fa
Feedback
Ajeba Emmanuel united church

Ajeba Emmanuel united church

رفتن به کانال در Telegram

እውነት እላችኋለሁ፤ ቃሌን የሚሰማ፣ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።” — ዮሐንስ 5፥24 (አዲሱ መ.ት)

نمایش بیشتر
259
مشترکین
-224 ساعت
-27 روز
-430 روز
آرشیو پست ها
ግን ባንተ.mp35.16 MB

ደካማ ሆኜ አገኘኸኝ ኃጥያተኛ ሆኜ አገኘኸኝ የማልጠቅም ሆኜ አገኘኸኝ ከሰይጣን እጅ ሆኜ አገኘኸኝ ግን ባንተ ከዚህ ሁሉ ወጥቻለሁ ግን ባንተ የእግዚአብሔር ልጅ ተብያለሁ ግን ባንተ ከዚህ ሁሉ ወጥቻለሁ ግን ባንተ የእግዚአብሔር ልጅ ተብያለሁ ዛሬ አርገኸኛል የብርሃን ልጅ እኔን ኢየሱስ ወሰደህ ጨለማዬን/4*/ ይቺ ፅዋ ከኔ ትለፍ ብትል እንኳ ኢየሱስ ታዘአል እንዳያልፈኝ የሕይወት ፅዋ የእግዚአብሔር በግ አስቀድመህ የታረድከው ሌባው እንዳያርደኝ እንዳልጠፋ እንዳልሞት ነው ለምን ተውከኝ ብለህ ስትጮህ አብ ዝም ያለህ እኔ እንዳልጣል እንዳልተው ሁሌ ፊትህ ደዌ እመሜን ተቀበልህ ተሸከምህ እኔ ያንተን ሕይወት ደኅንነትን እንድቀበል የብርሃን መልዕክቴ ነህ ኢየሱስ ልቤ ላይ በራህ ሰማሁህ የምስራቼ ድኛለሁ ወንጌል ሰምቼ በአመድ ፈንታ ሆነኽልኛል አክሊሌ በለቅሶ ፈንታ የደስታ ዘይት ነሆ ለኔ በአዘን ፈንታ የደስታ መጎናፀፊያ አረከኝ እኔን የምሕረትህ ማሳያ ጋሽ ሆነህ ግን ተወጋህ ጎንህን እረኛ የሆንከው ልክ እንደ በግ ተነዳህ የአለም ጌታ በምድር ጌታ ፊት ቆመሀል ምንጭ የሆንከው አንተ የኔ ኢየሱስ ተጠምተአል እንደ ፀሐይ የሚያበራ ፊት እያለህ ግን እኔ እንዳበራ እንድደምቅ ተተፋብህ ሰማይ ምድርን የምትጠቀልል ልክ እንደ ጨርቅ ግን ኢየሱስ ለኔ ተጠቅልለህ መቃብር ሆንክ ይሁን ስትል የሚሆንልህ አንተ ላይ ይሁን አሉብህ ግን ዝም አልክ አልመለስክም አይተህ ነው እኔን ደስታህን ለወጉህ እጆች ኃይላቸው ነበርክ ፈጣሪ ለሰደቡህ አፎች አንተ ነህ የእነርሱ ሰሪ ፈቀድክላቸው አልከለከልካቸውም የምትሞተው በጦር ለወጉህ ለእነርሱም ዘማሪ ይድነቃቸው ተካ💓💗

በዚህ ንባብ ጳውሎስ በቆሮንጦስ ቤተ ክርስቲያን ሀሰተኞች መሪ ነን በሚል የቅዱሳንን ማህበር በመከፋፈል እያወኩ የነበሩ ሰዎችን አታላይ ሰራተኞች ሲላቸው ይስተዋላል። ጳውሎስ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ የተሾመ እውነተኛ ሐዋሪያ ቢሆንም እነዚህ ሰዎች ግን የጳውሎስን ሐዋሪያነት በመቃወም እኛ ነን እውነተኞቹ መሪዎች በሚል የጳውሎስን መሪነት በመቃወም የቅዱሳንን ማህበር ይከፋፍሉ የነበረ እንደመሆኑ መጠን ጳውሎስ አታላዮች ሲላቸው ይነበባል። በዚህ የጳውሎስ ንግግር አታላይ የተባለው በእግዚአብሔር ሳይሾም ነገር ግን በእግዚአብሔር እንደ ተሾመ በሀሰት በመናገር የቅዱሳን ማህበር የሚከፋፍልን ሰው ለመግለጽ የገባ አገላለጽ እንጂ ስድብ አለመሆኑን መገንዘብ ይቻላል። ፊል 3፡2 “ ውሾች” በዚህ ንባብ በፊልጵስዩስ ቤተ ክርስቲያን በመግባት እነ ጳውሎስ ከሰበኩት ወንጌል በተጨማሪ የሙሴን ህግ (ስርዓትና ባዕላት) መጠበቅ ድነት እንደሚሰጥ ያስተምሩ የነበሩ ሰዎችን ጳውሎስ ውሾች ሲላቸው ይነበባል። ጳውሎስ እነዚህ ሰዎች ውሻ ያለበት ምክንያት በዘመኑ ውሻ በየሰው ቤት ደጃፍ እየተዘዋወረ ፍርፋሪ በመለቃቀም በጫካ የሚኖር እንስሳ የነበረ በመሆኑ ይህንን የውሻ ባህሪ መሰረት በማድረግ ከአንድ ቤተ ክርስቲያን ወደ ሌላ ቤተ ክርስቲያን በመዘዋወር ንጹሁን ወንገል የሚበርዙ ሀሰተኛ መምህራንን ውሾች ሲላቸው ይስተዋላል። በመሆኑም በጳውሎስ አገላለጽ ውሻ ማለት ዘዋሪ እንደ ማለት እንጂ ስድብ አይደለም። መደምደሚያ ከላይ የገለጽኩዋቸው ንባባት ብዙ ጊዜ በእቅበተ እምነት አገልግሎት ላይ እንደ ተሰማሩ የሚናገሩ እንዳንድ ወንድሞች ሀሰተኛ መምህራንን ጠቅሰው ሲጠቀሙዋቸው ይስተዋላል። ምንም እንኩዋን መጽሐፍ ቅዱስን ጠቅሶ መናገር ጠቃሚ ቢሆንም በቅድሚያ የንባባቱን ታሪካዊ እንዲሁም አውዳዊ ፍቺ በአንክሮ ማጥናት ተገቢ ነው። ይህ ግን ሲዘወተር አይታይም። ጌታ ኢየሱስ በክፋት ጎዳና ላይ ያሉ ሰዎችን “ተኩላ”፥ “እውር”፥ “በኖራ የተለሰነ መቃብር”፥ “እባብ፥ የእፉኝት ልጅ”፥ “ቀበሮ”እንዲሁም “የዲያቢሎስ ልጆች” እንዲሁም ሐዋሪያው ጳውሎስ ሀሰተኞችን “አታላይ”ና “ውሾች” ስላሉ የገለጻዎቹን ፍቺ በአንክሮ ሳያጠኑ መጠቀም ከአስተማሪነት ይልቅ ወደ ተሳዳቢነት የሚያመዝን ያደርገዋል። ከዚህ ባሻገር ጌታ ኢየሱስና ጳውሎስ እንዲና እንዲያ ብለዋልና እኔም በዘመኔ የሚገኙ ሀሰተኞችን በራሴው ዘመን ቁዋንቁዋ ልጥራቸው ብሎ መወረፍ የሚሰማውን የማያንጽ ሀሰተኛውንም የማይመልስ ስድብ በመሆን ለእቅበተ እምነት አገልግሎት እንቅፋት ይሆናል። እቅበተ እምነትና ስድብ ለየቅል ናቸው። ጌታ ሀሰተኞችን ስለተሳደብን ያዝንብናል እንጂ ጎሽ አይለንም። ስለዚህም የከበረው የእቅበተ እምነት አገልግሎት ከጠቀሜታው ይልቅ ጉዳቱ እንዳያመዝን ለአንደበታችን ጠባቂ ልናኖር ይገባል። “ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ።” ኤፌ 4፡29 ጋሽ ዘላለም 💓

እቅበተ እምነትና ተሳዳቢነት:- የተለያየ ወይስ የተመሳሰለ? የእቅበተ እምነተ አገልግሎት ጥንቃቄ የሚፈልግ አገልግሎት ነው። ልናደርግ ከሚገባው ጥንቃቄ አንዱ ደግሞ የምንጠቀመው ቋንቋ ነው። በአሁን ጊዜ በእቅበተ እምነት ስም ብዙዎች በስድብ አንደበታቸውን ሲከፍቱ ይስተዋላል። ይህ ማንንም የማያንጽ ከመሆኑ ባለፈ አሰናካይነቱ ይህ ነው አይባልም። አንዳንድ ጊዜ ስድብን ለመደገፍ ጌታ ኢየሱስ እንዲሁም ጳውሎስ ሐሰተኞችን እንዲህና እንዲያ ብለው አልነበረ? እየተባለ ስድብን ትክክል ለማድረግ ወደ መጽሐፍ ቅዱስ ሲገባ ይታያል። በዛሬው ጽሁፌ ብዙ ጊዜ ለመሳደብ የሚጠቀሱ ንባባትን በማንሳት አውዳዊና ታሪካዊ ፍቺያቸውን ለማሳየት እሞክራለሁ። ማቴ 7፡15 “ነጣቂ ተኩላ” ጌታ በዚህ ንባብ ስለ ሐሰተኛ ነቢያት ባህሪ ሲያወራ“በውስጣቸው ነጣቂ ተኩላዎች ሆነው ሳሉ የበግ ለምድ ለብሰው•••” እንደሚመጡ የተናገረው አመጣጣቸው ድብቅና አጥፊ አመጣጥ መሆኑን ለማስረዳት ነበር። ስለዚህም ጌታ በማቴ 7፡15 ሐሰተኛ ነቢያትን “ነጣቂ ተኩላ” ብሎ መግለጹ በፍጹም ከስድብ ጋር የሚገናኝ አይደለም። ይህ ገለጻ በዚህ ንባብ ብቻ ሳይሆን በሐዋ 20፡29 ሀሰተኞችን ለመግለጽ ጥቅም ላይ ውሎ እናገኘዋለን። ማቴ 15፡14 “ዕውር መሪዎች” ጌታ በዚህ ንባብ ፈሪሳዊያንን “ዕውር መሪዎች” ያለበት ምክንያት የህጉን ትክክለኛ ትርጉም የማያውቁ የህግ መምህራን መሆናቸውን ለማመላከት ነበር። በዚህ ክፍል የጌታ ደቀ መዛሙርቱ እጃቸውን ሳይታጠቡ መብላታቸውን ተከትሎ ፈሪሳዊያን የሽማግሌዎች ወግ ተጣሰ ሲሉ ይደመጣል። የሽማግሌዎች ወግ ሙሴ የሰጠው ህግ አይደለም። ይልቁንም ህጉ እንዴት እንደሚተረጎም የሚናገር የአይሁድ መምህራን አፋዊ ማብራሪያ (oral tradition) ነው። ምንም እንኩዋን የሽማግሌዎች ወግ ህጉን ያብራራል ቢባልም ከህጉ መንፈስ የራቀ ትርጉም የሚሰጥ በመሆኑ ለህጉ ቆሙዋል የሚሉት የሽማግሌዎች ወግ ከህጉ ትክክለኛ የትርጉም መንፈስ የራቀ ነበር። ለሚሳሌ ህጉ ምግብ ሲበላ እጅ መታጠብ እንደሚገባ አይናገርም። ነገር ግን እንደ ፈሪሳዊያን ያሉ የህግ መምህራን ግን ምናልባት በእጃችን የረከሱ አህዛብን ሰላም ብለን ሳናውቅ ማዕድ ላይ ልንቀመጥ ስለምንችል ከማዕድ በፊት እጃችንን ልንታጠብ ይገባል በሚል የሽማግሌዎች ወግ አዳብረው ነበር። ይህ አካሄድ አግላይ አካሄድ በመሆኑና ህጉም ያልደነገገው በመሆኑ ጌታ ኢየሱስ ፈሪሳዊያን ህጉን የማያውቁ የህግ መምህራን መሆናቸውን ለማሳየት “ዕውር መሪዎች” ሲላቸው ይደመጣል። በዚህ አውድ እውርነት አለማወቅ የሚለውን ሃሳብ ተክቶ የገባ አገላለጽ ነው። ጌታ ፈሪሳዊያንን “ዕውር መሪዎች” ያለው ትክክለኛ ትርጉሙን የማያውቁትን ህግ በድፍረት የሚያስተምሩ የሃይማኖት መሪዎች መሆናቸውን ለማመላከት የተጠቀመው አገላለጽ በመሆኑ ከስድብ ጋር በምንም የሚገናኝ አለመሆኑን መረዳት ይገባል። ሉቃ.11፡44 “ሰዎች ሳያውቁ በላዩ የሚሄዱበትን የተሰወረ መቃብር ስለምትመስሉ” ሉቃ.11፡44 ላይ ያለው ንባብ በማቴ 23፡27 በውስጡ ሙት ነገር የያዘ “በኖራ የተለሰነ መቃብር” በሚል የቀረበ ነው። ጌታ በዚህ ንባብ የፈሪሳዊያንን ግብዝነት “ወዮላችሁ” እያለ ሲቃወም ካደረጋቸው ንግግሮች መካከል ፈሪሳዊያንን ከላይ የገለፀበት ገለፃ አንዱ ነው። በጥንት ዘመን እንደ ፋሲካ፥ ባለ 50••• የመሳሰሉ ትልልቅ የአይሁድ በአላትን ለማክበር ወደ ኢየሩሳሌም አይሁዳዊያን ከመምጣታቸው በፊት በኢየሩሳሌም የሚኖሩ አይሁዳዊያን በኖራ የተለሰኑ መቃብሮቻቸው ላይ የሚበቅለውን ሳር ጠራርገው ያጸዱ ነበር። ይህንን የሚያደርጉት ባዕላቱን ለማክበር የሚመጡ አይሁዳዊያን ሳያውቁ በሚያረክስ የመቃብር ስፍራ ላይ እንዳይቆሙ፥ እንዳያርፉና እንዳይጋደሙ ለመጠበቅ ነበር። ስለዚህም ጌታ ግብዝ ፈሪሳዊያንን “ሰዎች ሳያውቁ በላዩ የሚሄዱበትን የተሰወረ መቃብር ስለምትመስሉ ወዮላችሁ” ያለበት ምክንያት ልክ ግልጽ ያልሆነ መቃብር በዓላትን ለማክበር የመጣን አይሁዳዊ እንደሚያረክስ ፈሪሳዊያንም ሌሎችን በግብዝነታቸው የሚያረክሱ መሆናቸውን ለማመላከት እንደ መሆኑ መጠን ከስድብ ጋር ጨርሶ የሚገናኝ ገለጻ አለመሆኑን መረዳት ተገቢ ነው። ማቴ 23፡33 “እባቦች፥ የእፉኝት ልጆች” ጌታ በዚህ ንባብ ፈሪሳዊያንንና ጸሃፍትን “እባቦች፥ የእፉኝት ልጆች” ያለበት ምክንያት እግዚአብሔር መልዕክት ሰጥቶ የሚልካቸውን ነቢያት፥ ጠቢባንንና መምህራንን ተቀብለው ድምጹን ከመስማት ይልቅ የሚገድሉ፥ የሚሰቅሉና የሚገርፉ በመሆናቸው ምክንያት ይህንን እኩይ ምግባራቸውን ይገልጥ ዘንድ ተናድፎ በሚገድል እባብ ሲመስላቸው ይታያል። ጌታ ኢየሱስ ይህንን አገላለጽ ሲጠቀም ቅሉ እነዚህን የሃይማኖት መሪዎች ለመስደብ ሳይሆን የእግዚአብሔርን ድምጽ የማይሰሙ ይልቁንም ሀቀኛ መልዕክተኞችን በማጥፋት ድምጹን የማይሰሙ መሆናቸውን ለማሳየት ነው። ሉቃ 13፡32 “ቀበሮ” በዚህ ንባብ በሮማዊያን ፈቃድ የይሁዳና የፔሪያ ገዢ የነበረውን ሄሮድስ አንቲፐስ “ቀበሮ” ሲይ ይነበባል። ቀበሮ ከበግ መንጋ መካክል ሊበላ የሚፈልገውን በግ ስልታዊ በሆነ መልኩ ከመንጋው ነጥሎ የሚበላ መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት ቀበሮ የሚለው አገላለጽ ክፉ ሃሳቡን በስልታዊ መልኩ ተግባራዊ የሚያደርግን ብልጣብልጥ ሰው ለመግለጽ ጥቅም ላይ ይውል ነበር። በመሆኑን ጌታ ኢየሱስ በዚህ አግባብ ሄሮድስን ቀበሮ ሲል እየተሳደበ ሳይሆን ብልጣብልጥ መሆኑን ለመግለጽ የተጠቀመው አገላለጽ መሆኑን እንረዳለን። ዮሐ 8፡44 “እናንተ የአባታችሁ የዲያቢሎስ ናችሁ” ጌታ በዚህ ንባብ የሃይሁድ መምህራንን “የአባታችሁ የዲያቢሎስ ናችሁ” ሲል ምግባራቸው እግዚአብሔር ልጅ የሆኑ የማያደርጉት ክፉ ምግባር መሆኑን ተከትሎ የእግዚአብሔር ወገን አለመሆናቸውን ለማሳየት ጥቅም ላይ የዋለ ገለጻ ነበር። ጌታ በተመላለሰበት ዘመን በስጋ የአብርሃም ልጅ በመሆን ብቻ የእግዚአብሔር ልጅ መሆን እንደሚቻል ይታመን የነበረ እንደመሆኑ መጠን የአብርሃም ልጅነት ንስሃና የንስሃ ፍሬ እስከሌለው ድረስ ዋስትና እንደማይሆን በሚያሳይ መልኩ የአይሁድ መምህራንን ሲገልጻቸው ይታያል። ልክ እንደ ጌታ ኢየሱስ ሁሉ መጥምቁ ዮሐንስ በሉቃ 3 ከሚመጣው የእግዚአብሔር ቁጣ ለማምለጥ የዮሐንስን የንስሃ ጥምቀት ተጠምቀው የንስሃ ፍሬ እያፈሩ ከመኖር ይልቅ በአብርሃም ልጅነታቸው ብቻ እንደሚድኑ ለሚያስቡ አይሁዳዊያን ምሳር ( መጥረቢያ) በዛፍ ስር እንዳለና ፍሬ የማያፈራ እንደሚቆረጥ ማለትም የአብርሃም ልጅነቱ እንደማያድነው ሲናገር ይነበባል። እንዲያውም መጥምቁ እግዚአብሔር ከፈለገ ከድንጋዮች መካከል የአብርሃም ልጆችን ማስነሳት እንደማይሳነው በመናገር የአብርሃም ልጅነት ከጥፋት የማያድን ትምክህት መሆኑን ሲያሳስባቸው ይደመጣል። ጌታም ይህንኑ በሚያጎላ መልኩ በአብርሃም ልጅነታቸው ታብየው ነገር ግን ደግሞ በክፉ ተግባር የሚኖሩ የአይሁድ መምህራንን የእግዚአብሔር ልጆች ሳይሆኑ የዲያቢሎስ ልጆች መሆናቸውን መናገሩ እየተሳደበ ሳይሆን ሃቅ እየተናገረ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል። 2ቆሮ 11፡13_15 “አታላይ ሰራተኞች”

#ሀሌ_ሉያ !! ዛሬ በሃላባ አማኑኤል ህብረት ቤተ ክርስቲያን ስር በአጃባ አማኑኤል ህብረት ቤተ ክርስቲያን 17 ሰዎች የውሃ ጥምቀት ወስደዋል !! እንዲሁም የጌታ ራት ፕሮግራም ጊዜም ነበረን ጌታ መልካም ጊዜ ሰጥቶናል። ➘ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።” — ማቴዎስ 28፥19-20 እግዚአብሔር ሰሙ ይባረክ !!

🚨ኑሮህን ጨርሰህ በእኔ ኑር😭😭 ━━━━━⊱✿⊰━━━━━ 🚨እጅግ የተባረኩበት ድንቅ ዝማሬ ነው! 🚨ሀያላን ለአንድ ሳምንት የስልካችሁ ጥሪ አድርጉት!🙏🙏🙏🙏 🚨ሙሉ ዝማሬውን በዚህ ሊንክ ታገኙታላችሁ ተጫኑት!👇 https://youtu.be/qrEZ26LEw9E https://youtu.be/qrEZ26LEw9E sʜᴀʀᴇ💯 sʜᴀʀᴇ 💯 sʜᴀʀᴇ💯                                          ቻናሉን ይቀላቀሉ     ✨ @HolyTubeEthiopia✨     ✨ @HolyTubeEthiopia

#ለአእምሮ_የሚመች_አገልግሎት👇 እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው።” — ሮሜ 12፥1 ወንድም ታራቀኝ ኤልያስ 💓

ቀን. 05/12/2016 ዓ.ም ለተከታታይ 5ት ሳምንታት...ከዶ/ር መንግሥቱ ጋር እንቀጥላለን። #አምስቱ_ሶለዎች! 1.የእግዚአብሔር ቃል የበላይ ይሁን! ➘ የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል። — 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥16-17 ➘ የእግዚአብሔር ቃል ለምን ተጻፈ፦ 👉 ለትምህርት 👉 ለተግሣጽ 👉 ልብንም ለማቅናት 👉 በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል። ➘ለየትኛውም ውሳኔ (ነገሮችን) ለመወሰንና ለመፈጸም ከእግዚአብሔር ቃል አንፃር ማየት አለብን ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል የበላይ ነው። ➘ የሰው አመለካከት ሳይሆን የእግዚአብሔር ቃል ምን ይላል ማለት ይሁን። ➘ የእግዚአብሔር ቃል የበላይ ከሆነ መስማት ያለብን የእግዚአብሔርን ቃል ነው። ➘የእግዚአብሔርን ቃል መስማት፦ ➘ ደስተኛ ያደርጋል ➘ጠቢብ ያደርጋል ➘ እምነትን ይፈጥራል 👉እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። — ሮሜ 10፥17 ➘ የእግዚአብሔር ቃል #ትክክለኛ ሕይወት_እንድንኖር ያደርጋል! ➘ በእውነትህ ቀድሳቸው፤ ቃልህ እውነት ነው። — ዮሐንስ 17፥17 #የእግዚአብሔር ቃል ተራ አይደለም። ዕብራውያን 4 ¹² የእግዚአብሔር ቃል፦ ➘ ሕያው ነውና፥ ➘የሚሠራም፥ ➘ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ➘ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ ➘የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤ ¹³ እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው እንጂ፥ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም። 👉 ጕልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል? ቃልህን በመጠበቅ ነው። — መዝሙር 119፥9 👉 ስለዚህ ፦ ➘ የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ፤ በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ፤ በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ በጸጋው በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ — ቆላስይስ 3፥16 👉 በየትኛውም አጥቢያ ቤተክርስቲያን ባለስልጣን መሆን ያለበት የእግዚአብሔር ቃል ብቻ እና ብቻ ነው።🙌 SOLA holy Bible💗

Muluwongel church doctrinal.pdf110.87 MB

#መጽናናት_ሆኖልናል!😄 👇 . . . . ➘ለእስራኤል የመዳን ተስፋ👇 ➘ ለእስራኤል የመጽናናት ተስፋ👇 ➘ ለእስራኤል የመክበር ተስፋ መሢህ ብቻ ነበረ ስምዖን የእስራኤልን መዳን የእስራኤልን መጽናናት እና ክብር በተስፋ (በእምነት) ይጠባበቅ ነበረ። ይህንን የመዳንን ተስፋ ብቻ ለእስራኤል ሳይሆን ለአህዛብም በመሢሁ ሥራ መዳን መጽናናት እና መክበር ሆኖልናል አሜን። #በመዳንህ_ደሰ_ብሎኛል። ➫ሐናም በመዳንህ ደስ ብሎኛል።” — 1ኛ ሳሙኤል 2፥1 ሉቃ2:25-32 #ከምን_ነው_የዳንነው? ✒ እኛ በክርስቶን ያመንን ከእግዚአብሔር ቁጣ /ከኃጢአት ፍርድ ድነናል (ሮሜ 5፡9፤ 1 ተሰሎንቄ 5፡9)። ኃጢአታችን ከእግዚአብሔር ለየን የኃጢአትም መዘዝ ሞት ነው (ሮሜ 6፡23)። መጽሐፍ ቅዱሳዊ ድነት ከኃጢአት መዘዝ ነፃ መውጣታችንን ስለሚያመለክት የኃጢአት መወገድንም ይጨምራል። ስለዚህ ከኃጢአት ኃይልም ቅጣትም ድነናል። ➫መዳን ከእግዚአብሔር እና በእግዚአብሔር ብቻ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምረናል። ...በእውነት የእስራኤል መዳን በአምላካችን በእግዚአብሔር ዘንድ ነው። — ኤርምያስ 3፥23 ➫ በኃጢአትና በበደል ምክነያት መዳን ከሰው ርቆ ነበረ ... መዳንም ከእኛ ዘንድ ርቆአል። — ኢሳይያስ 59፥11 ደግሞ ይህንን መዳን ማለትም ሰው በኃጢአት ምክንያት ያጣውን እግዚአብሔር ለሰው ልጅ እንዳዘጋጀ/ እንዳስነሳ እናያለን። ➫ከጥንት ጀምሮ በነበሩት በቅዱሳን ነቢያት አፍ እንደ ተናገረ፥ በብላቴናው በዳዊት ቤት የመዳን ቀንድን አስነስቶልናል፤ — ሉቃስ 1፥69-70 ↪️ሉቃስ 1 ⁷⁴-⁷⁵ በእርሱም ከጠላቶቻችን እጅ ድነን በዘመናችን ሁሉ ያለ ፍርሃት በቅድስናና በጽድቅ በፊቱ እንድናገለግለው ሰጠን። ⁷⁶ ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና፤ ⁷⁷ እንደዚህም የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፤ … ⁷⁹ ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል። ሉቃስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁵ እነሆም፥ በኢየሩሳሌም ስምዖን የሚባል ሰው ነበረ፥ ይህም ሰው የእስራኤልን መጽናናት ይጠባበቅ ነበር፤ ጻድቅና ትጉህም ነበረ፥ መንፈስ ቅዱስም በእርሱ ላይ ነበረ። ²⁶ በጌታም የተቀባውን ሳያይ ሞትን እንዳያይ በመንፈስ ቅዱስ ተረድቶ ነበር። ²⁷ በመንፈስም ወደ መቅደስ ወጣ፤ ወላጆቹም እንደ ሕጉ ልማድ ያደርጉለት ዘንድ ሕፃኑን ኢየሱስን በአስገቡት ጊዜ፥ ²⁸ እርሱ ደግሞ ተቀብሎ አቀፈው እግዚአብሔርንም እየባረከ እንዲህ አለ፦ ²⁹ ጌታ ሆይ፥ አሁን እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ፤ ³⁰-³¹ ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና፤ ³² ይህም ለአሕዛብ ሁሉን የሚገልጥ ብርሃን ለሕዝብህም ለእስራኤል ክብር ነው። #ኤፌሶን 2 ¹² በዚያ ዘመን ከእስራኤል መንግሥት ርቃችሁ ለተስፋውም ቃል ኪዳን እንግዶች ሆናችሁ በዚህም ዓለም ተስፋን አጥታችሁ ከእግዚአብሔርም ተለይታችሁ ያለ ክርስቶስ ነበራችሁ። ¹³ አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል። ¹⁴-¹⁵ እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን ያዋሐደ በአዋጅ የተነገሩትንም የትእዛዛትን ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ፤ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ፥ ➫ከምንም ነገር ይልቅ እኛ የዳነን ሰዎች መደሰት ያለብን ነገር ብኖር በመዳናችን ነው እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከግብፃውያን እጅ እንዴት እንዳደነቸው በብዙ ድንቅና ታምራት ከባርነት እንዳወጣቸው በኦሪት መጽሐፍት በግልጽ ተቀምጧል። በተመሳሳዩ እግዚአብሔር እኛን ከኃጢአት ባርነት ነፃ ለመውጣት የገዛ ልጁን ለመዳናችን ለመትረፈችን መስዋዕት እንዲሆን ዘንድ ለእኛ ልኮልናል። ➘ እግዚአብሔር አምላክ እኛን በሚደንቅ አዳዳን ከኃጢአት ባርነት አድኖናል። አሁን ባሪያዎች አይደለንም ልጆች ነን። ገላ 4:4 ➘ እግዚአብሔር እንዴት አዳነን? እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ አዳነን (ዮሐ. 3፡17)። በተለይ፣ መዳናችንን ያገኘው የኢየሱስ የመስቀል ሞት እና ትንሳኤ ነው (ሮሜ 5፡10፤ ኤፌሶን 1፡7)። ቅዱሳት መጻሕፍት ግልጽ ናቸው መዳን በጸጋ፣የሚገኝ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው (ኤፌሶን 2፡5፣ 8) እና የሚገኘው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ብቻ ነው (ሐዋ. 4፡12)። #መጽናናት_ሆኖልናል መልካም ምሽት ይሁንላችሁ 💓

በፀጋው ብቻ በእምነት ብቻ በኢየሱስ ድነናል ወደ አብ መግባት ሆኖልናል በፀጋው ብቻ በኢየሱስ ብቻ በእምነት ፀድቀናል ወደ አብ መግባት ሆኖልናል Hana 💓👈

በጨለመው አለም ምንም በሌለበት ልቤን ያሞቀዋል ያንተ መልካምነት ያንተ መልካምነት ኢየሱስ🙏🙏❤️❤️

ሰው ሙሉ ልብሱን ግጥም አርጎ ለብሶ አደባባይ እንደሚወጣ የእግዚአብሔር ባሪያዎች ሆይ ዕለት ዕለት ኢየሱስን ለብሳችሁት ውጡ:: በቆማችሁበት ስፍራ ሁሉ እርሱ የፅድቅ መጎናፀፊያና የሞገስ አክሊል ይሆንላችዃል:: Lalem💗👈