ዕቅበተ አእምሮ
رفتن به کانال در Telegram
ይህ #Telegram# ቻናል የወለህ ነቅዐ ሕይወት የ፬ቱ ጉባኤያት ምስክር ትምህርት ቤት ገጽ ነው ። የተከፈተበት ዓላማ ኦርቶዶክሳዊ አእምሮን ለመጠበቅና አንድነትን ለመመለስ ነው ። የሚከፋፍሉ አጀንዳዎችን ፖስት ማድረግ ክልክል ነው።።።።
نمایش بیشتر1 997
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
پستهای کانال
| 2 | ሣልሳዊ ሕገ ወጥ ጵጵስና
መስቀላዊት ቤተ ክርስቲያን በውስጥም በውጭም ሰዎች እንደዚህ ዘመን የተገፋችበት ጊዜ የለም።
በተለየ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ህልውና የሚጠበቅበት ቅዱስ ሲኖዶስ አንድ መንበር የሚለው ከምእመናን ኅሊና እንዲጠፋ ከትናንት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ጠላቶቻችን የሚሠሩበት ነው።
በመጀመሪያ በእነሳዊሮስ መሪነት ኦሆዴዳዊ የጵጵስና ሹመት ተፈጸመ።
የምእመናን ደም በቤተ መቅደሱ ፈሰሰ ጥቁር ለበስን እስከ ዛሬ ድረስ ልባችን ሳይሽር እንኖራለን።
ሁለተኛ በትግራይ መንበረ ሰላማ የሚል አንዲት ቤተ ክርስቲያንን በእጅጉ እየፈተነ ያለ ጵጵስና ተፈጸመ።
አሁን ደግሞ ዳግማውያን ሠለስቱ ምዕት የሚል በውስጥም በውጭም በተቀናጀ መንገድ ዘርዕንና ጎሳን መሠረት በማድረግ ሃይማኖት የሌላቸው ሃይማኖት አለን የሚሉ የሥልጣን ጥመኞች በመናፍቃን አቀንቃኝነትና በሥርዓቱ ከፋፋይነት ለመሾም እንቅስቃሴ እያደረጉ ነው።
የዘርዕ ሲኖዶስንና ጵጵስናን እስከ ሞት ድረስ እንቃወማለን። | 0 |
| 3 | አስቸቋይ ጥያቄ ለዳግማዊ ሠለስቱ ምእት ቤተ ክህነት ነን ባዮች። አስቸኳይ ጥንቃቄ ለኦርቶዶክሳወያን ምዕምዕመናን በሙሉ።
ዳግማዊ ሠለስቱ ምዕት ቤተ ክህነት የሚል ተቋምን እነማናቸው የመሠረቱት?እነማን ናቸው የሚያቀሳቀሱት?
ሚድያ ላይ እንዳየሁት ከሆኑ ።
፩ መጠሪያ ስሙን በሠለስቱ ምእት ሰይሞ እየተንቀሳቀሰ እንዳለ እያየን ነው።
፪ አባ ጳውሊ በሚባል ሰው በኩልም መግለጫ እየሰጠ ነው። በመግለጫውም የቤተ ክርስቲያን አሥራት ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እንዳሄድና ለነርሱ ዓላማ እንዲውል አውጆ፡ ይህን ያላደረገ እርምጃ እንደሚወሰድበት ያስጠነቅቃል ፨
፫ ሎጓቸውም ብዙ አይነት ሎጎ አይቻለሁ አንደኛው የሃይማኖት ተቋማት የሚመስል ሁሉን ቤተ እምነቶች ያካተተ ነው ። በዚህም የሃይማኖት ተቋማት ቤተ ክህነት ማለቴ የሙስሊሙም የፕሮቲስታንቱም ነው የተቋቋመ አስብሎኛል ሁለተኛው የአንበሳ ምስል ያለው ሎጎ አይቻለሁ ተጨማሪ ሌሎች ሎጎዎችንም እያየን ነው
፬ የቤተ ክርስቲያንን መከራ ደጋግሞ ያወሳል የቤተ ክህነቱን አላስፈላጊነት ይናገራሉ ። ከመከራው ምንን ነው ለማዋለድ የፈለጉት? የብሔር ሲኖዶስን? ወይስ የጵጵስና ፍቅራቸውን?
የርግብ ክንፍ ተሰበረ ብለን እባብን እንድንወዳጅ? በግ ጠፋ ብለን ተኩላን እንድንገዛ ፣ ጎመን ደረቀ ብለን ሳማን አብላሊትን ኩትኩተን እንድናሳድግ ነው የሚፈልጉት?
፭ እነዚህን መጠየቅ እፈልጋለሁ??
፧፧፦ አባ ጳውሊ ማን ነው?እኔ የማውቀው የአለም ብርሀን አቀንቃኝ እንደ ነበረ ነው። የዓለም ብርሃን ቤተ ክህነት ሊያቆቁም ይሆን?
፧፧፧፦ ከዚህ ግለ ሰብእ ጀርባ ያሉ እነማን ናቸው ? ጳጳሳት ፣ ሊቃውንት የፖለቲካ እጆች ይኖሩበት ይሆን? የብቻውን ሲኖዶስ ሊመሠርት አይችልምና።
፧፧፧፦ በገር ቤት ነው የተመሠረተው ወይስ ከውጭ ባሉ አካላት??
፧፧፦ ሴራውን ያልተረዱ የዋሀን ካህናት ዲያቆናት ጳጳሳት ምዕመናን ይኖሩበት ይሆን??
፧፧፧፦ ሲኖዶስን በሲኖዶስ አጥፍቶ ቤተ ክርስቲያኗን ለመበተን ብዙ ሀሰተኛ ሲኖዶሶችን ለማቋቋም የታሰበወን እቅድ ለማስፈጸም ይሆንን?
፧፧፦ የነዚህ ሰዎች ጠላታቸው ማን ነው ቤተ ክርስቲያን ወይሰ ፖለቲካው? ፖለቲካወስ ከሆነ ቤተ ክርስቲያኗን ከምድረ ገጽ ለማጥፋት ምን አነሳሳቸው?
በአትኩሮት እንከታተለው ዘንድ መልክቴ ነው። | 0 |
| 4 | بدون متن... | 0 |
| 5 | https://youtu.be/EY36rMjleIA?si=7pjCSXvJx3KFL5Jj | 0 |
| 6 | ንጽሐ ሰብእና
ኃጢያትን ከሥራ ማራቅ የመንገሥተ ሰማያት ቁልፍ ነው።የጥፋተኝነት ስሜትም ወደ ፊት እንድንሔድ ማድረግ ካልቻ በራሱ ሌላ ውድቀትን ሊያመጣ ይችላል።
፧፧፧፦ ከስህተት መማር አዳማዊነት ነው አለመማርም ሠይጣናዊነት ነው። ብዙዎች ይስታሉ ትንሾቹ ከስተታቸው ይማራሉ ። ከስተታቸው የሚማሩት ። ጠቢባን ሲሆኑ ከስተታቸው ተምረው የማይለወጡ አብዳን ዝንጉዐን ይባላሉ። ስለ ዚህም ብዙ ሰዎች ይሰሳታሉ ትንሽ ሰዎች ከስተታቸው ይማራሉ
፧፧፧፦ ሕይወት ትርጉም እንዲኖረው ከእግዚአበሔር ጋር ማየያዝ የሰው ልጅ ክብር ፈላጊ ነው ክብር ደግሞ የሚፈልገው ክብር ከጎደላቸውና ክብር ከሌላቸው ነው።
ክብር ከሌላቸው ነገረች ክብርን አለመፈለግ ።ሕይወት ከእግዚአብሔር ጋር ካልተየያዘች ትርጉም አልባ ናት ሕይወት ትርጉም የሚኖረው በእግዚአብሔርና በቃሉ ሲመሠረት ነው። ሁሉም ፍጡራን በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረውን ውሳጣዊ ሕይወታቻን ማርካት አይችሉም ነፍሳችንና ልባችን የሚያረካው ፈጣሪ ነውና።
፧፧፧፦ ስናገኛቸው በሚጠፉ ነገሮች አለጨነቅ ። የማይጠፋውን መውረስ ነው
የሚያስጨንቁን ነገሮች ስናገኛቸው የሚጠፉ ነገሮች ናቸው
ስለ ዚህዓለም የምናስበው ነገር ሁሉ ከንቱ ነው
ከእግዚአብሔር ውጭ ያለ ሕይወት ከንቱ ነው
፧፧፧፧፦ ስነ ፍጥረትን ከተፈጠረለት ዓላማ አንጻር መጠቀም።
እግዚአብሔር የፈጠረውን ዓለም ለምን ከንቱ ይለዋል?ሥነ ፍጥረትን ያላግባብና ያለቦታቸው ስለተጠቀመባቸው ከንቱ ተባለ።ስነ ፍጥረት ከንቱ የሚሆነው ያለአግባብ ስንጠቀምበትና ስንረዳው ነውና ።
፧፧፧፧ ከንቱ ሕሊናን ማራቅ
ከንቱ ሕሊና መንድን ነው? ከንቱ ሕሊና ማለት በከንቱ ነገረች ላይ ትኩረት ያደረገ ሕልውና ማለት ነው
እግዚአብሔር ዓለምን ስለኛ ፈጠረው እንጅ እኛን ስለዓለም አልፈጠረንም ማለት ዓለም የእኛ ባሪያ ሊሆን እንጅ እኛ የዓለም ባሪያ ልንሆን አልተፈጠርንም ማለት ነው ።ከንቱ ሕሊና ማለት የክፉ አሳብ ባርያ ማለት ነውና።
መጻሕፍትም የሚነግሩን ተስፋ እንድንቆርጥ ሳይሆን ተስፋ ወደ ሚያስቆርጥ ከንቱ ነገር እንዳንሔድ ነው።
በጎ ሕሊናን ማሳደግ ማጽናት በከንቱ ነገሮች ላይ ትኩረት አንዳያደርግ ሕሊናን መጠበቅ
ሰው ሕይወትን በምድራዊ ዕሴቶች ዐይንየሚመለከታት ከሆነ የድካሙ ሁሉ ትርፍና ውጤት ምንድን ነው
ከንቱ ነገር ፍሬ የለውም ፍሬ የሌለው ነገርም ኃይል የለውም ሰው የዓለሙን ከንቱነት ለመረዳት ከዓለሙ መነጠል አለበት ቅዱስ አብሮስ ።። መዳን የሚፈልግ ሰው ሁሉ ከዓለም በላይ ከፍ ይበል።
አሁን የምፈልገው ከእግዚአብሔር የሚያስታርቀኝ እንጅ የሚያጣላኝ የሚያቀርበኝ እንጅ የሚያርቀኝ አልፈልግም
ብዙ ጥፋት አጥፍተናል እግዚአብሔር ግን ይወደናል ይፈልገናል። ሠናይ አስረሴ | 0 |
| 7 | ነቅዐ ሕይወት የሕይወታችን እናት እንኳን ደኅና መጣሽልን | 0 |
| 8 | بدون متن... | 0 |
| 9 | ፧፧፧፦ የክርስቶስ ደም በሕሊናም በሥጋም የሞቱትን ቀስቅሷል።
የሠማዕታቱም ደም መከራ የሚያደርሱባቸውን ሳይቀር አሥነስቷል ። የአርሲ ሰማእታት ደም አልቀሰቅሰን ያለው በምን አይነት አመሟት ብንሞት ነው???
፧፧፧፦ በአርሲ የሚፈጸመው የሞት አዋጅ ለሁላችንም የተቃጣ ሰይፍ መሆኑን እግዚአብሔር እየነገረን ነበር እኛ ግን ጆሮ ነፈግነው። | 0 |
| 10 | እመቤቴ ሆይ
የተሰደደች ሔዋንን ወደገነት ለመመለስ አንቺ መላ ዘመንሽን በስደትና በእንግልት አሳለፍሽ ።
✔️ልደትሽ ወደ አድባረ ሊባኖስ ተራሮች በመሰደድ በሊባኖስ ተራሮች መካከል ተደረገ።
ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋራ ነዪ ከሊባኖስ ከእኔ ጋራ ነዪ ከአማና ራስ ከሳኔርና ከኤርሞን ራስ ከአንበሳዎች መኖሪያ ከነብሮችም ተራራ ተመልከች መኃ ፬÷፰
✔️እድገትሽ ገና በሦስት አመትሽ ጀምሮ ከእናት አባትሽ እንዲሁም ከወገኖችሽ ተለይተሽ በስደት ሆነ
ልጄ ሆይ ስሚ እዪ ዦሮሽንም አዘንብዪ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት ርሺ ንጉሥ ውበትሽን ወዶታልና
መዝ ፵፬÷፲
✔️የዓለም መድኃኒት ክርስቶስን እንደወለድሽም ተሰደድሽ
እነርሱም ከሄዱ በኋላ እንሆ የጌታ መልአክ በሕልም ለዮሴፍ ታይቶ ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይፈልገዋልና ተነሣ ሕፃኑንና እናቱንም ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ እስክነግርህም ድረስ በዚያ ተቀመጥ አለው እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን በሌሊት ያዘና ከጌታ ዘንድ በነቢይ ልጄን ከግብጽ ጠራሁት የተባለው እንዲፈጸም ማቴ፪÷፲፫~፲፭
✔️ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ ነፍስ ተሰደድሽ።
የጠፋ በግ አዳምን የፈለገው በአገኘውም ጊዜ የተሸከመው እውነተኛ ቸር ጠባቂ ካንቺ የተወለደ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ እግዚአብሔር በሲዖል የጣላት የሔዋን ጽኑ ፍዳ ባንቺ የጠፋ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ
ሃይ አበ ፷፮÷፴፮
በሚያስደንቅ ግብርም ከባሕርዩ ተወለደ፤ እርሱ እግዚአብሔር ቃል ሲሆን በሚያስደንቅ ምሥጢር ከሰው መወለድን እንደ እኔ ገንዘብ አደረገ፤ በድንግልና ሳለች ከእርስዋ ተወልዶ ድንግል ማርያምን እናቴ አላት፤ ከፈጠራት ጀምሮ በምንም በምን ከድንግልናዋ አልተለወጠችምና። ሃይ አበ ፶፫÷፳፪
✔️በዘርዐ ብእሲ ከመጽነስ እንበለ ዘርዕ ወደመጽነስ ተሰደድሽ።
እንደ እኔስ በዘር በሩካቤ ተወልዶ ቢሆን ብዙ ሰዎች ዕሩቅ ብእሲ ባሉት ነበርአምላክነቱንም በካዱ ነበር እንዲህስ እንዳይሉት ከድንግል ተወለደ በወለደችውም ጊዜ
ድንግልናዋን ያለመለወጥ አጸና ድንቅ በሚሆን ፅንሷ ለደገኛው ሃይማኖት መሪ ትሆን ዘንድ ሃይ አበ ፴፰÷፴፪
✔️ቅድመ ጸኒስ ጊዜ ድኅረ ጸኒስ ቅድመ ወሊድ ጊዜ ወሊድ ድኅረ ወሊድ ከተፈትሖ ማኅተመ ድንግልና ተሰደድሽ።
ስለዚህ ሕፃን ክርስቶስ ከእሷ ከተወለደ በኋላ ድንግል ንጽሕት ማርያምን ማኅተመ ድንግልናዋን ሳይለውጥ ጠበቃት እሱ ድንቅ ድንቅ ሥራን የሚሠራ የባሕርይ አምላክነውና አሁንም እሱ በሰው ዘንድ ከተሠሩ ከታወቁ ከሦስቱ ግብራት ንጹሕ ነው፤ እነዚህም ሩካቤ ዘር የድንግልና መለወጥ ናቸው ሃይ አበ ፻፲÷፳፱
✔️በዚህ ዓለም ካላ ተድላ ሥጋ ተሰደድሽ።
እናቱን ማርያምንም እንሆ የብዙዎች ልብ ዐሳብ ይገለጥ ዘንድ ይህ በእስራኤል ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሟል ባንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል አላት ሉቃ ፪÷፴፭
✔️አንቺ ያልተሰደድሽ ከእግዚአብሔር ብቻ ነው።
መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት መንፈስ ቅዱስ ባንቺ ላይ ይመጣል የልዑልም ኀይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል ሉቃ ፩÷፴፭
መንፈስ ቅዱስ በሥጋ በነፍስ አንጽቶ ያድርብሻል ኀይለ ልዑል ወልድም ከሦስቱ ግብራት ይከለክልሻል።
ሃይ አበ ፹፰÷፫ | 0 |
| 11 | 🇪🇹⚡️በአርሲ፣ አሰኮ ወረዳ ከሰሞኑ በደረሰው ጥቃት ዙርያ መሠረት ሚድያ ከመንግስት ምንጮች እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ያሰባሰበው አዲስ መረጃ!
ህይወታቸው እንዳለፈ የተረጋገጠ= 53
ያሉበት ያልታወቀ ሰዎች= 190
የቆሰሉ= 47
የታገቱና ገንዘብ የተጠየቀባቸው= 6
የተቃጠለ ቤት= 308
የተቃጠለ ቤተክርስቲያን= 2
ተፈናቅለው እሬቻ ማካኤል የተጠለሉ= 789
ተፈናቅለው ሱንቴ ማርያም የተጠለሉ= 691
ተፈናቅለው አሰኮ ከተማ የተቀመጡ= 262
ተፈናቅለው ሌንጫ ኦዳ፣ ወራንቡስ፣ ቦግዶ፣ ኮበሬ የተጠለሉ= 133
ጠቅላላ የተፈናቀሉ= 1,875
*የአካባቢው ነዋሪዎች ዛሬ ለሚድያችን እንደተናገሩት ተኩሱ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ቆሟል፣ ነገር ግን የተፈናቀለው ህዝብ ወደ ቀዬው መመለስ አልቻለም።
| መሠረት ሚድያ |
*-*-*-*-
"ከመንግሥት ምንጮች፣ ከመንግሥት ፍንጮች፣ እንደ መንግሥት ዘገባ …" የሚል ተቀጽላ ያለባቸው መረጃዎችን ከኢትዮጵያ ካነበባችሁ፣ መረጃው የሓሰት ወይም የሚታመን ያልሆነ መረጃ ነው ማለት ነው። የሚነግራችሁ ይሄንን ነው፣ አይታመንም፣ ተዓማኒነቱ ያጠራጥራል፣ አትመኑት! ነው። ካነበባችሁም፣ ያልተፃፈውን፣ በመስመሮች መካከል የማይታየውን፣ እዩ! | 0 |
| 12 | بدون متن... | 0 |
| 13 | بدون متن... | 0 |
| 14 | بدون متن... | 0 |
| 15 | ጥሪያችንንን አድርሱልን
👉ለሀገር ወዳድ እና ለኦርቶዶክሳውያን የጸጽታ አካላት።
◈በብልጽግና ሥርዓት ሀገራችን እና ነባር እምነታችን መጥፋት ከጀመረ እነሆ ስምንት ዓመታት ተቆጠሩ።
◈እናንተ ሀገር ለመጠበቅ የወጣችሁለት ሥርዓት ሀገር የሠሩ ኦርቶዶክሳውያንን ሀገር አልባ አድርጎ ማሳደድ፣ማፈናቀል፣ቤተ መቅደሳችንን ማቃጠል፣..ከጀመረ ስምንት ዓመት ሁኖታል።
👉ሀገር የሚባለው፦
1.)◈ባንድ ሀገረ መንግሥት ጥላ ሥር የሚኖሩ ሕዝቦች፤
2.)◈በነጻ የህሊና ፈቃዳቸው መርጠው የሚያምኑትን ሃይማኖት ማምለክ 3.)የሚችሉ ሕዝቦች፤
4.)◈ማንንም ያላገለለ ሁሉን ያቀፈ ሥርዓተ መንግሥት ያላቸው ሕዝቦች፤
5.)◈ትናንትን የሚያቀብል ሕያው የታሪክ ምሥክር ያላቸው ሕዝቦች፤
6.)◈የተከበረ የታፈረ የሀገር ወሰን ዳር ድንበር፣የሀገር ስያሜ ያላቸው ሕዝቦች፤
7.)◈ያልተበረዘ ያልተከለሰ ያልተዋሱት በራሳቸው ያፈለቁት ቅብብሎሻዊ ባህል ያላቸው ሕዝቦች፤
8.)◈ከትውስት ንጹሕ የሆነ ሰውን ሁሉ ማኖር የሚችል ዕሴት ያላቸው ሕዝቦች፤
9.)◈የዕውቀት ማስተላለፊያ መንገዶች፦ፊደል፣ቁጥር፣የራስ መገለጫ ፍልስፍናዎች ያላቸው ሕዝቦች።
10.)◈የዳበረ የተኖረ ራስ በቅ ማኅበራዊ ፍልስፍና ያላቸው ሕዝቦች፤
11.)◈ውስጣዊ የሀገር አንድነት እና የመንፈስ ነጻነት ያላቸው ሕዝቦች፤
12.◈ሀገር በቀል ሀብቶችን ያነገቡ ራሳቸውን ያበቁ እና ያነቁ ርቱዓን ሕዝቦች፤
13.)◈ፍትህ ርትዕን በትክክል ያለነገድ አድልኦ ያሰፈኑ፣ድሀ ተበደለ ፍርድ ተጓደለ የሚሉ ሕዝቦች።
14.)◈ትንናንትን የሚቀበሉ ዛሬን የሚጠብቁ ለነገው ትውልድ የሚጨነቁ ሕዝቦች።
15.)◈የተፈጥሮ ደንብ እና የጨዋ ሥርዓት ያላቸው ሕዝቦች፤
16.)◈ኅብረታዊነትን የማያስቀጥሉ የመልካምነት መገለጫ የሆኑ የሥነ ሥርጸት ጸጋዎች ያልተቋረጠባቸው ሕዝቦች፤
17.)◈ከእግዚአብሔር እና ከሰው ጋራ፣ከሰውና ከሰው ጋራ፣ከሥነ ፍጥረት እና ከሰው ጋራ ያለው ግንኙነት ያልተቃወሰባቸው ሕዝቦች፤
18.)◈የተፈጥሮ ሕግን የማያዛቡ ሥርዓተ ቤተ ሰብእ እና ሥርዓተ ሕዝብ የተገነባባቸው ሕዝቦች፤
19.)◈አንድ ሰንደቅ እና ትርጉም ያላቸው ሕዝቦች፤
20.)◈የጎደላቸውን የሚቀበሉ ያላቸውን የሚያስቀጥሉ ተዋሕዶ በተዓቅቦ የሆኑ ሕዝቦች፤....እነዚህን እና የመሳሰሉት ያሉት ሀገር እውነተኛ ሀገር ይባላል።
እናተ የምታገልግሉት ሥርዓት እነዚህን ሁሉ ጸጋዎቻችንን ከመጠበቅ ይልቅ ማጥፋት ከጀመረ ስምንት ዓመታት ሁነውታል።
◈እኛ ኦርቶዶክሳውያንም መሳደድ፣መገ.ደል፣መፈናቀል፣መቅደሳችን መንደድ፣ቅርሳችን መው.ደ.ም ከጀመረ ስምንት ዓመታት ተቆጥረዋል።
◈ሀገር ወዳድ ወንድሞቻችን እናንተ የቆማችሀለት ሕዝብና ሀገር የትኛው ነው?
ስለሆነም፦
1.)የመከላከያ አካላት
2.)የፖሊስ አካላት
3.)የደኅንነት አካላት
4.)የሚኒሻ አካላት
5.)የአድማ ብተና አካላት
6.)የልዩ ኃይል አካላት
7.)ለጥበቃ አካላት
8.)ለአየር ኃይል አካላት
9.)ባሕር ኃይል አካላት
10.)ለደንብ አስከባሪ አካላት
የሀገር እና የሃይማኖት ፍቅር ያላችሁ ሁሉ ራሳችሁን ከዚህ ጸረ ሀገር ሥርዓት ለይታችሁ ለሀገራችሁና ለሃይማኖታችሁ ትቆሙ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን ጩኸት ይድረሳችሁ።
ኦርቶዶክሳውያንን የሌሉባት ሀገር፣የሚሳደዱባት ሀገር፣የሚፈናቀሉባት ሀገር፣የሚገደ.ሉ.ባት ሀገር፣ቤተ መቅደሳችን የሚነድባት ሀገር ለእናንተ ምናችሁ ናት? | 0 |
| 16 | بدون متن... | 0 |
| 17 | ትናንትን ማሰብ ዛሬን መገንባት ነገን መኖር👇
➜የታሪክ አትላን ወደ ታሪክ ድፍድፍነት መቀየር የሚቻለው በልጆች ነው።
➜የነገን ሰላም መገንባት የሚቻለው ዛሬ ላይ ልጆችን በአብነት ትምህርት አእምሯቸውን በመገንባት ነው።
➜ዛሬ የምንመኛትን ሀገር ለነገ መቅረጽ የምንችለው የሕጻናትን አእምሮ ዛሬ ላይ በአብነት በመቅረጽ ነው።
➜አእምሮዉ በሀገር በቀል ዕውቀት ማለትም በአብነት ያልተሰራ ትውልድ ሀገርንም ትውልድንም ያፈርሳል።
➜በአብነት ያልተገነባ ትውልድ ማዕበሉ ሞገዱ በተነሳባት ጊዜ ከመስጠም የምተርፍበት መልኅቅ የሌላት መርከብ ማለት ነው።
➜አብነት የሞራል ልዕልና ነው።
➜አብነት የሕይወት መርህ ነው።
➜አብነት የስልጣኔ ቁንጮ ነው።
➜አብነት የዕውቀት መሠረት ነው።
➜አብነት የመኖር ክንፍ ነው።
👉ልጆቹን ለአብነት አብነቱን ለልጆች፨ | 0 |
| 18 | https://t.me/gubaaabetbuneheragedam2018 | 0 |
