህ ብትጸልይ መልካም ቢሆንም ለጊዜው ግን ጭራሽ ከምታቆመው በአፍህ ውስጥ ያለው የቃለ እግዚአብሔርን መንኳኳት የሚሰሙ አጋንንት መሸሻቸው አይቀርምና መቼም ቢሆን ጸሎትህን አትተው፡፡ አጋንንትንም ማባረር አንድ ታላቅ ጥቅም ነውና፡፡ ብዙ ከመጸለይህም አንጻር አንዳንድ ጊዜ ልብህ የሚወድቅባት ቃል ተጠራቅማ ወደ እግዚአብሔር ታደርስሃለች። እናም ልጄ ልብህ ምንም ዝርው ቢሆንም አፍህም የእግዚአብሔር ፍጥረት ነውና ይህንንም እንዳታቆመው። አሁን አንዱን ይዘህ ወደፊት ደግሞ ሁለቱንም ለማገናኘት መጣር ይኖርብሃል እንጅ አንተው በዳይ አንተው አኵራፊ ሆነህ ጭራሽ ከአምላክ ርቀህ የጠላት ሰይጣን መጫወቻ እንዳትሆን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!
نمایش همه...
👍 35 9👏 3
Photo unavailableShow in Telegram
#ለ5_ቀናት_የሚቆይ_ፓኬጅ! እነዚህ 8 የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ መጻሕፍት የሽፋን ዋጋቸው 2,420 ብር ሲኾኑ እስከ ቅዳሜ በአንድ ላይ በፓኬጅ ለሚገዙ በ1,700 ብር ብቻ አዘጋጅተን እንጠብቃችኋለን። __ ባኮስ መጻሕፍት መደብር - ይጎብኙን - ደርዛቸውን የጠበቁ አዳዲስና ነባር ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍትን ያገኛሉ! ለበለጠ መረጃ በ0920888887 ይደውሉ። አድራሻችን፦ አምስት ኪሎ ቅድስት ማርያም፥ አሐዱ ባንክ ፊት ለፊት
نمایش همه...
6