MTULSU(Mizan Tepi University Law students Union👩🎓👨🎓
رفتن به کانال در Telegram
A channel that aims to connect MTU law students of all years with a sense of unity and to exchange information. contact us Dawit Amanuel(MTULSU president) 👉0983225745 Dirshaye kida (Vice president) 👉 0965754565 Please join and Invite others too @MTULSU
نمایش بیشتر586
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-17 روز
+3330 روز
آرشیو پست ها
Repost from MTU School of Law
“የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የወንጀል ሕግ ትርጉም ውሳኔዎች ስብስብ (በየጉዳዮች የተደራጀ ልዩ እትም) ታትሞ ወጥቷል።”
Call for
Essay competition organized by MTULSU
The role of international law in domestic law of Ethiopia
Submit and ask questions
Via
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
Yordulaw@gmail.com
OR
dirshayelawyer@gmail.com
Repost from Law School Media
ድሬዳዋ ፦ የወላጅ አባቱን ሀብት ለመውረስ በማሰብ ፍጹም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ አሰቃቂ ግድያ የፈጸመው ግለሰብ ላይ የሞት ፍርድ በተባባሪው ላይ ደግሞ የ20 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈረደ።
ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም እኩለ ሌሊት በድሬዳዋ ከተማ ማሪያም ኮንዶሚኒየም አካባቢ 1ኛ ተከሳሽ ቤካ ኑረዲን አሊዬ ከአዲስ አበባ በምስጢር መጥቶ ከግብረ አበሩ 2ተኛ ተከሳሽ ሊበን ወንደሰን ጋር በመሆን የወላጅ አባቱን ህይወት በአሰቃቂ ሁኔታ ያጠፋሉ።
ወንጀለኞቹ ድርጊቱን ከፈጸሙ በኋላ ዱካቸውን ለማጥፋትና በከተማዋ እንዳልነበሩ ለማስመሰል ወዲያውኑ ወደ አዲስ አበባ በያዙት የግል ተሽከርካሪ ይኮበልላሉ።
ነገር ግን ወንጀለኞቹ ከህግ ማምለጥ አልቻሉም።
የድሬዳዋ ከተማ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ወንጀለኞቹ ጥለውት የሄዱትን አነስተኛ ፍንጮች በመከተል በአጭር ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል።
ፖሊስ ያደራጀውን የምርመራ መዝገብ የተረከበው የፌዴራል ፍትህ ሚኒስቴር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት (አቃቤ ህግ)፣ የቀረቡትን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች በመተንተን ክሱን በፍርድ ቤት ሲከታተል ቆይቷል።
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ድሬዳዋ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ፦
1ኛ ተከሳሽ ቤካ ኑረዲን የወላጅ አባቱን ህይወት በመቅጠፉ በሞት ቅጣት እንዲቀጣ
2ኛ ተከሳሽ ሊበን ወንደሰን በቅንጅት በመሳተፉ በ 20 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኖባቸዋል።
ይህ የሞት ፍርድ ቅጣት የሚፈጸመው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ርዕሰ ብሔር ፍርዱን ሲያፀድቁ ብቻ ነው። የመዝግቡ ግልባጭም ለርዕሰ ብሔሩ ጽ/ቤት እንዲላክ ፍርድ ቤት አዟል።
ቪድዮ፦ ድሬዳዋ ፖሊስ
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
Join Us For More Accessibility of Laws
@Law_School_Media
እኛም በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች፣ የሁለተኛ ዓመት የማርኬቲንግ ተማሪ ወጣት ፅዮን መላኩ ህይወት ማለፏን በሰማን ጊዜ እጅግ አዝነናል።
ለውዷ ቤተሰቦቿ፣ ለጓደኞቿ፣ ለመምህራኖቿ እና ለመላው የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ከልብ የመጽናናት ምኞታችንን እንገልጻለን።
እግዚአብሔር ለቤተሰቦቿና ለሚወዷት ሁሉ መጽናናትንና ብርታትን ይስጥ።
እህታችን ፅዮን፣ ነፍስሽን በገነት ያኑርልን፤ በሰላም እረፊ።🙏🙏🙏🙏🙏
Repost from የሕግ መረጃ/ Legal Info
Call for papers to Undergraduate students
The 19th National Students Research Forum(NSRF)
St. Mary's University
የኛ ሕግ
@legal_infoo
Repost from ETHIOPIAN LAW STUDENT ASSOCIATION
My Advice for newly graduated law students
Graduating from law school and stepping into the professional world is a massive achievement, but the transition can be incredibly challenging, especially in a competitive legal market.
Practical advice for newly graduated law students, incorporating your points along with a few extra recommendations.
1. Do Not Be Picky About Your First Job
When you first graduate, your primary goal is to get your foot in the door. Whether it is working as a junior assistant at a small firm, a legal clerk, or in a corporate legal department, do not reject opportunities just because they don't sound glamorous. Every role teaches you the practical mechanics of the law that university didn't cover.
2. Always Be Prepared and Keep Reading
Passing your exit exam was just the beginning. The law is dynamic; it breathes and changes. Proclamations are amended, and Federal Supreme Court Cassation decisions set new binding precedents. A good lawyer is a lifelong student. Read every day, stay updated on current affairs and rehearse what you have learnt.
3. Cultivate Deep Patience
Do not rush the process or expect overnight success.
4. Do Not Let Rejection Depress You
The job hunt can be brutal, and you will likely face many rejections or months of unemployment. Understand that this is normal and it does not define your intelligence or your worth as a lawyer. Protect your mental health, stay resilient, and treat the job hunt itself as your daily job until you secure a position.
5. Master "Soft Skills":
Being a great lawyer isn't just about knowing the law; it is about how well you communicate, negotiate, and handle human emotions.
THANK YOU SO MUCH!!!
@EthiopianLawStudentAssociation
@EthiopianLawStudentAssociation
@EthiopianLawStudentAssociation
@EthiopianLawStudentAssociation
Repost from ህግ ቀልድ እና ቁም ነገር⚖️😂
የፅናትና የስኬት ማማ፡ ከቀን ስራ ወደ ህግ ምሩቅነት!
ትናንት ኑሮን ለማሸነፍና ለነገው ማንነቱ መሰረት ለመጣል በከባድ የቀን ስራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው ይሄው ጠንካራ ወጣት፣ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ (Mizan-Tepi University) በህግ ትምህርት ዘርፍ በደማቅ ሁኔታ ተመርቆ የድካሙን ፍሬ አጭዷል።
ይህ ለነገ እቅዳቸውና ህልማቸው ሌሊት ከቀን ለሚደክሙ በርካታ ወጣቶች ትልቅ ተስፋንና መነቃቃትን የሚፈጥር እውነተኛ የስኬት ማማ ነው።
ማንኛውም ሰው አሁን ያለበት አስቸጋሪ ሁኔታ የህይወቱን የመጨረሻ ምዕራፍ ሊወስን እንደማይችል ይህ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የተመዘገበው ደማቅ ታሪክ ህያው ምስክር ነው።
በትጋትና በቆራጥነት ከተሰራ ትናንት በከባድ የጉልበት ስራ ውስጥ የነበረው ማንነት፣ ዛሬ የፍትህና የህግ ባለሙያ ሆኖ ለመቆም እንደሚያስችል በሚገባ ያሳየናል።
እኛም ለዚህ ብርቱ ወጣት ለደረሰበት ትልቅ የስኬት ምዕራፍ ያለንን ጥልቅ አድናቆት እየገለጽን፣ ለቀጣዩ የሙያ ህይወቱ መልካም ምኞታችንን እንመኛለን።
ህልም ኖሯችሁ ነገር ግን መንገዱ አልጋ በአልጋ ላልሆነላችሁ ወጣቶች ሁሉ ይህ አስደናቂ ጉዞ ትልቅ ብርታትና መማሪያ እንደሚሆን እናምናለን።
👏👏👏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/hig_keld_ena_kumneger
https://t.me/hig_keld_ena_kumneger
Congratulations our school Hero's!!!
♥️♥️♥️♥️♥️♥️♥️♥️♥️♥️♥️♥️♥️♥️
"
So incredibly happy for you guys! Passing that law Exit Exam is no joke. I know how much you stressed over those massive law books, but you finally did it! Huge congrats to my favorite juniors. No more exams—now go celebrate, you’ve earned every bit of it!🎉⚖️" With best Regards, Leul Girma
ውድ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች፤
የህግ ትምህርት ጉዞ እጅግ አድካሚ፣ ብዙ ትዕግስት እና ጥልቅ ንባብን የሚጠይቅ መሆኑ ይታወቃል። እናንተ ግን ይህን ሁሉ ፈተና በብቃት አልፋችሁ፣ የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተናቹሁን በአስደናቂና በከፍተኛ ዉጤት በማለፍ የፈተናውን ቀን በድል አጠናቃችኋል። የትላንቱ ልፋት እና ድካም ዛሬ ላይ በደስታ እና በስኬት በመተካቱ እንኳን ደስ አላችሁ!
ይህ ድል የናንተ ብቻ ሳይሆን፣ ለዚህ ታላቅ አላማ ላበቁ ቤተሰቦቻችሁ እና ለመምህራኖቻችሁም ጭምር የኩራት ምንጭ ነው። በህግ ሙያ ውስጥ ያላችሁን እውቀትና ክህሎት ተጠቅማችሁ፤ ህግን በማስከበር፣ ፍትህን በማረጋገጥ እና ለህብረተሰቡ አርአያ በመሆን በሀገራችን የፍትህ ስርአት ላይ ጉልህ አሻራ እንደምትጥሉ ሙሉ እምነት አለኝ።
የጀመራችሁትን የላቀ የህግ ባለሙያነት ጉዞ በስኬት እንድትቀጥሉ መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ። ጉዟችሁ የዕውቀት፣ የስኬት እና የላቀ የፍትህ አገልጋይነት ይሁንላችሁ!
እጅግ ታላቅ የሆነውን የድል አክሊል በመጎናጸፋችሁ እንኳን ደስ አላችሁ!
93,92,91,91,90,89,88,87,85,86...
ቁጥር መሆናቸዉን ነበር ማዉቀዉ ለካ ዉጤትም መሆን ይችላሉ👏👏 አኩርታቹሁናል ወደ ፊት ከፍ ብላቹሁ በስራዉ አለም ድመቁበት።
Fasil z 👏👏👏👏
እንኳን ደስ ያላችሁ ጀግኖቸ
የእናንተን ውጤት ስሰማ የተሰማኝን ጥልቅ ደስታና ኩራት በቃላት መግለፅ ይከብደኛል 93፣ 91፣90፣ 88፣ 87፣ 86፣ 80... ይሄ አስደናቂ ውጤት ያሳያችሁትን ብቃትና የለፋችሁበትን የሌሊት እንቅልፍ ማጣት በተግባር የመሰከረ ታላቅ ድል ነው።
ምን ያህል እንደኮራሁባችሁና ውስጤ በደስታ እንደተሞላ ልነግራችሁ አልችልም በደንብ ተፈትኖ አልፎ የወጣ ወርቅ የትም ቦታ አንጸባራቂ መሆኑን በድጋሚ አስመስክራችኋል።
ይህ ስኬት በድጋሚ ያረጋገጠው አንድ ትልቅ እውነታ ዩኒቨርሲቲያችንን በአገር አቀፍ ውድድሮች እና በብሔራዊ ፈተናዎች ላይ ሁልጊዜም ስሙን በኩራት ከፍ አድርገው ከሚያስጠሩ ጥቂት ቀዳሚ የትምህርት ክፍሎች መካከል የሕግ ትምህርት ቤታችን ግንባር ቀደሙ መሆኑን ነው!
ይህ በየዓመቱ የማይቋረጠው የሕግ ትምህርት ቤት ስኬት፣ ተቋሙ ተጨባጭና አስደናቂ ፍሬ ማፍራት የሚችል ትልቅ አቅም እንዳለው ማረጋገጫ ነው። በመሆኑም የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ይህንን ውጤታማ ትምህርት ቤት ይበልጥ ስሙን የሚያስጠራበትና ብቁ የሕግ ባለሙያዎችን የሚያመርትበት ዘርፍ እንዲሆን፣ ከምንጊዜውም በላይ በትኩረት ሊሠራበት ይገባል። በትምህርት ግብዓቶች ማሟላት፣ በቤተ መጻሕፍት አደረጃጀት፣ በቴክኖሎጂ አጠቃቀምና መምህራንን በማበረታታት ዙሪያ አስተዳደሩ በብዙ ዘርፎች በሰፊው ኢንቨስት እንዲያደርግበትና ልዩ ድጋፍ እንዲሰጠው እንጠይቃለን። ሁልጌዜም ለውጤታማው አካል የሚሰጥ እውቅናና ድጋፍ የጠቅላላው ዩኒቨርሲቲያችንን ስምና ክብር ከፍ ማድረጉ ስለማይቀር አስተዳደሩ ይህንን ወርቃማ ዕድል ተጠቅሞ የሕግ ትምህርት ቤቱን ይበልጥ እንዲያዘምነውና እንዲያጠናክረው በዚሁ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ለተመራቂዎች በድጋሚ እንኳን ደስ ያላችሁ እያልኩ ፈጣሪ ወደ ቀጣዩ የሕይወታችሁ ምዕራፍ በድል ስትሻገሩ መንገዳችሁን ሁሉ ያሳምርላችሁ! ልክ እንደ ዛሬው ሁሉ በነገው የስራና የሕይወት ዓለም ላይም ታሪክ የምትሰሩ ለሀገራችን የፍትህ ስርአት ደማቅ ብርሃን የምትሆኑ መሆኑን ሙሉ እምነት አለኝ።
ለእናንተ፣ ለቤተሰቦቻችሁ፣ ላስተማሩዋችሁ ውድ መምህራኖቻችሁ ባጠቃላ ለሁላችንም እንኳን ደስ አለን!
©🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝
🎉 Congratulations to the 2018 E.C. Exit Exam Graduates of Mizan Teppi University School of Law! 🎓
Dear Law Graduates,
Heartfelt congratulations on successfully passing the National Exit Examination! This remarkable achievement reflects your dedication, perseverance, discipline, and commitment throughout your legal education journey.
Today marks not only the successful completion of an important academic milestone but also the beginning of a new chapter in your professional lives. Your hard work has paid off, and you have demonstrated the competence and determination required to join the legal profession.
As you move forward, may you continue to uphold justice, integrity, and the rule of law in your future careers. May your knowledge and skills contribute positively to society and inspire those who follow in your footsteps.
On behalf of the Mizan Teppi University law students, we celebrate your success and wish you continued excellence, prosperity, and achievement in all your future endeavors.
Congratulations once again, Class of 2026 / 2018 E.C.! 🎉⚖️🎓
Best wishes to all Mizan Teppi University law students who successfully passed the Exit Exam. 🎓⚖️✨
“Success is the result of hard work, determination, and the courage to never give up.”
