cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Marcel Planiol

Laws, law books, case discussions, cassation decisions, proclamations, regulations, directives, articles, law journals and commentaries!

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
205
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-17 روز
+330 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ስለ ቤት ሽያጭ ውል፤ ክፍል ፫ (የመጨረሻ) ሌላው የምዝገባ ሂደት ሲሆን ይህ ፎርማሊቲ ዋነኛ ዓላማው ሦስተኛ ወገኖች በንብረቱ ላይ የሽያጭ ውል እንደተደረገ እውቅና እንዲኖራቸው ማስቻል ነው፡፡ የመመዝገብ ሂደት በተዋዋይ ወገኖች የቀረበውን የሽያጭ የውል ሰነድ ቅጂ ተቀብሎ የመዝገቡ አካል የማድረግ ወይም በሚመለከተው ማህደር ውስጥ የመያያዝ ተግባርን ያጠቃልላል፡፡ ሆኖም አንድ የሽያጭ ውል በመዝጋቢው አካል የአስተዳደራዊ ስራዎች ማለትም ማህተም የማሳረፍ፣በፕሮቶኮል ቁጥር የመትከል፣ስመ ሀብት የማዞር እና የመሳሰሉት ተግባራት ባይፈፀሙም ውሉ ከማህደሩ ጋር ከተያያዘ እንደተመዘገበ ይቆጠራል፤ (ሰ/መ/ቁ/ 23989፣16109)፡፡ በፍ/ህ/ቁ 2878 መሰረት የሽያጭ ውል በሦስተኛ ወገኖች ላይ መቃወሚያ ሆኖ መቅረብ የሚችለውም ውሉ ሲመዘገብ ብቻ ነው፡፡ በአንድ ቤት ላይ ከአንድ በላይ ሰዎች መብት አግኝተው እንደሆነ አስቀድሞ ያስመዘገበው ሰው ቅድሚያ ይሰጠዋል፤ (ሰ/መ/ቁ/165009)፡፡ ይህም ማለት በአንድ የቤት ሽያጭ ውል መነሻነት ስም ለማዞር የሚያስችል የውክልናና ሌሎች ሰነዶችን ገዥ ተረክቦ እያለ ስመሀብቱ ወደ የመጀመሪያ ገዥ ከመተላለፉ አስቀድሞ ሻጭ እንደገና ቤቱን ለሌላ ሰው ከሸጠው እና ህጉን ተከትሎ ለሁለተኛው ገዥ ስሙ ከተላለፈ የመጀመሪያው ገዥ በሁለተኛ ገዥ ላይ ተቃውሞ ሊያቀርብ አይችልም፤(ሰ/መ/ቁ/ 123761)፡፡ የምዝገባ ሂደትን ተከትሎ ቤቱን የገዛ ሰው ሻጭ ንብረቱን በስሙ ያስመዘገበው በሕገ ወጥ መንገድ የነበረ ቢሆን እንኳ ገዥ የሚጠበቅበትን ጥንቃቄ ስላደረገ የሕግ ጥበቃ ይደረግለታል፤(ሰ/መ/ቁ/185059)፡፡ በቤቱ ላይ በካርታው ያልተጠቀሰ ባለመብት ቢኖር ሕጉን ተከትሎ ውሉ የምዝገባ ሂደቱን ካጠናቀቀ ገዥ በቤቱ ላይ መብት አለን ከሚሉ ሰዎች የሕግ ጥበቃ ያገኛል፤(ሰ/መ/ቁ/ 220204)፡፡ ሌላው እና መታለፍ የሌለበት ጉዳይ የቤት ለቤት ለውጥ ዉል ልክ እንደ ሽያጭ ውል ሁሉ በጽሁፍ መደረግ፣መረጋገጥ እና መመዝገብ የሚጠበቅበት መሆኑ ነው፤(ሰ/መ/ቁ/ 154915)፡፡ ማጠቃለያ ቤት ከፍተኛ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች ያሉት ንብረት ከመሆኑ አኳያ በንብረቱ ላይ የሚደረግ ሽያጭ የተለየ የውል ፎርማሊቲዎች እንዲሟሉ በፍ/ህ/ቁ 1723፣2878 እና በሌሎች ቁጥሮች ተደንግጎ ይገኛል፡፡እነዚህ ፎርማሊቲዎች ውሉ በጽሁፍ መደረግ፣በአዋዋይ ፊት መረጋገጥ እና መመዝገብ ናቸው፡፡ በቤት ላይ የሚደረግ የሽያጭ ውል በጽሁፍ ካልተደረገ አይጸናም፡፡ የውል መረጋገጥ አስፈላጊነት ለውሉ ፅናት ወይስ ለማስረጃነት የሚሉ የአተያይ ልዩነቶች በችሎት ዳኞች መካከል ጭምር የተስተዋለ ሲሆን ሰበር ሰሚ ችሎቱ ለውሉ ጽናት ዓላማ ውል መረጋገጥ እንዳለበት በአብላጫ ድምፅ ወስኗል፡፡ ያልተረጋገጠ ወይም ያልተመዘገበ ውል በተለምዶ “የመንደር ውል” ተብሎ የሚጠራ እና በመርህ ደረጃ ውጤት የሌለው ቢሆንም በተወሰኑ ልዩ ሁኔታዎች አስገዳጅነት ሊኖረው ይችላል፡፡ እነዚህ ሁኔታዎችም በግራ ቀኙ ውል መኖሩ ከታመነ፣ ውሉ በከፊል ወይም በሙሉ ከተፈፀመ፣መዝጋቢ አካል ከሌለ/ካልተደራጀ፣ የሽያጭ ውሉ በማህበር ቤቶች ላይ የተረገ ከሆነ እና የሊዝ መብትን የማስተላለፍ ውል ከሆነ ናቸው፡፡ ውልን የመመዝገብ ዋና አላማው ውሉ ስለመደረጉ ለ3ኛ ወገኖች ማሳወቅ ነው፡፡ ስልጣን ባለው አካል ያልተመዘገበ የቤት ሽያጭ ውል በ3ኛ ወገኖች ላይ መቃወሚያ ሆኖ ሊቀርብ አይችልም፡፡ ህጉን ተከትሎ የቤቱን ያስመዘገበ ወይም ስመ-ሀብቱን ያዞረ ገዥ በንብረቱ ላይ ጥቅም አለኝ ከሚል 3ኛ ወገን የህግ ጥበቃ ያገኛል፡፡ የቤቱ ስመ ሃብት ወደ ሻጭ የዞረው በህገ ወጥ መንገድ መሆኑ፣ ከቤቱ ከባለሃብቶቹ ውስጥ በሻጭ ስም ብቻ ተመዝግቦ የነበር መሆኑ ወይም ቤቱ ለሌላ ሰው ቀድሞ ተሸጦ የነበር መሆኑ ቢረጋገጥ እንኳ ሽያጩን ቀድሞ ባስመዘገበ ጠንቃቃ ገዥ ላይ የሚቀርብ መቃወሚያ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
نمایش همه...
GMS Law Office | Addis Ababa

GMS Law Office , Addis Ababa, Ethiopia. 1,578 likes · 13 talking about this. ይህ ገጽ በተለያዩ የሕግ ጉዳዮች ዙሪያ ጠበቆች የሕግ አሳቦችን፣የፍርድ ቤት ውሳኔዎችንና ውይይቶችን የሚያቀርቡበት ነው። ክህሎት ያላቸውን ጠበቆችም ያገኙበታል።

ስለ “መንደር ውል” የቀጠለ፤ ክፍል -፪ GMS Law Office በክፍል አንድ ስለቤት ሽያጭ ውል አጠቃላይ ሁኔታዎች የተመለከትን ሲሆን በዚህ ክፍል ደግሞ ያልተመዘገበ የቤት ሽያጭ ውል ወይም በተለምዶ የመንደር ውል ሕጋዊ ስለሚሆንባቸው ልዩ ሁኔታዎች እንመለከታል። ——— እነዚህም ውሉ ከታመነ፣ መሰረታዊ የውሉ አካል ከተፈፀመ፣ መዝጋቢ አካል ከሌለ፣ ቤቱ የማህበር ቤት ከሆነ እና ውሉ የሊዝ መብትን የማስተላለፍ ውል ከሆነ ናቸው፡፡ እነዚህን ሁኔታዎች በዝርዝር እንመልከታቸው፡፡ 1. የቤት ሽያጭ ውሉ በተዋዋይ ወገኖች የታመነ ከሆነ፡- የመንደር ውል የሚፀናው በተከራካሪ ወገኖች ውል መኖሩ የታመነ እንደሆነ ነው፡፡ በውል ላይ በሚነሱ ክርክሮች ውል መኖሩን አምነው ነገር ግን ውሉ ባለመመዝቡ ውሉን የሚቃወሙ ከሆነ ተከራካሪዎች በውሉ ይገደዳሉ፡(ሰ/መ/ቁ/ 36887፣137130፣134083 ፣90282)፡፡ ሆኖም ያልተመዘገበ የቤት ሽያጭ ውል ወይም የመንደር ውል ከተካደ ወይም የቤት ሽያጭ የለም፣ ረቂቅ ነው፣ የሸጥሁት ባዶ ቦታ ነው እና የመሳሰሉ መቃወሚያዎች በቀረቡበት ጊዜ ውሉ አስገዳጅቱን ያጣል፡፡ ውሉ የተካደው ከጋራ ባለ-ንብረቶች በአንዱ ቢሆን (ሰ/መ/ቁ/ 167022) ወይም በተወካይ ታምኖ በወካይ ቢካድ (ሰ/መ/ቁ/ 215444፣158102፣161917) እንኳ ውጤቱ ተመሳሳይ ነው፡፡ የመንደር ውል በተካደ ጊዜ ውሉ ስለመደረጉ በሰው ምስክር ወይም በሌላ ማስረጃ ማስረዳት አይቻልም፤(ሰ/መ/ቁ/ 218459)፡፡ ዐይነ ስውራን እና ማንበብ እና መፃፍ የማይችሉ ማይማን ውላቸውን በውል በአዋዋይ ፊት እንዲያደርጉ፣ከዚያ ውጭ በሚደርጓቸው ውሎች እንደማይገደዱ በፍ/ሕ/ቁ 1728(3) ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ሆኖም እነዚህ ሰዎች ውሉን እና በውሉ ላይ የተመለከተውን ፊርማ እስካልካዱ ድረስ ወይም ውል መኖሩን ካመኑ በውሉ ይገደዳሉ፤(ሰ/መ/ 191024)፡፡ ውሉም የፀና ይሆናል፡፡ 2. የቤት ሽያጭ ውሉ በሙሉ ወይም በከፊል መፈጸም፡- ሳይመዘገብ የተደረገው የቤት ሽያጭ ውል በከፊል ወይም በሙሉ የተፈፀመ እንደሆነ ውሉ የፀና ይሆናል፡፡ ይህም ተዋዋይ ወገኖች ውል መኖሩን ተቀብለው፣ ውሉን ለመፈፀም ተንቀሳቅሰው፣ መሰረታዊውን የውሉ አካል በከፊል ወይም በሙሉ ከፈፀሙት ቀሪውን የውል አካል ለመፈፀም ይገደዳሉ ወይም ውሉ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ተፈፅሞ እያለ የሽያጭ ውሉ ፎርማሊትን ባለመከተሉ ምክንያት ብቻ ውሉ ፈራሽ ሊሆን አይገባውም ማለት ነው፤(ሰ/መ/ቁ/ 206083)፡፡ 3. የቤት ሽያጭ ዉሉ ያልተመዘገበው በመዝጋቢው አካል አለመኖር መክንያት ከሆነ፡- ተዋዋይ ወገኖች ውሉን ለማስመዝገብ ተገቢውን ጥረት አድርገው ነገር ግን የምዝገባ ስራን የሚሰራ የመንግስት መዋቅር ባለመኖሩ (ባለመደራጀቱ) ምክንያት ሳይመዘገብ ከቀረ በግራ ቀኙ የተገባው ውል ባይመዘገብ እንኳ አስገዳጅነት ይኖረዋል፤(ሰ/መ/ቁ/ 98079)፡፡ 4. የቤት ሽያጭ ውሉ የተደረገው በማኅበር ቤት ላይ ከሆነ፡- በማኅበር በመደራጀት የሚሰራ ቤት ስመ ንብረት ለማስተላለፍ ከማኅበሩ የስራ አመራር ኮሚቴ ፈቃድ ማግኘት የሚጠበቅበት ሆኖ ማስተላለፍ የሚችለውም የሚተላለፍለትን ወገን በማኅበሩ ውስጥ በመተካት የማኅበሩ ዓባል እንዲሆን በማድረግ ብቻ ነው፡፡ ከስሙም እንደምንረዳው የማኅበር ቤቶች ሰዎች በማኅበር በመደራጀት የሚገነቧቸው ናቸው፡፡ ማኅበራቱ የሚገዙበት ልዩ ሕግና የማኅበራት የውስጥ አስተዳደራዊ አሠራር ያለ በመሆኑ የማኅበር ቤቶች የማስተላለፍ ጉዳይም የራሱ የሆነ የተለየ ስርዓት የሚከተል በመሆኑ በፍ/ህ/ቁ 1723 የተቀመጠው ቅድመ ሁኔታ ተፈፃሚነት አይኖረውም፤(ሰ/መ/ቁ/ 36294)፡፡ 5. ውሉ የሊዝ መብትን ለማስተላለፍ የተደረገ ከሆነ፡- የሊዝ መብትን ማስተላለፍ ከዚህ በላይ እንዳየናቸው ሙሉ በሙሉ የቤት ሽያጭ ውል ነው ለማለት የማያስደፍር ቢሆንም በሊዝ የተገኘን ቦታ ለማስተላለፍ ልዩ ፎርማሊቲ አይጠይቅም፡፡ ነገር ግን ይህ የመንደር ውል ተቀባይነት የሚኖረው ውሉ በሊዝ በተገኘ ቦታ ላይ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት ወይም ግንባታው ተጀምሮ በግማሽ ከመጠናቀቁ በፊት የተደረገ ከሆነ ብቻ ነው፤(ሰ/መ/ቁ/ 191095)፡፡ በሊዝ በተገኘ ቦታ ላይ የተጀመረ ግንባታ ከግማሽ በላይ ከተጠናቀቀ ውሉ በሊዝ የመጠቀም መብት ብቻ ሳይሆን በቦታው ላይ የተሰራውን ሕንፃ ጭምር የሚያጠቃልል በመሆኑ ተገቢውን የምዝገባ ፎርማሊቲ መከተል ይጠበቅበታል፤(ሰ/መ/ቁ/ 225796)፡፡ ክፍል ፫ ይቀጥላል!
نمایش همه...
GMS Law Office | Addis Ababa

GMS Law Office , Addis Ababa, Ethiopia. 1,578 likes · 13 talking about this. ይህ ገጽ በተለያዩ የሕግ ጉዳዮች ዙሪያ ጠበቆች የሕግ አሳቦችን፣የፍርድ ቤት ውሳኔዎችንና ውይይቶችን የሚያቀርቡበት ነው። ክህሎት ያላቸውን ጠበቆችም ያገኙበታል።

የቤት ሽያጭ ውል፤ GMS Law Office ክፍል ፩ አከራካሪው ‹‹የመንደር›› ውል ጉዳይ፤ በዚህ ጽሁፍ የማይንቀሳቀስ ንብረት ምንነት፣ ቤት እና በቤት ላይ የሚደረጉ የሽያጭ ውሎች ሊከተሏቸው ስለሚገቡ የውል ፎርማሊቲዎች፤ ማለትም በጽሁፍ የመደረግ፣ የመረጋገጥ እና የመመዝገብ ሂደቶችን በዝርዝር እናያለን፡፡ በተጨማሪም በሚመለከተው የውል አዋዋይ መዝጋቢ አካል ፊት ያልተደረገ የቤት ሽያጭ ውል፤ በተለምዶ ደግሞ ‹‹የመንደር ውል›› እየተባለ የሚጠራው የሽያጭ ውል የሚፀናባቸውን ልዩ ሁኔታዎች እንዳስሳለን፡፡ የማይንሳቀስ ንብረት ማለት በአጭር አገላለፅ ቤት ወይም መሬት ማለት ነው፡፡ መሬት በሕገ መንግስቱ እንዳይሸጥ እንዳይለወጥ ክልከላ የተደረገበት ንብረት ነው፡፡ ስለሆነም ለዚህ ጽሁፍ ዓላማ በማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ላይ ስለሚደረጉ ግብይቶች እና ውሎች ስናወራ ቤትን እና በቤት ላይ ስለሚደረጉ የግብይት ወይም የሽያጭ ውሎች ማለታችን እንደሆነ ግንዛቤ ይወሰድልን፡፡በዚህ ጽሁፍ በቤት ላይ ስለሚደረጉ የሽያጭ ውሎች እንመለከታለን፡፡ ቤት ካለው ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ አንጻር በቤት ላይ የሚደረጉ ግብይቶች የተለዬ የውል ፎርማሊቲ እንዲከተሉ ሕግ ያስገድዳል፡፡ ቤት ቤት ነው፡፡ ትንሽ ትልቅ፣ ዘመናዊ ባህላዊ፣ የቀበሌ የግለሰብ፣ ኮንደሚንየም አፓርታማ፣የመኖሪያ የንግድ ቢሆን እንኳ የቤትነት እሴቱን አይቀንሰውም፡፡ ቤት ሃብት ነው፤ ቤት ገመና ከታች ነው፤ ቤት መጠለያ ነው፤ ቤት ውሎ መግቢያ ነው፤ ቤት ታሪክ ነው፤ ቤት ቅርስ ነው፤ ቤት ሁሉ ነገር ነው፡፡ ሰዎች ከቤት ጋር የተለየ ቁርኝት አላቸው፡፡ ከአራቱ የሰው ልጅ መሰረታዊ ፍላጎቶች ውስጥም አንዱ መጠለያ ወይም ቤት ነው፡፡ በሕግም አንድ ሰው በአንድ ቤት የተለዬ ጥቅም (special interest) አለው ተብሎ ይገመታል፡፡ ለዚያም ነው በውል ሕግ አፈጻጸም ውል በግድ ከሚፈጸምባቸው ውለታዎች ውስጥ የቤት ሽያጭ ውል አንዱ የሆነው፤የፍ/ሕ/ቁ 1776ን ይመለከቷል፡፡ ቤት በተጋነነ ዋጋ ከሚሸጥባቸው ሀገራት ተርታ በምትመደብ ሃገራችን፣ በዚህ ንብረት ላይ የሚደረጉ ግብይቶች በአግባቡ መምራት ካልተቻለ እሳት ላይ ቤንዚን እንደማርከፍከፍ ያክል የከፋ ውጤትን ያስከትላል፡፡ በእርግጥ በአንፃራዊነት የቤት ዋጋ ዝቅተኛ ነው በሚባልባቸው ሃገራትም ጭምር በዚሁ ንብረት ላይ በሚደረጉ ግብይቶች ላይ የተለየ ቁጥጥር እና የውል ፎረማሊቲዎችን ያስቀምጣሉ፡፡ ሰዎች በተጭበረበረ ግብይት፣ በመታለል፣ በመገደድ ወይም ውጤቱን በውል ባመረዳት በሚገቧቸው ውሎች የተነሳ ይህን ውድ ንብረት ሊያጡት ይችላሉ፡፡ ሰዎች ቤት ለመግዛት የከፈሉት ገንዘብ ፍትሃዊነት በጎደለው ግብይት ምክንያት ቀልጦ ሊቀር ይችላል፡፡ በንብረቱ ላይ መብት ያላቸው ሦስተኛ ወገኖችም ባልተካፈሉበት እና ባልተስማሙበት ግብይት መብታቸው አደጋ ላይ ሊወድቅ ይችላል፡፡ በኢትዮጵያ የሕግ ስርዓት ውስጥ በመርህ ደረጃ ተዋዋይ ወገኖች የውሎቻቸውን ፎርማሊቲ የመወሰን መብት አላቸው፡፡ ከፈለጉ በጽሁፍ፣ ካልፈለጉ በቃል፣ ካሻቸው በጥቅሻ ወይም በሌላም መንገድ መዋዋል ይችላሉ፡፡ ታዲያ ለዚህ ጠቅላላ መርህ በልዩ ሁኔታ ከሚጠቀሱት የውለታ አደራረጎች መካከል የቤት ሽያጭን ጨምሮ በማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ላይ የሚደረጉ ውሎች ናቸው፡፡ ከዚህ በላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው ቤት ካለው ጠቀሜታ አንጻር ልዩ ጥበቃ እና ጥንቃቄ የሚሻ በመሆኑ በንብረቱ ላይ ሚደረጉ ውሎች የተለየ ፎርማሊቲ እንዲከተሉ ሕግ ያስገድዳል፡፡ የቤት ሽያጭ ውሎች በጽሁፍ መደረግ፣ ውልን ለመመርመርና ለመመዝገብ ስልጣን ባለው አካል ፊት ቀርበው መረጋገጥ እና መመዝገብ አለባቸው፡፡ እነዚህ ፎርማሊቲዎች የተለያዩ ውጤቶች ያሏቸው ቢሆንም አስተማማኝ የቤት ሽያጭ ውል አነዚህን ፎርማሊቲዎች እንዲያሟላ ይጠበቃል፡፡ በጽሁፍ የተደረገ ውል ማለት በእጅ ወይም በኮምፒውተር ተጽፎ በተዋዋይ ወገኖች እና ቢያንስ በሁለት እማኞች የተፈረመ ውል ነው፡፡ መረጋገጥ (authentication) ሲባል በተዋዋይ ወገኖች መካከል የተደረገው ውል ከሕግ እና ከሞራል የማይቃረን፣ ተዋዋይ ወገኖች ወደው እና ፈቅደው፣ የሚያስከትለውንም ሕጋዊ ውጤት ተረድተው የተዋዋሉት እንዲሁም ተዋዋይ ወገኖች በንብረቱ ላይ ለመዋዋል መብት ያላቸው መሆኑን በማረጋገጥ በሚመዘግብ ተቋም ውስጥ የሚከናወን ተግባር ነው፡፡ ይህም በፍርድ ቤት፣ በውል እና ማስረጃ ወይም በሰነዶች ምዝገባ እና ማረጋገጫ ኤጀንሲ በኩል የሚፈፀም ነው፤(ፍ/ህ/ቁ/ 1723(1))፡፡ መመዝገብ (registration) ማለት ደግሞ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች የመመዝገብ እና የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ የመስጠት ስልጣን ባለው ማዘጋጃ ቤት ወይም የከተማ ቦታ ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ በኩል የሚፈፀም የምዝገባ ሂደት ነው፤(ፍ/ህ//ቁ/ 2878)፡፡ ከላይ እንዳየነው በቤት ላይ የሚፈፀሙ የሽያጭ ውሎ እነዚህን ሦስት ፎርማሊቲዎች ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡ እነዚህ ፎርማሊቲዎች ዓላማ በጠቅላላው ለውሉ ጽናት፣ ውሉ ለመደረጉ እርግጠኛነት፣ ለማስረጃነት እንዲሁም ውሉ ስለመደረጉ ሦስተኛ ወገኖች እንዲያውቁት ለማድረግ፣ ለመጠበቅ እና ለመከላከል ነው፡፡ በጽሁፍ የመደረግ ፎርማሊቲ ዓላማ ለውሉ ጽናት ነው፡፡ የቤት ሽያጭ ውል በጽሁፍ ካልተደረገ በስተቀር ከጅምሩ ውል እንደተደረገ አይቆጠርም፡፡ ምንም አይነት ሕጋዊ ውጤትም አይኖረውም (ፍ/ህ/ቁ/ 2877) ፡፡ ስለሆነም በጽሁፍ መደረጉ ለውሉ ጽናት (validity) ቅድመ ሁኔታ ነው፤ (ፍ/ህ/ቁ/ 1723(1) ይመለከቷል፡፡ በፍ/ህ/ቁ/ 1723 መሰረት የሚደረግን የውል መረጋገጥ አስመልክቶ የተለያዩ አተያዮች አሉ፡፡ የሃሳብ ልዩነቶች ዋና ማጠንጠኛ ስልጣን ባለው አካል የውል መረጋገጥ ዓለማ ለዉሉ ፅናት ወይስ ለማስረጃነት የሚለው ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የውል መረጋገጥ ዋነኛ ዓላማ ለውሉ ጽናት ነው የሚል አቋም በመያዝ የተለያዩ ውሳኔዎችን ሰጥቷል፡፡ ሰበር ሰሚ ችሎቱ ዘርዘር ያለ ሃተታ በሰጠበት አንድ ውሳኔ ላይ የሽያጭ ውል በህግ ፊት የፀና የሚሆነው የጽሁፍ ውል ሥልጣን በተሰጠው አዋዋይ ክፍል ወይም በፍርድ ቤት የተከናወነ ሲሆን ነው፡፡ በ1723(1) መሰረት የማረጋገጥ መስፈርት ውሉ በሶስተኛ ወገኖች ላይ ውጤት እንዲኖረው ብቻ ሳይሆን ውሉ በተዋዋይ ወገኖች መካከል ውጤት እንዲኖረውም ነው በማለት አብራርቷል፤ (ሰ/መ/ቁ/ 21448 ቅፅ 4)፡፡ የዚህ ጉዳይ አከራካሪነት በግልፅ በተስተዋለበት አንድ ውሳኔ የውል መረጋገጥ የሚያስፈልገው ለውሉ ፅናት ነው በማለት ከ5ቱ ዳኞች ሶስቱ በአብላጫ ድምፅ ሲወሰኑ የቀሩት ሁለት ዳኞች በልዩነት ሃሳብ የሽያጭ ውል መኖሩ አከራካሪ ካልሆነ ወይም ከታመነ ባይረጋገጥ እንኳን አስገዳጅነት እንደሚኖረው በመ/ቁ/ 36887 ውሳኔ የሰጠ በመሆኑ፣ የውል መረጋገጥ አስፈላጊነት ለውል ፅናት (validity) ሳይሆን ለማስረጃነት አላማ (evidentiary purpose) ነው፡፡ ሰበር ሰሚ ችሎቱ በመ/ቁ/ 21448 የውል መረጋገጥ ለውሉ መፅናት አላማ እንደሆነ በመውሰድ ውሳኔ ሰጥቶ የነበር ሲሆን በቅርቡ በመ/ቁ/ 36887 ውሉ ከታመነ ባይረጋገጥም አስገዳጅነት እንዳለው ውሳኔ ሲሰጥ ውሉ ስለመደረጉ ለማረጋገጥ መሆኑን ድምዳሜ ላይ በመድረስ የወሰነ ስለሆነ፤ የቀደመውን ውሳኔ ለውጦታል ማለት ይቻላል በማለት አስቀምጠዋል፤ (ሰ/መ/ቁ/162843)፡፡
نمایش همه...
GMS Law Office | Addis Ababa

GMS Law Office , Addis Ababa, Ethiopia. 1,578 likes · 13 talking about this. ይህ ገጽ በተለያዩ የሕግ ጉዳዮች ዙሪያ ጠበቆች የሕግ አሳቦችን፣የፍርድ ቤት ውሳኔዎችንና ውይይቶችን የሚያቀርቡበት ነው። ክህሎት ያላቸውን ጠበቆችም ያገኙበታል።

ውል ለማዋዋልና ለማረጋገጥ ስልጣን ባለው አካል ቀርቦ የተረጋገጠ ውል በተዋዋይ ወገኖች መካከል የፀና ይሆናል፡፡ አንድ የሽያጭ ውል ውሎችን ለማረጋገጥ ስልጣን በተሰጠው አካል ሳይረጋገጥ አልፎ በቀጥታ ንብረቱን ለመመዝገብ ስልጣን በተሰጠው አካል ወይም ማዘጋጃ ቤት ተመዝግቦ ቢገኝ እንኳ ውሉ ህጋዊ ውጤት አይኖረውም፤(ሰ/መ/ቁ/ 34803 ቅፅ 8)፡፡ ሁሉም የቤት ሽያጭ ውሎች በጽሁፍ ተደርገው ውልን የማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት መረጋገጥ እና መመዝገብ እንደሚጠበቅባቸው ከላይ የገለጽነው ጉዳይ ነው፡፡ በጽሁፍ ተደርጎ ነገር ግን ስልጣን ባለው አካል ያልተረጋገጠ/ያልተመዘገበ የቤት ሽያጭ ውል በተለምዶ ‹‹የመንደር ውል›› በመባል ይታወቃል፡፡ እነዚህ ውሎች በልዩ ሁኔታ ሕጋዊ ውጤት የሚያስከትሉበት ጊዜ አለ፡፡ (ክፍል ሁለት ይቀጥላል)
نمایش همه...
በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች የወንጀል ችሎቶች፡ ሰብአዊ መብቶች የት አሉ? የክስ ይዘቱ ፍትሓብሔራዊ ባህርይ ስላለው የሕጋዊነት መርህን አያሟላም በሚል በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ሲነሳ ስላላው አተገባበር -የፍትሐ ብሔር ጉዳዮች ወደ ወንጀል ሲቀየሩ፡ ፍትህ ተከልክሏል ወይስ ዘገየ? ፀሓፊው፡ አልማው ወሌ ጭማቂ ሃሳብ ይህ ጽሑፍ የሕጋዊነት መርህ አተገባበርን እና የወንጀል ክሱን የፍትሓብሔራዊ ባህርይን በሚመለከት በኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት ውስጥ በወንጀል ጉዳዮች እንደ መጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ሊነሱና ሊዳኙ የሚችሉትን የዳኝነት አካሄድ በወፍ በረር ይመረምራል። የሰነድ ማስረጃዎችን ችላ በማለት በአሁኑ ወቅት እንዲህ ዓይነት መቃወሚያዎችን ወደ ስረ ነገር የክርክር ደረጃ የማስተላለፍ አሠራር፣ ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍና አህጉራዊ የሰብዓዊ መብት ሰነዶች፣ እንዲሁም ከብሔራዊ ሕጎችና በወንጀል ሕግ ፍልስፍና መርሆች ጋር የማይጣጣም ነው ሲል ይሞግታል። ሕግንና አተገባበርን በመጠኑ ባካተተ የአስተምህሮ ጥናት ዘዴ የሕጎቹን ይዘትና መንፈስ በመተንተን የእነዚህን መርሆች በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ የክርክር ደረጃ የበለጠ ጠንካራ እና ሰብአዊ መብትን ያከበረ የወንጀል ክርክር አመራር ስርዓት ተግባራዊነት እንዲኖር ፍርድ ቤቶች በሕግ የተጣለባቸውን ኃላፊነት ሊወጡ ይገባል በሚል ይጠቁማል፡፡ ቁልፍ ቃላት፡ የሕጋዊነት መርህ፣ ፍትሓብሔራዊ ባህርይ፣የመጀመሪያ ደረጃ ተቃውሞዎች፣ ሰብዓዊ መብቶች፣ የወንጀል ሕግ፣ የፍርድ ሂደቶች፣ የሰነድ ማስረጃዎች፣ የኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት ፩. መግቢያ ከሕግ ውጪ ያለመታሰር፣ ፍትሃዊ ዳኝነት እና የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት ሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ ህገ መንግስት ከፍተኛ አጽንኦት ተሰጥቶአቸው ጥበቃ ያገኙ ሲሆን ኢትዮጵያ ያፀደቀቻቸው አለም አቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብቶች ሰነዶችን ጨምሮ የዓለም አቀፍ የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን (ICCPR) ፣ የአፍሪካ የሰዎች እና የህዝቦች መብቶች ቻርተር (ACHPR)፣ እና ፕሮቶኮል ለአፍሪካ የሰብአዊ እና ህዝቦች መብቶች በአፍሪካ የሴቶች መብት ቻርተር (ማፑቶ ፕሮቶኮል)። እነዚህ ሰነዶች ንፁህ ሆኖ የመገመት፣ስለ ክሱ ምንነት እና መንስኤ እንዲሁም ማስረጃ በፍጥነት እና በዝርዝር የማወቅ መብት እና መከላከያ ለማዘጋጀት በቂ ጊዜ እና ጠበቃ የማግኘት መብትን ያረጋግጣሉ ። ፍትሓዊ ዳኝነት የማግኘት ሰብአዊ መብት ጋር የተያያዘውና ሕጎቹ ከፍተኛ ትኩረት የሰጡት ጉዳይ ከሕጋዊነት መርህ ጋር የተያያዘው ጉዳይ ሲሆን ይህ መርህ አንድ ድርጊት ወይም አልድርጊት በተፈጸመበት ጊዜ ወንጀል ስለመሆኑ በግልጽ የሚደነግግ ሕግ ሳይኖር ማንም ሰው ጥፋተኛ ሊደረግ የማይገባ መሆኑን የሚያስቀምጥ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህ መርህ በሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን (ICCPR) አንቀጽ 15(1) ፣የአፍሪካ የሰዎች እና የህዝቦች መብቶች ቻርተር (ACHPR) እና የኢፌዲሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 2 ላይ በግልፅ ተጠብቋል። እንዲሁም መርሁ ግልጽ እና ተገማች የሆኑ የወንጀል ሕጎች አስፈላጊነት ላይ አፅንዖት በመስጠት ግለሰቦች ሕጉን የሚያዉቁበትና ራሳቸውን ከጥፋት ሊያርቁ የሚችሉበት ስርዓት ሊኖር እንደሚገባ፤ስለ ሕጉ በግልጽ የሚያውቁበት ፍትሃዊ ማስታወቂያ እንዲኖራቸው እና ባህሪያቸውን በዚህ መሰረት ማስተካከል እንዲችሉ መደረግ እንደአለበትም የግድ ይላል፡፡. በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ውስጥ የሕጋዊነት መርህ እና ከዚሁ መርህ ጋር ተዛማጅነት ያለው የፍትሃብሔር ባህርይን የሚመለከት መርህ በወንጀል ጉዳዮች እንደ ቀዳሚ መቃወሚያዎች በብዛት ይነሳሉ። እነዚህ መቃወሚያዎች የዐቃቤ ህግን ክስ መነሻ አድርገው የሚነሱ ሲሆን ክሱ ውስጥ የተዘረዘረው ድርጊትም የወንጀል ጥፋት አለመሆኑን ወይም በፍትሐ ብሔር ህግ ስር የሚሸፈን ስለመሆኑ በመግለጽ ሊቀርቡ የሚችሉ ናቸው፡፡ነገር ግን ፍርድ ቤቶች በዚህ ረገድ የሚቀርቡ መቃወሚያዎችን ብዙውን ጊዜ ጎን በመተው ጉዳዮቹ በፍሬ ነገር ክርክር በማስረጃ የሚነጥሩ ናቸው በሚል የሚያልፉበት ሙሉ የሙከራ ደረጃ በማዘዋወር፣ በማስረጃነት ብቻ ወደ ጎን የሚሰለፉበት አሳሳቢ አዝማሚያ ተፈጥሯል። ይህ አሰራር ብዙውን ጊዜ ከክሱ ጋር ተያይዘው እንዲሁም ከመጀመሪያ መቃወሚያ ላይ በጽሑፍ ከሚሰጥ አስተያዬት ጋር ተያይዘው የቀረቡትን የሰነድ ማስረጃዎች ችላ በማለት እና በወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ስለመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ነጥቦች አይነትና ብዛት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም ለመተግባር ባለመፈለግ የተከሳሹን ፍትሃዊ ዳኝነት የማግኘት ሰብአዊ መብት ሊጣስ ይችላል። ይህ አጭር ጽሑፍ በህጋዊነት መርህ ላይ ተመስርቶ በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት በሚቀርበው የወንጀል ክስ ፍትሃብሔራዊ ባህርይን በተመለከተ በዓለም አቀፍ እና በአህጉራዊ የሰብአዊ መብት ሰነዶች፣ በብሄራዊ ህጎች እና አሁን ባለው የፍርድ ቤት አሰራር መካከል ያለውን ያለመጣጣም በመመርመር ይህንን ችግር በአጭሩ ለመተንተን ያለመ ነው። የሕጎቹንና የጉዳይ ጥናቶችን ባካተተ የአስተምህሮ ምርምር ዓለምአቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብት ሰነዶች፣ የኢትዮጵያ ህጎች እና በሕግ ትርጉም የተቋቋሙ የህግ መርሆዎች፤ የህጋዊነት እና የፍትሐብሔራዊ ይዘትን የሚመለከቱ መርሆዎችን እንደ መጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ በማንሳት እንዴት መተግባር እንደሚቻልና እንዴት እንደሚያስገነዝቡ፣ አሁን ያለው የአገራችን ፍርድ ቤቶች በተለይም የፌዴራል ፍርድ ቤቶች እንዲህ ያሉትን መቃወሚያዎች ወደ ሥረ ነገር የክርክር ደረጃ የማስተላለፍ ልምድና አሰራር ከእነዚህ ከተመሰረቱ መርሆች ጋር የሚጋጭ የሚሆነው በምን መንገዶች እንደሆነ፣. ይህ አሰራር በተከሳሹ ላይ የሚያስከትለው መዘዝ እና የኢትዮጵያ የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ስርዓት አጠቃላይ ታማኝነት ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተጽእኖ ምንነት፣ የህጋዊነት እና የወንጀል ክስ የፍትሓብሔራዊ ይዘት ያለው ነው በሚል በመቃወሚያነት ሲነሱ እነዚህን መርሆችን የበለጠ ውጤታማና እና መብትን ያከበረ አሰራርን ለማረጋገጥ የሚያስችል የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ የክርክር አመራር ስርዓቶችን ማሻሻል የሚቻልባቸው መንገዶችን ያሉ መሆን ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን በመመስረት፣ ጭብጦቹን ከብዙ ጥቂቶቹን ለመዳሰስና ፀሐፊው ሊሆን ይገባል በሚለው አግባብ ለመመለስ ይሞከራል፡፡ ሆኖም ለጽሑፉ መነሻ የሆኑ ተጨባጭነት ያላቸው ጉዳዮች የፍርድ ሂደቱን ያልጨረሱም ስላሉ ጽንሰ ሀሳቦቹንና የሰበር ውሳኔ ከመመርመር ውጪ ለጊዜው በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ከመጥቀስ ተቆጥቤአለሁ፡፡ ወደፊት ጉዳዮቹ ሲያልቁ ግን ፁሑፉ ተገቢነት ያለውን የምርምር ስራ ማጣቀሻ ደንቦችን በመከተልና በርካታ መዛግብቶችን በመፈተሸ ተሻሽሎ ሊቀርብ እንደሚችል ሙሉ ተስፋ አለኝ፡፡ ፪. የጽንሰ ሐሳና የሕግ ማዕቀፎች 1. ዓለምአቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብቶች ሰነዶች፣የኢትዮጵያ ህጎች እና የህግ መርሆዎች
نمایش همه...
የኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን (ICCPR) እና የአፍሪካ የሰዎችና ሕዝቦች መብቶች ቻርተር (ACHPRን) ጨምሮ አገሪቱ ያጸደቃቸውን ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብት ስምምነቶችን የማክበር ግዴታ አለበት። ለዚህም ሕገ መንግስቱ በአንቀጽ 13 (1) ስር በሕገ መንግስቱ ምዕራፍ ሶሶት ስር የተካተቱን የመሰረታዊና የነጻነት ሰብአዊ መብቶች ድንጋጌዎችን በየትኛውም እርከን የሚገኙ ሶስቱም የመንግስት አካላት የማክበርና የማስከበር ኃላፊነትና ግዴታ አለባቸው በሚል የተቀመጠውን ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌ በዋቢነት መጥቀስ የሚቻል ከመሆኑም በላይ ከላይ የተጠቀሱት የሰብአዊ መብት ሰነዶችም ጭምር የሚደነግጉ ግዴታ ነው፡፡ እነዚህ ስምምነቶች ከኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት እና ከወንጀለኛ መቅጫ ሕጉ ጋር በመሆን የሕጋዊነት መርህን ለማስከበርና ፍትሐዊ ዳኝነት የማግኘት ሰብአዊ መብቶችን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሰፊ ማዕቀፍ የዘረጉ ናቸው፡፡ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 9 (4) አግባብ የአገሪቱ የሕግ አካል የሆኑት አለም አቀፍ ስምምነቶች እና በወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀፅ 2(2) ስር የተደነገገው የህጋዊነት መርህ ማንኛው ድርጊት ወይም አልድርጊት በወንጀል ሕጉ አስቀጪነቱ በግልጽ ካልተመለከተ በስተቀር የወንጀል ጥፋት እንደሌለና ተጠያቂነትን ሊያስከትል እንደማይችል በግልጽ ያውጃል። ይህ መርህ ከዚህ አገላለጽ በተጨማሪ በተከታዮቹ ሁለት የወንጀል ሕግ ፍልስፍናዎች የተደገፈና የተጠናከረ ስለመሆኑ በዘርፉ የተደረጉ በርካታ ጽሑፎች ዋቢ ናቸው፡፡ እነዚህ ፍልስፍናዎች፡“nullum crimen sine lege” እና የዚሁ መርህ ተጓዳኝ የሆነው "nulla poena sine lege," ሲሆኑ በህግ እስካልተገለፀ ድረስ ወንጀል ነው። ይህ መርህ የወንጀል ወንጀሎች እና ቅጣቶች በግልፅ ተብራርተው ለህዝብ ተደራሽ እንዲሆኑ በሚጠይቀው "Nullum Crin Sine Lege" ጽንሰ-ሀሳብ እና በተጓዳኝ "nulla poena sine lege" የተጠናከረ ነው፡፡ እነዚህ ጽንሰ ሐሳቦች እንደ ቅደም ተከተላቸው ያለ ሕግ ወንጀል የለም፣ያለ ሕግ ቅጣት ሊኖር እንደማይችል የሚያስገነዝቡ ስረ መሰረታቸው የሮማዊያን ሕግ እንደሆነ የሚመሰከርላቸው፤ ረዥም ታሪክ ያላቸውና የዳበረ የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ባላቸው በርካታ አገራትም በሰፊው የሚሰራባቸው፣በርካታ አለም አቀፍና አህጉዊ ሰብአዊ መብቶችም ከብዙ አመታት በፊት እውቅና የሰጧቸው መሰረታዊ መርሆዎች ናቸው፡፡ በተጨማሪም የወንጀል ክስ ፍትሃብሔራዊ ባህርይ ላለው ድርጊት ወይም አልድርጊት ሊኖረው አይገባም የሚለው መርህ "ultima ratio" ከሚለው ሐረግና ጥሬ ትርጉሙም የመጨረሻው አማራጭ ከሚለው የላቲን ቋንቋ ፍቺ ጋር የተቆራኘ ጽንሰ ሐሳብ ሲሆን ከወንጀል ፍትህ አስተዳደር ጋር ተያይዞ ሲታይ መሰረተ ሀሳቡ የወንጀል ህግ የመጨረሻ አማራጭ መሆን አለበት የሚለውን የወንጀል ህግ አተገባበር የሚያሳስብ ነው፡፡ ይኼው መርኽ የወንጀል እና የፍትሐ ብሔር ጥፋቶችን የመለየት አስፈላጊነትን አፅንዖት የሚሰጥ ሲሆን የወንጀል ህግ የህዝብን ፀጥታ እና ደህንነትን አደጋ ላይ ሊጥሉ ለሚችሉ ጥፋቶች ጠንከር ያሉ እርምጃዎችን ለመውስድ የተቀመጠ የሕግ አማራጭ መሆኑን የሚያረጋግጥ ከመሆኑም በላይ የወንጀል ሕግን ለመጠቀምና ለመተግበር የሚቻለው ይኼው ሕግ የመጨረሻው አማራጭና አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ብቻ ስራ ላይ እንዲውል የሚያሳስብ ጭምር ነው፡፡ በዚህ መርኽ መሰረተ ሀሳብ አግባብ እያንዳንዱ ጎጂ እርምጃ ወንጀል መሆን የሌለበት ሲሆን የፍትሐ ብሔር ጥፋት የውሉን መጣስ ወይም በቸልተኝነት ጉዳት ሊያስከትል የሚችል ቢሆንም ትኩረቱ ተጎጂውን በመካስ ላይ የተመሰረተ መሆኑን ያስረግጣል፡፡. የወንጀል ጥፋቶች በአጠቃላይ ለህብረተሰቡ ጎጂ ናቸው ተብለው የሚታሰቡ ሐሳቦች ወይም ግድየለሽነቶች ተገቢው ቅጣት የሚገባቸው ናቸው.ተብለው የሚታመኑ ናቸው፡፡ ተጠቃሹ መርኽ የወንጀል ጥፋቶች በእርግጥም እውነተኛ ጥፋተኝነትን የሚያሳዩ፤ተገቢ ያልሆነ ድርጊቶችን ለመግለጽ የሚያስችሉ፣ በግለሰቡ ሆነ ተብሎ፣ በግድየለሽነት ወይም በቸልተኝነት የሚፈጸሙ ሲሆኑ አነስተኛ ወንጀሎች ወይም ያልታሰቡ ጉዳቶች በእውነት ተጠያቂነትን የሚያስከትሉ ናቸው ተብለው እንደ ወንጀል የመቆጠር እድላቸው አነስተኛ መሆኑንም የሚያገነዝብ መርኽ ነው፡፡ በአጠቃላይ ይህ መርኽ የወንጀል ህግ እንደመጨረሻ አማራጭ በጥቂቱ ጥቅም ላይ መዋል ያለበት ስለመሆኑ እና በእውነት ተወቃሽ ለሆኑ እና በህብረተሰቡ ሰላምና ደህንነት ላይ ስጋት ለሚፈጥሩ በጣም ከባድ ወንጀሎች ላይ ብቻ ስለመሆኑና ያነሱ ከባድ ስህተቶች ብዙውን ጊዜ በፍትሃ ብሔራዊ የሕግ ማዕቀፎች በተሻለ ሁኔታ ሊዳኙ የሚችሉ መሆኑን በግልጽ ያስረዳል፡፡ 2. በወንጀል ክስ ስለሚቀርቡ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች፡ በጥቂቱ በ1954 የወጣው የኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ህግ የክሱን ትክክለኛነት ለመቃወም እና ፍትሃዊ የዳኝነት መብቶችን ለማረጋገጥ የሚያስችል ማዕቀፍ ቢያስቀምጥም በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ሊቀርቡ የሚችሉ ምክንያቶችን አመላካች በሆነ መልኩ አስቀምጦ ከማለፉ ውጪ ዝግ አላደረገውም፤ ምክንያቶቹ ተዘርዝረው አላለቁም፡፡ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 74353(ቅጽ-14) በተሰጠ የህግ ትርጉም ይኼው የድንጋጌ ሙሉ ይዘት ተብራርቶ ድንጋጌው አመላካች ምክንያቶችን ማስቀመጡን ግልጽ የሆነ የሕግ ትርጉም የተሠጠበት ሲሆን ተዘርዝረው ከአላለቁትና በመቃወሚያነት ሊቀርቡ ከሚችሉት ምክንያቶች አንዱ ደግሞ የህጋዊነት መርህን የሚመለከት ጉዳይ እንደሆነ፣ በዚህ መርህ አግባብ ደግሞ የአቃቤ ሕግ ክስ የፍትሃ ብሔር ባህርይ ያለው ከሆነ ከሕጋዊነት መርህ ጋር አብሮ ሊሄድ የማይችል በመሆኑ ይህንኑ የመከራከሪያ ነጥብ መሰረት በማድረግ ክርክር ሲቀርብ ፍርድ ቤቶች በሚገባ አጣርተው መወሰን የሚገባቸው መሆኑን ያስገነዝባል፡፡ ይህ የሰበር ችሎቱ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም እጅግ ተገቢና አስተማሪ የሆነ ስለመሆኑ እንደ እነ ስሜነህ ኪሮስ ባሉ የዘርፉ እውቅ ምሁራን ጭምር ውዳሴ የተቸረው ነው፡፡ ይህ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ቢኖርም የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 130(2) እስካሁን በሌላ ተራማጅና ግልጽ በሆነ ድንጋጌ አልተተካም፡፡ 3. አሁን ስላለው የፍርድ ቤቶች ተግባር ከላይ እንደተጠቐሰው ግልጽ የሆኑ የሰብዓዊ መብት ሰነዶችና ብሔራዊ ሕጎች ስለ ሕጋዊነትና የወንጀል ክስ ፍትሃ ብሄራዊ ይዘት እንደመቃሚነት መቅረብ መቻል እና ፍርድ ቤቶቹም ወደ ስረ ነገሩ ከመግባታቸው በፊት ተገቢውን ማጣራትና ምርመራ አድርገው ተገቢውን ብይን የመስጠት ግዴታ ያለባቸው መሆኑን የሚያስገነዝቡ ቢሆንም በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች ያለው አሠራር ግን እነዚህን መርሆች ከማስከበር አኳያ ብዙ ጉድለት ያለበት ነው፡፡ ፍርድ ቤቶቻችን እንደዚህ አይነት መቃወሚያዎችን በስረ ነገር ክርክር ጊዜ በማስረጃ የሚጣሩ ናቸው በሚል ውድቅ ሲያደርጉ እና ጠባብ የሆነ አካሄድን ሲመርጡ ይስተዋላል፡፡ ይህ አካሄድ እጅግ ጉልህ የሆነ የስነ ስርዓት ግድፈት ያለበት መሆኑን ነጥሮ የሚታየው ደግሞ ደግሞ አቃቤ ህግ ክሱን ሲያቀርብ ከክሱ ማመልከቻ ጋር ለማስረጃነት የዘረዘራቸው ሰነዶች ይዘት እና ተከሳሹ ደግሞ በመቃወሚያው ላይ አስተያየቱን በጽሑፍ ሲያቀርብ አያይዞ የሚያቀርበው የሰነድ ማስረጃ ይዘትን ባለመመልከት ዝም ተብሎ ታልፎ በሚሰጥበት ጊዜ ነው፡፡ እንደዚህ አይነት አካሄድ ችግሩን የበለጠ ያባብሰዋል። በአቃቤ ሕጉ ክስ
نمایش همه...
ወይም ከተከሳሹ መቃወሚያ አስተያዬት ጋር ተያይዘው የቀረቡት የሰነድ ማስረጃዎች ለክሱ መሰረት የሆነውን ድርጊት ወይም አልድርጊት የወንጀል ተጠያቂነትን የማያስከትል ወይም የፍትሓ ብሔራዊ ባህርይ የተላበሰ መሆን ያለመሆኑን ከወዲሁ ለመመርምር ወሳኝ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡. ለምሳሌ፡- የውል ስምምነቶች (ማንኛውም ዓይነት)፣ ወይም ሌሎች ሰነዶች ክርክሩ በመሠረቱ የውል ጉዳይ መሆኑን ወይም በፍትሐ ብሔራዊ ባህርይና መፍትሔዎች ውስጥ ሊካተት እንደሚችል መነሻ ሊሆኑ ይችላሉና። በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያቃዎች አቀራረብና ብይን አሰጣጥ ሂደት እንደዚህ አይነት ማስረጃዎችን በዝምታ ማለፍ የመቃወሚያዎችን መሰረታዊ ዓላማ ትርጉም አልባ ከማድረጉም በላይ የተከሳሹን የክሱን ትክክለኛነት ለመቃወም ያለውን ፍትሃዊ እድልም የሚገድብና የሚያሳጣ ነው፡፡ ከላይ የተጠቀሰው አይነት አካሄድና አሰራር አሉታዊ ውጤት ከፍተኛ ነው፡፡. በወንጀል ችሎት በመጀመሪያ ደረጃ በፍፁም ሊፈረድበት በማይገባ መልኩ ግለሰቦች ለጭንቀት፣ ለወጪ እና ለመልካም ስም ጉዳት ይዳርጋቸዋል፡፡ ይህ ደግሞ ፍትሃዊ ዳኝነት የማግኘት መብታቸውን የሚጋፋ ብቻ ሳይሆን ህዝቡ በአገሪቱ የወንጀል ፍትህ ስርዓት ላይ ያለውን እምነት የሚያሳጣ ነው፡፡ ስለሆነም እንዲህ አይነት አካሄድ ለትክክለኛ ፍትህ እና የሰብአዊ መብት ጥበቃ ትኩረት ከማድረግ ይልቅ ሕጉን መሰረት ላላደረገ የሥነ ሥርዓት ፎርማሊቲዎች ቅድሚያ የሚሰጥ የሚያስመስለው በመሆኑ እጅጉን ሊወገዝ የሚገባው ነው፡፡። 4. መደምደሚያ እና መፍትሔዎች 4.1. መደምደሚያ በህጋዊነት መርህ እና በክሱ ፍትሐ ብሔራዊ ባህርይ መቃወሚያዎች ላይ ተመስርተው የሚቀርቡትን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎችን በሚመለከት በአገራችን የወንጀል ችሎቶች አሁን ያለው አሰራር በወፍ በረር እንኳን ሲታይ ከክሱና ከመቃወሚያው ጋር ተያይዘው የሚቀርቡትን አግባብነት ያላቸውን የሰነድ ማስረጃዎችንና አስገዳጅነት ያለውን የሰበር ውሳኔ ጭምር ወደ ጎን በመተው ወደ ስረ ነገር ክርክር ደረጃ እንዲሻገሩ ማድረግ መሆኑን የሚያስገነዝብ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ከአገሪቱ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ የሰብአዊ መብት ግዴታዎች እና በህገ መንግስቱ እና በአገራዊ ህጎቿ ላይ ከተቀመጡት መርሆዎች ጋር የሚቃረን ነው። ይህ አሰራር ፍትሃዊ ዳኝነት የማግኘት መብትን የሚጎዳ፣ ተከሳሾችን ላልተፈለገ ችግር የሚያጋልጥ፣ ህዝቡ በወንጀል ፍትህ ስርዓቱ ላይ ያለውን እምነት የሚሸረሽም ነው። ፍርድ ቤቶች የአገሪቱ የበላይ የዳኝነት አካል የሰጠውን አስገዳጀ የሕግ ትርጉም ተግባራዊ ባለማድረግ የሰበር ችሎቱን የአስገዳጅ ውሳኔ ትርጉም አልባ ማድረጋቸውም የዳኝነት አካሄዳቸው ተገማችና ወጥነት እንዳይኖረው በማድረግ የዚህ ስርዓት ውጤታማ ያለመሆን ማሳያ ለመሆን ችለዋል፡፡ 4.2 መፍትሔዎቹ የሕጋዊነትንና የፍትሓ ብሔር ባህርይ ያለው ክስን መሰረት አድርገው የሚቀርቡትን መቃወሚያችን በትክክል በመተግበር ረገድ በአገሪቱ የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ሥርዓት ውስጥ ቀድሞ በነበረውና አሁን ባለው አሠራር የተስተዋሉትን ድክመቶች ትርጉም ባለው መልኩ ለመፍታት እንዲቻል ብዙ ማሻሻያዎችን ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ይታመናል። በዚህም መሰረት ስለ አቃቤ ሕግ የሙያ ግዴታ የሚመለከቱ የተለያዩ አለም አቀፍ ሰነዶችን ጨምሮ ሌሎች የወንጀል ስነ ሕግ ጽሑፎችን እንዲሁም የአገራትን ተሞክሮ በሚመለከት ሳንሳዊ የምርምር ዘዴን በመከተል ጥልቀት ያለውን ጥናት አድርጎ በትክክል ተግባራዊ ሊደረጉ የሚገባቸውን አማራጮችን ለይቶ ማውጣት እንደተጠበቀ ሁኖ በዚህ አጭር ጽሑፍ ደሰሳ መነሻ ግን ታከታዮቹ ጉዳዮች እንደመፍትሔ ሊጠቆሙ ይችላሉ የሚል እምነት አድሯል፡፡ እነዚህም፡- • የክስ መቃወሚያ ሂደቶችን ማጠናከር፡- በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁጥር 245/2/ እንደተመለከተው የወንጀል ክስ መቃወሚያ ላይ የተሟላ የዳኝነት ክለሳ ስርዓትን ተግባራዊ ለማድረግ ወይም በፍርድ ቤት ስርዓት ውስጥ ልዩ ልዩ የቅድመ ስረ ነገር ችሎት ክፍሎችን በማቋቋም በህጋዊነት እና በፍትሃብሄር ባህርይ ላይ የተመሰረቱ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎችን በጥልቀት ለመመርመር የሚያስችል ስርዓት መታሰብ ይገባዋል፡፡ ይህንኑ ለማድረግ የተለያዮ አገሮችን መልካም ተሞክሮ በሰፊው ማሰጠናትና ከአገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አዛምዶ ስርዓት ማበጀት ተገቢነት ይኖረዋል፡፡ • ከክሱና ከመቃወሚያው ጋር ተያይዞ የሚቀርቡትን ሰነዶችን ይዘት በሚገባ መመርመርና ማገናዘብ፡- ፍርድ ቤቶች በከሳሽ ወገን ከክሱ፣ በተከሳሽ ወገን ደግሞ ከክስ መቃወሚያ አስተያዬቱ ጋር ተያይዘው የቀረቡትን፣ አግባብነትና ብቃት ያላቸውን የሰነድ ማስረጃዎች ይዘት አንድ ላይ፤ በሙሉ በጥንቃቄና በጥልቀት የመመርመርና የማጣራት ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌዎች፣አዲሱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ እና የአገሪቱ የህግ አካልወ የሆኑ በርካታ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ የሰብአዊ መብቶች ሰነዶች የጣሉባቸው ኃላፊነትና ግዴታ ያለባቸው መሆኑን በቅድሚያ መገንዘብና ለመተግበርም ቁርጠኝነት ሊኖራቸው ይገባል፡፡ • ስልጠና እና ግንዛቤ፡- ዳኞች፣ ዓቃብያነ ህጎች እና ጠበቆች ስለ ህጋዊነት መርህ አስፈላጊነት፣ ስለ አንዳንድ የወንጀል ክሶች የፍትሓ ብሔር ይዘትና ባህሪ፣ ስለ ወንጀል ክስ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቀራራብና በማስረጃ ስለሚረጋጥበት እንዲሁም ስለ ሕጎቹና ስለ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ይዘትና አተገባበር፣ የህግ ትርጉሙን ያለማክበር ሊያስከትለው ስለሚገባ ተጠያቂነት እንደዬተቋማቱ ነጻነትና ቅንጅታዊ ስራ እየታዬ በተናጠል ወይም በጋራ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ፡፡ ይህ የወንጀል ክስ የሚያዘጋጅ አቃቤ ሕግ የሕጋዊነት መርህን በሚገባ አገናዝቦ ክሱን እንዲያቀርብ የሚያደርግ ሲሆን ይህንኑ ሲያልፍ ደግሞ መቃወሚያውን የሚያቀርቡ ባለሙያዎች መቃወሚያውን ሲያቀርቡ ሊወስዱ ስለሚገባው ጥንቃቄና የማስረጃ ማቅረብ ግዴታ በውል እንዲገነዘቡ ፣ ዳኞች ደግሞ ሕጋዊነትና ፍትሃ ብሄራዊ ይዘትን መሰረት አድርገው የሚቀርቡ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያን በአግባቡ ስለማስተናገድ የሚያስችል ብቃትና ጥንካሬ እንዲኖራቸው የሚያስችል ነው ተብሎ ይታመናል፡፡ እንደዚህ አይነት ስልጠና ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብት ስምምነቶች ላይ ያላትን ግዴታዎች እንዲሁም በህገ መንግስቱ እና በአገራዊ ህጎች ውስጥ የተካተቱትን መርሆች ሊያጎላ ይገባል። • የህግ ግልፅነት፡-ህግ አውጭዎች በወንጀል ህግጋት ማረቀቅ የስራ ሂደት ግልጽ እና ትክክለኛ እንዲሆን ተገቢውን ጥንቃቄና ጥረት በማድረግ የዘፈቀ አተገባበርን ከወዲሁ የሚከላከልና የሚቀንስ የወንጀል ስነ ስርዓት ሕግ እንዲኖር ማድረግ አለባቸው። ከህጋዊነትና ከፍትሃ ብሄራዊ ይዘት ጋር ተያይዞ የሚነሱትን መቃወሚያዎች ከስረ ነገሩ በፊት በማስረጃ አጣርቶ ለመወሰን የሚያስችል የክርክር አመራር ስርዓት የሚዘረጋ ድንጋጌ በአዲሱ የወ/መ/ሥ/ሥ/ሕግ እንዲገባ ቢደረግ ተመራጭ ነው፡፡ በአጠቃላይ እነዚህን ስርዓቶችን በመከተልና ማሻሻያዎች በማድረግ የወንጀል ጉዳይ የክርክር አመራር ስርዓት ከስረ ነገር በፊት መቃወሚያዎችን በአግባቡ በማስተናገድ መሰረተ ቢስ ወይም አላግባብ የሚቀርቡ ክሶችን መከላከል መቻል አለበት፡፡ ይህ ካልሆነ በዓለም አቀፍና በአህጉር ደረጃ የወጡና የአገሪቱ የሕግ አካል የሆኑ የሰብአዊ መብት ሰነዶች የተከሳሾችን መብት ለማስጠበቅ እና ፍትሃዊ የህግ ስርዓት /Fair Trial/ መርሆዎችን ለማስከበር ያስችላሉ በሚል የደነገጓቸውን ድንጋጌዎችን ትርጉም ባለው መልኩ መተግበር አይቻልም፡፡
نمایش همه...
በአልማው ወሌ (የቀድሞ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰ/ሰ/ችሎት ዳኛ!)
نمایش همه...
ከሳሽና ተከሳሽ ከሆኑት ወገኖች በተጨማሪ በክርክር ሂደት ሌሎች በክርክሩ ውስጥ ገብተው የሚሳተፉበት ሥርዓት የመጀመሪያው በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 40(2) መሠረት ፍርድ ቤቱ በራሱ አስተያየት ወይም በተከራካሪዎች አመልካችነት የሚቀርበውን ክርክር በመመልከት ለውሳኔ አሰጣጥ አስፈላጊና ምቹ መሆኑን ያረጋገጠ እንደሆነ ማንኛውም አግባብ ያለው ሠው በተከሳሽነት በክርክሩ እንዲገባ ሊያዝ እንደሚችል ተመልክቷል፡፡ ሁለተኛው በክርክሩ ተካፋይ መሆን የሚገባው ወገን እና በክርክሩ ባይሳተፍ መብቱ የሚነካበት መብቱን ወይም ጥቅሙን ለማስጠበቅ በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 41 መሠረት ጣልቃ መግባት የሚችል ስለመሆኑ የተመለከተ ነው፡፡ ሦስተኛው በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 43 መሠረት ስለተከሳሽ ሆኖ ድርሻ/ኃላፊነት የሚወስድ ሰው በተከሳሽ ጠያቂነት ወደ ክርክሩ የሚገባበት ሥርዓት ነው፡፡
نمایش همه...
ፍትህ

ምን እናግዞት ?