በክርስቶስ
779
مشترکین
-124 ساعت
-37 روز
-2230 روز
- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
معدل نمو المشتركين
در حال بارگیری داده...
ኢየሱስ አማላጅ ነው!!!
" የ ኢየሱስ ምልጃ በ መፅሐፍ ቅዱስ "
"ክፍል አንድ"
👉 ምልጃ ማለት በሁለት አካላት መካከል ባለ ጠላትነት ወይም በተፈጠረ አለመስማማት በሌላ ሶስተኛ ወገን የሚቀርብ ፀሎት ፣ልመና እና የማስታረቅ ክንውን ነው።
👉 ምልጃ በ በዳይ እና በ ተበዳይ አካላት የተፈጠረን ግጭት ለመፍታት ሌላ ሶስተኛው ወገን በ በዳዩ ስም ተበዳዩን የሚለምነው ልመና ነው።
👉 አማላጅ ማለት ደግሞ በሁለት የተጣሉ፣ የተራራቁ፣ የተቀያየሙ አካላት መካከል ገብቶ እርቅን ለማምጣት ወይም ለማስታረቅ ምልጃን የሚያቀርብ ነው።
📌 ኢየሱስ አማላጅ ነው ወይም ያማልዳል ሲባል በ ሰው እና በ እግዚአብሔር መካከል የነበረውን ጠላትነት ለመሻር ፣የሰውን ልጅ ከ እግዚአብሔር ጋር ለማስታረቅ ፀሎትን ፣ ልመናን እና ምልጃን የራሱን ደም በማፍሰስ አቅርቦለናል ማለት ነው ።
📌 የ ኢየሱስ ክርስቶስ ምልጃ በ መፅሐፍ ቅዱስ ዉስጥ ከ ብሉይ ኪዳን ጀምረን እስከ አዲስ ኪዳን ያሉትን ከዚህ በታች እንመልከት:-
📌 1). “ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።”
— ኢሳይያስ 53፥12
👉 ነብዩ ኢሳያስ ከ ኢየሱስ ልደት ሰባት መቶ ዓመት አስቀድሞ ስለ ኢየሱስ ምልጃ ተናግሯል።
👉 ኢሳያስ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ ማለቱ ሃጥያተኞች ሳለን አመፃችንን እንዳይቆጥርብን ወደ እግዚአብሔር ለመነልን ።( ሉቃ 23:34)
👉 " ማለደ " የሚለው ቃል የ ዕብራይስጥ አቻው (יַפְגִּֽיעַ׃) ወይም (yap-gî-a‘) የሚል ነው ትርጉሙም አማለደ ማለት ነው።
👉 የ እንግሊዘኛ አቻውም ( made intercession ) የሚል ነው ትርጉሙ ምልጃን አደረገ ማለት ነው።
📌 2).
ኢሳይያስ 59
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁵ እውነትም ታጥቶአል፥ ከክፋትም የራቀ ሰው ለብዝበዛ ሆኖአል። እግዚአብሔርም አየ ፍርድም ስለሌለ ተከፋ።
¹⁶ ሰውም እንደሌለ አየ፥ ወደ እርሱ የሚማልድ እንደሌለ ተረዳ ተደነቀም፤ ስለዚህ የገዛ ክንዱ መድኃኒት አመጣለት፥ ጽድቁም አገዘው።
👉.እግዚአብሔር አምላክ ወደርሱ ምልጃን ሊያቀርብ የሚችል ማንም ሰው እንደሌለ በተረዳ ጊዜ የገዛ ክንዱ (ኢየሱስ ) መድሃኒት አመጣለት አማላጅም ራሱ ልጁ ሆነለት።
📌 3 ).“በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።”
— ዮሐንስ 1፥29
👉 ዮሐንስ ኢየሱስን የ እግዚአብሔር በግ ያለበት ምክንያት በ ሙሴ ሕግ ለ ሀጥያት ስርየት የሚሆነው ከ መንጋው በጎች በደል የሌለበት በግ ስለሆነ ነው
ዘሌዋውያን 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ ማናቸውም ሰው ኃጢአት ቢሠራ፥ እግዚአብሔርም፦ አትሥሩ ካላቸው ትእዛዛት አንዲቱን ቢተላለፍ፥ ባያውቅም፥ ያ ሰው በደለኛ ነው፥ ኃጢአቱንም ይሸከማል።
¹⁸ ነውር የሌለበትን አውራ በግ ከመንጋው ለበደል መሥዋዕት እንደ ግምጋሜህ መጠን ወደ ካህኑ ያመጣዋል ካህኑም ሳያውቅ ስለ ሳተው ስሕተት ያስተሰርይለታል፥ እርሱም ይቅር ይባላል።
¹⁹ እርሱም የበደል መሥዋዕት ነው፤ በእውነት በእግዚአብሔር ፊት በደለኛ ነው።
👉 ስለዚህ ኢየሱስ ለ ምልጃ የሚቀርብ የ አዲስ ኪዳን በግ ነው ስለታረደም አማለደን።
📌 4).ሉቃስ 22
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³¹ ጌታም፦ ስምዖን ስምዖን ሆይ፥ እነሆ፥ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤
³² እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ አማለድሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አጽና አለ።
👉.ጌታ ራሱ ስለ አንተ አማለድኩ ብሎ እንዳማለደ በራሱ አፍ ተናግሯል።
👉."አማለድሁ" የሚለው የ ግሪክ ተመሳሳይ ፍቹ "ἐδεήθην" ወይም " edeēthēn"(ኤዴቴን ) የሚል ሲሆን ቀጥተኛ ፍቺው "መለመን "የሚል ነው።
📌5).ሮሜ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³³ እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን ይከሳቸዋል? የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው፥ የሚኰንንስ ማን ነው?
³⁴ የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።
👉. እዚህ ላይ ጳውሎስ ራሱ" ስለኛ የሚማልደው "ብሎ ኢየሱስ እንደሚያማልድ እና በ ምልጃዉም ጳውሎስ ራሱ ተጠቃሚ እንደሆነ ነግሮናል ።
👉."የሚማልደው" የሚለው ቃል አገላለፁ አንድ ጊዜ ብቻ ተደርጎ ስለምያበቃ ምልጃ ሳይሆን ቀጣይነት ስለሚኖረው ምልጃ መሆኑን ያሳያል ።
👉. "የሚማልደው " የሚለው ቃል የ ግሪኩ ተመሳሳይ ቃሉ " ἐντυγχάνει" (ኢንቱግካኖ)
የሚል ነው ትርጉሙም የሚያማለድ ወይም አማላጅ ማለት ነው ።
👉. እንግሊዘኛውም " interceding" ይላል አማላጅ ማለት ነው ።
👉 የ ግዕዙ ቃል ደግሞ "ወይትዋቀስ በ እንቲአነ " ይላል ትርጉሙም ስለኛ ይከራከራል የሚል ነው ይህም ምልጃውን የሚያሳይ ነው።
📌6).
ዕብራውያን 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²³ እነርሱም እንዳይኖሩ ሞት ስለ ከለከላቸው ካህናት የሆኑት ብዙ ናቸው፤
²⁴ እርሱ ግን ለዘላለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው፤
²⁵ ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል።
👉. ጳውሎስ በሚገርም ሁኔታ የ ኢየሱስን ምልጃ ሲያስረዳ ምልጃው ያለፈ እና ከዚህ በኃላ የማይሰራ አድርገን እንዳናስበው ሲል "ሊያማልድ" ብሎ ነው ቀጣይነቱን የገለፀው።
👉. እዚህ ላይም "ሊያማልድ " ለሚለው ቃል በ ግሪኩ " ἐντυγχάνειν " ( ኢንቱግካኖ ) የሚል ነው ( to intercede ) ይህም ምልጃውን ሚናገር ቃል ነው ።
👉. እዚሁ ቃል ላይ ማወቅ ያለብን ነገር የ ኢየሱስ ምልጃ ከ ብሉይ ኪዳን ካህናት የተለየ መሆኑን ነው የሚለየውም የነሱ ምልጃ የሚለወጥ እና በ ሞት የሚቋረጥ ሲሆን የ ኢየሱስ ግን ማይለወጥ እና ዘላለማዊ ነው ( ዕብ 7: 23-24)
👉. እዚህ ላይ " ሊያማልድ " ለሚለው ቃል ግዕዙ " ተንበለ " ይለዋል ይህም ምልጃውን ሚናገር ነው።
📌7).
1ኛ ጢሞቴዎስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤
⁶ ራሱንም ለሁሉ ቤዛ ሰጠ፥ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ፤
👉. መካከለኛው ማለቱ ኢየሱስ ሰውን እና እግዚአብሔርን ለማስታረቅ በመካከል የገባ ስለሆነ ነው ።
👉. ኢየሱስ የ አዲስ ኪዳን መካከለኛ ያስባለው ምክኒያት ለሰው ልጆች በደል እና ሀጥያት ሲል ያፈሰሰው ደም የሚናገር፣ የሚጮህ እና የሚለምን ስለሆነ ነው ። “የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳችኋል።”
— ዕብራውያን 12፥24
@jjjeesuuss
🤷♀🤷♀🤷♀🤷♀🤷♀🤷♀
✨✨✨✨✨✨✨✨
🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍
@jjjeesuuss
📍እኛ እንኳን አደረሳቹ የምንባባለው የጨዋታውን ውጤት ስለምናውቅ ነው እንጂ ይሄ ቀን ለደቀመዛሙርቱ ጭንቅ ነበር ያው ውጤቱን የሚያውቅ በጨዋታው በሀል በጭንቅት ቁጭ ብድግ አይልም
እንደውም ቁጭ ብድግ ለሚለው ውጤቱን ነግሮ ያረጋጋዋል!!{ወንጌል}
”“በእኔ ሰላም እንዲኖራችሁ፣ ይህን ነግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዟችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።”“
ዮሐንስ 16:33 NASV
#ኢየሱስ_እየተመራ_ይመስላል_ግን_አሸንፏል
#እንኳን_አደረሰን
@jjjeesuuss
❤ 2
👩💻👩💻 #ስለ_መጽሐፍ_ቅዱስ🧑💻🧑💻
❖ የመጀመሪያው መጽሐፍ ቅዱስ የተፃፈው በእብራይስጥ፣ በአረማይክ እና በኮይኔ ግሪክ ቋንቋዎች ነው።
❖ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
• 66 መጽሐፍት
• 1,189 ምዕራፎች
• 31,173 አንቀፆች
• 810,697 ቃላት
• 3,566,480 ፊደላት ይገኛሉ።
❖ በጣም ረጅሙ መጽሐፍ- መዝሙረ ዳዊት ሲሆን
• በጣም አጭሩ መጽሐፍ- ሶስተኛ ዮሐንስ
• በጣም ረጅሙ ምዕራፍ- መዝሙረ ዳዊት 119
• አጭሩ ምዕራፍ መዝሙረ ዳዊት 117 ነው።
❖ የመጽሐፍ ቅዱስ አማካይ ስፍራ መዝሙረ ዳዊት 118:8 ነው።
❖በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የብዙ ሰዎች መጠሪያ የሆነው ስም ዘካሪያስ ነው።
❖ ሙሉው መጽሐፍ ቅዱስ እና የትንቢተ ኢሳይያስ መጽሐፍ አስደናቂ መመሳሰል አላቸው።
ይኸውም፦
• መጽሐፍ ቅዱስ #66 መጽሐፍ ሲኖሩት ትንቢተ ኢሳይያስ #66 ምዕራፎች አሉት።
• የመጀመሪያው #39 የመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍት የሚተርኩት ስለ እስራኤል ህዝብ ነው። እንደዚሁም የመጀመሪያው የትንቢተ ኢሳይያስ #39 ምዕራፎች የሚተርኩት ስለ እስራኤል ህዝቦች ነው።
• የመጨረሻው #27 የመጽሐፍት ቅዱስ መጻህፍት የሚያስተምሩት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፤ እንደዚሁም የመጨረሻዎቹ #27 የትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፎች የሚተርኩት ስለ ክርስቶስ መምጣት ነው።
❖ መጽሐፍ ቅዱስ ተፅፎ ያለቀው በ1600 ዓመታት የጊዜ ልዩነት ውስጥ ሲሆን ይህም ከ1500 ዓመተ ዓለም እስከ 100 ዓመተ ምህረት ድረስ ያለውን ዘመን ያጠቃልላል።
❖ መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው የጻፉት መጽሐፍ ነው።( 2ጴጥ 1:21)
❖ በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ 49 የምግብ ዓይነቶች ተጠቅሰዋል፤ በተለይ "ጨው" #30 ጊዜ ተጠቅሷል።
❖ ከቤት እንሰሳት መካከል ስሟ ያልተጠቀሰ እንሰሳ "ድመት" ብቻ ናት።
ውሻ #14 ጊዜ ተጠቅሷል።
❖ በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ ውስጥ እራሳቸውን በራሳቸው ያጠፉ ሰዎች ሰባት ሲሆኑ
እነርሱም፦
1. አቤሜሌክ
2. ሳምሶን
3. ሳዖል
4. የሳዖል ወታደር
5. አኪጦፌል
6. ዚምራ
7. ይሁዳ ናቸው።
❖ በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ
ስለ ፀሎት 400 ጊዜ
ስለ እምነት 500 ጊዜ
ስለ ገንዘብና ሐብት ደግሞ 2,000 ጊዜ ተፅፏል። መጽሐፍ ቅዱስ ገንዘብን መውደድ የኃጢአት ሁሉ ስር ነው ይለዋል።
❖ መጽሐፍ ቅዱስ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎመው በ 1388 ዓ.ም ነው።
ምንጭ፦ ቅዱሳን መፅሐፍት
@jjjeesuuss
👍 4