cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Ethio Lawyers Insight

የቻናሉ አላማ ህግ እና ህግ ነክ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የተሸለ እዉቀትን ለማዳበር የተከፈተ ቻናል እና ግሩፕ ሲሆን፣ የሀገር ዉስጥ እና አለም አቀፍ የህግ መፅሀፍትንና የተለያዩ የህግ የምርምር ስራዎችን ያገኙበታል። Ethiopia

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
2 618
مشترکین
+324 ساعت
+127 روز
+3930 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

በውጭ ሃገር የተሰጠ ፍርድ ወይም የግልግል ዳኝነት ውሳኔ የሚፈፀምበት ሁኔታ በፍትሕ ሚኒስቴር ንቃተ ህግ ትምህርት እና የስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ https://t.me/ethiolawreviews
نمایش همه...
በውጭ_ሀገር_የተሰጠ_ፍርድ_ወይም_የግልግል_ዳኝነት_ውሳኔ_የሚፈፀምበት_ሁኔታ.pdf1.23 KB
👍 6
አንድ ተጠርጣሪ በምርመራ ሂደት ላይ የዋስትና መብቱ ተነፍጎ /ውድቅ ሆኖበት/ የጊዜ ቀጠሮ የሚያየው ፍ/ቤት ዐ/ህግ በ15 ቀን ውስጥ ክስ እንዲያቀርብ በማለት የጊዜ ቀጠሮ መዝገብ ቢዘጋውና በ15 ቀኑ ክስ ባይቀርብ ተጠርጣሪው አዲስ ነገር ተከስቷል በማለት ድጋሚ ለ2ኛ ዙር የዋስትና ጥያቄ ማቅረብ ይችላልን? ይህን ጉዳይ በተመለከተ ፍ/ቤት ምን ማድረግ አለበት?
نمایش همه...
👍 14 3
Directive on monitoring, control, and investigation of civil society organization No.1002/2024 ስለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ክትትል፣ ቁጥጥር እናምርመራ የወጣ መመሪያ ቁጥር 1002/2016
نمایش همه...
1002-2024.pdf4.04 KB
👍 9 1
አንድ ድርጅት ባልተከፋፈለ ትርፍ ላይ ግብር እንዲከፍል የማይጠየቀው ድርጅቱ በአንድ የሂሳብ ጊዜ(የበጀት ዓመት) ውስጥ የተገኘውን ያልተከፋፈለ ትርፍ የሂሳብ ጊዜው በተጠናቀቀ በ12 ወራት ጊዜ ውስጥ የአባላቱን የአክስዮን ድርሻ መጠን እና የድርጅቱን ካፒታል በተገኘው ትርፍ መጠን ያሳደገ እንደሆነ ነው፡፡ ድርጅቱ ያልተከፋፈለ ትርፍ የሌለው መሆኑን የሚያስረዳው በአንድ የሂሳብ ጊዜ(የበጀት ዓመት) ውስጥ የተገኘው የተጣራ ትርፍ የባለአክስዮኖችን የአክስዮን ድርሻ መጠን እና የድርጅቱን ካፒታል ለማሳደግ የዋለ መሆኑን በሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ኤጀንሲ የፀደቀ ቃለ-ጉባኤ እና ከንግድ ሚኒስቴር ወይም አግባብነት ካለው የክልል/የከተማ አስተዳደር ቢሮ የድርጅቱ ካፒታል ማደጉን የሚገልጽ ሰነድ በጣምራ በማቅረብ ነው በማለት የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡
نمایش همه...
👍 12 2🖕 1
አዲሱ ተግባራዊ የሚሆነው ውልና ማስረጃ ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች የሚከፈል የአገልግሎት ክፍያን ለመወሰን በወጣው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 543/2016 መሰረት የአገልግሎት ክፍያ ማሻሻያ ደንብ ከታች ይመልከቱ 👇
نمایش همه...
👍 6
Directive on monitoring, control, and investigation of civil society organization No. 1002/2024-ስለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ክትትል፣ ቁጥጥር እናምርመራ የወጣ መመሪያ ቁጥር 1002/2016
نمایش همه...
1002-2024.pdf4.04 KB
👍 6
የፌ/ጠ/ፍ/ሰ/ሰ/ችሎት በሰ/ መ/ቁጥር 205206 (ያልታተመ) ላይ በሕገ-መንግሥቱ የክልል ፍርድ ቤቶች የፌዴራል ጉዳይን በውክልና እንዲመለከቱ የተሠጣቸው ሥልጣን መሠረቱ የፌደራል አወቃቀር በመሆኑ ሊነሳ የሚችለው በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 78/2 ላይ በግልፅ እንደተመለከተው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2/3ኛ ድምጽ ብቻ በመሆኑ ይህ በሕገ መንግስቱ የተሠጣቸውን የውክልና ሥልጣን በሕግ አግባብ እስካልተነሳ ድረስ ጉዳዮቹ ለፌደራል ፍርድ ቤት በቀጥታ ሊቀርቡ አይችሉም በማለት አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል።
نمایش همه...
205206_የክልል_ፍርድ_ቤቶች_የውክልና_ስልጣን.pdf1.12 MB
👍 14🏆 1
ቀለብ የመስጠት ግዴታን አለመወጣት ያለውን የወንጀል ተጠያቂነት። የቀለብ ገንዘብ መጠራቀም አይችልም፤ ቀለብ ተቀባዩ ለኑሮ አስፈላጊ መሆኑን የሚያሳይ ማረጋገጫ ካላቀረበ በስተቀር ቀለቡን መቀበል ካለበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ሶስት ወራት ውስጥ ቀለቡን ያልተቀበለ ወይም ያልጠየቀ እንደሆነ የተጠራቀመውን ቀለብ መጠየቅ አይችልም፡፡ ቀለብ ተቀባይ የሆነ ሰው በቀለብ ሰጪው ላይ ወይም በቀለብ ሰጪው ወደላይ እና ወደታች በሚቆጠሩ ወላጆች ወይም ተወላጆች ወይም ባል ወይም ሚስት ህይወት ወይም ንብረት ላይ የወንጀል ተግባር የፈጸመ ወይም ለመፈጸም የሞከረ እንደሆነ ቀለብ የማግኘት መብቱን የሚያጣ ይሆናል፡፡ በቂ ምክንያት በህግ መሰረት ሊሰጥ የሚገባውን ቀለብ ለባለመብቶቹ አልሰጥም ያለ ወይም መስጠትን ያስተጓጎለ የወንጀል ተጠያቂነት የሚኖርብት ሲሆን የግል አቤቱ ሲቀርብ ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም በገንዘብ መቀጮ ሊቀጣ ይችላል።
نمایش همه...
ቀለብ_የመስጠት_ግዴታን_አለመወጣት_ተጠያቂነት_የሚያስከትል_ስለመሆን_ያውቃሉ_.pdf1.14 KB
👍 11🥰 1
📎የትራፊክ ደምብን በመጣስ በቸልተኝነት በሰው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ እና የወንጀል ተጠያቂነት ➡️ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 59(2) ግልፅ ንባብ እንደምንረዳው በወንጀል ህጉ ላይ ያስቀጣል ተብሎ በግልፅ ካልተደነገገ በስተቀር በቸልተኝነት የሚፈፀም ማንኛውም ድርጊት በወንጀል አያስቀጣም። በመሆኑም አንድ በቸልተኝነት የተፈፀመ ድርጊት በወንጀል ሊያስጠይቅ የሚችለው በወንጀል ህጉ ልዩ ክፍል ውስጥ ድርጊቱ ወንጀል መሆኑ በግልፅ ተደንግጎ ሲገኝ ብቻ ነው። ሰለቸልተኝነት ይህን ካልን የትራፊክ ደምብን በመጣስ በቸልተኝነት በሰው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ በወንጀል ያስጠይቃል ተብሎ በህጉ በግልጽ ተደንግጓል ወይስ አልተደነገገም የሚለውን እንመለከታለን። ➡️ የትራፊክ ደምብን በመጣስ በቸልተኝነት በሰው ንብረት ላይ ጉዳት በደረሰ ግዜ ጉዳቱን  ያደረሱ ሰዎች በወንጀል ሊጠየቁ ይገባል ወይስ አይገባም በሚለው ጉዳይ ላይ በህግ ባለሞያዎች መካከል ልዩነት የሚስተዋል ሲሆን ከዚህ ጋር በተያያዘ ሊነሳ የሚችለው ድንጋጌ የወንጀል ህግ አንቀጽ 572 ስር የተመለከተው ነው። ➡️ አንዳንድ የህግ ባለሞያዎች የትራፊክ ደምብን በመጣስ በቸልተኝነት በሰው ንብረት ላይ ጉዳት ያደረሱ ሰዎች በወንጀል ህግ አንቀጽ 572(1) ስር ሊጠየቁ ይገባል ሲሉ ሌሎቹ ደግሞ የወንጀል ህግ አንቀጽ 572 የሚደነግገው የትራፊክ ደምብን በመጣስ ሌሎችን ለ አደጋ ስለሚያጋልጡ ሰዎች እንጂ የትራፊክ ደምብን በመጣስ በቸልተኝነት በሰው ንብረት ላይ ጉዳት ስለሚያደርሱ ሰዎች አደለም ስለዚህ በደምብ መተላለፍ አንቀጽ 856  ሰር ካልሆነ በስተቀር የወንጀል ህግ አንቀጽ 572 ስር በወንጀል ሊጠየቁ አይገባም በማለት ይከራከራሉ። ➡️ የፌ/ጠ/ፍ/ቤ/ሰ/ሰ/ችሎት የትራፊክ ደምብን በመጣስ በቸልተኝነት በሰው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ በወንጀል ህጉ ያስቀጣል ተብሎ በግልፅ አለተደነገገም። የወንጀል ህግ አንቀፅ 572 የተደነገገው የትራፊክ ደምብን በመጣስ የሰዎችን ህይወት፣ አካል ወይም ንብረት ለአደጋ የሚጋልጡትን ለመቅጣት እንጁ የትራፊክ ደምብን በመጣስ በሰው ንብረት ላይ በቸልተኝነት ጉዳት የሚያደርሱትን ለመቅጣት አይደለም በማለት በመ/ቁ/194880 ላይ አስገዳጅ ውሳኔ ሰጥቷል። እንዲሁም በመ/ቁ.200948 /ያልታተመ/ ለይም በተመሳሳይ መልኩ ውሳኔ ሰጥቷል። ➡️ ለምሳሌ (A) እግረኛ ነው ብንል ለእግረኞች ባልተፈቀደ በኩል መንገድ በሚያቋርጥበት ግዜ (B) ባልተገባ ፍጥነት እያሽከረከረ ስለነበረ (A) ላይ ጉዳት እንደይደርስ በማሰብ መሪውን ወደሌላ አቅጣጫ ለማዞር በሚሞክርበት ሰዓት መኪናው ከቁጥጥር ውጪ ስለሆነበት (C) እያሽከረከረ ከነበረው መኪና ጋር ይጋጭና ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል። በፌ/ጠ/ፍ/ቤ/ሰ/ሰ/ችሎት ውሳኔ መሠረት ከላይ ባነሳነው ምሳሌ ላይ የወንጀል ህግ አንቀፅ 572 የተፈፃሚነት ወሰን ሲታይ (C) እያሽከረከረ በነበረው መኪና ላይ በቸልተኝነት ጉዳት ያደረሰውን (B)'ን ለመቅጣት የተደነገገ ሳይሆን ለእግረኞች ባልተፈቀደ ቦታ ላይ ሲያቋርጥ B እና C ለ አደጋ እንዲጋለጡና ግጭት እንዲፈጥሩ ያደረገው (A)'ን ለመቅጣት ነው። ➡️ እንደሚታወቀው የፌ/ጠ/ፍ/ቤ/ሰ/ሰ/ችሎት የሚሰጣቸው ውሳኔዎች በማንኛውም የሀገሪቱ ፍርድ ቤት አስገዳጅነታቸው የማያጠያይቅ ቢሆንም ችሎቱ የወንጀል ህግ አንቀጽ 572 ን የተረጎመበት አግባብ ህግ አውጪው ሊደስበት ያሰበውን አላማ የሚያሳካ መስሎ በኛ በኩል አልታየንም። አንዳንድ የህግ አካላትም ይህንን የሰበር ውሳኔ የተቀበሉት አይመስልም። ለምሳሌ ይህ የሰበር ውሳኔ (ቁ.194880) ታትሞ ከወጣ በኋላ የኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ቢሮ የትራፊክ ደምብን በመተላለፍ በቸልተኝነት በሰው ንብረት ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ሰዎች ላይ የወንጀል ህግ አንቀፅ 572 ስር ክስ እንዲመሠርቱ በስሩ ላሉት ዐቃቤ ህጎች መመርያ ሰጥቷል። ➡️ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ማብራራው (ሐተታ_ዘምክንያት) ላይ የወንጀል ህግ አንቀጽ 572 የተቀረፀበት ዋና ምክንያት እንደሚከተለው ሰፍሯል "ድንጋጌው ከዚህ በፊት በነበረው የወንጀል ህግ ያልነበረ አዲስ ድንጋጌ ሲሆን፣ ብዙን ግዜ ተሽከርካሪ በሚንቀሳቀስባቸው መንገዶች ላይ እግረኞች ግራ ቀኙን ሳያዩ ሲያቋርጡ ወይም ትክክለኛ መስመራቸውን ትተው ሲጓዙ የተሽከርካሪዎችን እንቅስቃሴ ከመግታትም በላይ ተሽከርካሪዎች እርስ በእርስ ሊጋጩ ወይም በዕግረኞች ላይ አደጋ ሊያደርሱ የሚችሉበት ሁኔታ ይከሰታል። በሌላ በኩል ተሽከርካሪዎች በትራፊክ ደምቦች ላይ የተሰጠውን ልዩ ልዩ ምልክት በመጣስ እና ትክክለኛ መስመራቸውን ባለመያዝ አንዳንድ ግዜም በግረኛ መንገድ ላይ በመውጣት በሰው ሕይወት ፣ አካል ወይም ንብረት ላይ ጉዳት ለማስከተል የሚችሉበት ሁኔታ ሲፈጠር ይታያል። ይህ አንቀፅ የተቀረፀው የዚህ አይነቱን ድርጊት ለመከላከል ነው።" ➡️ ከማብራሪያው የምንረዳው ድንጋጌው በ አድስ መልኩ የተጨመረበት ዋናው ምክንያ የትራፊክ አደጋ አስከፊ እየሆነ በመምጣቱ እግረኞችም ሆኑ አሽከርካሪዎች በሰው ህይወት፣ አካል ወይም ንብረት ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ ለመከላከል ሲሆን ጉዳት ደርሶ ቢገኝ ደግሞ አጥፊዎችን መቅጣት የህግ አውጪው ሀሳብ መሆኑን ይጠቁማል። ➡️ ስለዚህ በድንጋጌው ላይ "የትራፊክ ደምብን በመጣስ ለአደጋ ማጋለጥ " የሚለው ህግ አውጪው ሊደርስበት ካሰበው አላማ ጋር  በሚጣጣም መልኩ መተርጎም ይኖርበታል፣ በተለይ የትራፊክ አደጋ ከቀን ወደ ቀን በሰው ህይወት, አካል እና ንብረት ላይ እያደረሰ ያለው ጉዳት አስከፊነት እየጨመረ በመምጣቱ ድንጋጌው ይህንን አደጋ መከላከል በሚያስችል መልኩ ስራ ላይ መዋል ይኖርበታል። ➡️ በመሆኑም የወንጀል ሕግ አንቀፅ 572 ላይ "የትራፊክ ደምብን በመጣስ የሰውን ሕይወት ፣ አካል ወይም ንብረት ለአደጋ ማጋለጥ" በሚል የተገለፀው በቸልተኛነት የትራፊክ ደንብን በመጣስ በሌላ ሰው ንብረት ላይ ጉዳት የሚያደርሱትን ጭምር ለመቅጣት የተደነገገ አንቀፅ ነው ባይ ነን። ➡️ ነገር ግን የፌ/ጠ/ፍ/ቤ/ሰ/ሰ/ችሎት በመ/ቁ.194880 እና 200948 ላይ የሰጠው ውሳኔ በሌላ ውሳኔ እስከሚሻር ድረስ አስገዳጅ መሆኑ የማያጠያይቅ ጉዳይ ነው።
نمایش همه...
👍 20👏 3👎 1
Murtii DhIMMWF Lakk.Galmee 235844 ta’e irratti gaafa Onkololeessa 06 Bara 2016 kennamee:- Maqaan abbaa qabeenyumnaa maqaa Abbaa manaa fi Haadha manaatiin  galmaahun qoftii qabeenya sana qabeenya waliinii isaani kan hin taasisnee ta'u. Maqaan abbaa qabeenyummaa qabeenya hin sochonee(mana jireenyaa) maqaa Abbaa manaa fi Haadha manaatiin galmaahee kan jiru ta'uus isaan keessaa tokko qabeenyi ykn manni kun kan dhunfaa isaa ta'u hubachiisu yoo danandahe qabeenyi ykn manni kun qabeenya waliinii isaani otoo hin taane kan dhunfaa isaa dha. ሰ-መ-ቁ 235844 ጥቅምት 06 ቀን 2016 ዓ.ም የማይንቀሳቀስ ንብረት (መኖሪያ ቤት) ስመ ሀብቱ የተመዘገበው በባልና ሚስት ስም ቢሆንም አንደኛው ተጋቢ ንብረቱ የግሉ መሆኑን ማስረዳት ከቻለ ንብረቱ የግል እንጂ የጋራ ሀብት አይደለም። ስመ ሀብቱ በተጋቢዎቹ ስም መመዝገቡ ብቻውን በትዳር ውስጥ የተፈራ የጋራ ንብረት አያደርገውም።
نمایش همه...
235844 qabeenya dhunfaa dhirsaa fi nitii.pdf6.63 KB
👍 9
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.