cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Bilaluna Edris (Xuqal.X.Qafarey)

♡_ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራ ሰውን አጅር ያህል ያገኛል"(አመላካች የሰሪውን ምንዳ ያገኛል)(ﷺ) « ከናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ ፣ በመልካም ስራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ» ﷻ                  ቁርኣን[ 3:104 ] መወያያ ግሩፓችን ☞ https://t.me/+1qmNqy265XoyNGY0

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
415
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+57 روز
+4030 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ፍቅር ጥግ …… ፊዳከ አቢ ወኡሚ ያ " ረሱለሏህ !
نمایش همه...
የመጀመሪያዎቹ ኢትዮጵያውያን ሑጃጆች ወደ ሳዑዲ ዐረቢያ በረራ የሚያደርጉበት ቀን ታወቀ #Ethiopia |~ መጅሊስ ለተጓዦች ስለ ሐጅ አፈፃፀም የሚሰጠው ሥልጠና በዛሬው እለት ይጀምራል ። ለ1445 ዓ.ሂ የሐጅ ሥነ ሥርዐት ከተመዘገቡ ኢትዮጵያውያን ውስጥ የመጀመሪያዎቹ ተጓዦች በረራ የሚያደርጉበት ቀን ታወቀ። “ሚንበር ቲቪ” ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) የሐጅ እና ዑምራ ዘርፍ እንደሰማው የመጀመሪዎቹ ተጓዦች በረራ የሚከናወነው ግንቦት 13፣ 2016 ነው። ምክር ቤቱ ለዘንድሮው ዓመት የሐጅ ሥነ ሥርዐት ለመላክ በእቅድ የያዘው የምዕመናን ቁጥር መጠን 12 ሺሕ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል። “ሚንበር ቲቪ” ከመጅሊስ ኃላፊዎች ማረጋገጥ እንደቻለው በተያዘው ዓመት ለሐጅ ክንውን ወደ ሳዑዲ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን ምዕመናን ቁጥር ከአምናው በ1 ሺሕ 62 ብልጫ ያለው ነው። መጅሊስ ለጉዞው የመዘገባቸውን ምዕመናን ከዛሬ ማክሰኞ ሚያዝያ 22/2016 አንስቶ ሥልጠና መስጠት እንደሚጀምር ታውቋል። ይህ ሥልጠና ለስድስት ቀናት የሚቆይ ነው። የዘንድሮው ዓመት የሐጅ ሥነ ሥርዐት ሰኔ 7/2016 ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል። በመላው ዓለም የሚገኙ ወደ 2 ሚሊዮን ገደማ የሚቆጠሩ ምዕመናን ሥነ ሥርዐቱን ለመፈፀም ከግንቦት 1/2016 ጀምሮ ወደ ሳዑዲ ዐረቢያ መግባት እንደሚጀምሩ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገባ ያመለክታል። ምንጭ  = ሚንበር ቲቪን የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
نمایش همه...
Bilaluna Edris (Xuqal.X.Qafarey)

♡_ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራ ሰውን አጅር ያህል ያገኛል"(አመላካች የሰሪውን ምንዳ ያገኛል)(ﷺ) « ከናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ ፣ በመልካም ስራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ» ﷻ                  ቁርኣን[ 3:104 ] መወያያ ግሩፓችን ☞

https://t.me/+1qmNqy265XoyNGY0

"የነቢዩ (ﷺ) ሰሃባዎች (ስራቸውን አላህ ይውደድላቸው) ገንዘባቸውንና ቤታቸውን ለአላህ ሲሉ በመተዋቸው…አላህ ዱንያን ሙሉ በሙሉ በእጃቸው አደረገላቸው፡፡" #ኡስታዝ_በድሩ_ሁሴን
نمایش همه...
#አላሙዲን_በገባው_ቃል_መሠረት_ስራውን_ጀምረዋል ለ27 አመታት ግንባታው ተቋርጦ የነበረው የሱልጣን አሊሚራህ ኢስላማዊ ኮለጅ ግንባታ ሸህ መሀመድ ሁሴን አላሙዲን በሰኔ 06/2013 ቃል በገቡት መሠረት የፕሮጀክቱን ግንባታ በይፋ ጀምረዋል። ከወራት በፊት ግንባታ የተፈቀደው ለመስጅድ ብቻ ነው የሚለው ሀሳብ ደስታች ጎዶሎ አድርጎት ነበር። ዛሬ ደግሞ  የመድረሳው ግንባታ አብሮ እንዲቀጥል አላሙዲን መፍቀዳቸውና በቀጣይ ሳምንት ስራ እንደሚጀመር  ስንሰማ ተደስተናል። አላሙዲን በገቡት ቃል መሠረት በቃላቸው በማገኘት ግንባታው ተጀምረዋል ከወራት ቡሗላ ይጠንቀቅ ተብሎ ይጠበቃል።   አሁን የቀረው የክልሉ መንግስታችን የገባልን ቃል ብቻ ነው። እሱም በፕሮጀክቱ ላይ የሚገኘው 25 ሚሊዮን ብር እዳ ጉዳይ ነው። የክልሉ መንግሥት የኮንትራክተሩን ክፍያ በሰኔ 06/2013 ልክ እንደአላሙዲን ለአሳይታ ህዝብ እዳውን እንደሚከፍል በመድረኩ ቃል ገብተዋል። እዳውን ለማክፈል ድርሻውን ወስደዋል። እስካሁን የክልሉ መንግስት በገባው ቃል መሠረት የኮንትራክተሩን ክፊያ አልከፈለም። መንግሥታችን በመስጅዱ ላይ ያለው እዳ በገባው ቃል መሠረት እንደሚከፍል ተስፋ አለን። እዳው ተከፍሎ ከእዳ ነፃ ስንሆን እና  የፕሮጀክቱ ግንባታ ስጠናቀቅ ያኔ ደስታችን ሙሉ ይሆናል። አላህ የዛ ሠው ይበለን! Via @Aloyayyo @ https://t.me/Xuqal
نمایش همه...
"እውነተኛ ታማኝ ነጋዴ አኸራ ላይ ከነብያቶች ፣ ከሲዲቆች እና ከሰማእታት ጋር ነው" ረሱል ﷺ
نمایش همه...
2
“አላህ ዘንድ መልካም ጎደኛ ማለት ለጎደኛው መልካም የሆነው ነው። አላህ ዘንድ መልካም ጎረቤት ማለት ለጎረቤቱ መልካም የሆነው ነው።” ረሱል ﷺ
نمایش همه...
👍 1
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ                            ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የሐጅ ቪዛ ሳይይዙ ሐጅ ማድረግ እንደማይቻል የሳዑዲ የሐጅ ሚኒስቴር አስጠነቀቀ። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሚያዝያ 21፣ 2016 (አዲስ አበባ) - የሳዑዲ አረቢያ የሐጅ እና ዑምራ ሚኒስቴር፣ የሐጅ ቪዛ ሳይይዙ ሐጅ ማድረግ እንደማይቻል በመግለጽ ዘንድሮ ሐጅ የማድረግ ኒያ ያላቸው ምዕመናን "ሐጅ እናስደርጋለን" በሚሉ የግል ኩባንያዎች እንዳይታለሉ በጥብቅ አስጠነቀቀ። ሚኒስቴሩ ይህን ማስጠንቀቂያ ይፋ ያደረገው፣  በተለያዩ ሀገራት በማኅበራዊ ትስስር አውታሮች የሐጅ ቪዛ እንሰጣለን የሚሉ ሐሰተኛ ኩባንያዎች በስፋት የሚያሰራጩት ማስታወቂያ መበራከቱን ከተመለከተ በኋላ መኾኑን በመግለጫው ጠቅሷል። ሐጅ ለማድረግ ሳዑዲ አረቢያ ከመገባቱ በፊት የሐጅ ቪዛ ማግኘት የግድ አስፈላጊ መኾኑን የጠቀሰው ሚኒስቴሩ፣ በጉብኝት ቪዛ፣ በሥራ ቪዛ፣ በቱሪስት ቪዛ፣ በትራንዚት እና በመሳሰሉት ቪዛዎች ሳዑዲ አረቢያ በመግባት ሐጅ ማድረግ እንደማይቻል አሳስቧል። ሚኒስቴሩ አክሎም፣ ሐጅ ማድረግ የሚቻለው ጉዳዩ የሚመለከተው የሳዑዲ አረቢያ ሚኒስቴር በየሀገራቱ የሐጅና ዑምራ ጉዳይ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመተባበር በሚሰጠው የሐጅ ቪዛ እና፣ እነዚህ ተቋማት በሌሉባቸው ሀገራት ደግሞ "ኑሱክ ሐጅ" በሚሰኘው ፕላትፎርም አማካይነት ብቻ መኾኑን መረዳት ያስፈልጋል ብሏል። ሐጅ ለማድረግ፣ ሳዑዲ አረቢያ ከመገባቱ በፊት ራሱን የቻለ የሐጅ ቪዛ ማግኘት የግድ አስፈላጊ እንደኾነ የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፣ ከሳዑዲ የሐጅና ዑምራ ሚኒስቴር ጋር ግንኙነት ካላቸው የየሀገራቱ የሐጅና ዑምራ ተቋማት ውጪ የሐጅ ቪዛን ማግኘት እንደማይቻል በመግለጽ ምዕመናን ከመታለል እንዲጠነቀቁ አሳስቧል። "ሐጅ እናስደርጋለን" በሚሉ አጭበርባሪ ኩባንያዎች መታለል ከሚያስከትለው የገንዘብ ኪሳራ በተጨማሪ፣ የጓጉለትን ሐጅ ለማድረግ አለመቻልን በማስከተል ከባድ ሐዘን ላይ ሊጥል እንደሚችል ሚኒስቴሩ አሳስቧል። @ https://t.me/Xuqal
نمایش همه...
Bilaluna Edris (Xuqal.X.Qafarey)

♡_ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራ ሰውን አጅር ያህል ያገኛል"(አመላካች የሰሪውን ምንዳ ያገኛል)(ﷺ) « ከናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ ፣ በመልካም ስራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ» ﷻ                  ቁርኣን[ 3:104 ] መወያያ ግሩፓችን ☞

https://t.me/+1qmNqy265XoyNGY0

ከጥቂት ቀናት በፊት በግብፅ ብሄራዊ ደህንነት ኢንተለጀንሶች በኩል አንድ መልዕክት ተላከ። ከዋሽንግተን ነበር። ለቀሳሙ መሪ ለየህያ ሲንዋር።   ለግሉ 15 ቢሊዮን ዶላር ስጦታ፣ ምቹና ቅንጡ መኖርያ፣ ጋዛ ከተማን መልሶ ለመገንባት ቃል የሰፈረበት ደብዳቤ! በምትኩ የህያ ሲንዋር ቀሳሞችን ከውስጥ በኩል ሰርስሮ በመናድና በመሰነጣጠቅ ህብረታቸውን እንዲንድላቸው ይጠይቃል። አደራ ይላል መልዕክቱ መጨረሻ ላይ "አደራ ከግብፅ አስታራቂዎች በኩል የቀረበውን ልዩ ጥያቄ ተጠቀምበት ይህ እድል እንዳያመልጥህ" በማለት ይቋጫል። የህያ ሲንዋር ከአራት ቀናት በኋላ ለዚህ ጥያቄ በአንድ አንቀጽ ምላሽ ሰጠ እንዲህ ይላል፡- فَلَمَّا جَاءَ سُلَيْمَانَ قَالَ أَتُمِدُّونَنِ بِمَالٍ فَمَا آتَانِيَ اللَّهُ خَيْرٌ مِّمَّا آتَاكُم بَلْ أَنتُم بِهَدِيَّتِكُمْ تَفْرَحُونَ "ሱለይማንንም በመጣው ጊዜ አለ «በገንዘብ ትረዱኛላችሁን አላህም የሰጠኝ ከሰጣችሁ የበለጠ ነው፡፡ ይልቁንም እናንተ በገጸ በረከታችሁ ትደሰታላችሁ"                    [አን-ነምል 36] @ https://t.me/Xuqal
نمایش همه...
👍 1