cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

What does the law say? Law and information discussion channel

Legality for all

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
221
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+37 روز
+1330 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

የአዕምሮ ሕመም እና የወንጀል ኃላፊነት የአዕምሮ ሕመም አልፎ አልፎ ቢሆንም በሀገራችንም ሆነ በሌሎች ሀገራት የወንጀል ኃላፊነትን ለማስቀረት እንደመከላከያ የሚነሣ አከራካሪ ጉዳይ ነው። ክርክሩን የሚያወሳስበው ደግሞ ሐሳቡ የተመሠረተው በሕግ ላይ ብቻ ሳይሆን በቀላሉ በማይታወቀው እና በዘርፉ ጥልቅ እውቀትን በሚጠይቀው በአዕምሮ ጤና ሁኔታ ላይ መሆኑ ነው። የወንጀል ሕጋችን አንቀጽ 48 “አንድን ወንጀል የፈፀመ ሰው በመደበኛ ቅጣቶች የሚቀጣው ለድርጊቱ ኃላፊ ከሆነ ብቻ ነው” ይላል። ለወንጀሉ ኃላፊ ለመሆን ደግሞ አንዱ መስፈርት የሆነውን የወንጀሉን የሐሳብ ክፍል ‘ድርጊቱን ሆነ ብሎ ወይም በቸልተኝነት ለመፈፀም የሚያስችል’ የማሰብ አቅም ሊኖር ይገባል። ይህን የወንጀል ኃላፊነት ከማያስከትሉ ምክንያቶች አንዱ ደግሞ ከአዕምሮ የጤና ሁኔታ ጋር የተያያዘ ነው። ይህም የሚሆነው ወንጀል ፈፃሚው ወንጀሉን በሚፈፀምበት ጊዜ የድርጊቱን ዓይነት ወይም ውጤቱን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል ለመገንዘብ ወይም ተገንዝቦ ራሱን ለመቆጣጠር የማይችል መሆኑ ሲረጋገጥ ነው። ከነዚህ የፍፁም ኢ-ኃላፊነት ወይም የከፊል ኃላፊነት ምክንያቶች መካከል በወንጀል ሕጋችን አንቀፅ 48/2/ ላይ የተጠቀሱት በሕመም፣ በዕድሜ መግፋት በሚመጣ መጃጀት፣ ባልተለመደ የዕድገት መዘግየት ወይም ጥልቅ የአዕምሮ የመገንዘብ ወይም የማመዛዘን ችሎታ መቃወስ፣ በአዕምሮ ሕመም፣ በአዕምሮ ዕድገት መገታት ወይም ሌላ ተመሳሳይ ሕነ-ሕይወታዊ ምክንያት የሚከሰቱ ከአዕምሮ ሕመም ጋር የተያያዙ የወንጀል ኃላፊነትን ሊያስቀሩ የሚችሉ መከላከያዎች ናቸው። ሕጉ የአዕምሮ ሕመም መኖሩ ብቻ የወንጀል ተጠያቂነትን ያስቀራል አላለም። የአዕምሮ ሕመም ኖሮባቸውም የሚያደርጉትን ነገር እና ውጤቱን ማገናዘብ የሚችሉ ሰዎች ለወንጀል ቅጣት ተጠያቂ የሚያደርገውን የሐሳብ ክፍል አሟልተዋልና ይጠየቃሉ። ስለዚህ የአዕምሮ ሕመምን እንደ መከላከያ የሚያነሣ ተከሳሽ ከአዕምሮ ሕመሙ በተጨማሪ ወንጀሉን በሚፈፀምበት ጊዜ የድርጊቱን ዓይነት ወይም ውጤቱን ለመገንዘብ ወይም ተገንዝቦ ራሱን ለመቆጣጠር የማይችል የነበረ መሆኑን ማስረዳት አለበት። የወንጀል ሕጉ ከላይ ባነሣናቸው ምክንያቶች ተጠያቂነት እንዲቀር ያደረገበት መሠረታዊ ዓላማዎች መካከል ዐበይቶቹ የሚከተሉት ናቸው፦ ነፃ ፍቃድ፦ ተከሳሹ ሕጉን ለመጣስ ሆን ብሎ ለመወሰን የሚችልበት ሁኔታ ላይ ባለመሆኑ እና የወንጀል ድርጊቱን የሚፈፅመው ካለበት የአዕምሮ ችግር የተነሣ በመሆኑ፤ የቅጣት ዓላማ፡- የሚያደርገው ነገር ትክክለኛ ይሁን ስህተት መለየት የማይችል ሰውን ባህሪ በወንጀል የእስር ቅጣት ማረምም ሆነ ማስተማር ስለማይቻል እና ከአዕምሮ ችግሩ የተነሣ ለፈፀመው ወንጀል መቅጣት የወንጀል ቅጣት አላማን ስለማያሟላ፤ ለአጥፊው ከማሰብ አንፃር፡- በአዕምሮ ሕመም የተነሣ ለፈፀመው ወንጀል ኃላፊነት የለበትም የተባለ ግለሰብ ለኅብረተሰቡ አደገኛነቱ እንደይቀጥል መብቱ ተገድቦ በጥበቃ ስር ሕክምና ሚያገኝበት ማገገሚያ ውስጥ መግባቱ በእስር ቤት ከሚሆን የተሻለ እንዲያገግም ስለ ሚረዳው መሆኑን የወንጀል ሕግ ላይ የተጻፉ መጽሐፍት ይጠቁማሉ።
نمایش همه...
ሰለ አደራ ዙሪያ ህጎቻችን ምን ይላሉ በሥራ ላይ ያለው የፍትሐብሔር ሕግ ስለ አደራ የሚከተሉትን አንቀፆች አካቶ ይጠኛል። በ1952 የወጣው  ይህ የፍትሐ ብሔር ሕጋግ አደራን የዕቃ ጥበቃ፣ በዕቃ የመጠቀም ወይም የመገልገል የውል ግንኙነቶች ውስጥ ይመድበዋል። የፍትሐ ብሔር ሕጋችን በቁጥር 2779 ላይ ለአደራ የሰጠው ትርጉም አደራ የጠባቂነት ስምምነት ሲሆን አደራ ተቀባይ ከአደራ አስቀማጭ የሌላ ሰው የሆነውን ዕቃ ተቀብሎ ጠብቆ እንዲያስቀምጠው በስምምነት የሚገባው የውል ግዴታ መሆኑን ይገልጻል። አደራ በመሠረቱ አደራ ተቀባዩ ለሰጠው አገልግሎት ክፍያ የማይጠይቅበት ቢሆንም ነገር ግን በሚያደርጉት ውል አደራ ሰጪው እና አደራ ተቀባይ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 2784 መሠረት አደራ ተቀባዩ የድካሙ ዋጋ እንዲከፈለው መስማማት ይችላሉ። አደራ ተቀባዩ በአደራ ዕቃውን የሚጠብቀው ለምን ያህል ጊዜ ነው? የሚለውን ጉዳይም ተዋዋዮች በውላቸው ላይ የሚወስኑት ነው። ይህ ጊዜ በውሉ ላይ ያልተወሰነ ከሆነ አደራ ሰጪው በመሰለው ጊዜ ዕቃውን እንዲመለስለት አደራ ተቀባዩን መጠየቅ ተቀባዩም ሰጪውን አደራህን ውሰድልኝ ማለት ይችላል። ከተስማሙበት ጊዜ በላይ አደራ ተቀባዩ ጋር ዕቃው ከቆየ ወይም በአደራ ተቀባዩ ባልሆነ ጥፋት አደራ ማስቀመጡ ጉዳት ካደረሰበት አደራ ሰጪው ኪሳራውን የመክፈል ግዴታ አለበት። በአደራ የተቀመጠ ዕቃን አስቀማጩ ካልፈቀደ ተቀባዩ ሊገለገልበት ወይም ሊጠቀምበት አይችልም። ሳያስፈቅድ ከተጠቀመበት አደራው ወደ ዕቃ ኪራይ ይለወጥና አደራ ሰጪ የዕቃ አከራይ፣ አደራ ተቀባይ ደግሞ ተከራይ እንደሚሆኑ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 2783(2) ይደነግጋል። በአደራ የተቀመጠው ጥሬ ገንዘብ ወይም አላቂ ዕቃ ከሆነና አደራ ሰጭው ተቀባዩ እንዲገለገልበት ከፈቀደለት ግንኙነታቸው የአላቂ ነገር ብድር ይሆናል። ሰለዚህ አደራ ሰጪው ሲጠይቅ ተቀባዩ በገንዘቡ ወይም በዕቃው ቢጠቀምበትም መተካት አለበት። ያልታሽገ ጥሬ ገንዘብ በአደራ የተረከበ አደራ ተቀባይ ግን ሰጪው ባይፈቅድለትም ሕጉ አደራውን እንደ ብድር እንጂ እንደ አደራ ስለማይቆጥረው መጠቀም ይችላል። የመክፈያ ጊዜ ሲደርስ ግን መመለስ አለበት። በነገራችን ላይ የአደራ ውል ባንክ ገንዘብ እና የከበሩ ማዕድናትን ማስቀመጥንም የሚመለከት ነው። በንግድ ሕጋችን ቁጥር 896 “ባንክ በምንም ዓይነት የተቀመጠ ገንዘብ ቢሆን ባንኩ በገንዘቡ የመጠቀም መብት ቢኖረውም አደራ አስቀማጭ ነው” ይላል። በፖስታ ቤትም ሆነ በሰው በኩል ዕቃ እና መልዕክት መላላክም ለሦስተኛ ወገኖች (ለተቀባዮች) እንዲደርስ የሚሰጥ አደራ ነው። አደራ ተቀባይ ዕቃውን በውሉ በተስማማው የአጠበባቅ ሁኔታ ማስቀመጥ አለበት። ሆኖም አጋጣሚ ካስገደደው እንደሚመቸው ሊያሰቀምጠው ይችላል። ዕቃውን የሚያበላሽ ወይም ሚያጠፋ አደጋ የሚደርስ ከሆነ መሽጥ ወይም ለሌላ ሰው በአደራ ማስተላለፍም ይችላል። አደራው ለሦስተኛ ወገን (ከተቀባይ እና ከሰጪ ውጪ ለሆነ ሰው) የተቀመጠ ከሆነ እና ይህ ሰው አደራው እንዲቀመጥለት ከተስማማ ካለእርሱ ፈቃድ ለአደራ ሰጪውም ቢሆን ዕቃው አይመለስም። ሁለት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች ያስቀመጡት አደራ ከሆነ እና ስለ አመላለሱን በተመለከ ካልተስማሙ ለማን ይመለስ የሚለውን ሚወስነው ፍርድ ቤት ነው። አደራ ለተቀባዩ አስገዳጅ የሚሆንበት ጊዜ አለ። በሁለት ወገኖች መካከል በተነሣ ክርክር ጉዳዩ እስኪጣራ ተከራካሪዎቹ የመረጡት ሰው ወይም በፍርድ ቤት የተመረጠ ሰው ዕቃውን በአደራ እንዲጠብቅ ይታዘዛል። ይህ ባለአደራ ፍ/ቤት ካላዘዘው ወይም ሁለቱም ባለጉዳዮች ካልተስማሙ ዕቃውን መመለስ አይችልም። አስፈላጊ አደራ ምንድን ነው? ይህ የአደራ ዓይነት አደራ ሰጪው የማይታገድ እርግጠኛ አደጋ ሊደርሰባቸው ሲል ዕቃዎቹን ለሌላ ሰው በአደራ የሚሰጥበት ሲሆን በፍ/ሕ/ቁ 2801 መሠረት በዚህ ሁኔታ አደራ እንዲቀበል የተጠየቀ ሰው ትክክለኛ ምክንያት ከሌለው አደራውን አልቀበልም ማለት አይችልም። ሆኖም አደራ ማስቀመጡ ከአንድ ሳምንት በላይ ለሆነ ጊዜ ከሆነ በአደራ የጠበቀበትን ዋጋ ከአደራ አስቀማጩ መጠየቅ ይችላል። አደራ እና የወንጀል ኃላፊነት በወንጀል ሕጋችን 675 መሠረት እምነት ማጉደል ማለት ለራስ ወይም ለሌላ ሰው ተገቢ ያልሆነ ብልፅግና ለማግኘት በማሰብ የሌላ ሰውን ለተወሰነ አገልግሎት (በውሰት) ወይም በአደራ የተቀበለውን ዋጋ ያለው ነገር ወይም ጥሬ ገንዘብ በሙሉ ወይም በከፊል ለራሱ ያደረገ፣ የወሰደ፣ ያስወሰደ፣ የሰወረ፣ ለራሱ ወይም ለሌላ አገልግሎት ያዋለ ወይም መሰል ድርጊቶችን የፈፀመ እንደ ነገሩ ሁኔታ በቀላል እስራት ወይም ከአምስት ዓመት በማይበልጥ እስራት ይቀጣል። በእምነት ወይም በአደራ የተቀበለውን ዕቃ ወይም ጥሬ ገንዘብ አደራ ተቀባዩ መመለስ ወይም መክፈል አለበት። ይህን ማድረግ ካልቻለም ዕቃው ያለበትን ሁኔታ ማሳየት ወይም ለተገቢው አገልግሎት ያዋለው መሆኑን የማስረዳት ግዴታ አለበት። እነዚህን ግዴታዎቹን መወጣት ካልቻለ ግን ንብረቱን ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ያልተገባ ጥቅም የማዋል ሐሳብ እንዳለው የወንጀል ሕጋችን ይገምታል። በዚህ መልዕክት ጽሑፉን ስንቋጭ። አደራን ከማክበር በተጨማሪ ዕቃዎችን በአደራ ከመቀበል በፊት ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል በወንጀል ሊያስጠይቁ የሚችሉ ነገሮች ሊያጋጥሙ ይችላሉና። ለምሳሌ በወንጀል ሕግ ሐሰተኛ መሆናቸውን አውቆ የሐሰት ሰነዶችን በአደራ ማስቀመጥ በቀላል እስራት ወይም በመቀጮ ወይም ነገሩ ከባድ ከሆነ እስከ 2 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ያስቀጣል። እንዲሁም የወንጀል ፍሬ የሆኑ ወይም ወንጀል የተፈፀመባቸው ንብረቶችን ወይም ለአንዳንድ አደገኛ ወንጀሎች መፈፀሚያ የተዘጋጁ ነገሮችን እያወቁ ወይም በቸልተኝነት በአደራ ማስቀመጥ የወንጀል ኃላፊነት ሊያስከትል ሰለሚችል ተገቢው ጥንቃቄ መደረግ አለበት እንላለን ። እናመሰግናለን !!
نمایش همه...
ክፉ ምላስ በሕግ ዐይን - በመሳደብዎ ሕግ እንደሚቀጣዎ ያውቃሉ? ** ለዛሬው የሕጉ ምን ይላል ጽሑፍ መነሻ የሆነው በዚሁ ኢቢሲ ሳይበር ላይ "ክፉ ምላስ - የስድብና የመጥፎ ቃላት ወረርሺኝ በዘመናችን" በሚል እርዕስ የወጣው ጽሑፍ ላይ የእስልምና፣ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና የፕሮቴስታንት እምነቶች ሊቃውንት እንደየ ሃይማኖታቸው አስተምህሮዎች የስድብ እና ማዋረድ ድርጊቶች በመንፈሳዊም በዓለማዊም እሳቤ የተጠሉ በመሆናቸው ከክፉ ምላስ እንድንታቀብ ያስትላለፉት መልክት ነው። ለመሆኑ ስድብ እና ማዋረድ በሕግ ዐይን ምን ዓይነት ኃላፊነት ያስከትላሉ? “የምላስ ወለምታ በቅቤ አይታሽም!!” ይባላል - ባለማስተዋል ሳት ብሎን የሰውን ክብር መንካት እንኳን በቀላሉ እንደማይመለስ ለመግለጽ። አሁን አሁን ግን ከማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች መስፋፋት ጋር የስድቡም፣ የመሳደቢያ ዘዴ እና ዓይነቱም የበዛ ይመስላል። ስድብ ጥግብ ማለት ከፈለጋችሁ የትም አትሂዱ፤ እዚሁ የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ላይ የሆነች አነጋጋሪ ነገር ጻፉ ወይም አንዱ ጽሑፍ ላይ የሆነ አስተያየት ስጡ። ለመጻፍ ቀርቶ ለማሰብ የሚከብዱ ፀያፍ ቃላት እንደ ጉድ ይዘንቡባችኋል። “ይህ ሰው ለምን ሰደበኝ? በሐሳቤ ካልተስማማ መተቸት ያለበት ሐሳቤን አይደለም እንዴ?” ብላችሁ ብትጠይቁም መልስ የለም። ይሄን ጽሑፍ አንብባችሁ ወደ አስተያየት መስጫው ወረድ ስትሉ ጉድለትን የሚጠቁሙ፣ የሚያነጋግሩ፣ የሚያበረታቱ፣ የሚያርሙ፣ የሚያዝናኑ መልካም አስተያየቶች እና ጥያቄዎችን እንደምታዩት ሁሉ ከተነሣው ጉዳይ ጋር የማይገናኙ ፍረጃዎችን እና ስድቦችም ቀላል እንዳይደሉ መታዘብ ትችላላችሁ። አንዳንዶች ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ በስድብ አንደኛ ሲሆኑባችሁም “ይህ ነገር በባህልም፣ በሃይማኖትም፣ በሕግም ክልክልነቱ ቀረ እንዴ?!” ብላችሁ ልታስቡ ትችላላችሁ። ስድብ ግን የተፈቀደ እስኪመስለን ቢጧጧፍም ወንጀል ነው። በወንጀል ሕጋችን በአንቀፅ 615 ሥር ስድብ እና ማዋረድ በክብር ላይ ከሚፈፀሙ ወንጀሎች መሐል አንዱ ሆኖ ተደንግጓል። ማንም ሰው ተበዳዩን በቀጥታ በመናገር፣ በአሽሙር ስድብ ክብሩን ከነካ፣ በምልክት ወይም በሌላ በማናቸውም ሁኔታ ካዋረደ እና ተበዳዩ ክስ ካቀረበበት በወንጀል ይቀጣል። ቅጣቱም ከሦስት ወር የማይበልጥ እስራት ወይም እስከ ሦስት መቶ ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት ነው። ተሳዳቢዎችን በሦስት ከፍለን ማየት እንችላለን የመጀመሪያው ‘ተራ ተሳዳቢ’ ነው። እንዲያው ልማድ ሆኖበት አፉን የሚበላው፣ ያገኘውን ሁሉ የሚሳደብ፣ ሚሰድበው ቢያጣ ራሱን ወይም እንሰሳትን፣ ግዑዝ ነገሮችን ሁሉ የሚዘልፍ የስድብ ሱሰኛ ነው። ሁለተኛው ‘ሰድቦ ለሰዳቢ የሚሰጥ’ ነው። በአደባባይ ሰው እስኪሰማ ጠብቆ ተሳድቦ እንድትሰደቡ ለቢጤዎቹ የሚያቀብላችሁ ወይም “ልክ ልኩን ነገርኩት፣ ሙልጭ አደረኩት፣ እስኪበቃው አስታጠኩት!” እያለ የተሳደባቸውን ስድቦች በየአጋጣሚው እያወራ የሚነዛ ነው። ሦስተኛው ‘ሰድቦ አሳዳቢ’ ነው። የፈለገ ጨዋ ብትሆኑም ደኅና አድርጎ ሲዘረጥጣችሁ ወይም የሆነ አስፀያፊ ነገር ሲያደርግባችሁ ያለመሳደብ ትህትናችሁ ተንዶ እንድትሞልጩት የሚያስገድዳችሁ እና የስድብ ሙያ ምዘና ቢኖር ተሸላሚ ተሳዳቢ የሚሆን ዓይነት ሰው ነው። በሦስተኛ ደረጃ ያስቀመጥናቸው ሰድቦ አሳዳቢዎችን ሕጉም ያውቃቸዋል። እነዚህ ተሳዳቢዎች አይደለንም በናንተ ላይ ሌላ ሰው ላይ ሲሆን የሚቀፍ እጅግ አሳፋሪ፣ አስፀያፊ ወይም አስቀያሚ ትችት ሊሆን በሚችል ተግባር ቀስቅሰዋችሁ ወይም ገፋፍተዋችሁ ብትሳደቡ እና ብትከሰሱ በወንጀል ሕጉ አንቀፅ 616 መሠረት ፍርድ ቤቱ ላይቀጣችሁ ይችላል። በተለይ ምላሻችሁ ወዲያውኑ እና ከተሰደባችሁት ስድብ ጋር ተመጣጣኝ ከሆነ ሁለታችሁንም ወይም አንደኛችሁን ከቅጣት ነፃ ሊያደርጋችሁ ይችላል። ምክንያቱም እነዚህ ዓይነትን ተሳዳቢዎች ችሎ ማለፍ እንደሚከብድ ሕጉም ራሱ ተረድቶታል። በስድብ ተከሳችሁ ጉዳዩ እየታየ እያለ ያለአግባብ ነው የተሳደብኩት “ምነው ያን ቀን ምላሴን በቆረጠው!” በሚል ስሜት መጸጸታችሁን ከገለጻችሁም ፍርድ ቤቱ ቅጣቱን ሊያቀልላችሁ ይችላል። ተሳዳቢው ከሳሹን በሽማግሌ ይቅርታ ጠይቆ “አፉ ብዬሀለሁ!” ካለውም በእርቅ ክሱ እንዲቋረጥ ማድረግ ይቻላል። ስድቡ ቀላል ነው የሚባል ስድብ ወይም ማዋረድ ከሆነ፣ ነገሩ ለተሰዳቢው ለራሱም ካልገባው፣ ስድቡ ካልተሰራጨ ወይም ከሰዳቢ እና ከተሰዳቢ ውጭ ሌላ ሰው ካልተረዳው ቅጣቱም እንደ ስድቡ እና እንደ አሰዳደቡ ቀላል ነው። ይህ ዓይነቱ ስድብ በወንጀል ሕጋችን አንቀፅ 844 ስር የደንብ መተላለፍ ጥፋት በመሆኑ እስከ መቶ ብር የገንዘብ ቅጣት ወይም በስምንት ቀን የማረፊያ ቤት እስር ሊያስቀጣ ይችላል። ተሳዳቢው የተሳደበው ግዴታውን በማከናወን ላይ ያለን የመንግሥት ሠራተኛን ከሆነ ወይም ከመንግሥት ሥራው ወይንም ተግባሩ ጋር በተያያዘ መንገድ አስቦበት ከሆነ በአንፃራዊነት ቅጣቱ ከባድ ነው። ቅጣቱ ከስድስት ወር ማይበልጥ እስር እና ከአንድ ሺህ ብር ማይበልጥ መቀጮ ነው። የሀገራችንን መንግሥት በአደባባይ መስደብ፣ ማዋረድ፣ የፌዴራሉን ወይም የክልል ሰንደቅ ዓላማዎችን በተንኮል ወይም በንቀት ወይም በመሰል ማንኛውም ሐሳቦች ተነሥቶ የመስደብ፣ የመድፈር ወይም የማዋረድ ድርጊቶችም በወንጀል ሕጋችን አንቀፅ 244 እንደተደነገገው ከሦስት ወር በማያንስ እስራት ወይም በገንዘብ መቀጮ ያስቀጣሉ። የውጭ ሀገር መንግሥትን ወይም መሪን፣ በሀገራችን የሚገኘውን የውጭ ሀገር የዲፕሎማቲክ አባልን ወይም ተጠሪን መስደብ ወይም ማዋረድ፤ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላማዊ ወዳጅነት ያለውን መንግሥት የሉዓላዊነት ምልክቶችን በተለይም የዚሁ ሀገር ተጠሪ የሚያውለበልበውን አርማ ወይም ሰንደቅ ዓላማ፣ በመንግሥታት መካከል የተቋቋሙ እና ሀገራችን አባል የሆነችባቸውን ድርጅቶች ወኪልን ወይም የታወቀ ምልክቱን ባደባባይ ማዋረድም በቀላል እስር ወይም በገንዘብ መቀጮ ያስቀጣል። ይህ ዓይነቱ ክስ የሚቀርበው ግን የተሰደበው ሀገርም ተመሳሳይ ጥበቃ የሚሰጥ ሲሆን እና የሀገሪቱ መንግሥት ተሳዳቢው እንዲከሰስለት ጠይቆ የፍትሕ ሚኒስትሩ ሲፈቅዱ ብቻ ነው። “ቢቆስልም ይድናል የተደበደበ ስድብ ግን ይኖራል እንዳንገበገበ!!” ብለዋል ባለቅኔው ክቡር ዶ/ር ከበደ ሚካኤል። ስድብ አነሰም በዛ ማስከፋቱ አይቀርም። ስለዚህ ሐሳብ የመግለጽ ነፃነታችንን ስንጠቀም ስሜታዊ ባንሆን እና ሳንሳደብ ሐሳብን በሐሳብ በመሞገት ወይም መልካም ቃላትን ብቻ በመጠቀም ብንተች ወይም ብንቃወም ይመረጣል። የስድብ እና የማዋረድ ተግባር ላይ በተለያየ መልኩ ምንሳተፍ ሰዎችም የሕጉን ኃላፊነት ፈርተን ብቻ ሳይሆን ይህን የተወገዘ ተግባር ማስወገድ ይኖርብናል። ስናጠቃልለውም "ክፉ ምላስ" በሚል ርዕስ የተጻፈውን እና በመግቢያችን ላይ የጠቀስነውን የሃይማኖት አባቶችን መልዕክት ተግባራዊ በማድረግ እና የራሳችንንም ኅሊና አክብረን ባለመሳደብ፣ ለሌሎችም አርአያ በመሆን፣ ጨዋነትን ማሳየት በየእምነታችን የሚጠበቅብን ግዴታ ከመሆኑም ባሻገር ከጠቀስናቸው በስድብ ምክንያት ሊመጡ ከሚችሉ የወንጀል ቅጣቶችም ያድነናልና ልብ ልንለው እና ተግባራዊ ልናደርገው ይገባል። ፔጃችንን ስለሚከታተሉ እና እንዲሁም ስለሚሰጡን አስተያየት እናመሰግናለን !!🙏
نمایش همه...
👍 2
Share ክፉ ምላስ በሕግ ዐይን - በመሳደብዎ ሕግ እንደሚቀጣዎ ያውቃሉ.docx
نمایش همه...
ባለዉ የመጀመሪያ ቀጠሮ ካልቀረበ ነበር፡፡ ያለዉ አሰራር ግን ሁለት የክርክር ቀን የዘረጋ በመሆኑ በአንዱ ያመለጠዉ በሌላዉ የሚገባበት፣የመጀመሪያዉን ቀጠሮ አክብሮ የቀረበ ወገን በሁለተኛዉ የክርክር ዘርፍ ባለመገኘቱ ከክርክሩ ዉጪ የሚደረግትን ወጥነት የሌለዉ አሰራር እንዲዘረጋ አድርጓል፡፡ ይህ የሆነበት ዋና ምክንያት ሕጉ አንድ ጊዜ ያደረገዉን ክስ መስማት በልምድ ሁለት ጊዜ እንዲደረግ በመደረጉ ነዉ፡፡ ሶስተኛዉ ችግር ለቀጠሮ መራዘም እና መጓተት ምክንያት መሆኑ ነዉ፡፡ የሥነ-ሥርዓት ሕግ ዋና ዓላማዉ ክርክሮች በተፋጠነ፣ግልጽ እና ወጪ ቆጣቢ በሆነ መልኩ ክርክሮች እንዲቋጩ ማድረግ ነዉ፡፡ ይህን ለማሳካትም በሥነ-ሥርዓት ሕጉ የተቀመጠዉ የእያንዳንዱ ቀጠሮ ጊዜዉ እና ሂደቱን ጠብቆ በጥብቅ መፈፀምን ይጠይቃል፡፡ ከሥነ-ሥርዓት ዉጪ ክስ መስማትን የመቃወሚያ እና የፍሬ ነገር ክርክር ብሎ በሁለት ዘርፍ ማከራከር በአንድ ቀን የሚያልቅን ስራ በሁለት ቀን እንደመስራት የሚያስቆጥር ነዉ፡፡ ይህ አሰራር ደግሞ የፍርድ ቤቶችን ጊዜ እና አቅም ከማባከኑ በተጨማሪ ተከራካሪ ወገኖች ላልተፈለገ ጊዜ ክርክራቸዉ እንዲራዘም ያደርጋል፡፡  በተጨማሪም የክርክሩ ዘርፍ በመቃወሚያ እና በፍሬ ነገር ተብሎ የሚከፈል በመሆኑ በመሃከል ያልተፈለጉ መጓተቶች እንዲፈጠሩ ምክንያት ይሆናል፡፡ እንደ መዉጫ! በተነሱት ሶስት ጉዳዮች ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ማስተካከል የሚቻለዉ ሕጉን እንደ ተፃፈ በመተግበር መሆኑ የሚታመን ቢሆንም በአንዳንድ ሁኔታዎች ላይ ችግሩን ለመፍታት ሕጉን እና አሰራሩን ማቀናጅትና ማስተሳሰር ይጠይቃል፡፡ የመጀመሪያዉን ጉዳይ በተመለከተ በተከራካሪዎች የሚቀርቡ ክርክሮችን ከመጀመሪያዉ ጀምሮ ማስረጃዎችንም የሚያካትት መሆን ይኖርበታል፡፡ ከሳሽ በማስረጃ ዝርዝሩ በፍርድ ቤት እንዲቀርብለት የሚጠይቀዉ ማስረጃ ካለ አስቀድሞ ማስረጃዉ ተሰብስቦና ተጠቃሎ ተከሳሹ መልስ እንዲሰጥበት ሊደረግ ይገባል፡፡ ተከሳሹም መልስ ሲሰጥ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዲቀርብለት የሚጠይቀዉ ማስረጃ ካለ መልስ ማቅረቡን ተከትሎ ማስረጃዉ ቀድሞ እንዲቀርብ እና የክስ መስማቱ አካል እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በክርክር ሂደት ለትክክለኛ ፍትሕ  አስፈላጊ ሲሆን ማስረጃ እንዲቀርብ የሚደረግበት ሁኔታ ቢኖርም ማስረጃ የማሰባሰቡ ስራም ከክስ መስማት በፊት ሊጠናቀቅ ይገባል፡፡ ይህንን ማድረግ ከተቻለ ክርክሩ ከተጠናቀቀ በኋላ የሰነድ ማስረጃ እንዲቀርብ እየተባለ የሚሰጠዉን እና ከዋናዉ ክርክር ያልተናነሰ መመላለስ የሚፈጀዉን ሌላ የክርክር ምዕራፍ ማስቀረት ይቻላል፡፡ በተጨማሪም ፍርድ ቤቶች በተከራካሪዎች ጠያቂነት የሚመጡ ማስረጃዎች ተከራካሪዎች ራሳቸዉ ማቅረብ የማይችሏቸዉ መሆናቸዉን ማረጋገጥና መመርመር ይኖርባቸዋል፡፡ ይሄም ፍርድ ቤቶች አከራክሮ የመወሰን ሚናቸዉን እንዲያስጠብቁ ይረዳል፡፡ ሁለተኛዉ ጉዳይ በተመለከተ ከፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 238(1) ድንጋጌ ይዘት እና ክስና መልስ በሬጅስትራር ተመርምረዉ እንዲቀርቡ ከሚደረግበት ዓላማ  አንፃር በሬጅስትራር በኩል መልስ የማቀባበል ስራ መሰራቱ ተገቢነት አጠያያቂ ሊሆን የሚገባ አይደለም፡፡ ሆኖም አሰራሩን ከሥነ-ሥርዓት ሕጉ ጋር አዋህዶ መፈፀም የማይቻል ከሆነ ክርክሩ ላይ አሉታዊ ዉጤት ይኖረዋል፡፡ መልስ በሬጅስትራር በሚቀባበልበት ዕለት የቀጠሮ ምክንያት ባለመፈፀሙ ወይም የሚቀርቡ መልሶችን ተከትሎ  ተለዋጭ ትዕዛዝ መስጠት አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ በዕለቱ መዝገቡ ዳኛዉ ፊት ቀርቦ ትዕዛዝ የሚሰጥበት ሁኔታ እንዲኖር ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ይህን ማድረግ ዳኞች ከሚኖራቸዉ የቀጠሮ ፖሊስ ወይም በዕለቱ ሊኖራቸዉ ከሚችለዉ ሌላ ስራ አንፃር ምቹ ሊሆን እንደማይችል የሚጠበቅ ቢሆንም ሥነ-ሥርዓት ሕጉ  የሚለዉ እንዲፈጸም ከተፈለገ ብቸኛ አማራጭ በዕለቱ  ትዕዛዝ እንዲሰጥ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ይህንን ተግባራዊ ማድረግ ካልተቻለ አሰራሩ በክርክሩ ከሚኖረዉ አዎንታዊ ዉጤት ይልቅ አሉታዊ ዉጤቱ እንዲጎላ ያደርገዋል፡፡ መልስ ለመቀበል በተቀጠረበት ዕለት መሰጠት ያለባቸዉ ትዕዛዞች በቀጠሯቸዉ ቀን እንዲሰጡና የተገለፁት ችግሮች እንዲቀረፍ መልስ የማቀባበሉ ስራ በችሎት ሊሆን የሚገባዉ ነዉ፡፡ ሶስተኛዉ ጉዳይ መቃወሚያ እና ፍሬ ነገርን ለያይቶ ክስ የሚሰማበት ስርዓትን በተመለከተ ሕጉ ግልጽ እና የማያሻማ በመሆኑ ሕጉን መተግባር ያስፈልጋል፡፡ ሥነ-ሥርዓት ሕጉ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ቀድሞ መወሰን አለበት በማለት በግልፅ ያስቀመጠዉ ክስ የሚሰማበትን ቀን ከሁለት ለመክፈል አስቦ ሳይሆን በፍሬ ነገሩ ላይ ማስረጃ ከመሰማቱ እና ከመመዘኑ በፊት በመቃወሚያ የሚቋጭ ከሆነ በአጭር ዕልባት እንዲያገኝ በሚል ነዉ፡፡ ክስና መልስ ሲሰማ በክሱና መልሱ የተጠቀሱ መከራከሪያዎች ሁሉ ተነስተዉ ክርክር የሚደረግባቸዉ እንደመሆኑ ክስ መስማቱን ለመቃወሚያ እና ለፍሬ ነገር ብሎ መክፈል አያስፈልግም፡፡ ከክስ መስማት ቀጥሎ ያለዉ የክርክር ሂደት ዋናዉ ሙግት የሚጀመርበት ወይም ግራ ቀኙ በፍሬ ነገሩ ላይ በተያዘዉ ጭብጥ ላይ ማስረጃዎቿቸዉ የሚያስረዱላቸዉን ነገር እያስመዘገቡ ማስረጃ የሚያሰሙበት የክርክር ሂደት እንደሆነ ግልፅ ነዉ፡፡ መቃወሚያዉ ቀድሞ መወሰን አለበት የሚባለዉም ፍሬ ነገሩን መነሻ በማድረግ ማስረጃ ከመሰማት ወይም ከመመርመሩ በፊት እንጅ በፍሬ ነገሩ ላይ ክርክር ከመደረጉ በፊት አለመሆኑን መረዳትና ሥነ-ሥርዓቱን በትክክል መተግበር ያስፈልጋል እንላለን ፡፡ ፔጃችንን ስለሚከታተሉ እንዲሁም ስለሚሰጡን አስተያየት እናመሰግናለን !!
نمایش همه...
እንዲቀርብ የሚሰጠዉ ትዕዛዝ ራሱን የቻለ የክርክር ምዕራፍ ሲሆን ይታያል፡፡ በቀረበዉ ማስረጃ ላይ ግራ ቀኙ የየራሳቸዉን ሃሳብ ስለሚያቀርቡበት ነገሩን ለማጣራት ተደጋጋሚ ትዕዛዞች ስለሚሰጡ ረጅም ጊዜ ይወስዳል፡፡ ክሱ ሲቀርብ ጀምሮ ቅድሚያ እንዲቀርብ ቢደረግ ማስረጃዉ ላይ የሚደረገዉ ማጣራት እኩል ከክርክሩ ጋር ሊጠናቀቅበት የሚችልበት እድል አለ፡፡ያለዉ አሰራር  ግን ማስረጃዉ ቅድሚያ ስለማይቅርቡና ነገሩ ሊወሰን ሲል እንዲቀርብ ስለሚደረግ ሌላ የክርክር ምዕራፍ ሆነ እንዲቀጥል ያደርገዋል፡፡ይህ ሁኔታ አንድ ክርክር መጠናቀቅ የሚኖበትን ጊዜ እንዲራዘም የማድረግ ዉጤት እንዲኖረዉ ከማድረግ አልፎ በአንድ ክርክር ሁለት የክርክር ምዕራፍ እንዲኖር እያደረገ ይገኛል፡፡ ለ. መልስ በሬጅስትራር ማቀባበል   አንድ ክስ ተከፍቶ ሲቀርብ  ጉዳዩ ለሚመራለት ችሎት ከመቅረቡ በፊት ሬጅስትራር የቀረበዉ የክስ አቤቱታ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 222 መሰረት አንድ ክስ ማሟላት ያለበትን ነገሮች አሟልቶ መቅረቡን፣ከክሱ ጋር የሚቀርቡ ሰነዶች ዋናዎቹንና ግልባጮቹን እና በከሳሹ የቀረበ መሆኑን የማረጋገጥ ስራ እንደሚሰራ በግልጽ በፍትሐ ብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕጉ ተደንግጓል፡፡ ሬጅስትራር ክስን መርምሮ እንደሚያሳለፍ ሁሉ መልስ እንደሚቀበል በሕጉ በግልፅ የተቀመጠ ነገር ባይኖርም አመላካች ድንጋጌዎች አሉ፡፡  ሬጅስትራር ክሱ ላይ የሚመረምረዉ ነገር፣ዋናዉ እና ግልባጩን የሚያረጋግግጠዉ ሰነድ እንዲሁም በሚመለከተዉ አካል መቅረቡን የማረጋገጥ ስራ በተመሳሳይ መልስ ሲቀርብ የሚሰራ በመሆኑ  መልሱን መርምሮ መቀበሉ ከሕግ ዉጪ ነዉ ሊያስብለዉ የሚችል አይደለም፡፡ የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 238(1) ድንጋጌ መንፈስም መረዳት የሚቻለዉ መከላከያ ማስረጃ ሲቀርብ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 229 በተቀመጠዉ መሰረት በሬጅስትራር በኩል ሊመረመር እንደሚገባ ነዉ፡፡ ካለዉ ጥቅም አንፃር ሲታይም መሰረታዊ ከሆኑ የዳኝነት ስራዎች ወጪ የሆኑ ጉዳዮች በሬጅስትራር መረጋገጣቸዉ ለስራዉ ዉጤታማነት ተገቢ ከመሆኑም በላይ የዳኞችን የስራ ጫና የመቀነስ ዉጤት ይኖረዋል፡፡ ሆኖም መዝገብ ተከፍቶ ክሱ ከዳኛ ፊት ቀርቦ ክርክሩን ለማስቀጠል ለችሎት ከተመራ በኋላ መልስ ለማቀባበል ወደ ሬጅስትራር የሚመለስበት አሰራር የስራዉን ጥራት ከማረጋገጥ እና ጫናዉን ከማቅለል ባለፈ ምን ዓይት ዉጤት እንደሚኖረዉ መመልከት ያስፈልጋል፡፡ ዉጤቱን ለመመዘን በቅድሚያ ለመልስ መቀባበል ወደ ሬጅስትራር የሚመለስበት አሰራር ማየት ተገቢ ነዉ፡፡ አሁን ባለዉ የፍርድ ቤቶች አሰራር መዝገብ ተከፍቶ ለችሎት ሲቀርብ  ዳኛዉ ሁለት ቀጠሮዎችን ይሰጣል፡፡ አንዱና ቀዳሚዉ ቀጠሮ በሬጅስትራር በኩል መልስ ለመቀባበል ሲሆን ቀጣዩ ቀጠሮ ለክስ መስማት ተብሎ የሚሰጥ ነዉ፡፡ መልስ ማቀባበሉ ስራ በሬጅስትራር ከተከናወነ ቀጣዩ ቀጠሮ ክስ መስማቱ ይሆናል፡፡ ከዚህ አሰራር ጋር ተያይዞ የሚነሳዉ በሬጅስትራሩ የመልስ ማቀባበሉ ቀጠሮ ባልተፈፀመ እና መልስ ለማቀባበል በሚቀጠርበት ዕለት  ተለዋጭ ትዕዛዞች  መሰጠት በሚያስፍልግበት  ወቅት ምን መሆን ይኖርበታል የሚለዉ ነዉ፡፡ ባለዉ አሰራር በሬጅስትራር መልስ ቀረበ አልቀረበ፣ተለዋጭ ትዕዛዝ መስጠት ቢያስልግ ባያስፈልግም በዕለቱም ምንም የሚባል ነገር አይኖርም፡፡ ሬጅስትራሩ በዕለቱ የቀረበዉን ነገር በመመዝገብ ቀደም ብሎ ተቀጥሮ ለነበረዉ ክስ መሰማት ቀጠሮ መዝገቡን ያስተላልፋል፡፡ በዚህ አሰራር መልስ ለመቀበል በተቀጠረበት ዕለት ሊፈፀሙ የሚችሉ ተግባሮች ሳይከናወኑ ክስ በሚሰማበት ቀጠሮ ዳኛዉ እንዲፈጽማቸዉ እንዲሻገሩ ይደርጋል፡፡ ነገሩን ግልጽ ለማድረግ መልስ በሚቀባበልበት ወቅት ሊሰጡ የሚችሉ ትዕዛዞችን ማየት አስፈላጊ ነዉ፡፡ መልስ ለመቀበል በተቀጠረበት ዕለት መልስ ሊቀርብም ላይቀርብም የሚችልበት እድል ይኖራል፡፡ በዚህ ቀጠሮ ሊሰጡ ከሚችሉት የትዕዛዝ አማራጮች ዉስጥ  አንደኛ ተከሳሹ መጥሪያ ደርሶት ካልቀረበ ወይም በራሱ ጉድለት ምክንያት መልሱን ሳያቀርብ ከቀረ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 199(1) መሰረት በዚያዉ በቀጠሮዉ ቀን የጽሁፍ መልስና ማስረጃዎቹን የማቅረብ መብቱ የሚታለፈዉ (default proceeding) ነዉ፡፡ ሁለተኛ  ተከሳሽ መልሱን ይዞ ቀርቦ የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ወይም የመቻቻል ጥያቄ ካቀረበ ክስ ከመሰማቱ በፊት ከሳሽ መልስ እንዲሰጥበት ትዕዛዝ የሚሰጥበት ነዉ፤ይህም የሚደረገዉ መልስ በቀረበ በዕለቱ ነዉ፡፡ ሶስተኛ ተከሳሹ መልስ ሲሰጥ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 40(2) በአባሪነት ወይም በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 43 መሰረት ዋቢ እንዲገባለት የሚጠይቀዉ ወገን ካለ በተመሳሳይ  ትዕዛዙ የሚሰጠዉ የመልስ መቅረቡን ተከትሎ ነዉ፡፡ አራተኛ ከሳሽ  መጥሪያ ለማድረስ ተከሳሹ ያላገኘዉ መሆኑን ከገለፀ አማራጭ የመጥሪያ አፈፃፀም ሂደቶች እንዲፈጸሙ ትዕዛዝ የሚሰጠዉም መልስ ለመቀበል በተቀጠረበት ዕለት ነዉ፡፡ አምስተኛ ከሳሽ ለተከሳሽ ክሱን ለማድረስ መጥሪያ ወጪ ካላደረገና ክርሩን ሳይከታል ከቀረ፣ መጥሪያ ወጪ  ካደረገ በኋላ መጥሪያ ማድረሱን ወይም የገጠመዉን ነገር ቀርቦ ካላስረዳ ለተከሳሽ መጥሪያ መድረስ አለመድረሱ ሳይረጋገጥ ወደ ፊት ቀጠሮ ሊሰጥ ስለማይችል በተመሳሳይ የቀጠሮዉ ምክንያት በከሳሽ ጉድለት እንዳልተፈጸመ ተቆጥሮ መዝገቡ እስከ መዝጋት የሚደርስ ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡ እነዚህ ትዕዛዞች ሁሉ መልስ ለመቀበል በተቀጠረበት ዕለት ሊሰጡ የሚችሉ ናቸዉ፡፡ ትዕዛዞቹም የሚሰጡት በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 199(1) መሰረት በዚያዉ ቀጠሮ እንጅ ሌላ ቀጠሮ ጠብቀዉ  ሊሆን እንደማይገባ ግልጽ ነዉ፡፡  በተግባር ባለዉ አሰራር ወይም በሬጅስትራር መልስ በመቀባበሉ ምክንያት መልስ ለመቀበል በተቀጠረበት ዕለት ሊሰጡ የሚችሉ ትዕዛዞች ሁሉ በዕለቱ እንዳይሰጡ የማድረግ ዉጤት አስከትሏል፡፡ ይህ የሆነበት ዋና ምክንያት መልስ በሬጅስትራር የማቀበባል ስራ በሚሰራበት ዕለት መልስ ካልቀረበና መልስ ቀርቦም ተለዋጭ ትዕዛዝ መስጠት ካስፈለገ በዕለቱ ትዕዛዝ የሚሰጠበት አሰራር ስላልተፈጠረ ነዉ፡፡ አሰራሩ ክስ ለመስማት በተቀጠረበት ዕለት ዳኛዉ የሚጠብቀዉን ክስ የመስማት ስራ ብቻ እንዳይሆን አድርጎታል፡፡ ክስ በሚሰማበት ዕለት ዳኛዉ የሚጠብቀዉ ስራ ክስ መስማት ብቻ ሳይሆን መልስ መቅረብ አለመቅረቡን፣ መልስ ካልቀረበ መጥሪያ የደረሰ መሆን አለመሆኑን፣ መልስ ከቀረበም የተከሳሽ ከሳሽነት ወይም የመቻቻል ጥያቄ መቅረብ አለማቅረቡን፣በክርክሩ አባሪ ወይም ዋቢ እንዲገባ የተጠራ ወገን መኖር አለመኖሩን የማረጋገጥ እንዲሁም መጥሪያ ደርሶ መልስ ካልቀረበ መልስ የማቅረብ መብትን የማለፍ ስራ ይጠብቀዋል፡፡ በሌላ አገላለጽ  ክስ በሚሰማበት ዕለት ዳኛዉ ትኩረቱ ክስ መስማት ላይ ብቻ ሳይሆን ክስ ከመሰማቱ በፊት ባሉ ሂደቶች ሊፈፀሙ የሚገባቸዉ ነገሮች መሟላት አለመሟላታቸዉን ተመልሶ እንዲያጣራ የሚያደርግ ነዉ፡፡ ከጅምሩ ክስ ለመሰማት መቀጠር ያለበት ክስ ከመሰማቱ በፊት ያሉ ሂደቶች መፈፀማቸዉ ተረጋግጦ ነዉ፡፡ ከክስ መሰማት በፊት ያሉ ሂደቶች ገና ይፈፀማሉ በሚል በታሳቢነት ክስ ለመስማት እንዲቀጠር ሥነ-ሥርዓት ሕጉ አይፈቅድም፡፡ አሰራሩ በተለያዩ የክርክር ሂደቶች የሚሰጡ ትዕዛዞችንም በአንድ ላይ በመስጠት ሥነ-ሥርዓት ሕጉ የክርክር ሂደት ላይ ብዥታን ይፈጥራል፡፡ ለምሳሌ፡-በሥነ-ሥርዓት ሕጉ የተለያዬ ሂደት ያላቸዉን   የጽሁፍ መልስና ማስረጃዎቹን የማቅረብ መብትን ማለፍ (default proceeding) እና በሌለበት (ex-parte) በአንድ ቀጠሮ እንዲሰጡ የማድረግ ዉጤትን ይፈጥራል፡፡ መጥሪያ ባልደረሰ እና
نمایش همه...
በፍትሐብሔር ክርክር ቅድመ-ሙግት ሂደት ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ከህጎቻችን አንጻር ሲቃኝ የዚህ ጽሑፍ ዋና ትኩረት  ከሙግት በፊት ያሉ ሥነ-ሥርዓታዊ ሂደቶች አንድን ክርክር ላይ ያላቸዉን  ሚና ማጉላት እና ፋይዳቸዉን ማሳየት ነዉ፡፡ በፍትሐ ብሔር ክርክር ሂደት ቅደመ ሙግት የሚባለዉ ለክርክሩ መሪ ጭብጥ ተይዞ ግራ ቀኙ ማስረጃ ማሰማት ከመጀመራቸዉ በፊት ያለዉ ሂደት ነዉ፡፡ በፍትሐ ብሔር ክርክር ዋናዉ ሙግት የሚጀምረዉ ጭብጥ ተይዞ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 257 እና ተከታይ ድንጋጌዎቹ ተከራካሪዎች ማስረጃዎቻቸዉ የሚያስረዷቸዉን ጭብጥ እያስመዘገቡ ማስረጃ ማሰማት ሲጀምሩ ነዉ፡፡ ከዋናዉ ሙግት በፊት ባለዉ  የቅድመ ሙግት ሂደት በዋናነት ክስና ማስረጃ ማቅረብ፣ መጥሪያ ማድረስ፣ መልስ እና ማስረጃ መቅረብ፣ ክስ መሰማት እና የክስ መቃወሚያዉ ላይ የመወሰን ተግባሮች ይፈፀማሉ፡፡ ይህ የክርክር ሂደት ክርክሩን ለመምራት ዋና መሰረት የሆነዉ ነዉ፡፡ የክርክሩ አቅጣጫ የሚወሰነዉም በዚህ የክርክር ደረጃ ላይ  በሚሰሩ ስራዎች ነዉ፡፡ ክርክሩን ግልፅ እና አጭር በሆነ ሂደት ለመፈፀም የሚያስችለዉም የቅድመ ሙግት ሂደቱ ጤናማ መሆን ከቻለ ነዉ፡፡ ክርክሩ ሳይንዛዛ እንዲያልቅ ከተፈለገ በቅደመ ሙግት ሂደት መከናወን ያለባቸዉ ነገሮች ሁሉ ጥንቅቅ ብለዉ መከናወን ይጠበቅባቸዋል፡፡ ክርክሩ ወደ ኋላ እንዳይመለስ ከተፈለገም በቅድመ ሙግት ሂድት የሚከናወነዉ መጥሪያ አደራረስ ሰርዓት በተገቢዉ መንገድ መፈፀም ይኖርበታል፡፡ ከሙግት በፊት በዳኛዉ ሆነ በሬጅስትራር  ሊከናወኑ የሚገቡ ብዙ ጉዳዮች ያሉ ቢሆንም ለዚህ ጽኁፍ ዓላማ ሲባል ሶስት ጉዳዮች ላይ ብቻ ትኩረት ይደረጋል፡፡ የመጀመሪያዉ ክስ እና መልስ ሲቀርብ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 145 መሰረት እንዲቀርብ የሚጠየቀዉን ማስረጃ ይመለከታል፡፡ ሁለተኛዉ መልስ በሬጅስትራር የማቀባበል ስርዓት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጉዳዮች ናቸዉ፡፡ ሶስተኛዉ ክስ ከመስማት ጋር በተገናኘ መቃወሚያ እና ፍሬ ነገር ክርክሮች የሚደረጉበት ሁኔታ ይመለከታል፡፡ ይህ ጽሑፍም ሶስቱን ጉዳዮች በሕግ ያላቸዉን ማዕቀፍ እና ተግባራዊ አፈፃፀማቸዉን በመዳሰስ ከሥነ-ሥርዓት ሕጉ ዓላማ አንፃር ለክርክር ፍጥነት፣ ግልፅነት እና ፍትሐዊነት ያላቸዉን አስተዋጽዖ ይዳስሳል፡፡ ሀ. በፍ/ብ/ስ/ሕ/ቁ 145 መሰረት በፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሚቀርብ ማስረጃ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 145 መሰረት የሚቀርቡ ማስረጃዎች በሁለት ዓይነት ሁኔታ የሚቀርቡ እንደሆኑ ከድንጋጌዉ መረዳት ይቻላል፡፡ አንደኛዉ አማራጭ ፍርድ ቤቶች በራሳቸዉ አስተያየት እንዲቀርብ ትዕዛዝ የሚሰጡት ሲሆን   እንደ ነገሩ ሁኔታ ፍርድ ቤቱ ትክክለኛ ፍትሕ ለመስጠት እና ነገሩን ለመወሰን አመች ነዉ ብሎ ሲያምን  በማንኛዉም የክርክር ደረጃ ሊቀርብ የሚችል ነዉ፡፡ ሁለተኛዉ አማራጭ ተከራካሪ ወገኖች ሲያመልክቱ የሚቀርብ ነዉ፡፡ በተከራካሪዎች አመልካችነት እንዲቀርብ የሚጠየቀዉ ማስረጃ አቀራረብ ፍርድ ቤቱ በራሱ አስተያየት ከሚያስቀርበዉ የተለዬ መንገድ ይከተላል፡፡  በመርህ ደረጃ ተከራካሪ  ወገኖች ማስረጃዎቻቸዉን ሁሉ ከክስ እና መልሳቸዉ ጋር አጠቃለዉ ማቅረብ ስላለባቸዉ እንደፈለጉ  እና በፈለጉት የክርክር ደረጃ የሚያቀርቡበት እድል በሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ ነዉ፡፡ ከጅምሩ ተከራካሪ ወገኖች በፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዲቀርቡላቸዉ የሚጠይቋቸዉ ማስረጃ ማንኛዉንም ማስረጃ ሳይሆን ማቅረብ የማይችሉትን ማስረጃ ነዉ፡፡ እነዚህ ማስረጃዎች ደግሞ በበቂ ምክንያት ወይም ሳይገኙ ቀርተዉ በክርክሩ ሂደት እንዲቀርቡ ካልተጠየቀ የግዴታ ክስ እና መልስ ሲቀርብ በማስረጃ ዝርዝር እንዲቀርቡ የሚጠየቁ ናቸዉ፡፡ ክስ እና መልስ ሲቀርብ ማስረጃም አብረዉ እንዲቀርቡ የሚያስፈልገበት ዋና ዓላማ የክርክሩ መናሻ አካል የሚሆኑት በክሱ እና በመልሱ የጠቀሱት ጉዳዮች ብቻ ሳይሆን በግራ ቀኙ የሚቀርቡ ማስረጃዎችም የክርክሩ አካል መሆን ስለሚኖርባቸዉ ነዉ፡፡የክርክር ጭብጥም የሚመሰረተዉ በክስና መልስ ከተገለፁ ነገሮች ብቻ ሳይሆን ማስረጃዎችም የጭብጥ አካል ሆነዉ ምዘና ስለሚደረግባቸዉ የግድ ቀድመዉ እንዲቀርቡ ይጠበቃል፡፡ በፍ/ብ/ስ/ሕ/ቁ 233 ተከሳሽ ለክሱ መልስ እንዲሰጥ የሚላክለት ክሱ እና ከክሱ ጋር የቀረበዉ ማናቸዉም በአስረጅነት የቀረቡ ማስረጃ ጭምር እንደሆነ ይገልፃል፡፡ ይህ የሚያመለክተዉ ተከሳሽ መልስ የሚሰጠዉ በክሱ ለተገለፁ ጉዳዮች ብቻ ሳይሆን በማስረጃዎችም ላይ እንደሆነ ነዉ፡፡ በተመሳሳይ ከሳሽ ክስ ሲያቀርብ ማቅረብ የማይችለዉ ማስረጃ እንዳለ ገልፆ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 145 መሰረት ማስረጃ እንዲቀርብለት በሚጠይቀዉ ማስረጃ ላይም ተመሳሳይ ዉጤት ይኖረዋል፡፡ ክሱ ለተከሳሽ ከመድረሱ በፊት ከሳሽ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 145 እንዲቀርብለት የጠየቀዉ ማስረጃ ክሱ ለተከሳሽ ከመላኩ በፊት እንዲቀርበ ተደርጎ  ከክሱ ጋር በተከሳሽ መልስ እንዲሰጥበት ይጠበቃል፡፡ ተከሳሽ መልስ ሲያቀርብ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ማስረጃ እንዲቀርብለት ከጠየቀ ማስረጃዉ ክስ ሲሰማ ቀርቦ የክርክሩ አካል እንዲሆን ያስፈልጋል፡፡ በተግባር የሚታየዉ ከዚህ የተለየ ነዉ፡፡ በፍርድ ቤት በሚቀርቡ በአብዛኛዉ ተከራካሪ ወገኖች በፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዲቀርቡላቸዉ የሚጠይቋቸዉ ማስረጃዎች ከሁለት መመዘኛዎች አንፃር በተግባር ያለዉን ክፍተት የሚያሳዩ ናቸዉ፡፡ አንደኛዉማስረጃዎች በፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ሊያሟሉ የሚገባቸዉ ሁኔታዎች ባልተሟሉበት ሁኔታ ማስረጃዎች እንዲቀርቡ የሚታዘዝበት አሰራር ነዉ፡፡ በሥነ-ሥርዓት ሕጉ በግልፅ እንደተቀመጠዉ ተከራካሪዎች በፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዲቀርብ ሊጠይቁ የሚችሉት ማስረጃዉን በራሳቸዉ ለማቅረብ የማይችሉ መሆኑን ሲያሳዩ ነዉ፡፡ ሆኖም በተግባር ተከራካሪዎች በራሳቸዉ ሊያቀርቧቸዉ የሚችሉትን ማስረጃዎች ሁሉ እንዲቀርቡላቸዉ ሲጠይቁ ይታያል፡፡ ለምሳሌ፡- በአንድ ፍርድ ቤት መዝገብ የተሰጠን ዉሳኔ ማስረጃ ማድረግ የሚፈልግ ተከራካሪ ወገን በራሱ የዉሳኔ ግልባጭ ጠይቆ ማግኘት እና ከማስረጃዎቹ ጋር ማቅረብ እየቻለ ፍርድ ቤቱ እንዲያስቀርብ ሲጠየቅ ይስተዋላል፡፡ ፍርድ ቤቶችም ተከራካሪዎች ማቅረብ የሚችሉትን ማስረጃ ራሳቸዉ እንዲያቀርቡ ከማስደረግ ይልቅ እንዲቀርብ ትዕዛዝ የሚሰጡበት ሁኔታ ፍርድ ቤቶችን አከራክሮ ከመወሰን ሚናቸዉ አዉርዶ  ተከራካሪዎችን በመተካት ማስረጃ የማሰባሰብ ስራ እንዲሰሩ ያደርጋቸዋል፡፡ ተከራካሪዎች ራሳቸዉ ማቅረብ የሚችሉት ማስረጃ ፍርድ ቤት ለማስቀረብ ትዕዛዝ ሲሰጥም ለተጨማሪ ቀጠሮ ምክንያት ስለሚሆን ክርክር የማራዘም ዉጤት ይኖረዋል፡፡ ሁለተኛዉ መመዘኛ ማስረጃዉ የሚቀርብበት የክርክርን ደረጃ ይመለከታል፡፡  በተግባር ያለዉ አፈፃፃም ከሳሽ ክስ ሲያቀርብ እንዲቀርብለት የሚፈልገዉን ማስረጃ በማስረጃ ዝርዝሩ ገልፆ ቢያቀርብም ቀድሞ ማስረጃዉ ቀርቦ ተከሳሽ መልስ እንዲጥበት ሲደረግ አይታይም፡፡ በተመሳሳይ ተከሳሽ መልስ ሲሰጥ በማስረጃ ዝርዝሩ እንዲቀርብለት ቢጠይቅም ቀድሞ ቀርቦ ክስ ሲሰማ የክርክሩ አካል አይደረግም፡፡ በአብዛኛዉ ተከራካሪዎች እንዲቀርቡላቸዉ የሚጠይቋቸዉ ማስረጃዎች እንዲቀርቡ የሚደረጉት ክስ ተሰምቶ፣ምስክር ተሰምቶ ክርክሩ ከተጠናቀቀ በኋላ ክርክሩ ሊወሰን ጫፍ ሲደርስ ነዉ፡፡ የሚቀርቡ ማስረጃዎች ላይ ግራ ቀኙ በጽኁፍ አስተያየት እንዲሰጡበት እድል የሚሰጥበት ሁኔታ ቢኖርም ማስረጃዎች የሚቀርቡት ክርክሩ ከተጠናቀቀ በኋላ በመሆኑ ራሱን የቻለ ሌላ የክርክር ምዕራፍ እንዲኖረዉ አድርጓል፡፡ በሌላ አገላጽ ክርክሩ ከተጠናቀቀ በኋላ የሰነድ ማስረጃ
نمایش همه...
ተለዋጭ ትዕዛዝ በሚሰጥበት ወቅትም ክስ ለመስማት የተቀጠረዉን ቀጠሮ  ቀይሮ ወደ ኋላ ይመልሰዋል፡፡  በተጨማሪም ሕጉ በሚያስቀምጠዉ መሰረት በቀጠሮዉ ዕለት መሰጠት ያለባቸዉ ትዕዛዞች በሙሉ እንዳይሰጡ ያደርጋል፡፡ ይህ አሰራር  ደግሞ ሥነ-ሥርዓታዊ ካለመሆኑ በተጨማሪ ለአንድ ቀጠሮም ቢሆን ክርክሩን የማራዘም ዉጤት ይኖረዋል፡፡ ተከራካሪ  ወገኖችንም ለድካም እና ለእንግልት ይዳርጋል፡፡ ሐ. ክስ መስማት ከክስ መስማት ጋር በተገናኘ በተለይም የክስ የመጀመሪያ ደረጃ  መቃወሚያ በቀረበበት ክርክር  በተለያየ መልኩ ክሱ ሲሰማ ይስተዋላል፡፡ አብዛኛዉ በሚባል ደረጃ በፍርድ ቤቶች ያለዉ አሰራር  ክስ  ሁለት ጊዜ የሚሰማ ሲሆን መቃወሚያዉ እና ፍሬ ነገር ክርክር ተብሎ በመነጣጠል የሚሰማ ነዉ፡፡ በፍሬ ነገሩ/በዋናዉ ጉዳይ ላይ ክስ የሚሰማዉ የክስ መቃወሚያዉ ከታለፈ ብቻ ሲሆን የክስ መቃወሚያ በፍሬ ነገሩ ወይም በዋናዉ ጉዳይ ላይ ከመገባቱ በፊት መወሰን አለበት ከሚል አስተሳሰብ የመጣ ነዉ፡፡ ይህ አሰራር እያደበረ በመምጣቱ ተገቢነቱና አዋጭነቱ  ከሥነ-ሥርዓት ሕጉ እና ዓላማዉ  አንፃር መዳሰስ አስፈላጊ ነዉ፡፡ ክስ የሚሰማዉ በጽሑፍ ክስ እና መልስ ተሰብስቦ እንዳበቃ ቀጥሎ ባለዉ የመጀመሪያዉ ቀነ ቀጠሮ እንደሆነ ግልፅ ነዉ፡፡  ክስ የሚሰማበት ሂደት በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 241 በተቀመጠዉ መሰረት ሲሆን ተከራካሪ ወገኖች አለመቅረባቸዉ የሚያስከትለዉን ዉጤት የሚገልጹት ድንጋጌዎች የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 69(2)፣70(ሀ) እና 73 ክርክሩ እንዲሰማበት የተወሰነዉ ዕለት የሚሉትም ከመልስ መቀባበል ቀጥሎ ያለዉን የመጀመሪያ ቀነ ቀጠሮ  ነዉ፡፡ በዚህ ዕለት ተከራካሪዎች ስላቀረቡት ክስ እና መልስ ግልጽ ያልሆነዉን ነገር ግልጽ እንዲደርጉ የሚመረመሩበት፣እምነት እና ክህደት ቃላቸዉን የሚሰጡበት እና ስለክርክራቸዉ ማብራሪያ እንዲሰጡ የሚደረጉበት ነዉ፡፡ ይህ የክርክር ደረጃ በክስና መልስ የተጠቀሱ ነገሮች ማስረጃዎችን ጨምሮ ክርክር የሚቀርብበት ሂደት ነዉ፡፡ የክስ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያም ቀርቦ ከሆነ የመልሱ አካል እስከሆነ ድረስ ክርክር ይደረግበታል፡፡ በፍሬ ነገር ደረጃም የግራ ቀኙን ክስና መልስ መነሻ በማድረግ የሚመረመረዉ በዚሁ ዕለት ነዉ፡፡ ይህ የክርክር ደረጃ አንድ ቀን የሚደረግ ለመሆኑ ከድንጋጌዉ በግልጽ መረዳት የሚቻል ነዉ፡፡ የክስ መሰማቱ ሂደት እንደተጠናቀቀ ቀጣዩ የሚሆነዉ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ቀርቦ ከሆነ መቃወሚያዉን አስቀድሞ መወሰን መቃወሚያ ካልቀረበ ለክርክሩ መሪ ጭብጥ በመያዝ ማስረጃ የማሰማት ወይም ዋና ሙግት ሂደቱ ይቀጥላል፡፡ የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 244(1) በግልጽ እንደሚያመላክተዉ  በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ላይ ዉሳኔ የሚሰጠዉ ማስረጃ ተቀብሎ ከመመርመሩ  በፊት ወይም ምስክሮች ከመሰማቱ በፊት እንደሆነ ነዉ፡፡ ይህ ድንጋጌ በግልጽ የክስ መቃወሚያ ሊወሰን የሚችለዉ  ማስረጃ ተቀብሎ ከመመርመሩ ወይም ምስክር ከመሰማቱ በፊት እንደሆነ የሚገልፅ እንጅ በዋናዉ ጉዳይ ላይ ክርክር ከመደረጉ በፊት አይልም፡፡ ሕጉ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ እና የፍሬ ነገር ክርክርን በሁለት ደረጃ ከፍሎ ማከራከር አስፈላጊ እንደሆነ ታስቢ አድርጎ ቢሆን ኖሮ የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 244(1) ድንጋጌ መቃወሚያዉ ከፍሬ ነገር ክርክሩ በፊት መወሰን አለበት በማለት ያስቀመጥ ነበር፡፡ ድንጋጌዉ በግልፅ የሚያመላክተዉ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 241 መሰረት ክሱና መልሱ ላይ የቀረበዉ ጠቅላላ ነገር በክስ መስማቱ ዕለት መጠናቀቅ እንዳለበት ሆኖም በፍሬ ነገሩ ጭብጥ ተይዞ ማስረጃ ከመሰማቱ በፊት መቃወሚያዉ መወሰን እንዳለበት የሚገልፅ ነዉ፡፡ ይህን የሚያጠናክረዉ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 246(1) የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዉ እንደተወሰነ ፍርድ ቤቱ የሚያደርገዉ ስራ  ቀጣዩን የክርክር ሂደት የሚመራዉን የክርክር ጭብጥ መለየት እንደሆነ የሚገልፀዉ ነዉ፡፡ እነዚህ ድንጋጌዎች ከፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 241 ጋር በጥምረት ሲታዩ ክስ የመስማት ዕለት አንድ ጊዜ እንደሆነ፣ ክስ የሚሰማዉም ግራ ቀኙ በክሳቸዉና በመልሳቸዉ እንዲሁም ማስረጃቸዉን መነሻ በማድረግ እንደሆነ፣በዕለቱ ግልጽ ያልሆነን ነገር ማብራራት፣የሚታመን እና የሚካድን በመጠየቅ እንደሆነ መረዳት ይቻላል፡፡ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያም የመልስ አካል እንደመሆኑ ክስ በሚሰማበት ክርክር ተደርጎበት የሚጠናቀቅ ሲሆን የፍሬ ነገሩ ክርክርም በዕለቱ የሚያልቅ ነዉ፡፡ ሥነ-ሥርዓት ሕጉ መቃወሚያዉ ቀድሞ እንዲወሰን የሚያስቀምጠዉ በፍሬ ነገሩ ላይ ጭብጥ ተይዞ ማስረጃ ከመሰማቱ እና ከመመርመሩ በፊት እንደሆነ እንጅ ክርክሩን ከፍሬ ነገሩ ተነጥሎ እንዲታይ በሚል አይደለም፡፡ በተግባር የሚታየዉ እና እንደ ሕግ እየዳበረዉ የመጣዉ አሰራር ግን ከሕጉ ጋር አብሮ የሚሔድ አይደለም፡፡ አሰራሩ ክስ መስማትን የመቃወሚያ እና የፍሬ ነገር ክርክር ብሎ በሁለት ደረጃ የከፈለ ነዉ፡፡ ይህ አሰራር በዋናነት ሶስት መሰረታዊ ችግሮችን ይፈጥራል፡፡ አንደኛዉ ከሕግ ዉጪ መመራትን ያስከትላል፡፡ ሕጉ በግልፅ ክስና መልስ መቀባል ቀጥሎ ያለዉን የመጀመሪያ ቀነ ቀጠሮ ክርክሩ የሚሰማበት ወይም ክስ የሚሰማበት ዕለት በማለት ለዚህም የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 241 በአንድ ጊዜ ክስ ተሰምቶ የሚሰማበትን ሂደት አስቀምጦ እያለ ክስ መስማትን በሁለት ዘርፍ መክፈል ከሕግ ዉጪ  የሆነ አሰራር ነዉ፡፡ ይህ ደግሞ ፍርድ ቤቶችን በሥነ-ሥርዓት ሕግ ከመመራት  ይልቅ ከሥነ-ሥርዓት ዉጪ የመመራት ባህል እንዲያዳብሩ ያደርጋል፡፡ ሁለተኛዉ የክርክር ሂደት መፋለስን ያስከትላል፡፡ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 69፣70(ሀ) እና 73 መሰረት ክስ በሚሰማበት ዕለት ተከራካሪዎች ሳይቀርቡ ሲቀሩ የሚያስከትለዉ ዉጤት በግልጽ ተመላክቷል፡፡ ዉጤቱ ተከሳሹ ከቀረ በሌለበት ክርክሩ እንደሚቀጥል፣ተከሳሽ እና ከሳሽ ሳይቀርቡ ሲቀሩ መዝገቡ ሊዘጋ እንደሚችል ተደርጎ ተቀምጧል፡፡ ክስ መስማቱ በመቃወሚያዉ እና በፍሬ ነገር ላይ ተነጣጥሎ የሚሰማ ከሆነ ተከራካሪዎች ሳይቀርቡ ቢቀሩ በሌለበት ክርክሩ የሚቀጥለዉ ወይም መዝገቡ የሚዘጋዉ ለየትኛዉ ክርክር እንደሆነ ለመፈፀም ያስቸግራል፡፡ በዚህ ሁኔታ ተከሳሹ በሌለበት ክርክሩ እንዲቀጥል ሊወሰን የሚችለዉ በመቃወሚያ ክርክር ወቅት ሲቀር  ነዉ ወይስ በፍሬ ነገር ክርክር ወቅት ሲቀር የሚለዉ ምላሽ መስጠትም አስቸጋሪ ያደርገዋል፡፡ በተግባር እንደሚገጥመዉ በመጀመሪያ ቀነ ቀጠሮ  በሚደረገዉ መቃወሚያ ክርክር ቀርቦ ክርክሩን ያደረገ ተከሳሽ በፍሬ ነገር ክርክር ወቅት ሲቀር በሌለበት ክርክሩ እንዲቀጥል ይባላል፡፡ እንደ ሥነ-ሥርዓት ሕጉ የመጀመሪያ ቀነ ቀጠሮ የሚባለዉ ክስና መልስ መቀባባል አብቅቶ ክሱ የሚሰማበት የመጀመሪያዉ ቀን ነዉ፡፡ በዚህ ቀን የቀረበ ተከሳሽ ክሱ በሚሰማበት ዕለት የተገኘ በመሆኑ በሌለበት ክርክሩ ሊቀጥል አይችልም፡፡  ሆኖም በአሰራር በተፈጠረዉ ሁለተኛ የክርክር ደረጃ ወይም የፍሬ ነገር ክርክር ወቅት አልቀረበም ተብሎ በሌለበት ክርክሩ እንዲቀጥል ይደረጋል፡፡ በሌላ በኩልም በጀመሪያዉ ቀነ ቀጠሮ ሳይቀርቡ የቀሩ ተከራካሪዎች በመጀመሪያ ቀነ ቀጠሮ አለመቅረባቸዉ ተመዝግቦ ክርክሩ በሌሉበት እንዲቀጥል ወይም ከሳሽ ከሆነ እንዲዘጋ ማድረግ እየተቻለ ምንም ሳይባል የመቃወሚያዉን ክርክር አሳልፎ በሁለተኛ ምዕራፍ በሚደረገዉ የፍሬ ነገር ክርክር ሲቀርብ የክርክሩ አካል ሆኖ እንዲቀጥል ይደረጋል፡፡ እንደ ሥነ-ሥርዓት ሕጉ ቢሆን ተከሳሽ በሌለበት ክርክሩ እንዲቀጥል ወይም ከሳሽ ከሆነ መዝገቡ እንዲዘጋ የሚደረገዉ ከመልስ ማቀባባል ቀጥሎ
نمایش همه...
Share በፍትሐብሔር ክርክር ቅድመ-ሙግት ሂደት ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ከህጎቻችን አንጻር ሲቃኝ.docx
نمایش همه...