fa
Feedback
6 Kilo Muslim Students' Jeme'ah Official Channel

6 Kilo Muslim Students' Jeme'ah Official Channel

رفتن به کانال در Telegram

Welcome to the 6 Kilo Muslim Students Jemea Official Telegram Channel! This channel serves as the primary source of information and updates for Muslim students at Main and FBE campuses. Join our discussion group https://t.me/+XuCYoS85wvhiZmVk

نمایش بیشتر
368
مشترکین
+324 ساعت
+247 روز
+7430 روز
آرشیو پست ها
ወንድም አንዋር ዩሱፍ(የሶፍያ ልጅ) "የሙስሊም ተማሪዎች ህይወት በዩኒቨርሲቲ ቆይታ፡ ከፍሬሽ እስከ ጂሲ" ሲል በሰየመው መጽሐፉ ውስጥ 'በጀመዓ ጉያ' ከተሰኘች ንዑስ ርዕስ ሥር ሳነብ ያገኘኋትን አጠር ያለች ግጥም ልጋብዛችሁ። ተማሪን ሰብስቦ አቅፎና ደግፎ ይታደጋቸዋል ከሐራም ከመጥፎ ዲኑንም ተምረው አውቀው እንዲወጡ ከዒልሙ ገበታ አካፍለው ሚሰጡ ለኡማው በሙሉ ጠቃሚ እንዲሆኑ ባልባሌ ቦታ ውለው እንዳይመክኑ ዘብ ሆኖ ይቆማል በሄዱበት ሁሉ። መስጂድ አዘውትረው ሰላት እንዲሰግዱ ቁርአን ኪታቡን ቀርተው እንዲሄዱ ጉዞ እንዲቀላቸው የህይወት መንገዱ። ኪሱ ባይሞላለት ቢቸገር ተማሪ ሀንዳውቱን ሊገዛ ቢያጣ አበዳሪ ጀመዓው አለለት ችግሩን ተጋሪ የተማሪው አጋር የቅርብ ተጠሪ። አልገባህ እያለ ትምህርቱ ቢከብደው አሳይመንቱ ከብዶት ጉልበቱን ቢያርደው ቱቶር ያዘጋጃል ተማሪ እንዲረዳው። ህመም ቢጠናበት ከቤተሰብ ርቆ ህክምና ተቋም ያሳክማል ወስዶ። ጀመዓን መጠጋት መቅረብን ልመዱ በዲኑ ጠንክሩ ዒልሙንም ውሰዱ። ዒልሙንም ለመቅሰም ዕድሉ ያላችሁ ጊቢ ላይ መሆኑን በሚገባ አውቃችሁ ተግታችሁ ልፉ ሁሌም በርትታችሁ።

𝐈𝐫𝐫𝐚 𝐝𝐞𝐞𝐛𝐢𝐢𝐧 𝐞𝐞𝐛𝐛𝐢𝐟𝐚𝐦𝐭𝐨𝐨𝐧𝐧𝐢 𝐤𝐞𝐞𝐧𝐲𝐚 𝐛𝐚𝐠𝐚 𝐠𝐚𝐦𝐦𝐚𝐝𝐝𝐚𝐧! 𝐫𝐚𝐛𝐛𝐢𝐢𝐧 𝐝𝐚𝐚𝐧𝐝𝐢𝐢 𝐦𝐢𝐥𝐤𝐢𝐢 𝐠𝐚𝐧𝐝𝐚 𝐥𝐚𝐦𝐚𝐚𝐧𝐢𝐢 𝐢𝐬𝐢𝐧 𝐡𝐚𝐚 𝐡𝐚𝐲𝐲𝐢𝐬𝐮! 𝓐𝓵𝓲𝓯

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته‼️ ውድ የ 6-ኪሎ ጀመዓ አባላት፣ በተለይም በጀመዓው ዉስጥ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትሉ፣ከአመራርነት እስከ አባልነት ስታገለግሉ የቆያችሁ ተመራቂ ወንድምና እህቶቼ፣ወደ ቀጣዩ የህይወታችሁ ወሳኝ ምዕራፍ የምትሸጋገሩበት እርከን ላይ በመድረሳችሁ እንኳን ደስስስ አላችሁ! ደስ ብሎኛል! በቀጣዩ የህይወታችሁ ምዕራፍም ልክ እንደ በፊቱ ሁሉ፣ለኡማው ብሎም ለሃገር የሚጠቅሙ ስራዎችን እንደምትሰሩ ተስፋዬ ነው። አስከትዬ ለሁሉም የ አንደኛ አመት ተማሪ ወንድምና እህቶቼ፥ እንደሚታወቀው ከሳምንታት በፊት የጀመዓችንን ሙሉ ሃላፊነት በጋራ ተቀብለን ለቀናት ሃላፊነታችንን ለመወጣት ጥረት አድርገናል።ሆኖም በአማካኝ ከአንድ ወር እስከ ወር ከግማሽ እንቆያለን በሚል ብዙ አዳዲስና በፊትም ዪሰራባቸው የነበሩ ስራዎችን ለመስራት እቅዶችን አውጥተን ወደተግባር ለመቀየር ብንንቀሳቀስም ሦስት ሳምንታት ባልሞሉ የስራ ገዜያት ዉስጥ ግቢዉን እንድንለቅ ተደርጓል። የግዜው ማጠርና አንዳንድ እንደጀማሪ የተስተዋሉብን ስህተቶች ቢኖሩም፣ደስ የሚል የስራ ተነሳሽነትና ባቀድነው ልክ ባይሆንም እንኳ፣ጥሩ አፈጻጸም ነበረን ብዬ አምናለሁ። በአጠቃላይ እጅግ ደስ የሚል ቆይታ ነበረን።አላህ ለኔ ነው ይለን ዘንድ ዱዓችን ይሁን እላለሁ።በዚሁ አጋጣሚ ታከተኝ ሳትሉ ባላችሁ አቅም ሁሉ ለሰራችሁ ወንድም እህቶቼ፣እንደ አንድ ሃላፊነት እንደነበረበት ሰው ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።በቀጣይ ከእረፍት መልስ በአዲስ መንፈስ፣በጀመዓው የዉስጥ አሰራር ባየናቸው ክፍተቶችና ባገኘናቸው ልምዶች ጠንክረን እንደምንሰራ ተስፋ አደርጋለሁ።መልካም የእረፍት ጊዜ! ለሁሉም የ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች መልካም የእረፍት ጊዜ እመኝላችኋለሁ።አላህ በሰላም ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ይመልሰን! በድጋሜ ለተመረቃችሁ ወንድሞቼ እንኳን ደስ አላችሁ! ለሁለቱም ዓለም ስኬት የምትሰንቁበት ወሳኝ ጊዜ ነዉና አላህ ከናንተ ጋር ይሁን! 𝐀𝐬𝐬𝐚𝐥𝐚𝐚𝐦𝐮 𝐀𝐥𝐚𝐲𝐤𝐮𝐦 𝐰𝐚𝐫𝐚𝐡𝐦𝐚𝐭𝐮𝐥𝐥𝐚𝐚𝐡𝐢 𝐰𝐚𝐛𝐚𝐫𝐚𝐤𝐚𝐚𝐭𝐮𝐡! 𝐇𝐮𝐧𝐝𝐚 𝐝𝐮𝐫𝐚 𝐨𝐛𝐛𝐨𝐥𝐨𝐨𝐭𝐚 𝐤𝐨𝐨 𝐤𝐢𝐢𝐥𝐨𝐨-𝐣𝐚𝐡𝐚𝐚 𝐬𝐢𝐫𝐧𝐚 𝐞𝐞𝐛𝐛𝐚 𝐛𝐚𝐫𝐚𝐧𝐚𝐚𝐭𝐢𝐢𝐧 𝐠𝐞𝐞𝐭𝐭𝐚𝐧 𝐡𝐮𝐧𝐝𝐚𝐚𝐧 𝐛𝐚𝐠𝐚 𝐠𝐚𝐦𝐦𝐚𝐝𝐝𝐚𝐧 𝐣𝐞𝐜𝐡𝐮𝐮 𝐛𝐚𝐫𝐛𝐚𝐚𝐝𝐚. 𝐊𝐞𝐞𝐬𝐬𝐚𝐭𝐭𝐮𝐮 𝐰𝐚𝐫𝐫𝐨𝐨𝐧𝐧𝐢 𝐬𝐨𝐜𝐡𝐢𝐢 𝐣𝐚𝐦𝐚'𝐚𝐚 𝐤𝐞𝐞𝐬𝐬𝐚𝐭𝐭𝐢 𝐠𝐚𝐡𝐞𝐞 𝐠𝐮𝐝𝐝𝐚𝐚 𝐭𝐚𝐩𝐡𝐚𝐜𝐡𝐚𝐚 𝐭𝐮𝐫𝐭𝐚𝐧, 𝐨𝐟 𝐝𝐮𝐫𝐚𝐚𝐟𝐢𝐬 𝐪𝐚𝐚𝐦𝐚 𝐟𝐮𝐫𝐦𝐚𝐚𝐭𝐚𝐚 𝐫𝐚𝐤𝐤𝐨𝐨𝐥𝐞𝐞 𝐮𝐦𝐦𝐚𝐧𝐧𝐢 𝐤𝐞𝐞𝐧𝐲𝐚 𝐤𝐞𝐞𝐬𝐬𝐚 𝐣𝐢𝐫𝐮𝐮 𝐚𝐤𝐤𝐚 𝐭𝐚𝐚𝐭𝐚𝐧 𝐚𝐛𝐝𝐢𝐢 𝐠𝐮𝐝𝐝𝐚𝐚 𝐪𝐚𝐛𝐚. 𝐈𝐭𝐭𝐢 𝐚𝐚𝐧𝐬𝐮𝐮𝐧 𝐛𝐚𝐫𝐚𝐭𝐭𝐨𝐨𝐭𝐚 𝐰𝐚𝐠𝐠𝐚𝐚 𝐣𝐚𝐥𝐪𝐚𝐛𝐚𝐚𝐭𝐢𝐢𝐟 𝐞𝐫𝐠𝐚𝐚𝐧 𝐪𝐚𝐛𝐮:𝐚𝐤𝐤𝐮𝐦𝐚 𝐛𝐞𝐞𝐤𝐚𝐦𝐮 𝐭𝐨𝐫𝐛𝐞𝐞 𝐬𝐚𝐝𝐢 𝐝𝐮𝐫𝐚 𝐢𝐭𝐭𝐢 𝐠𝐚𝐚𝐟𝐚𝐭𝐚𝐦𝐮𝐦𝐦𝐚𝐚 𝐠𝐮𝐮𝐭𝐮𝐮 𝐣𝐚𝐦𝐚'𝐚𝐚 𝐤𝐞𝐞𝐧𝐲𝐚𝐚 𝐢𝐦𝐚𝐚𝐧𝐚𝐚𝐝𝐡𝐚𝐚𝐧 𝐰𝐚𝐥𝐢𝐢𝐧 𝐟𝐮𝐝𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐞, 𝐡𝐨𝐣𝐢𝐢𝐥𝐞𝐞 𝐝𝐮𝐫𝐚 𝐡𝐨𝐣𝐣𝐚𝐭𝐚𝐦𝐚𝐧 𝐢𝐫𝐫𝐚𝐭𝐭𝐢 𝐝𝐚𝐛𝐚𝐥𝐮𝐮𝐧 𝐡𝐨𝐣𝐢𝐢𝐥𝐞𝐞 𝐡𝐚𝐚𝐫𝐚𝐰𝐚 𝐤𝐚𝐫𝐨𝐨𝐫𝐬𝐢𝐧𝐞𝐞 𝐡𝐨𝐣𝐢𝐭𝐭𝐢 𝐡𝐢𝐢𝐤𝐮𝐮𝐟 𝐡𝐚𝐦𝐦𝐚 𝐝𝐚𝐧𝐝𝐞𝐞𝐧𝐲𝐮 𝐜𝐚𝐫𝐫𝐚𝐚𝐪𝐚𝐚 𝐭𝐮𝐫𝐫𝐞𝐞𝐫𝐫𝐚. 𝐇𝐚𝐚 𝐭𝐚'𝐮𝐮𝐭𝐢𝐢 𝐭𝐮𝐫𝐭𝐢𝐢𝐧 𝐧𝐮𝐭𝐢 𝐭𝐚𝐚𝐬𝐢𝐟𝐧𝐞 𝐚𝐤𝐤𝐚 𝐲𝐚𝐚𝐝𝐚𝐦𝐞 𝐣𝐢'𝐚 𝐭𝐨𝐤𝐤𝐨 𝐲𝐨𝐨𝐤𝐢𝐢𝐧 𝐭𝐨𝐤𝐤𝐨𝐨𝐟 𝐰𝐚𝐥𝐚𝐤𝐤𝐚𝐚 𝐨𝐬𝐨𝐨 𝐡𝐢𝐧 𝐭𝐚'𝐢𝐧 𝐡𝐚𝐟𝐞𝐞 𝐭𝐨𝐫𝐛𝐞𝐞 𝐬𝐚𝐝𝐢 𝐤𝐚𝐧 𝐡𝐢𝐧𝐠𝐮𝐮𝐧𝐧𝐞 𝐪𝐨𝐟𝐚 𝐡𝐨𝐣𝐢𝐢𝐫𝐫𝐚𝐭𝐭𝐢 𝐝𝐚𝐛𝐚𝐫𝐬𝐢𝐧𝐞. 𝐒𝐚𝐛𝐚𝐛𝐚 𝐤𝐚𝐧𝐚𝐚𝐧 𝐤𝐚𝐫𝐨𝐨𝐫𝐚 𝐤𝐞𝐞𝐧𝐲𝐚 𝐡𝐚𝐦𝐦𝐚 𝐛𝐚𝐫𝐛𝐚𝐚𝐧𝐧𝐮 𝐦𝐢𝐥𝐤𝐞𝐞𝐬𝐬𝐮𝐮 𝐡𝐢𝐧𝐝𝐚𝐧𝐝𝐞𝐞𝐧𝐲𝐞. 𝐇𝐚𝐚𝐭𝐚'𝐮𝐮𝐭𝐢𝐢,𝐭𝐮𝐫𝐭𝐢𝐢 𝐠𝐚𝐛𝐚𝐚𝐛𝐝𝐮𝐮 𝐭𝐚𝐧𝐚 𝐤𝐞𝐞𝐬𝐬𝐚𝐭𝐭𝐢 𝐲𝐨𝐨 𝐫𝐚𝐛𝐛𝐢 𝐟𝐞𝐝𝐡𝐞 𝐡𝐨𝐣𝐢𝐢𝐥𝐞𝐞 𝐠𝐚𝐠𝐠𝐚𝐚𝐫𝐢𝐢 𝐡𝐞𝐝𝐝𝐮 𝐡𝐨𝐣𝐣𝐚𝐧𝐧𝐞𝐞𝐫𝐫𝐚 𝐣𝐞𝐝𝐡𝐞𝐞 𝐲𝐚𝐚𝐝𝐚. 𝐂𝐚𝐫𝐫𝐚𝐚 𝐤𝐚𝐧𝐚𝐚𝐧 𝐨𝐛𝐛𝐨𝐥𝐨𝐨𝐭𝐚 𝐤𝐨𝐨 𝐡𝐚𝐥𝐤𝐚𝐧𝐢𝐢 𝐠𝐮𝐲𝐲𝐚𝐚 𝐨𝐬𝐨𝐨 𝐡𝐢𝐧𝐧𝐮𝐟𝐟𝐢𝐧 𝐲𝐞𝐫𝐨𝐨 𝐟𝐢 𝐡𝐮𝐦𝐧𝐚 𝐤𝐞𝐞𝐬𝐬𝐚𝐧 𝐚𝐚𝐫𝐬𝐚𝐚 𝐠𝐨𝐨𝐭𝐚𝐧 𝐫𝐚𝐛𝐛𝐢𝐢𝐧 𝐬𝐢𝐧𝐢𝐫𝐫𝐚𝐚 𝐡𝐚𝐚𝐪𝐞𝐞𝐛𝐚𝐥𝐮,𝐰𝐚𝐚𝐧 𝐬𝐚𝐧 𝐜𝐚𝐚𝐥𝐮 𝐛𝐚𝐤𝐤𝐚 𝐬𝐢𝐧𝐢𝐢𝐟 𝐡𝐚𝐚𝐛𝐮𝐮𝐬𝐮.𝐰𝐚𝐧𝐭𝐢 𝐝𝐡𝐚𝐚𝐦𝐮 𝐲𝐨𝐨 𝐣𝐢𝐫𝐚𝐚𝐭𝐞, 𝐤𝐚𝐧𝐚 𝐛𝐨𝐨𝐝𝐚𝐬 𝐜𝐚𝐚𝐥𝐚𝐚𝐭𝐭𝐢 𝐣𝐚𝐦𝐚'𝐚𝐚𝐭𝐭𝐢 𝐝𝐡𝐢𝐲𝐚𝐚𝐧𝐧𝐞𝐞, 𝐰𝐚𝐧𝐭𝐨𝐨𝐭𝐚 𝐚𝐤𝐤𝐚 𝐡𝐚𝐧𝐪𝐢𝐧𝐧𝐚𝐚𝐭𝐭𝐢 𝐚𝐠𝐚𝐫𝐫𝐞 𝐟𝐮𝐫𝐮𝐮𝐝𝐡𝐚𝐚𝐟 𝐡𝐚𝐦𝐦𝐚 𝐝𝐚𝐧𝐝𝐞𝐞𝐧𝐲𝐮𝐮𝐧 𝐭𝐚𝐭𝐭𝐚𝐚𝐟𝐚𝐜𝐡𝐮𝐮 𝐝𝐚𝐧𝐝𝐚'𝐮𝐮 𝐪𝐚𝐛𝐧𝐚. 𝐃𝐡𝐮𝐦𝐚𝐫𝐫𝐚𝐭𝐭𝐢 𝐫𝐚𝐛𝐛𝐢𝐢𝐧 𝐟𝐚𝐲𝐲𝐚𝐚 𝐠𝐮𝐮𝐭𝐮𝐮𝐝𝐡𝐚𝐚𝐧 𝐰𝐚𝐥𝐢𝐭𝐭𝐢 𝐧𝐮𝐡𝐚𝐚𝐝𝐞𝐞𝐛𝐢𝐬𝐮! 𝐛𝐨𝐪𝐨𝐧𝐧𝐚𝐚 𝐠𝐚𝐚𝐫𝐢𝐢 𝐬𝐢𝐧𝐢𝐢𝐟 𝐡𝐚𝐰𝐰𝐚! 𝐁𝐚𝐫𝐚𝐭𝐭𝐨𝐨𝐧𝐧𝐢 𝐦𝐮𝐬𝐥𝐢𝐦𝐚𝐚 𝐲𝐮𝐧𝐢𝐯𝐚𝐫𝐬𝐢𝐢𝐭𝐢𝐢 𝐟𝐢𝐧𝐟𝐢𝐧𝐧𝐞𝐞 𝐡𝐮𝐧𝐝𝐢 𝐛𝐨𝐪𝐨𝐧𝐧𝐚𝐚 𝐠𝐚𝐚𝐫𝐢𝐢 𝐚𝐤𝐤𝐚 𝐪𝐚𝐛𝐚𝐚𝐭𝐭𝐚𝐧 𝐬𝐢𝐧𝐢𝐢𝐟 𝐡𝐚𝐰𝐰𝐚! 𝐑𝐚𝐛𝐛𝐢𝐢𝐧 𝐧𝐚𝐠𝐚𝐲𝐚𝐚𝐧 𝐛𝐚𝐫𝐚 𝐡𝐚𝐚𝐫𝐚𝐚𝐭𝐭𝐢 𝐰𝐚𝐥𝐢𝐭𝐭𝐢 𝐧𝐮𝐡𝐚𝐚𝐝𝐞𝐞𝐛𝐢𝐬𝐮!

ከወንድማችን የማእረግ ተሸላሚ ሙስአብ አህመድ የቀድሞ የ4ኪሎ ጀመዓ አሚር የተላለፈው መልእክት "✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍ بسم الله الرحمن الرحيم " هَٰذَا مِن فَضْلِ رَبِّي لِ
ከወንድማችን የማእረግ ተሸላሚ ሙስአብ አህመድ የቀድሞ የ4ኪሎ ጀመዓ አሚር የተላለፈው መልእክት "✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍ بسم الله الرحمن الرحيم                   " هَٰذَا مِن فَضْلِ رَبِّي لِيَبْلُوَنِي أَأَشْكُرُ أَمْ أَكْفُرُ ۖ " «ይህ ከጌታዬ ችሮታ ነው፡፡ የማመሰግን ወይም የምክድ መኾኔን ሊሞክረኝ (ቸረልኝ)፡፡ " ۚوَمَا تَوْفِيقِي إِلَّا بِاللَّهِ ۚ عَلَيْهِ تَوَكَّلْتُ وَإِلَيْهِ أُنِيبُ" " መገጠሜም በአላህ እንጂ በሌላ አይደለም፡፡ በእርሱ ላይ ተመካሁ፡፡ ወደእርሱም እመለሳለሁ፤» አላቸው፡፡" ስኬት ሁሉ በአላህ እጅ ነው። ትልቁ ስኬት የነገው ዓለም ስኬት ነው። አላህ የሻለት ጥረት ያደረገ የሁለት ሀገር ስኬትን ይጎናፀፋል። በርሱ ላይ የተመካ ወደርሱ የተጠጋ ሁሌም ከግብ ይደርሳል። ያሰበው ይሳካል። ከርሱ የራቀ ግን የቀረበ ቢመስለውም ይርቃል ከመንገድ ይጠፋል። አላህ ወደ መንገዱ ይመልሰን🤲🤲 ይህን እንደመግቢያ ካልኩ ቡኋላ ከሁሉ አስቀድሜ አላህን ላመሰግነው እወዳለሁ። ማይቻለውን እንደሚቻል አሳይቶኛል። መንገድ መርቶኛል። ለዚህ እንድደርስ መንገዱን አግርቶልኛል። አሁንም ደግሜ ላመሰግነው እወዳለሁ። በመቀጠል ይህ ነገር እንዲሳካ በሃሳብ በዱዓ ከጎኔ የነበራችሁ ወንድምና እህቶቼ ምን እንደምላችሁ አላውቅም አላህ ይውደዳችሁ። መልካሙን ሁሉ ይግጠማችሁ። በመጨረሻ አደራ ምላችሁ አሁንም ገና ብዙ ይቀረናል። ሁሌም የተሻለ ለመሆን እንስራ። ለራስ ለቤተስብ ለኡማው ለሀገር የምንበቃ ልንሆን ይገባል። ለዛም ልንሰራ ይገባል። እኛ ምድር ላይ የአላህ ምትኮች ነን እና ምድርን በመልካም ልናለማት ይገባል። ይሄ በኛ ላይ የተጣለ ኅላፊነት ነው።ኃላፊነታችንን ለመወጣት በዲንም በዱንያም እንበርታ"

🥀Baga Gammaddan🥀2024      🥀Congratulations 🥀2024           🥀እንኳን ደስ አላችሁ🥀2024 ውድ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ምሩቃን በሙሉ ብዙ ልፋትና ድካምን አልፋችሁ እንኳን ለዚህ በቃችሁ ልላችሁ እወዳለሁ። በተለይም ውድ የ6ኪሎ ጀመዓ የስራ ባልደረቦቼና ጓደኞቼ በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ። ተመርቃችሁ ኡማውን በፍትህና ኡኩልነት የምታገለግሉ አሏህ ያድርጋችሁ። ወንድማችሁ (እስማዒል አብዱሮ) የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች 6ኪሎ ጀመዓ አሚር 🥀Baga Gammaddan🥀2024      🥀Congratulations 🥀2024           🥀እንኳን ደስ አላችሁ🥀2024 Eebbifamtoonni Barattoota Muslimaa Yunivarsitii Finfinnee hundi keessanuu baga guyyaa kanaan isin gahe jechuu barbaada. keessumattuu hiriyoota kiyyaa fi waahiloota hojii jama'aa 6 kilo baga Gammaddan, eebba milkii isinii haa ta'u, eebbifamaa wayyoomaa nama erga eebbifamtanii boodas biyyi isiniin toltu isin haa taasisu, nama biyya ofii fi hawaasa ofii sirnaan tajaajilu rabbiin isin haa godhu. Obboleessa keessan (Ismael Abduro) Amiira Barattoota Muslimaa Yunivarsiitii Finfinnee Jama'aa 6kilo)

🌙የማታ ዚክር ማድረግ አንርሳ !🌙 ኢብኑ ረጀብ የተባለ ዓሊም እንዲህ ይላል:
ስራ ሁሉ ያልቃል፤ ዚክር ግን አያልቅም መጨረሻም የለውም ። ስራ ሁሉ ዱንያ ሲያበቃ ያበቃል ። ከሷ( የዱንያ ስራ) አኼራ ላይ የሚቀር የለም። ዚክር ግን አይቋረጥም ። ሙዕሚን በዚክር ይኖራል ። በዚክር ይሞታል ። በዚክር ይቀሰቀሳል ።
🌙Zikrii Galgalaa Gochuu Akka Hin Irraanfanne !🌙 Aalimni Ibnu Rajab jedhame tokko akkas jedha:
Hojiin hundi ni dhuma. Zikriin garuu hin dhumu, xumuras hin qabu. Hojiin hundi yeroo addunyaan dhumtu ni xumurama. Isheerra(hojii duuniyaa irraa) aakiraa irratti kan hafu hin jiru. Zikriin garuu addaan hin citu. Mu'minni zikriidhaan jiraata, zikriidhaan du'a, zikriidhaan kaafama.
@aau6kilojemea

✅የዱሀ ሶላትን መስገድ አንርሳ ! አቡ ሁረይራ አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ ብለዋል: "ዱሀ(እረፋድ) ላይ ሁለት ረከአዎችን በመስገድ ላይ የዘወተረ ወንጀሉ ይማርለታል እንደ ባህር አረፋ የበዛ ቢሆንም እንኳን።"  ቲርሚዚይ ✅Salaata Duhaa salaatu akka hin irraanfanne ! Abu Hurayraa rabbiin isaan irraa haa jaalatu akka dabarsanitti ergamaan rabbii(sallallaahu alayhi wasallam) akkana jedhaniruu: "Namni duhaa irratti raka'aa lama salaatu irratti ture/dabarse maa'siyaan isaa osoo akka arafaa galaanaatti baay'ateyyu ni araaramaaf." Tirmiziyy @AAU6KiloJemea

☀️የጠዋት ዚክር ማድረግ አንርሳ !☀️ ኢብኑል ቀይም አላህ ይዘንለትና እንድህ ብሏል፡
ዚክር ማለት ቀልብ፣ ፊት እንዲሁም፣ የሰውነት አካል በሙሉ አብሪ ነው።
ቀናችንን በዚክር እንጀምር ! ☀️Zikrii ganamaa gochuu akka hin dagannee !☀️ Ibnul Qayyim Rabbiin isaaf haa rahmatu akkana jedhe:
Zikrii jechuun onnee, fuulaa fi qaama guutuu kan ibsudha.
Guyyaa keenya zikriidhaan haa eegalluu ! @aau6kilojemea

6.ኢስላማዊ ያልሆኑ ባንኮች ላይ በተማሩበት ሙያ ተቀጥሮ መስራት ይቻላል ወይ? ኢስላማዊ ያልሆኑ ባንኮች ከስማቸውና ተግባራቸው ራሱ እንደሚገልጹት ለ ኢስላም የማይሆኑ ናቸው።የ ገንዘብ ምንጫቸው ከ ወለድና ሌሎች ሃራም ስራዎች ነው።በወለድ ዙርያ ከተረገሙ አምስት ሰዎች መካከል አንዱ ውሉን ያስፈጸመው ሰው ነው።ስለዚህ ሃላል የሆኑ ኢስላማዊ ባንኮች ላይ መስራት ነው ሚቻለው። 7.ግዜ አመጣሽ የሆኑ መምጫቸው፡ ምክንያቱና ዓላማው ለብዙዎቻችን ግልጽ ያልሆነ የ ኦንላይን ስራዎች አሉ።በተለይ ያለ ምንም ልፋት ማንም ሰው እንደፈለገ ስልኩን ከፍቶ የስልኩን ስክሪን በጣቶቹ በመነካካት ብቻ ግንዘብ መስራት የሚችልበት መሆኑ ነገሩን ሁሉ ግልጽ እንዳይሆን ያደርጋል።እና ብዚህ ስራ ላይ መስራትና ገቢ ማግኘት እንዴት ይታያል? ይህ አይነቱን ስራ ከመሰራት መቆጠብ ነው ያለበት ሙስሊሙ። በተለይ ምንጩና ዕላማው የማይታወቅ ያለምንም ልፋትና እውቀት የሚሰራ፣ስራም ሳይሆን ጨዋታ ነው።በመሰረቱ የገቢ ምንጭ መሆን የሚገባው ሰው በላቡ ሰርቶ የሚያገኘው ወይም በውቀቱ ነው።ስለዚህ እንዲህ ዕይነቱን ስራ መስራት አይቻልም። 8.በ ጋዜጠኝነት ሙያ ላይ መሰማራት በ እስልምና ይፈቀዳል ወይስ አይፈቀድም? ከእስልምናስ አንጻር እንዴት ይታያል? ሁሌ እውነትን ብቻ የምንዘግብ ከሆነ ምንም ችግር የለዉም። አይከለከልም።ነገርግን እዉነት ለመሆኑ በደምብ ማጣራት አለብን።አጣሩ(ፈተበየኑ)ስለተባለ። 9.ከ ፈርድ ሰላት በኋላ የሚሰገዱ የሱና ሰላቶችን ለመስገድ ፈርድ የሰገድንበትን ቦታ መቀየር ግዴታ ነው? መሰረትስ አለው? ግዴታ ኣይደለም። ነገር ግን የሚወደድ ተግባር ነው። የውመል ቒያማ የሰገድንባቸው ቦታዎች መስካሪ ሆነው ይመጣሉ ።ሰላትንም ኣከታትላችሁ አትስገዱ የሚል ስላለ በዚህ የሚተረጉሙት አሉ።ነብዩ የዒድ ሰላትን መሄጃና መመለሻው የተለያዬ እንዲሆን ማመላከታቸውም ለዚሁ ነው። 10.አላህ በቁርአኑ إِنَّآ أَنزَلْنَا ٱلتَّوْرَىٰةَ فِيهَا هُدًۭى وَنُورٌۭ ۚ يَحْكُمُ بِهَا ٱلنَّبِيُّونَ ٱلَّذِينَ أَسْلَمُوا۟ لِلَّذِينَ هَادُوا۟ وَٱلرَّبَّٰنِيُّونَ وَٱلْأَحْبَارُ بِمَا ٱسْتُحْفِظُوا۟ مِن كِتَٰبِ ٱللَّهِ وَكَانُوا۟ عَلَيْهِ شُهَدَآءَ ۚ فَلَا تَخْشَوُا۟ ٱلنَّاسَ وَٱخْشَوْنِ وَلَا تَشْتَرُوا۟ بِـَٔايَٰتِى ثَمَنًۭا قَلِيلًۭا ۚ وَمَن لَّمْ يَحْكُم بِمَآ أَنزَلَ ٱللَّهُ فَأُو۟لَٰٓئِكَ هُمُ ٱلْكَٰفِرُونَ እኛ ተውራትን በውስጥዋ መምሪያና ብርሃን ያለባት ስትኾን አወረድን፡፡ እነዚያ ትዕዛዝን የተቀበሉት ነቢያት በእነዚያ አይሁዳውያን በኾኑት ላይ በርሷ ይፈርዳሉ፡፡ ሊቃውንቱና ዐዋቂዎቹም ከአላህ መጽሐፍ እንዲጠብቁ በተደረጉትና በርሱም ላይ መስካሪዎች በኾኑት (ይፈርዳሉ)፡፡ ሰዎችንም አትፍሩ፡፡ ፍሩኝም፡፡ በአንቀጾቼም አነስተኛን ዋጋ አትለውጡ፡፡ አላህም ባወረደው ነገር ያልፈረደ ሰው እነዚያ ከሓዲዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡ (5 : 44) وَكَتَبْنَا عَلَيْهِمْ فِيهَآ أَنَّ ٱلنَّفْسَ بِٱلنَّفْسِ وَٱلْعَيْنَ بِٱلْعَيْنِ وَٱلْأَنفَ بِٱلْأَنفِ وَٱلْأُذُنَ بِٱلْأُذُنِ وَٱلسِّنَّ بِٱلسِّنِّ وَٱلْجُرُوحَ قِصَاصٌۭ ۚ فَمَن تَصَدَّقَ بِهِۦ فَهُوَ كَفَّارَةٌۭ لَّهُۥ ۚ وَمَن لَّمْ يَحْكُم بِمَآ أَنزَلَ ٱللَّهُ فَأُو۟لَٰٓئِكَ هُمُ ٱلظَّٰلِمُونَ በእነርሱም ላይ በውስጧ «ነፍስ በነፍስ ዓይንም በዓይን አፍንጫም በአፍንጫ ጆሮም በጆሮ ጥርስም በጥርስ (ይያዛል)፡፡» ቁስሎችንም ማመሳሰል አለባቸው ማለትን ጻፍን፡፡ በእርሱም የመጸወተ (የማረ) ሰው እርሱ ለርሱ (ለሠራው ኃጢአት) ማስተሰሪያ ነው፡፡ አላህም ባወረደው ነገር የማይፈርድ ሰው፤ እነዚያ በደለኞቹ እነርሱ ናቸው፡፡ (5: 45) ይህ እና ሌሎችም አንቀጾች፡እንዲሁም ከታላላቅ ዓሊሞች በ ዓለማዊው ህግ ሰውን መዳኘትም ሆነ በሱ መዳኘት እንደማይሆን አጽንተው ሲናገሩ እንሰማለን። ታድያ ህግ መማር ለሙስሊም ተማሪ ይፈቀዳል? አንድ ሙስሊም ተማሪ የህግን ትምህርት መማሩ ለበጎ ዓላማ እስከ ሆነ ድረስ ችግር የለውም።ይህም ለማወቅና በዲኑ ሊመጡ ከሚችሉ ችግሮች ለመከላከል እና ሌሎችም ብዙ በጎ ዓላማዎች ለማዋል ከሆነ ይቻላል።ነገር ግን ተምሮ በሱ ለመዳኘት የሚደረግ ከሆነ ሰውዬው ወንጀለኛ ይሆናል።ከዛም አልፎ፣ ከ አላህ ህግ ከቁርዓን የተሻለ ነው ብሎ ሚያስብ ከሆነ ይከፍራል።በጥቅሉ የ ሙስሊም ተማሪዎች የህግን ትምህርት መማር አለባቸው። 11.እየሰገደ ጀርባው ቢገለጥ ሶላት ይኖረዋል? አንድ ሰጋጅ ዓውራው(ከ እንብርቱ እስከ ጉልበቱ)ከተገለጠ ሰላት የለውም።ነገርግን ሳያውቀው በድንገት ቢገለጥና ቶሎ ጊዜ ሳይሰጥ መልሶ ሚሸፍነው ከሆነ ሰላቱ ኣይበላሽም።ለምሳለ ሽርጥ ለብሶ በመስገድላይ እያለ ሽርጡ ቢፈታና ቢወርድበት፣ቶሎ ከመለሰው ሰላቱ አለ።ነገር ግን አንዱን የሰላት አርካን ጨርሶ ሚመልሰው ከሆነ ሰላቱ ይበላሻል። 12.ለሶላት እጃችንን ስናነሳ አንዳንድ ሰወች ዱዓ ለማድረግ እንደምናነሳው የውስጥ እጃቸውን ወደ ፊታቸው አዙረው ያነሳሉ። ይህ ትክክል ነው? ትክክል እይደለም ስህተት ነው።አንዳንድ ሰው ባለማወቅ ያን ያደርጋል። መሆን ያለበት ሁለት የ እጅ መዳፎቻችንን በ ትከሻችን ወይም በ ጆሮዎቻችን ትይዩ ሆኖ መዳፎቻችን ወደፊታችን ሳይሆን በተቃራኒው ወደ ፊለፊት ወይም ወደ ቂብላ መሆን ኣለባቸው። 13.የዳዒዎችንና የሼኾችን ፎቶ ለዳዕዋ ፕሮግራም ለማስተዋወቅ መስጅድ ለይ ማድረግ ይፈቀዳል? ባይደረግ ይመከራል።ሆኖም ግን ስጋቶች(ለፎቶው ትልቅ ቦታ ተሰቶት መመለክና መከበር ደረጃ እስካልደርሰ ድረስ) እስከሌሉና ከጉዳቱ ይልቅ ጥቅሙ እሚያመዝን ከሆነ ለትንሽ ግዜ ቢደረግም ችግር የለዉም። 14.ከቁርአንና ሐዲስ በመቀጠል ማወቅ ያለብን በክረምት እንድንቀራቸው የሚጠቁመን ኪታቦች ካሉ። ከ ቁርአንና ሃዲስ በመቀጠል የተጅዊድ፣ዕቂዳና ፊቅህ መጽሃፎችን በደረጃ ማንበብና መቅራት መክረዋል። ማሳሰብያ :ይህ ጽሁፍ የተዘጋጀው ፕሮግራሙ ላይ በተሳተፉ አራት ተማሪዎች ውይይትና አስተያየት የተወሰደ ቁንጽል ሃሳብ ነው እንጂ ሙሉ የ ሼኻችን ንግግር ቃልበቃል ተወስዶ አይደለም።

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته በ ትናንትናው የፈትዋ ፕሮግራም ላይ ተጠይቀው መልስ ያገኙ ጥያቄዎችን በመጠኑ ለመግለጽ እንሞክራለን። 1.በሰላት ላይ አንድ የመጀመሪያው ወይም ከዚያ በኋላ ያለው ረከዓ ያመለጠውና እሱን ለመሙላት የተነሳን ሰው ተከትሎ ወይም ኢማም አርጎ መስገድ ይቻላል? ከመልሳቸው የተገኘው ዋና ሃሳብ " 'በራሱ ተከታይ የሆነን ሰው ተከትሎ መስገድ አይቻልም' የሚሉ አንድ አንድ እይታዎች ቢኖሩም በጥቅሉ ለብቻ መጀመር የተመረጠ ሲሆን ተከትሎ መስገዱም የሚቻል መሆኑን ነው ይምንወስደው።ነገር ግን ልብ ማለት ያለብን ነገር ሰውየው(የምንከተለው)ኢማሙ ከጨረሰ በኋላ የተነሳ መሆኑን በደምብ ማወቅ ኣለብን። 2.በረመዳን ወር በታወቁ ምክንያቶች ጾም የፈታ ሰው፣ ቀዳ ሳይመልስ ሌላኛው ረመዳን ቢቀርብ፣ይህ ሰው እስከ ሻእባን የመጨረሻዎቹ ቀናት ቀዳዉን ለመመለስ መጾም አለበት ወይስ እንዳይጾም የሚገደብበት ጊዜ አለ? የረመዳንን ቀዳ ምክንያት ከሌለው ብግዜ ማውጣት ነው ያለበት። ሁኖም እዚህ የምኒዘው ምንም የሚገደብ ጊዜ የለውም።ረመዳን እስከሚገባ ድረስ ቀዳዉን መጾም ይችላል። 3.አላህ ለወደፊት እንዲሰጠን የምንመኘውን ነገር እንደሰጠን አድርጎ ማመስገን እንዴት ይታያል።ለምሳሌ እኔ ተማሪ ነኝ ለወደፊት መኪና እንዲኖረኝ እፈልጋለሁ፣ስለዚህ መኪና ስለሰጠሀኝ አመሰግንሃለሁ ቢባል እንዴት ይታያል? "መጀመርያ መች የሰጠንን አመስግነን ጨረስን" ይህ ሙሉ ለሙሉ ራስን ማታለል ነው። ይልቁንም የምንመኘዉን እንድናገኝ ዱዓ ነው ማድረግ ያለብን እንጅ የሌለንን ነገር እንዳለን ኣድርጎ ማመስገን አይቻልም። 4. ለወደፊት መሆን ምንፈልገውን ነገር፣እንደ ኡሥታዘ መሆን ,ባለሀብት መሆን ,ጥሩ ቤተሠብ መኖር የመሣሠሉት ባይነ ህሊና መቃኘት እንዴት ይታያል? ጥሩ ጥሩ ነገሮችን መመኘት ወይንም ባይነ ህሊና መቃኘት ችግር የለውም።አላህም በ ሓዲሰል ቁድስ እኔ ባሪያዬ በተመኘኝ ቦታ ነው ያለሁት ብሏልና ጥሩ ነገሮችን መመኘታችን ያንን ነገር እንድናገኝ ይረዳናል። 5.ቁርአን ዉስጥ በ ሱረቱ ዱሃ ምዕራፍ 93:8 እንዲህ ይላል፥ وَوَجَدَكَ عَآئِلًۭا فَأَغْنَىٰ ድኻም ኾነህ አገኘህ፤ አከበረህም፡፡ (93: 8) ይላል።በሌላ የ እናታችን ዓኢሻ ሃዲስም እሳቸው ቤት ለ 2 ወራት እሳት እንዳልነደደና በተምርና በዉሃ ብቻ እንደቆዩ ተገልጿል፣ባንጻሩ ደግሞ ነብዩ በህይወት ዘመናቸው ብዙ ምስኪኖችን እየሰበሰቡ ያበሉና ያጠጡ እንደነበር ይገለጻል።ባጭሩ እሳቸው ድሃ ናቸው ሃብታም? ሁለቱ ሃሳቦች ኣይጋጩብንም? እንዴት ነው ምናስታርቀው? ድኻም ኾነህ አገኘህ፣ሲል ነብዩ ከመላካቸው በፊት ሃብት አልነበራቸውም።ከተላኩ በኋላ ግን ሃብታም ሁነዋል።ይህም የሆነው ከመላካቸው በፊታ አስቀድመው በጀመሩትና ኋላ ብዙም ያልዘለቁበት የንግድ ስራ እንዲሁም በዋነኛነት የምርኮ ገንዘብና ንብረት 1/5 ለሳቸው ገቢ ስለሚሆን ነበር።ነገር ግን ይህ እንዲ እንዳለ እቤታቸው ዉስት ይቸገሩ እንደነበር ብዙ የሚያሳዩ ሃዲሶች አሉ።ለምሳሌ ተርበው ሆዳቸው ላይ ድንጋይያስሩ እንደነበር፣ቤታቸው ዉስጥ ለ 2 ወራት እሳት እንዳልነደደና በተምር እንዲሁም በዉሃ እንደቆዩ፣ባንጻሩ ደግሞ ብዙ ድሃዎችን ሰብስበው ይመግቡ ነበር።ለጥያቄዉም መልሱ ይህው ነው።የሚደርሳቸውን የምርኮ ንብረት ከራሳቸው ይልቅ ለድሆች ያከፋፍሉት ነበር። ስለዚህ ሃብቱም ነበራቸው ሆኖም እሳቸው ጋር እንኳን እንዲቆይ አያደርጉትም።ለዚህም ምሳሌው ባንዱ ቀን ከዓስር ሰላት በኋላ እንደጨረሱ ተቻኩለው ወጡ፣ሲጠየቁም የመለሱት ለድሆች መከፋፈል የነበረበት ግን የተዘነጋቸው ንብረት በሰኣቱ መኖሩን ነው። 

🌙የማታ ዚክር ማድረግ አንርሳ !🌙 ኢብኑ ረጀብ የተባለ ዓሊም እንዲህ ይላል:
ስራ ሁሉ ያልቃል፤ ዚክር ግን አያልቅም መጨረሻም የለውም ። ስራ ሁሉ ዱንያ ሲያበቃ ያበቃል ። ከሷ( የዱንያ ስራ) አኼራ ላይ የሚቀር የለም። ዚክር ግን አይቋረጥም ። ሙዕሚን በዚክር ይኖራል ። በዚክር ይሞታል ። በዚክር ይቀሰቀሳል ።
🌙Zikrii Galgalaa Gochuu Akka Hin Irraanfanne !🌙 Aalimni Ibnu Rajab jedhame tokko akkas jedha:
Hojiin hundi ni dhuma. Zikriin garuu hin dhumu, xumuras hin qabu. Hojiin hundi yeroo addunyaan dhumtu ni xumurama. Isheerra(hojii duuniyaa irraa) aakiraa irratti kan hafu hin jiru. Zikriin garuu addaan hin citu. Mu'minni zikriidhaan jiraata, zikriidhaan du'a, zikriidhaan kaafama.
@aau6kilojemea

✅የዱሀ ሶላትን መስገድ አንርሳ ! አቡ ሁረይራ አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ ብለዋል: "ዱሀ(እረፋድ) ላይ ሁለት ረከአዎችን በመስገድ ላይ የዘወተረ ወንጀሉ ይማርለታል እንደ ባህር አረፋ የበዛ ቢሆንም እንኳን።"  ቲርሚዚይ ✅Salaata Duhaa salaatu akka hin irraanfanne ! Abu Hurayraa rabbiin isaan irraa haa jaalatu akka dabarsanitti ergamaan rabbii(sallallaahu alayhi wasallam) akkana jedhaniruu: "Namni duhaa irratti raka'aa lama salaatu irratti ture/dabarse maa'siyaan isaa osoo akka arafaa galaanaatti baay'ateyyu ni araaramaaf." Tirmiziyy @AAU6KiloJemea

☀️የጠዋት ዚክር ማድረግ አንርሳ !☀️ ኢብኑል ቀይም አላህ ይዘንለትና እንድህ ብሏል፡
ዚክር ማለት ቀልብ፣ ፊት እንዲሁም፣ የሰውነት አካል በሙሉ አብሪ ነው።
ቀናችንን በዚክር እንጀምር ! ☀️Zikrii ganamaa gochuu akka hin dagannee !☀️ Ibnul Qayyim Rabbiin isaaf haa rahmatu akkana jedhe:
Zikrii jechuun onnee, fuulaa fi qaama guutuu kan ibsudha.
Guyyaa keenya zikriidhaan haa eegalluu ! @aau6kilojemea

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ዛሬ ሊካሄድ የታቀደው የ ፈትዋ ፕሮግራም ባማረና ደስ በሚል ሁኔታ ጅማሮዉን እድርጓል። ባንዳንድ ምክንያቶች በሰዓቱ መካሄድ ባይችልም፣በ አል-ኣቅሳ መስጂድ ቤተ መጽሓፍት ዉስጥ በ መስጂዱ ምክትል ኢማም ልጥያቄዎች ምላሾች ከነ ማብራሪያቸው ተሰተዋል። የድምጽ ቅጅ እንደሚለቀቅ ከዚህ በፊት አሳውቀን ቢሆንም ለዛሬ ባለመሳካቱ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን።መልሶቹን ከነ ማብራሪያቸው ማቅረብ ባንችልም ዋና ጭብጣቸውን ነገ በጽሁፍ እናሳውቃለን ኢንሻ አላህ።ባካል ላልመጣችሁ ጠያቂዎች በድጋሚ ይቅርታ እንጠይቃለን።ለወደፊቱ ለማስተካከል እንሞክራለን።

‼️ሽብር ዜና‼️ ፍሬሾች በሙሉ ግቢ ለቃችሁ ዉጡ ተብሏል! ጓዛችንን እየጠቀለልን ነው።ድሮም የሰው ነገር የሰው ነው🫤

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ለዛሬ ጥያቄዎችን እስከ ምሽቱ 2:30 ድረስ የምንቀበል መሆኑን እንገልጻለን!

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته‼️ በ 6-ኪሎ ጀመዓ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ሴክተር ሊዘጋጅ የታቀደው "ከዑለሞች እንጠይቅ!" የተሰኘው የፈትዋ ፕሮግራም ዝግጅቱን ጨርሷል።ዘወትር እሁድ ከ ዙህር ሰላት በኋላ የሚካሄድ ይሆናል።ጥያቄዎቻችሁን @sidistkilofetwabot ተቀብለን በ ምላሹ ለጥያቄዎቻችሁ የመለያ ቁጥሮች ይደርሷችኋል።ፕሮግራሙ በ አል-ኣቅሳ መስጂድ የሚካሄድ ሲሆን ባካል መምጣት ለማትችሉ ግሩፕ ላይ በሚለቀቅ የድምጽ ቅጂ መከታተል ይቻላል። የመጠይቅ ህጎች፥ 📌 ጥያቄዎች ግልጽ በሆነ መልኩ መላክ ኣለባቸው 📌 የጥያቄ መቀበያ ግዜው ከ ሰኞ ንጋት እስከ ጁምዓ ምሽት 2:00 ይሆናል 📌የጥያቄዎቻችሁ መልሶች የሚለቀቁት እሁድ ከምሽቱ 2:30 ነው። 👉የመጀመርያ ዓመት/ፍሬሾች🫢 ባካል ብንመጣና ብንከታተል ይመረጣል! እንጠይቅ! እንወቅ! እንተግብር!!

Assalamu Aleykum Warahmatulah Wabarakatuh Jama'aan barattoota Muslima 6kilo sagantaa gargaarsaa guyyootaaf gaggeessaa ture xumure. jaalatamtoota barattoota muslimaa Jama'aa 6kilo samoona karaa chanaalii Telegrama Jama'aatiin barataa Yuniveristii Bahir Dar kan ta’e Ahmaddiin Usuleeyman sababa dhibee kaansarii dhiigaatiin inni qabameef qarshii miiliyoona 5 kan gaafatame yoo ta’u nutis karaa Jama'aatiin obboleessa keenya kana waan dandeennuun bira dhaabbanna jennee sochii gara garaa kan akka mallaqa sassaabuu, profaayilii fi store jijjiiruu raawwachuun keenya ni yaadatama. sochii adeemsisne kanaan alhamdulilah hamma qarshii13730 sassaabuun isaaf galchii taasisneerra. hanga yaadame guddaa ta’uu baatuus kan eeguuf guddaadha. Namoonni yaamicha keenya kana dhagahuun gargaarasa kanarratti hirmaattan maqaa Jama'aa 6kilotiin isin galateeffachuun barbaada. Rabbiin waan isin dalagdan isinirraa haa jaalatuu. jireenya bareedaa har’aafi boris isin haa jiraachisu. yaadachiisa! hanga ammaatti qarshiin guurame walakkaa hanga barbaadamee waan hin guutiniif namni gargaaruu barbaaddan karaan banaadha. Jama'aa barattoota Musliima 6 kilo! https://t.me/AAU6kilojemea

አሰላሙ አሌይኩም ወረህመቱላህ ወበረካትህ 6ኪሎ ጀመዓ ለቀናት ስያከናወን የነበረውን የእርዳታ ጥሪ ዛሬ ማጠናቀቁን ገልጿል። ውድ የ6ኪሎ ጀመዓ ሙስሊም ተማሪዎች ሰሞን እንደሚታወቀው በጀመዓችን የቴሌግ
+8
አሰላሙ አሌይኩም ወረህመቱላህ ወበረካትህ 6ኪሎ ጀመዓ ለቀናት ስያከናወን የነበረውን የእርዳታ ጥሪ ዛሬ ማጠናቀቁን ገልጿል። ውድ የ6ኪሎ ጀመዓ ሙስሊም ተማሪዎች ሰሞን እንደሚታወቀው በጀመዓችን የቴሌግራም ቻናል ለባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ተማሪ አህመዲን ኡሱለይመን በደረሰበት የደም ካንሰር አምስት ሚልዮን ብር ተጠይቆ እኛም እንደ ተማሪዎች በቻልነው ነገር እናግዛለን ብለን የበጎነት ጥሪ ማድረጋችን ይታወቃል: እሱም ብር መሰብሰብ, ፕሮፋይል, ስቶሪ እና የተለያዩ ግሩፕ ላይ ሼር ማድረግ። በዚህም ጥቂት ቀናት ውስጥ አልሃምዱሊላህ ወደ 13730ብር መሰብሰብ ችለናል። እነደ ምጠብቀው ትልቅ ባይሆንም ለሚጠብቀው ትልቅ ነገር ነው። ጥሪያችንን ሰምታችው ይህንን የበጎነት ጥሪ ላይ የተሳተፈችው በሙሉ በ6ኪሎ ጀመዓ ስም ልናመሰግናችሁ እንወዳለን። አላህ ኸይር ስራቹን ይቀበላችሁ። ጥሩ ህይወት በዚህም ሆነ በአኺራ ይኑራችሁ። ማሳሰቢያ! አስካሁን የተሰበሰበው ብር ገና ግማሹን እንኳን ስላልደረሰ መስጠት ለምትፈልጉ በሩ ክፍት ነው። 6ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ! https://t.me/AAU6kilojemea

#6kJየበጎነት_ጥሪ_challange አንድ ወንድማችን እኔም ከዚህ የበጎነት ጥሪ አልቀርም ለወንድሜ ችግር መፍትሔ መሆን እፈልጋለሁ ብሎ 100 ብር ገቢ አድርጓል። አላህ ይቀበልህ። ለበርዘክህ ብርሃን
#6kJየበጎነት_ጥሪ_challange አንድ ወንድማችን እኔም ከዚህ የበጎነት ጥሪ አልቀርም ለወንድሜ ችግር መፍትሔ መሆን እፈልጋለሁ ብሎ 100 ብር ገቢ አድርጓል። አላህ ይቀበልህ። ለበርዘክህ ብርሃን ያደርግልህ። ማስረጃ የምሆንልህ ሰደቃ ያርግልህ። ጥሩ ህይወት ያኑርህ። Ammas Obboleessi keenya tokko challenge yaaminsa tola ooltummaa kanarraa hin hafu rakkoo obboleessa kiyyaaf furmaata ta'uu barbaada jedhee qarshii 100 galii taasise. rabbiin sirraa haa jaalatu, qabrii kee siif haa ibsu, sadaqaa ragaa siif taatu siif haa taasisu, jireenya milkaawaa si haa jiraachisu. @aau6kilojemea