fa
Feedback
Ministry of Mines- Ethiopia

Ministry of Mines- Ethiopia

رفتن به کانال در Telegram

ይህ የማዕድን ሚኒስቴር ትክክለኛ የTelegram Channel ነው።

نمایش بیشتر
1 543
مشترکین
-124 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
+230 روز
آرشیو پست ها
photo content

የኢትዮጵያ ወርቅ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ 5 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር የማስገኘት አቅም ፈጥሯል (ሰኔ 30ቀን 2018 ማዕድን ሚኒስቴር)፦ የኢትዮጵያ ወርቅ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ 5 ነጥብ 5 ቢሊየ
የኢትዮጵያ ወርቅ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ 5 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር የማስገኘት አቅም ፈጥሯል (ሰኔ 30ቀን 2018 ማዕድን ሚኒስቴር)፦ የኢትዮጵያ ወርቅ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ 5 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር የማስገኘት አቅም ፈጥሯል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በሰጡት የወርቅ እመርታዊ ውጤቶች ማብራሪያቸው፤ ከ1984 እስከ 2011 ዓ.ም ድረስ በሃያ ሰባት ዓመታት ውስጥ በድምሩ የኢትዮጵያ ወርቅ ከወጪ ንግድ 3 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማስገኘቱን አስታውሰዋል። በአንድ ዓመት ውስጥ ግን ከወርቅ ወጪ ንግድ 5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማገኘት የተቻለበትን አቅም መፍጠሩን አስታውቀዋል። በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበው እመርታ የ27 ዓመታት ሥራን እንደሚበልጥ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ዓይነቱ ስኬት እውነተኛ የዕድገት ማረጋገጫ መሆኑን አስምረውበታል። በኢትዮጵያ ቁጥር ሳይሆን የሚጨበጥና የሚዳሰስ የሚታይም ዕድገት ነው እየመጣ የሚገኘው ብለዋል። ለበለጠ መረጃ ማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችን በመከተል ይወዳጁን ትዊተር፦ https://twitter.com/MinistryofMine_ ድረ ገጽ፦ www.mom.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MinesandPetroleum/ Telegram: - https://t.me/+-aNetmkG-WY2YWM8 Email: info@mom.gov.et

የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ የኢኮኖሚ መዋቅሩን በዘመናዊ መንገድ መቅረጽ እና ማሻሻል የሚያስችሉ ስትራቴጂዎች ተቀርጸው ተግባራዊ ሆነዋል:: (ሰኔ 30 ቀን 2018ማዕድን ሚኒስቴር)፦ የኢትዮጵያን
+2
የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ የኢኮኖሚ መዋቅሩን በዘመናዊ መንገድ መቅረጽ እና ማሻሻል የሚያስችሉ ስትራቴጂዎች ተቀርጸው ተግባራዊ ሆነዋል:: (ሰኔ 30 ቀን 2018ማዕድን ሚኒስቴር)፦ የኢትዮጵያን ብልጽግና እና ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የኢኮኖሚ መዋቅሩን በዘመናዊ መንገድ መቅረጽ እና ማሻሻል የሚያስችሉ ስትራቴጂዎች ተቀርጸው ተግባራዊ መደረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ የኢትዮጵያን ብልጽግና እና ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የኢኮኖሚ መዋቅሩን በዘመናዊ መንገድ መቅረጽ እና ማሻሻል የሚያስችሉ ስትራቴጂዎች ተቀርጸው ወደ ተግባር ገብተዋል። በዚህም ግብርናን በቴክኖሎጂ በማዘመንና ቱሪዝምን በማስፋፋት፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና የውጭ ምንዛሬን ማሳደግ ቀዳሚ ተግባሩ ያደረገው የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ በመተግበር ስኬታማ መሆኑን ገልጸዋል። የዋጋ ንረትን በመቆጣጠር እና የግል ዘርፉን በማበረታታት መዋቅራዊ ለውጥ ማምጣት መቻሉንም ተናግርዋል። ይህ የኢኮኖሚ ለውጥ የዓለም አቀፍ ጫናዎችን የመቋቋም፣ እንቅፋቶችን ወደ ዕድል የመቀየር እና የራስን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበር መርሆዎችን በተግባር እያሳየ እንደሚገኝ ገልጸዋል።   በማዕድን ኢንዱስትሪ ዘርፍ በሲሚንቶ፣ በሴራሚክስ፣በድንጋይ ከሰል ከፍተኛ ውጤት ተመዝግቧል! ድንጋይ አንሸከምም ብለን ሁለት የሴራሚክስ ፋብሪካዎችን መርቀናል፤ሌሎች በቅርቡ የሚመረቁ አሉ፡፡ በለጠ መረጃ ማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችን በመከተል ይወዳጁ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል፡- ምርጫን በሚመለከት 👉 ለየ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል፡- ምርጫን በሚመለከት 👉 ለየትኛውም የፖለቲካ አካል ትምህርት የሰጠ ምርጫ ተካሂዷል። 👉 አትመዝገቡ፣ አትደግፉ፣ አትምረጡ የተባለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ማስፈራሪያዎችን ትቶ በንቃት በምርጫው ተሳትፏል። 👉 ምርጫ በማይወዱ አካላት ምርጫው ራሱ እንዳይከናወን የጥቃት ዒላማ ተደርጎ ነበር፤ ነገር ግን በስኬት ተጠናቋል። 👉 የኢትዮጵያ ሕዝብ ባደረገው የተባበረ ክንድ ለሀገሩ መጻዒ ዕድል ላደረገው አበርክቶ ከፍተኛ ክብር ይገባዋል። 👉 ኢትዮጵያውያን በአንድ ድምጽ ለሀገራቸው የሚበጀውን አሳውቀዋል፤ ለሀገራቸው የማይበጀውን ደግሞ አልሰሙም። 👉 አዛውንቶች፣ የወለዱ እናቶች፣ በህመም ላይ ያሉ ሰዎች፣ ጥይት እየተተኮሰባቸው ብሎም ምቹ ባልሆኑ ሁኔታዎች ጭምር ሆነው ኢትዮጵያውያን በምርጫው በንቃት ተሳትፈዋል። ለበለጠ መረጃ ማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችን በመከተል ይወዳጁን ትዊተር፦ https://twitter.com/MinistryofMine_ ድረ ገጽ፦ www.mom.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MinesandPetroleum/ Telegram: - https://t.me/+-aNetmkG-WY2YWM8 Email: info@mom.gov.et

ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያቀረቡላቸውን ጥያቄዎች ⁉️ ✍️ በከተሞች በተለይም በዝቅተኛ ገቢ የሚኖሩ ዜጎች የመኖሪያ ቤት እጥረትና የኪራይ ውድነት ጫናን
+3
ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያቀረቡላቸውን ጥያቄዎች ⁉️ ✍️ በከተሞች በተለይም በዝቅተኛ ገቢ የሚኖሩ ዜጎች የመኖሪያ ቤት እጥረትና የኪራይ ውድነት ጫናን በዘላቂነት ለመፍታት የመንግስትና የግሉ ዘርፍ እንዲሁም የማህበረሰብና የፋይናንስ ተቋማትን የሚያስተባብር ስትራቴጂ ተቀርጿል? ✍️ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተጀመሩ በርካታ የፌደራል መንገዶች፣ የመስኖ ፕሮጀክቶች፣ የኤሌክትሪክ እና የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በጸጥታ ችግሮች፣ በተቋራጮች አቅም ማነስ፣ በፋይናንስ እጥረት እና በካሳ ክፍያ መጓተት ምክንያቶች ተቋርጠው ወይም ሳይጠናቀቁ ይገኛሉ።በአሁኑ ወቅት የተጓተቱ ወይም በዝግታ እየተከናወኑ ያሉትን ወሳኝ የህዝብ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች በተጨባጭ የጊዜ ሰሌዳ ለማጠናቀቅ የተያዘው ሀገራዊ አቅጣጫ ምንድነው? ✍️ መንግስት ለዜጎች ዘመናዊ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ጥረት እያደረገ ቢሆንም በተለያዩ የጤና ተቋማት ውስጥ የሚየውን የህክምና መሳሪያ እጥረትና የአገልግሎት ክፍተት የህዝብ ዋነኛ ቅሬታ ሆነዋል፤ የመዲሀኒት አቅርቦት ችግር፣ የህክምና መሳሪዎችን እጥረትና እየተከሰቱ ያሉ የወረርሽኝ ስጋቶችን ለመቀነስ ምን አይነት ተጨባጭ እርምጃዎች እየወሰደ ይገኛል? ✍️ ወደውጭ የሚላኩ የሪፌራል ህክምናዎችን በሀገር ውስጥ አቅም የመተካት ብሎም ሜዲካል ቱሪዝምን ለማስፋፋት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ላይ ማብራራሪያ ቢሰጥ? ✍️ ኢትዮጵያዊ በለዉጥና በሽግግር ባለችበት በዚህ ወቅት መንግስት ጽፈንኝነትን ለመግታትና ሰላምን ለማናስፈን በወሰዳቸዉ ተከታታይ እርምጃዎች እጅግ በበርካታ አካባቢዎች ሰላም ሰፍኗል ።ይህ አንጻራዊ የሰላም ድባብ ሰባተኛዉ ጠቅላላ ምርጫ በአብዛኛዉ አካባቢ ሰላማዊና የተሳካ እንዲሆን ወሳኝ ሚና ተጫዉቷል።ይሁን እንጂ በአንዳንድ ኪስ አካባቢዎች አልፎ አል

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ እና ምላሽ ይሰጣሉ ************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት (ሰኔ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ እና ምላሽ ይሰጣሉ ************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት (ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም) የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባሉ። በ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይም ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሡ ጥያቄዎች ማብራሪያ እና ምላሽ ይሰጣሉ። ለበለጠ መረጃ ማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችን በመከተል ይወዳጁን ትዊተር፦ https://twitter.com/MinistryofMine_ ድረ ገጽ፦ www.mom.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MinesandPetroleum/ Telegram: - https://t.me/+-aNetmkG-WY2YWM8 Email: info@mom.gov.et See less

የማዕድን_ሚኒስትር_ኢንጅነር_ሀብታሙ_ተገኘ_በአርባምንጭ_ኮንፈረንስ_ሪዞርት_ምረቃ_ላይ_ያስተላለፉት_መልዕክት

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት፡- የሀገር ውስጥ ምርትን በራስ አቅም ማሳደግ የኢኮኖሚ ነጻነታችን እና የሉዓላዊነታችን መሰረት ነው። ‎ ‎ዛሬ በጋሞ ዞን የጎበኘነውና
+4
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት፡- የሀገር ውስጥ ምርትን በራስ አቅም ማሳደግ የኢኮኖሚ ነጻነታችን እና የሉዓላዊነታችን መሰረት ነው። ‎ ‎ዛሬ በጋሞ ዞን የጎበኘነውና በወርሃ ነሐሴ 2017 ዓ.ም ሥራ የጀመረው 'ዮ ሆልዲንግ’ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ፤ የኢንዱስትሪዎቻችንን ፍላጎት በሀገር ውስጥ በመተካት ከውጭ የሚገባ ምርትን ያስቀረ ሲሆን ለአካባቢው ነዋሪዎችም የሥራ ዕድል ፈጥሯል። ‎ ‎የሀገራችንን የተፈጥሮ ሀብት በጠንካራ ስራ በሀገር ውስጥ በማልማት የኢኮኖሚ ልዕልናችንን የምናረጋግጥበት ጉዞ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ለበለጠ መረጃ ማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችን በመከተል ይወዳጁን ትዊተር፦ https://twitter.com/MinistryofMine_ ድረ ገጽ፦ www.mom.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MinesandPetroleum/ Telegram: - https://t.me/+-aNetmkG-WY2YWM8 Email: info@mom.gov.et

የማዕድን ሚኒስቴር አመራሮች እና ሠራተኞች የ2018 ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2019 ዕቅድን ገመገሙ፡፡ (ሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ማዕድን ሚኒስቴር) የማዕድን ሚኒስቴር አመራሮች እና ሠራተኞች  የተቋሙን የ2018 ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2019 ዕቅድ ገመገሙ፡፡ የዘርፉ የዲታላይዜሽን ስራዎችም ቀርበው ውይይት ተደርጎበታል፡፡ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት 12 ወራት የተከናወኑ ተግባራት ቀርበው ተገምግመዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በዘርፉ ከፍተኛ ውጤት  ማስመዝገብ ተችሏል፡፡ የተመዘገበውን ውጤት ለማስቀጠልም የአመራሩና የሰራተኛው ቅንጅት ወሳኝ መሆኑ በውይይቱ ተነስቷል፡፡   የዘርፉ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በዝርዝር ቀርቦ የተገመገመ ሲሆን በ2018 የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል እና የታዩ ክፍተቶችን በመለየት  ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራባቸውን ስራዎችን ለመለየት ያስችላል ተብሏል፡፡በግምገማው አፈጻጸምና ዕቅድ ዙሪያ የጋራ ውይይት መደረጉ ስራዎችን ተግባብቶ በጋራ ለመስራት እንደሚያስችል ተሳታፊዎቹ ተናግረዋል፡፡ አመራሩና ሠራተኛው በቅንጅት መስራት እና ዕቅዱን የጋራ በማድረግ  ለመስራትም ያስችላል፡፡   በመድረኩ ተቋሙ እየተሰሩ ያሉ የዲጂታላይዜሽን ስራዎችም ቀርበው ተገምግመዋል፡፡ የማዕድን ዘርፍ የዲጂታላይዜሽን ስራዎች ከሐገራዊ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 መነሻ በማድረግ በተቋሙ የሚተገበሩ ናቸው፡፡ዲጂታላይዜሽን የወረቀት ስራዎችን በማስቀረት የተቋሙን አገልግሎት ፈጣን እና ቀልጣፋ ለማድረግ ዋነኛ ግብ መሆኑም ተጠቅሷል፡፡ የመድረኩ ተሳታፊ አመራሮችና ሠራተኞች በግምገማው  ጥያቄዎች፣አስተያየቶች እና ግብዓቶችን በማንሳት ማብራሪያ የተሰጠባቸው ሲሆን በዕቅዱ ላይ የጋራ መግባባት ተፈጥሯል፡፡የቀጣይ የስራ አቅጣጫዎች እና መመሪያዎችም  ተሰጥተዋል፡፡ ለበለጠ መረጃ ማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችን በመከተል ይወዳጁን ትዊተር፦ https://twitter.com/MinistryofMine_ ድረ ገጽ፦ www.mom.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MinesandPetroleum/ Telegram: - https://t.me/+-aNetmkG-WY2YWM8 Email: info@mom.gov.et

photo content
+2

photo content
+4

ካዳስተር በማዕድን ዘርፉ የሚሰጡ ፈቃዶችን እና አገልግሎቶችን የሚያቀላጥፍ መሆኑ ተገለጸ፡፡ (ሰኔ17 ቀን 2018 ማዕድን ሚኒስቴር) የማዕድን ሚኒስቴር ከሁሉም ክልል ለተውጣጡ የማዕድን ቢሮ ባለሙያዎ
+7
ካዳስተር   በማዕድን ዘርፉ የሚሰጡ ፈቃዶችን እና አገልግሎቶችን የሚያቀላጥፍ መሆኑ ተገለጸ፡፡ (ሰኔ17 ቀን 2018 ማዕድን ሚኒስቴር) የማዕድን ሚኒስቴር ከሁሉም ክልል ለተውጣጡ የማዕድን ቢሮ ባለሙያዎች የካዳስተር ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡ የማዕድን ፈቃድ አሰጣጥ ከፌዴራል እስከ ክልል የተናበበ እና ወጥነት እንዲኖረው ለማድረግ ካዳስተር ዋነኛ መሳሪያ ነው፡፡ ስልጠናውን የከፈቱት የማዕድን ሃብት ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ብርሐኔ ያዴሳ መንግስት ባደረገው የሃገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን እና በዘርፉ የተመዘገበውን ውጤት ማስቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ካዳስተር ወጥነት ያለው የማዕድን ፈቃድ አሰጣጥ በመከተል የአገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑንም አቶ ብርሐኔ  ተናግረዋል፡፡ የካዳስተር ሲስተም ከፌዴራል እስከ ክልል በወጥነት በመጠቀም ዲጂታል 2030 በዘርፉ ቀድሞ ዕውን ለማድረግ የሚያስችል አገልግሎት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በስልጠናው ስለ ማዕድን ፈቃድ አሰጣጥ፣ ስለ ማዕድን ሕጎችና የአካባቢ ጥበቃ ዙሪያ የሚሰጥ ሲሆን ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ ከፍተኛ የማዕድን ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ የስልጠናው ተሳታፊዎችም ስልጠናው የካዳስተር ሲስተምን በአግባቡ በየደረጃው ለመተግበር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለበለጠ መረጃ ማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችን በመከተል ይወዳጁን Twitter፦ https://twitter.com/MinistryofMine_ Website ፦ www.mom.gov.et Facebook፡- https://www.facebook.com/MinesandPetroleum/ Telegram: - https://t.me/+-aNetmkG-WY2YWM8

+5
IMG_8490.JPG1.77 MB

IMG_8426.JPG1.79 MB

በዘርፉ እየተከናወኑ ባሉ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ላይ የተሰሩ ስራዎች ቀርበው ውይይት ተካሄደ፡፡ ********************* (ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ማዕድን ሚኒስቴር) በማዕድን ዘርፍ እየተከናወነ ባለው የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የተከናወኑ ተግባራት ለተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ቀርበው ውይይት ተደረገባቸው፡፡የማዕድን ዘርፍ  በሁለተኛው ምዕራፍ (Wave 2) ወደ ሪፎርም መግባቱም ይታወቃል፡፡   የማዕድን ዘርፍ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት እና ማስፈጸሚያ ሰነዶች በየተዘጋጁበት አምድ ለማዕድን ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች ቀርበው  ውይይት ተካሂዷል፡፡   በማዕድን ዘርፍ ሪፎርም አጠቃላይ  ተግባራት ክንውን ፣ በአስተዳደራዊ ማሻሻያ(ኦዲት፣ ግዥና የስነ-ምግባር ኮድ) እና  መሰረታዊ ማሻሻያ (ፖሊሲ፣ስትራቴጂ ፣ አዋጆች እና ደንቦች) በዝርዝር ቀርበዋል፡፡ ለሪፎርሙ ትግበራ የዘርፉ ፖሊሲ ዝግጅት ዋና መሳሪያ መሆኑ  በውይይቱ ተጠቅሷል፡፡   ሪፎርሙ ሰባት አምዶች  ያሉት ሲሆን የመንግስት አስተዳደርና አደረጃጀት፣ የመንግስት ሠራተኞች የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ስርዓት መገንባት፣ ነጻና ገለልተኛ የአሰራር ስርዓት ማሳለጥ፣ ቀልጣፋና ተደራሽየአገልግሎት አቅርቦት ስርዓት መዘርጋት፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ብዝሃነትና አካታችነት፣ን ማረጋገጥ እና ገቢር ነበብ አመራርና ተቋም ግንባታን ማፋጠን ናቸው፡፡ በሁሉም አምዶች የተከናወኑ ተግባራት እና ቀሪ ስራዎች ቀርበዋል፡፡      ሪፎርሙ  የፐብሊክ ሰርቪስ ዘርፍን በማዘመን፣ አገራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራሙ አራት ምሰሶዎች (Pillars) አንዱ በመሆኑ በመንግስት ተቋማት ውስጥ ያለውን ውስብስብ ቢሮክራሲ በማስወገድ፣ በብቃት ላይ የተመሠረተ የሰው ኃይል ለመገንባት ያለመ ነው።   በሪፎርሙ የዝግጅት ምዕራፍ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች እየተዘጋጁ ሲሆን፤ የሪፎርም ፖሊሲው፣ አዋጁ እና  ስትራቴጂዎች ዝግጅትን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል፡፡ ለማዕድን ዘርፍ ሪፎርም ውጤታማነት  ሁሉም አመራርና ሠራተኛ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ በውይይቱ ተነስቷል፡፡ ለበለጠ መረጃ ማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችን በመከተል ይወዳጁን Twitter፦ https://twitter.com/MinistryofMine_ Website ፦ www.mom.gov.et Facebook፡- https://www.facebook.com/MinesandPetroleum/ Telegram: - https://t.me/+-aNetmkG-WY2YWM8

photo content
+6

photo content