ETBACK-ETHIOPIA
رفتن به کانال در Telegram
3 329
مشترکین
-324 ساعت
-247 روز
-13130 روز
آرشیو پست ها
3 329
የዒድ አል ፈጥር በዓል አርብ ይከበራል
1 ሺህ 447ኛው የዒድ አል ፈጥር በዓል በሳዑዲ አረቢያ ጨረቃ ባለመታየቷ በአርብ መጋቢት 11 ቀን ይከበራል፡፡
ዛሬ የሸዋል ወር ጨረቃ ባለመታየቷ 1447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ከነገ ወዲያ አርብ (ጁምዓ) ተከብሮ እንደሚውል ነው የተገለጸው፡፡
3 329
+1
#Update
የዘንድሮውን የረመዷን ጾም ፍጻሜ እና የዒድ አልፈጥር በዓልን ለመወሰን በሳዑዲ አረቢያ የጨረቃ ምልከታ እየተከናወነ ይገኛል።
ይሁን እንጂ በዋና ዋና የምልከታ ማዕከላት ያለው የአየር ሁኔታ ደመናማ መሆን ለምልከታው ፈታኝ ሁኔታን ደቅኗል።
የሳዑዲ አረቢያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የጨረቃ መታየት አለመታየቱን አስመልክቶ በቅርብ ሰዓታት ውስጥ ይፋዊ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ዛሬ ጨረቃ ከታየች የዒድ አልፈጥር በዓል ነገ ሐሙስ ይውላል። ጨረቃ ዛሬ ካልታየች ነገ የረመዷን 30ኛው ቀን ሆኖ በዓሉ አርብ (ጁምዓ) ይሆናል።
ይከታተሉን !
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 9 ቀን 2018 ዓ/ም
3 329
🎓 የ Exit Exam ውጤትዎን በቀላሉ እና በፍጥነት ይመልከቱ!
ያለ ምንም መቆራረጥ እና መጨናነቅ ትክክለኛውን የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ውጤት ማረጋገጫ አማራጮችን (Web, Telegram, SMS) በአንድ ቦታ አሰባስበንልዎታል።
💡 ውጤትዎን ካዩ በኋላም በእኛ 'Status Calculator' በመጠቀም ውጤትዎ ምን ማለት እንደሆነ ይወቁ!
👇 መላው ተማሪዎች እያዩበት ያለው ሊንክ ይሄው፡
https://www.google.com/search?q=techstudytips
3 329
🎓 የ Exit Exam ውጤትዎን በቀላሉ እና በፍጥነት ይመልከቱ!
ያለ ምንም መቆራረጥ እና መጨናነቅ ትክክለኛውን የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ውጤት ማረጋገጫ አማራጮችን (Web, Telegram, SMS) በአንድ ቦታ አሰባስበንልዎታል።
💡 ውጤትዎን ካዩ በኋላም በእኛ 'Status Calculator' በመጠቀም ውጤትዎ ምን ማለት እንደሆነ ይወቁ!
👇 መላው ተማሪዎች እያዩበት ያለው ሊንክ ይሄው፡
🔗 https://techstudytips.com/ethiopia-exit-exam-result/
3 329
የኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውንና አስከሬናቸውም መገኘቱን አንድ ከፍተኛ የእስራኤል ባለሥልጣን ለሮይተርስ ዜና ወኪል ገለጹ።
እስካሁን ድረስ ከኢራን በኩል የተሰጠ ይፋዊ ማረጋገጫ የለም።
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በሰጡት መግለጫ ደግሞ ፣ አያቶላ ኻሜኒ በእስራኤልና በአሜሪካ የአየር ጥቃት መገደላቸውን የሚያሳዩ በርካታ ምልክቶች መኖራቸውን ገልጸዋል።
“ዛሬ ማለዳ የአምባገነኑን ኻሜኒ ቅጥር ግቢ ደምስሰናል፤ ይህ አምባገነን ከእንግዲህ የሌለ መሆኑን የሚያሳዩ ብዙ ምልክቶች አሉ “ ሲሉ ተደምጠዋል።
ከኻሜኒ በተጨማሪ የገዥው ሥርዓት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የኢራን አብዮታዊ ዘበብ (RGC) አዛዦች እና የኑክሌር ፕሮግራም ቁልፍ ሰዎች መገደላቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
“ እስራኤል በቀጣይ ቀናትም በሺዎች የሚቆጠሩ የሽብር ሥርዓቱ ኢላማዎች ላይ ጥቃቷን ትቀጥላለች “ ሲሉ አስታውቀዋል።
በቴህራን የሚገኘው የኻሜኒ መኖሪያ ግቢ ከፍተኛ ውድመት እንደደረሰበት የሳተላይት ምስሎች ሲወጡ ውለዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩላቸው መሪው “ ደህና ናቸው “ የሚል መግለጫ ቢሰጡም እስካሁን ኻሜኒ በአካል ታይተው መግለጫ አልሰጡም።
3 329
የትንሹ ድርሻ ለትልቅ አርአያነት!
"ስታዲየማችን በራሳችን" በሚል መሪ ቃል ለአርባምንጭ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ የሚደረገውን ጥረት፣ አንድ ታዳጊ ህፃን እጅግ በሚያስደንቅና ልብ በሚነካ መልኩ ተቀላቅሏል።
ታዳጊ ደርሶልኝ ደስታ ይባላል። ይህ ህፃን ለከተማውና ለስፖርቱ ካለው ፍቅር የተነሳ፣ በቤት ውስጥ ከሚያረባቸው ዶሮዎች መካከል ሁለቱን በመሸጥ ያገኘውን 2,250 (ሁለት ሺህ ሁለት መቶ ሀምሳ) ብር ለስታዲየሙ ግንባታ እንዲውል በደስታ አበርክቷል።
* ስታዲየሙ የኔ ነው ብሎ በማመኑ።
* የሚወዳቸውን ዶሮዎች ለትልቅ ዓላማ አሳልፎ በመስጠቱ።
* "ለሀገሬ ምን አደረግሁ?" ብሎ ለሚጠይቅ ትልቅ ሰው ሁሉ ታዳጊው ደርሶልኝ በተግባር መልስ ሰጥቷል።
ዛሬ በሶሻል ሚዲያ በስፋት እየተዘዋወረ የሚገኘው የዚህ ታዳጊ ተግባር፣ "ለመስጠት የግድ ሀብታም መሆን አይጠበቅብንም፤ ቅን ልቦና ይበቃል!" የሚል ትልቅ መልዕክት ለሁላችንም አስተላልፏል።
በርታ ትንሹ ደርሶልኝ!
አንተ የነገዋ ኢትዮጵያ ኩራት ነህ! 🇪🇹✨
Made-in-Ethiopia
3 329
ከፌስታል ነፃ የሆነችው መርካቶ፤
የአዲስ አበቤዎች የሥልጣኔ ማሳያ…….
መርካቶ በመንገዴ ላይ....🙏
እንዴት ነህ ዛሬ የገጠመኝን ላካፍልህ ህዝባችን ህግ አክባሪ ሆኗል።መርካቶ ዛሬ አንድ ፌስታል የያዘ ሰው የለም።
ከጧት ጀምሬ መሀል መርካቶ በስራ ጉዳይ መኪናዬን አቁሜ በእግሬ ስዞር ቆይቻለሁ ።ፌስታል ይዞ የወጣም ሰው የለ ፌስታል ጣል አትጣል ሲታገል ያየሁትም ፖሊስ የለም።በቃ ህዝቡ በራሱ የወረደውን ህግ ተግብሯል ማለት ይቻላል።
አንዳንድ ህጎች በዱላ እና በሀይል አይተገበሩም።ህዝብ በፍቅር ከታዘዘ እማይተገበር ህግ አይኖርም። ምናለ የትራፊክ ህጉም እንደዚህ ተከብሮ እያንዳንዱ አሽከርካሪ የድርሻውን ቢወጣ አንድም አደጋ እና ሀዘን እንሰማም ነበር እንደ ሀገርም በጣም ትልቅ ለውጥ ልናመጣ እንችል ነበር!!
እውነት ለመናገር የአድስ አበባ ህዝብ ስልጡን ነው።እኔ ዛሬ ባየሁት ነገር ተገርሜያለሁ።በመንግስት የወጣ ህግ በህዝብ ተቀባይነት አግኝቷ በፍቅር ሲተገበር ያየሁበት ትዕይንት ነው።
የአዲስ አበባ ህዝብ አራዳ ነው ህግ አክባሪ ነው🙏
Via አህሙ ፍቅር
©️Driving In Addis
Made-in-Ethiopia
3 329
በሱዳኗ ከተማ የጦር ወንጀል መፈፀሙን የዓለም ዓቀፉ የጦር ወንጀሎች ፍርድ ቤት አረጋገጠ
የዓለም ዓቀፉ የጦር ወንጀሎች ፍርድ ቤት ምክትል ዓቀቢ ሕግ ናዝሃት ሻሜም ኻን፤ ለተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት አምባሳደሮች ባቀረቡት ማብራሪያ በሱዳን ዳርፉር ግዛት የጦር ወንጀል መፈፀሙን አረጋግጠዋል፡፡
ሱዳን ከሚያዝያ 2015 ጀምሮ በሀገሪቱ ጦር ኃይሎች እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ሚሊሻ መካከል ግጭት ውስጥ መግባቷ የሚታወቅ ነው። በሥልጣን ሽኩቻ የተጀመረው ግጭት በመላ ሀገሪቱ ወደ ጦርነት ተለውጧል፡፡ ጦርነቱ ከሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች በጣም ውድመት አድርሷል የተባለው በዳርፉር ክልል መሆኑን ለፀጥታው ምክር ቤት የቀረበው ሪፖርት ያመለክታል፡፡
የፍርድ ቤቱ ምክትል ዓቃቤ ሕግ፣ በዳርፉር የተፈጸመው ወንጀል የጅምላ ግድያ፣ ዘርን መሠረት ያደረገ ጥቃት፣ የግዳጅ እስር፣ ማሰቃየት እና ፆታዊ ጥቃቶችን ያጠቃልላል ሲሉ አስረድተዋል።
3 329
ትራምፕ የኢትዮጵያና ግብፅን መሪዎች ማገናኘት እፈልጋለሁ አሉ
ትራምፕ የግብፅና የኢትዮጵያ መሪዎችን ማገናኘት የሚፈልጉት፤ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ምክንያት በኢትዮጵያ እና በግብጽ መካከል የተፈጠረውን ውዝግብ የሚፈታ ስምምነት ለማበጀት እንደሆነ ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህን ያሉት፤ በስዊትዘርላንድ ዳቮስ በመካሄድ ላይ በሚገኘው የዓለም የኢኮኖሚ ፎረም ጎን ለጎን ከግብጹ አቻቸው ጋር ተገናኝተው በተወያዩበት ወቅት ነው።
ዝርዝሩን ከዕለቱ የዩቲዩብ ዜናችን ያገኙታል።
3 329
ባለስልጣኑ ፈቃድ አውጥተው የሚንቀሳቀሱ መገናኛ ብዙኃን ከ300 በላይ መሆናቸውን ገለጸ
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኋን ባለስልጣን በኢትዮጵያ ህጋዊ ፍቃድ አግኝተው የሚቀሳቀሱ የሚዲያ ተቋማት ቁጥር ሶስት መቶ ዘጠኝ መድረሱን አስታውቋል።
በተጨማሪም 55 አዳዲስ ሚዲያዎች ፈቃድ ወስደው በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ባለስልጣኑ ገልጿል።
የሚዲያዎቹ ቁጥር የብሮድካስት፣ የበይነ መረብ፣ የህትመት እና የዉጭ መገናኛ ብዙኃንን ያካተተ ሥለመሆኑም አመላክቷል።
በዚህም መሰረት 175 የብሮድካስት፣ 20 የህትመት፣ 35 የዉጭ ሚዲያ ክሮስፖንዳንት፣ 73 የበይነመረብ እና አምስት የክፍያ ኢንተርኔት ብሮድካስት፣ አንድ ነፃ የኢንተርኔት ብሮድካስት መገናኛ ብዙኃን ምዝገባ እና ፈቃድ አግኝተዉ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን አስታውቋል፡፡
3 329
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለረጅም ርቀት ጉዞዎች የሚውሉ አውሮፕላኖችን አዘዘ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለረጅም ርቀት ጉዞዎች የሚውሉ
ዘጠኝ 787-9 ድሪምላይነር ጄት አውሮፕላኖችን ከአሜሪካው የአውሮፕላን አምራች ቦይግን ለመግዛት ትዕዛዝ ሰጠ።
በአፍሪካ ቀዳሚው አየር ትራንስፖርት አቅራቢ ኩባንያ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ግዙፉ አውሮፕላን አምራች ቦይንግ ጥያቄው መቅረቡን አስታውቀዋል።
አውሮፕላኖቹ ተገንብተው ከአውሮፓውያኑ 2034 አስከ 2033 ባለው ጊዜ ውስጥ የሚቀርቡ ይሆናል ተብሏል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እነዚህ ዘመናዊ አውሮፕላኖች ለመግዛት ትዕዛዝ ያቀረበው በአሁኑ ጊዜ በመላው ዓለም ያሉትን 145 ዓለም አቀፍ መዳረሻዎቹን ለማስፋት ባለው ዕቅድ እንደሆነ ተነግሯል።
3 329
አትሌቶች መንግስት ቃል የገባውን የማበረታቻ ሽልማት ይፈፅምልን ሲሉ ጠየቁ
ኢትዮጵያን በመወከል በተለያዩ የአትሌትክስ ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ውጤት ያስመዘገቡ አትሌቶች መንግስት የገባልን ቃል ሊፈጽም ይገባል ብለዋል፡፡
አትሌቶቹ፣ የመንግስት የገንዘብ ሽልማት እንዲሁም የዕውቅና መርሀግብር እንደሚደረግላቸው ቃል ተገብቶላቸው እንደነበር ተገልጿል።
ነገር ግን መርሀ ግብሩ በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አናውቅም ሲሉ የገለጹት አትሌቶቹ ፤ መንግስት የሚሰጠን ማበረታቻ ለአትሌቶች ትርጉሙ ብዙ ነው ሲሉ መናገራቸውን ሃራምቤ ሬድዮ ዘግቧል።
3 329
ሩሲያና አሜሪካ በዝግ መምከራቸው ተገለጸ
የፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ልዩ መልዕክተኛ ከአሜሪካ ጋር ገንቢ ውይይት ተደርጓል አሉ።
ልዩ መልዕክተኛው ኪሪል ድሚትሪቭ በዳቮሱ የኢኮኖሚ ፎረም ጎን ለጎን ሩሲያና አሜሪካ ውይይት ማድረጋቸውን አሳውቀዋል።
የአገራቱ ባለስልጠናት በዝግ ከሁለት ሰዐታት በላይ መክረዋል።
በምን ጉዳይ ላይ ውይይት እንዳደረጉ ማብራሪያ ባይሰጥበትም" በርካታ አገራት የሩሲያ አቋም ምን ያህል ዋጋ እንዳለው ዕውቅና እየሰጡት ነው" ተብሏል።
የሞስኮው ተወካይ ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊት ኮፍ እና አማች ጃርድ ኩሽነር ጋር መምከራቸውን አርቲ በዘገባው አመልክቷል።
3 329
Repost from HahuPlus Market
+1
SAMSUNG Galaxy S20
Storage 128GB
Ram 12GB
Network 5G
Single SIM Card add slot and
Support esim
Battery 🔋 4000
Made in USA
Price 25,000
0914657085
0913149440
@abdy_et
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
