fa
Feedback
Secrets of Truth - 𝘽𝙮 𝙍𝙚𝙨𝙝𝙖𝙙

Secrets of Truth - 𝘽𝙮 𝙍𝙚𝙨𝙝𝙖𝙙

رفتن به کانال در Telegram

● ዲናችንና በሚመለከት ወቅታዊ መረጃዎችን ➶ Current information about Muslims and Islam 🔗 ሌሎችንም አንገብጋቢ ጉዳዮችን የምንተዋወስበት Channel ነው‼️ ➞ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አጠር ያሉ ስንኞች (በተለይም ስለ ፈለስጢን 🇵🇸) 🎯 አላማዬ:- የእውነትን ሚስጥሮች ማጋለጥ ነው‼️ #Free_Palestine 🇵🇸

نمایش بیشتر
213
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-17 روز
-430 روز
آرشیو پست ها
ረመዿን 9 🌙🕋 العمرة في رمضان 🕋🌙 በረመዿን ወር ውስጥ ዑምራ ማድረግ! ኢማም አል-ቡኻሪ እንዲሁም ሌሎችም በዘገቡት ሐዲስ  ኢብኑ ዓባስ እንዳስተላለፈው የአላህ መልዕክተኛﷺ ለ አንዲት ከአንሳሮች ለሆነች ሴት  (ስሟን ኢብኑ አባስ ጠቅሶታል ነገር ግን ሐዲስ አስተላላፊው ረስቶታል) ለምንድነው ከእኛ ጋር አብረሽ ሐጅ የማታደርጊው? አሏት እሷም እንዲህ አለች እኛ ሁለት መጓጓዣ ግመሎች ነበሩን አንዱን የእከሌ አባት እና ልጁ ተሳፈሩበት አለች (የራሷን ቧል እና ልጇን ማለቷ ነው)  ሁለተኛውን ደግሞ ለእኛ እዚሁ ብቻ የምንጓጓዝበትን አንድ አስቀሩልን አለቻቸው የአላህ መልዕክተኛምﷺ ቀጣይ ረመዿን ሲመጣ ዑምራ አድርጊ በረመዿን ውስጥ የሚደረግ ዑምራ ልክ እንደ ሐጅ ነው አሏት። ቡኻሪ በዘገበው  ዘገባ ላይ ኢብኑ ዓባስ እንዲህ ይላል የአላህ መልዕክተኛﷺ ሐጅ አድርገው ሲመለሱ ለ ኡሙ ሲናን አል አንሳሪይ  ከ ሐጅ ምን ከልክሎሽ ነው ያላደረግሽው? አሏት፤  እሷም የእከሌ አባት (ባሏን ማለቷ ነው) 2 ግመሎች ነበሩት አንዱን እሱ ሐጅ አደረገበት አንዱን ደግሞ ለእኛ ተወልን መሬታችንን እንዲያጠጣልን አለቻቸው እሳቸውም በረመዿን ዑምራ ማድረግ ከእኔ ጋር ሐጅ እንደማድረግ ነው አሏት። ኢብኑል ዐረቢ እንዲህ ይላል፤ በ ረመዿን ዑምራ ስለማድረግ የሚያወሳው ሐዲስ ሶሒሕ ነው እሱም ከአላህ የሆነ ፀጋ እና ትሩፋት ነው፤ ዑምራ የሐጅን ደረጃ ማግኘቱ ፤ ይህም የሆነው ከረመዿን ወር ጋር አብሮ በመያያዙ ነው። አላህ ይወፍቀን! 🔈 ሸይኽ አብዱልከሪም አል-ኹደይር  አላህ ይጠብቃቸውና

እርግጥ ነው፣ ሼክ ረቢዕ ኢብን ሃዲ ስለ አዛን ሲሰማ በቤት ውስጥ ስለመስገድ የሰጡትን ማብራሪያ በአማርኛ እነሆ፡- ጥያቄ፡- አዛን እየተሰማ በቤት ውስጥ መስገድ ይቻላልን? እንዲሁም የጀመዓ ሶላት በመስጂድ መኖሩ ግዴታ ሳይሆን የተመረጠ እንደሆነ አድርጎ መቁጠር (ይህ ይቻላልን)? መልስ፡- አንዳንድ ሊቃውንት የጀመዓ ሶላት በመስጂድ መገኘት የሶላት ትክክለኛነት ቅድመ ሁኔታ እንደሆነ ይቆጥሩታል፣ በዚህም ምክንያት በቤት ውስጥ የሚደረግ ሶላት ምክንያታዊ የሆነ ሰበብ ከሌለ አይፈቀድም። አንዳንድ ሊቃውንት ደግሞ የጀመዓ ሶላት የግል ግዴታ ነው፣ ነገር ግን በቤት ውስጥ የሚደረግ ሶላት (አሁንም) ትክክል ነው የሚል አስተያየት አላቸው። አንድ ሰው (በእስልምና) ምክንያታዊ የሆነ ሰበብ ካለው፣ አላህ ከሻው ይቅር ይለዋል፣ እንዲሁም ኒያውን ይጽፍለታል። ነገር ግን ሰበብ ከሌለው፣ ከሙስሊሞች ጋር በመስጂድ ውስጥ ሶላቱን መስገድ አለበት። ለዚህ አቋም ማስረጃው አቡ ሁረይራ ያስተላለፉት ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ማለታቸው ነው፡- “ነፍሴ በእጁ በሆነው እምላለሁ፣ በእርግጥም የማገዶ እንጨት እንዲሰበሰብ ለማዘዝ አስቤ ነበር፣ ከዚያም (ለሶላት ትእዛዝ) አዛን ተደረገ፣ ከዚያም ሰዎችን (በሶላት) እንዲመራ አንድ ግለሰብን አዝዛለሁ። ቀጥሎም (ለሶላት ጥሪ ምላሽ የማይሰጡ) ከኋላዬ ካሉ ሰዎች ጋር መጥቼ ቤታቸውን አቃጥላለሁ። ነፍሴ በእጁ በሆነው እምላለሁ፣ አንዳቸውም አንድ የስጋ አጥንት ወይም ሁለት የስጋ ቁርጥራጮች እንደሚያገኙ ቢያውቁ ለኢሻ ሶላት ይገኙ ነበር።” በተመሳሳይ ኢብኑ መስዑድ እንዲህ ብለዋል፣ “እኛ አንድ ግለሰብ ከሶላት የሚቀር ግብዝነቱ በታወቀ ግብዝ ወይም በታማሚ ሰው ብቻ ነው ብለን እናስብ ነበር፣ ታማሚ ቢሆንም እንኳ ወደ ሶላት እስኪደርስ በሁለት ሰዎች መካከል ይራመዳል።” እሱም ይህ ግለሰብ የጀመዓ ሶላትን ሆን ብሎ በመዘግየቱ ግብዝነቱ በሰዎች ዘንድ እንደሚታወቅ ማለቱ ነው። የጀመዓ ሶላት ከእስልምና ተግባራት አንዱ መለያ ባህሪ እና ከእስልምና ታላላቅ ተግባራት አንዱ ነው። ስለዚህ አንድ ሙስሊም ከእሱ መቅረት አይፈቀድለትም፣ እንደ እንቅልፍ መብዛት ወይም ህመም ያሉ (በእስልምና የተፈቀዱ) ሰበቦች ካልኖሩ በስተቀር። በሰበብ በቤቱ ከሰገደ፣ ምስጋና ሁሉ ለአላህ ብቻ ይሁን፣ ከእርሱም ይቀበለዋል። በሌላ በኩል፣ ሆን ብሎ (ከመቅረት) ከሆነ እና በዚህም ምክንያት ወደ እሱ ጥሪውን እየሰማ የጀመዓ ሶላትን በቤቱ ከሰገደ፣ አይሆንም። ወደ ሶላት ጥሪውን ከሰማህ፣ ለእሱ ምላሽ መስጠት ግዴታ ይሆንብሃል። ኢብኑ ኡሙ መክቱም ነቢዩን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) “የአላህ መልእክተኛ ሆይ፣ እኔ ዓይነ ስውር ሰው ነኝ፣ ቤቴም (ከመስጂዱ) የራቀ ነው፣ የሚረዳኝ መሪም አለኝ፣ ስለዚህ በቤት ውስጥ ለመስገድ ፈቃድ አለኝን?” ብለው በጠየቋቸው ጊዜ አስተላልፈዋል። ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)፡- “ጥሪውን ትሰማለህን?” አሉት። እርሱም “አዎ” ብሎ መለሰ። እርሱም (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)፡- “ለአንተ ፈቃድ ማግኘት አልችልም” አሉት። ስለዚህ ጉዳዩ በጣም አስፈላጊ ነው፣ ስለዚህ ሶላቶቻችሁን በመስጂዶች በጀመዓ ጠብቁ። ለምን ወደ ሶላት ይጠራሉ? ለምን ወደ ሶላት ኑ ይሉዎታል? ይድረሱ፣ ይገለጡ፣ ይታዩ እያሉዎት ነው። በአቡ ዓብዲል ዋሂድ ነጂብ አል አንጀለሲ የተተረጎመ። ምንጭ፡ فتاوى فضيلة الشيخ العلامة ربيع بن هادي عمير المدخلي http://pureislaam.com/2016/04/30/praying-at-home-when-adhan-is-heard-sheikh-rabee-ibn-haadi/ 👇👇👇 #በGemini ወደ አማርኛ የተተረጎመ

Praying At Home When Adhan Is Heard: Sheikh Rabee Ibn Haadi بسم الله الرحمن الرحيم Q: Is it permissible to perform prayer at home even though the adhan is heard? Likewise deeming the congregational prayer in the masjid to be preferred instead of obligatory (is this permissible)? A: Some scholars considered congregational prayer in the masjid to be a prerequisite for the validity of prayer, consequently the prayer at home is not allowed unless one is excused. Some scholars hold the opinion that congregational prayer is an individual obligation, yet prayer at home is (still) valid. If one is legitimately excused (in Islam), then Allah will overlook it if He wills and will write his intent. However if he is not excused then he must perform the prayer at the masjid along with the Muslims. The evidence for this position is what Abu Huraira narrated where the Prophet -sallahu alayhi wa salaam- said “I swear by Him in whose Hand is my soul, indeed I intended the ordering of firewood (to be gathered), then (the command for) the prayer and hence the adhan is called, then order an individual so that he can lead the people (in prayer). Next I will come behind some men (who do not answer the call to prayer) and burn their homes. I swear by Him in whose Hand is my soul if any of them knew that they would find a meaty bone or two pieces of meat he would have been present for Ishaa.” Likewise Ibn Masud said, “We held the opinion that an individual is not absent from the prayer except a hypocrite whose hypocrisy is known, or a sick person even though he is sick he still walks between two men until he reaches the prayer.” He means the people know of the hypocrisy of this individual due to his lagging behind on the congregational prayer intentionally. The congregational prayer is a distinguishing characteristic from the Islamic practices and from the greatest of Islamic practices. Therefore it is not permissible for a Muslim to be absent from it except with a (legitimate Islamic) excuse, like if he oversleeps or is sick. If he prays in his home while he is excused then all praise is for Allah alone and He will accept it from him. On the other hand, if he is deliberate (in being absent) and as such prays the congregational prayer in his home while he hears the summons to it, then no. If you hear the summons to prayer it becomes binding upon you to respond to it. Ibn Umm Makhtum narrated when he asked the Prophet -sallahu alayhi wa salaam-, “O Allah’s Messenger indeed I am a blind man with a home far away (from the masjid), and I have a guide who does not aid me, so is there for me a concession to pray at home?” The Prophet -sallahu alayhi wa salaam said: “Do you hear the summons?“ He replied, “yes.” He -sallahu alayhi wa salaam- said: “I can not find for you a concession.” Hence the subject is very important, so preserve your prayers in congregation at the masaajid. Why does one call to the prayer? Why does he say to you come to the prayer? He is saying to you arrive, appear, show up! Translated by Abu Abdil Waahid Najeeb Al Anjelesi Source: فتاوى فضيلة الشيخ العلامة ربيع بن هادي عمير المدخلي http://pureislaam.com/2016/04/30/praying-at-home-when-adhan-is-heard-sheikh-rabee-ibn-haadi/

The two sheikhs who have been consistently present in the front row for Taraweeh for 40 years, the two most senior Imams of M
The two sheikhs who have been consistently present in the front row for Taraweeh for 40 years, the two most senior Imams of Masjid Al Haram, Sheikh Salih bin Humaid & Sheikh Abdul Rahman Al Sudais (May Allah protect them).

እልፍ ዚክራዎችን መንገዳቸውን እያሰናከሉ ስለ ሴቶች መብት ይደሰኩራሉ። ~ ዚክራ ሰዒድ በወሎ ዩኒቨርሲቲ የሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል 3.99 አጠቃላይ ውጤት በማስመዝገብ የምስክር ወረቀት፣ የሜዳሊያ እ
እልፍ ዚክራዎችን መንገዳቸውን እያሰናከሉ ስለ ሴቶች መብት ይደሰኩራሉ። ~ ዚክራ ሰዒድ በወሎ ዩኒቨርሲቲ የሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል 3.99 አጠቃላይ ውጤት በማስመዝገብ የምስክር ወረቀት፣ የሜዳሊያ እና የሁለት ዋንጫዎች እንዲሁም ልዩ ተሸላሚ ሆናለች። ዚክራን አላህ ከራሷ አልፋ ለወገን የምትጠቅም ያድርጋት። ግን "በሴቶች ቀን የተመረቀች ጠንካራዋ ሴት" እያሉ መደለል አስመሳይነት ነው። የኢትዮጵያ የትምህርት ተቋማት የግፍና መድሎ አፀድ ናቸው። ከትግራይ እስከ ኦሮሚያ፣ ከአማራ እስከ ደቡብ፣ ከጉራጌ ዞን እስከ አዲስ አበባ ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ፣ እስከ ዩኒቨርሲቲዎች ድረስ ሙስሊም ተማሪዎችን በተለይም ሴቶችን ከትምህርት ገበታ ማግለል እና ፈተናና ፆም እየጠበቁ ማዋከብ የትምህርት ሚኒስቴር ዋና ስራ እስከሚመስል የተለመደና የሚጠበቅ ሀይ ባይ ያጣ ጉዳይ ሆኗል። እንደ ትምህርት ተቋማት ስለ መብት የሚሰበክበት፣ እንደ መምህራን ስለ መብት የሚያላዝን የለም። እንደነሱ ደግሞ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ በደል የሚያደርስ፣ መብት የሚጨፈልቅ የለም። "ተበደልኩ" እያለ ሰርክ የሚያለቅሰው ክፍል ሳይቀር ሙስሊሞችን በመበደል ላይ ከፊት ረድፍ ሲሰለፍ ይታያል። በዚህ ሃገር የብሄር ውጥንቅጥ እየገባችሁ አጉል መስዋእትነት የምትከፍሉ ሙስሊሞች ታሳዝናላችሁ። ህመምህን ብሶትህን ማታገያ እያደረገ ከጎኑ የሚያሰልፍህ ሁሉ በመከራ ጊዜው እንኳ እምነት እየለየ ከመግፋት ካልተመለሰ ጉልበት ቢኖረውና ምቹ ሁኔታ ቢያገኝ ምን ሊያደርገኝ ብሎ ማሰብ ይገባል። ለማንኛውም እንማር። ልጆቻችንንም እናስተምር። = የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor

Ramadaan is the school of life 📌 Shaykh Abdur Razzaaq al Badr حفظه الل #Ramadan_Reminder Join:- @Islamic_Info_4u @Islamic_Search

The Imaams of Masjid Al Haram & Masjid An Nabawi during Taraweeh
+6
The Imaams of Masjid Al Haram & Masjid An Nabawi during Taraweeh

ረመዿን 8 🌙 هدي النبي صلى الله عليه وسلم في الإفطار 🌙 የነብዩ ﷺ የኢፍጣር አኳኋን ረሱል (ﷺ) ከመስገዳቸው በፊት በእርጥብ ተምር ያፈጥሩ ነበር እሱን ካላገኙ በደረቅ ተምር ያፈጥራሉ እሱንም ካላገኙ በውሃ መጎንጨትን ይጎነጩ ነበር። አንድ ሰው እነዚህን 3ቱንም ካላገኘ ባገኘው ነገር ያፍጥር፤ ምንም ካላገኘ በኒያ ማፍጠርን ያስባል ልክ በሐዲስ እንደመጣው ሌሊቱ በዚህ አቅጣጫ መጥቶ ቀኑ ከተወገደ ፆመኛ ሰው በርግጥ ፆሙን ፈቷል (አፍጥሯል) ጣቱን ይምጠጥ ምናምን የሚሉት የአላዊቂዎች ንግግር ተቀባይነት የለውም! የተምር ጥቅም ውስጣችን ባዶ ሆኖ ቆይቶ ጣፋጭ በሆነ ተምር ስናፈጥር በቀላሉ ይቀበለዋል ጉልበትን በፍጥነት እንዲያገኝ ያደርገዋል ውሃም እንዲሁ ጉበታችንን በውሃ ረጠብ ስትል አገልግሎቷን በተገቢው እና በተሟላ መልኩ እንድታከናውን ይረዳል ለዚያም ነው የተጠማ ፣የተራበ ሰው ምግብ ከመመገቡ በፊት ውስጡን በውሃ እንዲያረጥበው የሚመከረው ከዚያም ምግቡን ይመገባል ማለት ነው ይህ የተምር እና የውሃ ጥቅም ለየት ባለ መልኩ ለልብ መስተካከልንም ትልቅ ተፅዕኖ እንዳለው የልብ ሀኪሞች ያውቁታል 🔈 ሸይኽ አብዱልከሪም አል-ኹደይር  አላህ ይጠብቃቸውና

في أجواء مفعمة بالسكينة والروحانية ‏تُقام صلاة التراويح في مسجد رسول الله ﷺ ‏ليلة ٨ رمضان ١٤٤٦هـ من نفحات يوم الجمعة المبارك
+2
في أجواء مفعمة بالسكينة والروحانية ‏تُقام صلاة التراويح في مسجد رسول الله ﷺ ‏ليلة ٨ رمضان ١٤٤٦هـ من نفحات يوم الجمعة المبارك ........ Imams of Masjid Al Nabawi during Salat Taraweeh tonight

በሳዑዲ አረቢያ መካ ከተማ አል-ሀረም መስጅድ የታላቁ የረመዷን ወር የመጀመሪያው የጁመአ ቀን ድባብ በምስል፦ © ሀሩን ሚድያ
+2
በሳዑዲ አረቢያ መካ ከተማ አል-ሀረም መስጅድ የታላቁ የረመዷን ወር የመጀመሪያው የጁመአ ቀን ድባብ በምስል፦ © ሀሩን ሚድያ

በፍልስጤም አል-አቅሳ መስጂድ ከ90ሺ በላይ ሰዎች የተገኙበት የታላቁ የረመጿን ወር የመጀመሪያው የጁመአ ሰላት በምስል፦ © ሀሩን ሚድያ
+3
በፍልስጤም አል-አቅሳ መስጂድ ከ90ሺ በላይ ሰዎች የተገኙበት የታላቁ የረመጿን ወር የመጀመሪያው የጁመአ ሰላት በምስል፦ © ሀሩን ሚድያ

. If a person enters the Masjid and people are praying Taraweeh and he still hasn’t prayed Isha, how should he pray? Shaykh Salih Al-Fawzan حفظه الله

ፍልስጤማዊው መምህር እስራኤል በጋዛ በፈፀመችው የቦንብ ጥቃት ሁለት እግሮቹን ቢያጣም በታላቁ የረመዳን ወር በራፋህ በነብዩ መስጂድ ልጆችን ቁርኣን እያስተማረ የሚገኝበት ክስተት በምስል፦ ©ሀሩን ሚድ
ፍልስጤማዊው መምህር እስራኤል በጋዛ በፈፀመችው የቦንብ ጥቃት ሁለት እግሮቹን ቢያጣም በታላቁ የረመዳን ወር በራፋህ በነብዩ መስጂድ ልጆችን ቁርኣን እያስተማረ የሚገኝበት ክስተት በምስል፦ ©ሀሩን ሚድያ

ለባለሃብቱ! 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 ለገቢዎች ባለስልጣን መስሪያ ቤት የምትከፍለውን ግብር እያሰብክ ከዘካ እንዳትዘናጋ። ዘካ ለደካሞች የሚሰጥ ሐቅ እንጂ ለሹማምንት የሚሰጥ ግብር ወይም ጉቦ አይደ
ለባለሃብቱ! 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 ለገቢዎች ባለስልጣን መስሪያ ቤት የምትከፍለውን ግብር እያሰብክ ከዘካ እንዳትዘናጋ። ዘካ ለደካሞች የሚሰጥ ሐቅ እንጂ ለሹማምንት የሚሰጥ ግብር ወይም ጉቦ አይደለም። አኺል ከሪም! ገንዘቡን የሰጠህ አላህ ነው። እንጂ ካንተ የበለጠ የሚለፉ ድሃዎች በዙሪያህ አሉኮ። በእውቀቴ አገኘሁት እንዳትል ካንተ የበለጠ የተማሩ ድሃዎች ሞልተዋልኮ። ጥለኸው ለምትሄደው ገንዘብ ብለህ በራስህ ላይ አትሳሳ። እውነተኛው ያንተ ገንዘብ ማለት ለአኺራህ ያሻገርከው ነው። ዐብዱላህ ብኑ ሺኺር - ረዲየሏሁ ዐንሁ - እንዲህ ይላሉ፦ "ነብያችን ﷺ ዘንድ መጣሁኝ። {በብዛት መፎካከር (ጌታችሁን ከመገዛት) አዘነጋችሁ} የሚለውን እየቀሩ ነው። ቀጥለው እንዲህ አሉ፦ 'የአደም ልጅ 'ገንዘቤ ገንዘቤ!' ይላል። የአደም ልጅ ሆይ! በልተህ ከጨረስከው፣ ለብሰህ ካሳለቅከው፣ ሶደቃ ሰጥተህ አጅሩን ካሻገርከው ውጭ ገንዘብ አለህ'ንዴ?' " [ሶሒሕ ሙስሊም፡ 2958] እወቅ! የምታወጣው ካጠቃላይ ገንዘብህ 2.5 ከመቶ ብቻ ነው። መቶ ብር ያለው ሰው ሁለት ብር ከሃምሳ ሳንቲም ቢያወጣ ብዙ ነው ወይ? ምስሉ ላይ በጣት የተጠቆመችዋን ተመልከት። ካጠቃላይ ሃብትህ ይቺን ታክል ለዘመዶችህ፣ ለጎረቤቶችህ፣ ለምታውቃቸው ምስኪኖች ብታወጣ ብዙ ነውን? በአኺራ እጥፍ ድርብ ምንዳ እንደሚጠብቅህ የቂን የለህም ወይ? ደግሞም እወቅ! ወላሂ ሶደቃ ሃብትን አይቀንስም። ይልቁንም ይበልጥ በረካ እንዲኖረው ነው የሚያደርግልህ። አላህ ትእዛዙን ለመፈፀም ያግራልህ። ©️Ibnu Munewor

Five minutes before iftar we feel hungry, five minutes after iftar we feel full. ‎That\'s the proof that this dunya is just about desire... and how quickly your desires change.. ‎وَمَا ٱلْحَيَوٰةُ ٱلدُّنْيَآ إِلَّا مَتَـٰعُ ٱلْغُرُورِ And what is the life of this world except the enjoyment of delusion. (Surah Aal e Imran:185)

ረመዿን 6 🌙 هل تدركه بعد ذلك 🌙 ከዚህ በኃላ የሚመጣውን ረመዿንን ታገኘዋለህ ወይ? 🌌 لا ندري هل سنعيش إلى رمضان آخر. 🌌 كم فقدنا من عزيز أو جار أو قريب في رمضان እስከመጪው ረመዿን ድረስ መኖራችንን አናውቅም በዚሁ ረመዿን ስንትና ስንት ወዳጆችን፣ ጎረቤት እና ቅርብ ሰዎችን አጥተናል! ይህ የተባረከ ወር በ ዓመት 1 ግዜ ብቻ የሚያልፍ የሆነ ወር ነው ቀጣይ ዓመት ይህን ወር ድጋሚ ማግኘትህን ወይም ደግሞ ከዚያ በፊት መሞትህን አታውቅም ስለዚህ በዚህ ወር ልትጠነክር እና ወደ አላህ የሚያቀርቡህን ነገራቶች በመተግበር ልትፈጥን ይገባል፤ እንዲሁም ከአላህ ቅጣት የሚያድኑህን ሰበቦችን ለመስራት ልትበረታ የአላህ መሃርታን የሚያስገኙ ወንጀልህን ሊያሰርዙ የሚችሉ መልካም ስራዎችን ልትሰራ ይገባል ምክንያቱም ቀጣይ ዓመት ይህን ወር ድጋሚ ማግኘትህን አታውቅም! በዚህ ወር ለሙስሊሞች የተወደደ ነው፤ ሌሊቱን በሰላት ሊቆሙ በላጩ ፤11 ረክዓ ሊሰግዱ ሁለት ሁለት እያደረጉ፤ በውስጧም ቁርዓንን አስተካክለው ባማረ መልኩ በኹሹዕ ሊያነቡ ይገባል በሰላቱም ሩኩዕ እና ሱጁድ ሲወርዱ በእርጋታ እና በኹሹዕ ሊሆን ይገባል በሰላታቸው አይቻኮሉ ጎንበስ ቀና ብቻ አያድርጉት፤ ዋናው የሚፈለገው ልክ ነብያችን ሲሰግዱ እንደነበረው በኹሹዕ በዕርጋታ እና ልባቸውን ሰጥተው በጥሞና ያማረ አቀራርን እየቀሩ እያስተነተኑ መሆን አለበት እንጂ አንዳንድ ሰዎች በሰላት ተራዊህ እንደሚሰግዱት የችኮላ ጎንበስ ቀና ሰላት መሆን የለበትም፤ ምናልባትም እንዲህ አይነት ሰላት ተቀባይነት የሌላትና የማትበቃ ሰላት ትሆናለችና። 🔈 የተከበሩ ሸይኽ አብዱልዓዚዝ ቢን ባዝ አላህ ይዘንላቸውና

“Perhaps this is my last Ramadan in life” | Shaykh Muhammad Raslan حفظه الله

“እወቁ! ለወንድሞቻችሁ ፊትን ፈታ እና ፈገግ ማደረግ መልካም ምንዳን የምታገኙበት መገለጫ ባህሪ ነው። በዚህ ባህሪ የታነፃ አላህ ሊያመሰግን ይገባል። እንዲጨምርለትም ይጠይቀው። ይህ ባህሪ የሌለው ነፍሱን በዚህ አኽላቅ ሊያለማምዳት ይገባል።” ✍ ኢብኑ ዐሰይሚን ረሂመሁላህ 📚 {አዲያኡ አል ላሚዕ (1/107)}

🛑 ተራዊህ በመስገድ ከሚገኙ ጥቅሞች 📌 ቀኑን በጾም ሌሊቱን በሰላት በማሳለፋችን ከደጋግ የአላህ ባሪያዎች እንመደባለን 📌 ቁርኣን በብዛት በማድመጣችን የአላህን እዝነት እናገኛለን 📌ተራዊሕ ብዙ ሩኩዕና ሱጁድ ስላለበት ሰፊ የዱዓና የዚክር እድል እናገኛለን 📌ከወንጀል ርቀን ጊዜያችንን በመልካም ስራ እናሳልፋለን 📌ዒባዳ ላይ ትዕግስትን እንማራለን 📌ሰላተል-ለይል እንለማመዳለን 📌በተደጋጋሚ ከኢማሙና ማእሙሞች ጋር "አሚን" በማለታችን ወንጀላችን ይማራል 📌 መስጂድ ስንሄድና ስንመለስ በእርምጃችን ልክ ወንጀሎች ተራግፈው መልካም ስራዎች ይጻፉልናል 📌 ሰላት እየጠበቀን በምናሳልፋቸው ጊዜያቶች መላኢካዎች ምህረት ይጠይቁልናል 📌 የሙስሊሞችን ጀማዓ በማብዛት ሸይጣንና አጋዦችን እናስቆጫለን 📌 ከመልካም ሰዎች ጋር በመቀላቀላችን መልካም ስራዎቻችን ወደ ሰማይ እንዲወጡና ተቀባይነት እንዲያገኙ እድል ይፈጥራል 📌 ከአልባሌ ነገሮች ለመራቅ ለወጣቱ መልካም አርዓያ እንሆናለን 📌 ካመኑበትና ጥቅሙን ካወቁት ሁሉም ነገር ቀላልና የሚቻል መሆኑን በተጨባጭ እናይበታለን 📌 ቁርኣንን በብዛት በመስማት የአላህን እዝነት እናገኛለን እንዲሁም ብዙ በመስማት ትክክለኛውን የቁርኣን አቀራርም እንማራለን 📌 በቁኑት ዱዓ ወቅት ብዙ እኛ ያላሰብናቸውና መግለጽ የማንችላቸው ነገሮች ዱዓ ተደርጎ "አሚን" በማለታችን ትርፋማ እንሆናለን 📌 ከኢማሙ ጋር እስከሰላቱ ፍጻሜ ድረስ አብረን እየሰገድን ከቆየን ሌሊቱን በሙሉ ሲሰግድ ያደረን ሰው እጅር /ምንዳ እንሸምታለን 📌 የቂያማ ቀን መቆምን ያቀልልናል፥ዱኒያ ላይ ለጌታው ብሎ ረጅም ሰዓት የቆመ የቂያማ ቀን መቆም አይከብደውም 📌 ሰግደን ስንመለስ የውስጥ ደስታና እፎይታና ሌሎችንም የዲንም የዱኒያ በርካታ ጥቅሞችን እናገኛልንና ተራዊህን ሳንሰለች እንስገድ። አላህ ያግራልን

The General Presidency provides more than 227 thousand Iftar meals in Masjid Al Nabawi daily.
+3
The General Presidency provides more than 227 thousand Iftar meals in Masjid Al Nabawi daily.